Monday, 25 March 2013 11:57

‹ኦዝ ፡ ዘ ግሬት ኤንድ ፓወርፉል› ገበያውን ይመራል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

‹‹ኦዝ ፡ ዘ ግሬት ኤንድ ፓወርፉል›› የተሰኘው ፊልም በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት 2013 ከፍተኛውን ገቢ ለማግኘት የበቃ ፊልም መሆኑን ሎስአንጀለስ ታይምስ አስታወቀ፡፡ በዋልት ዲዝኒ፣ በ215 ሚሊዮን ዶላር የተሰራው ፊልም ከሁለት ሳምንት በኋላ በመላው ዓለም ከ288 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አግኝቷል፡፡ ፊልሙ ለእይታ በበቃባቸው የመጀመርያዎቹ ሶስት ቀናት በዓለም ዙርያ ከ150 ሚሊዮን ዶላር በላይ ማስገኘቱ፣ የፊልሙ ቀጣይ ክፍሎችን የመስራት ሃሳቦችን አነሳስቷል፡፡

በጥንቆላ አፈታሪክ ዙርያ የሚጠነጥነው “አድቬንቸር ፋንታሲ” ፊልም፣ ጄምስ ፍራንኮ በመሪ ተዋናይነት ሰርቶበታል፡፡ ሚላ ኩኒስ፤ ራቼል ዊሴዝ እና ሜሸል ዊልያምም ተውነውበታል፡፡ ‹ኦዝ፡ ዘ ግሬት ኤንድ ፓወርፉል›፣ ከ74 አመታት በፊት ‹ዘ ዎንደርፉል ዊዛርድ ኦፍ ኦዝ› በተባለው ዘመን ያልሻረው መፅሃፍ ላይ በመመስረት በ3ዲ የተሰራ ነው፡፡ የፊልሙ ዲያሬክተር በስፓይደርማን ሶስት ፊልሞች ከፍተኛ አድናቆት ያተረፈው ሳሚ ራይሚ ነው፡፡

Read 2624 times