Print this page
Saturday, 30 March 2013 16:04

ሊል ዋይኔ ከሞት ተርፎ አዲስ አልበም አወጣ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የሊል ዋይኔ አዲስ አልበም ‹‹አይ አም ኖት ኤ ሂውማን ቢንግ 2›› በሳምንቱ አጋማሽ ላይ ለገበያ የቀረበ ሲሆን ሽያጩ እንደሚደራለት ከወዲሁ ተገምቷል፡፡ ከሳምንት በፊት ሊል ዋይኔ ከድንገተኛ የልብ ህመም ጋር በተገናኘ በገጠመው የጤና እክል ከሞት አፋፍ እንደተረፈ ተዘግቧል፡፡ በማህበረሰብ ድረገፆች አነጋጋሪ በመሆን በአንድ ሳምንት ውስጥ ከቀድሞው የ19ኛ ደረጃ ወደ ሁለተኛ ደረጃ የተመነደገው ራፐሩ፤ አጋጣሚው ለአዲሱ አልበሙ ጥሩ ማሻሻጫ ይሆንለታል ተብሏል፡፡ ራፐሩ ከሚወስደው ሃይል ሰጭ መጠጥ ጋር በተያያዘ ለህይወቱ የሚያሳስብ አደገኛ ደረጃ ላይ ደርሶ እንደነበረ ያወሱት ዘገባዎች ፤ ሆስፒታል ገብቶ በተደረገለት ከፍተኛ የህክምና ክትትል ህይወቱ እንደተረፈ ጠቁመዋል፡፡ ሊል ዋይኔ የገጠመው የጤና እክል ከጭንቀት ጋር በተያያዘ የተፈጠረ እንጅ በአደገኛ እፅ ተጠቃሚነት አለመሆኑን ያስተባበለው የአሳታሚው “ካሽ መኒ” ስራ አስኪያጅ ፤ በቂ እረፍት በመውሰድና ራሱን በማዝናናት ጤንነቱ እንደሚመለስለት ተናግሯል፡፡

ከ2013 ምርጥ አልበሞች አንዱ እንደሚሆን ተስፋ የተጣለበት የሊል ዋይኔ አዲስ አልበም በከፍተኛ ጉጉት ሲጠበቅ እንደቆየ የዘገበው ሮሊንግ ስቶን መፅሄት፤ በአልበሙ ላይ ኒኪ ማንጅ፤ ድሬክ፤ ቢግ ሲን፤ ገን ፕሌይ እና ሌሎች ራፐሮች በአጃቢነት እንደሰሩ አመልክቷል፡፡ የአልበሙን ሽፋን ምስል የሰራለት የሂፖፕ ሙዚቀኛው ካናዬ ዌስት እንደሆነ የገለፀው መፅሄቱ ፤ ሊል ዋይኔ የዓለም ምርጥ ራፐር መሆኑን ካናዬ መመስከሩንም ጨምሮ አስታውቋል፡፡ ራፐሩ ከሁለት ዓመት በፊት ‹‹አይ አም ኖት ኤ ሂውማን ቢንግ›› በሚል ስያሜ የመጀመርያውን የአልበሙን ክፍል ለገበያ እንዳበቃ የሚታወስ ነው፡፡ ሊል ዋይኔ ከአዲሱ አልበሙ ‹‹አይ አም ኖት ኤ ሂውማን ቢንግ 2›› በኋላ አጠቃላይ የስራዎቹን ብዛት 11 ያደረሰ ሲሆን በሙዚቃ ህይወቱ 95 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ ሃብት ማፍራቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 3383 times
Administrator

Latest from Administrator