Monday, 25 March 2013 11:55

አዴሌ በአጭር ጊዜ ሁሉንም ሽልማት ወስዳለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

እንግሊዛዊቷ ድምፃዊት አዴሌ በጥቂት አመታት ውስጥ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ሽልማቶችን ሁሉ በመሰብሰብ ስኬታማ እንደሆነች ቢዝነስ ኢንሳይደር ገለፀ፡፡ አዴሌ ከ3 ሳምንታት በፊት በ85ኛው የኦስካር ምሽት ላይ ለጀምስ ቦንድ ፊልም በሰራችው ሙዚቃ በምርጥ ኦርጅናል ዜማ ዘርፍ የኦስካር ሽልማት ወስዳለች፡፡ የ24 አመቷ አዴሌ አዲስ አልበም ለመስራት እንደማትቻኮል ወኪሏ ሰሞኑን ያሳወቀ ሲሆን፣ የመስራት ፍላጎት ቢኖራት እንኳን ዘንድሮ ጋብቻ ለመመስረት ማቀዷ ዝግጅቷን ያስተጓጉለዋል የሚሉ ዘገባዎች ወጥተዋል፡፡

አዴሌ በትልልቆቹ የኪነጥበቡ ኢንዱስትሪ ሽልማቶች ተሸላሚ የሆነችበት እድሜ በጣም የሚያስገርም ነው ያለው ዘ ቢዝነስ ኢንሳይደር፣ 9 የግራሚ፤ 4 የአሜሪካን ሚውዚክ አዋርድ፤ 12 የቢልቦርድ ሚውዚክ አዋርድ እና 4 የብሪት አዋርድ ሽልማቶችን በመሰብሰብ ወደር የለሽ ሆናለች፡፡ ‹21› የተሰኘው የአዴሌ ሁለተኛ አልበም በ2011 እና 2012 የዓለምን ገበያ ለመምራት የበቃ ሲሆን በአለም ዙርያ 12.5 ሚሊዮን ቅጂ ተሸጧል፡፡ አዴሌ ‹‹19›› በሚል ርእስ የመጀመርያ አልበሟን በመልቀቅ የዓለም የሙዚቃ ኢንዱስትሪን የተቀላቀለችው ከ4 ዓመታት በፊት ነበር፡፡

Read 2372 times