Sunday, 03 March 2013 08:36

“ጽንአት ቁጥር 2” በሒልተን ተመረቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በቁጥር አንድ መፅሐፉ የህወሐትን የትጥቅ ትግል ታጋዮችን ታሪክ በትግርኛ ያሳተመው ጋዜጠኛና ደራሲ ኃይላይ ሃድጉ፤ “ጽንአት ቁጥር 2” መፅሐፉን ከትናንት ወዲያ ከሰአት በኋላ በአዲስ አበባ ሂልተን አስመረቀ፡፡ በትግል ስሙ “ቃል (አል) አሚን” ተብሎ በሚጠራው ታጋይ የኋላእሸት ገብረመድህን ላይ ያተኮረውና በፎቶግራፎች የተደገፈው ባለ 320 ገፅ መፅሐፍ ሲመረቅ የህወሓት ነባር ታጋይ አቶ አባይ ፀሐዬ በክብር እንግድነት ተገኝተዋል፡፡ መፅሐፉን አንብበው አስተያየት ከሰጡት መካከል፤ የኢሠፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ፖሊት ቢሮ ተለዋጭ አባል እና የቀድሞ መንግሥት ከፍተኛ ባለስልጣን አቶ ፋሲካ ሲደልል እንዲሁም የኢህአፓ እና የኢዲዩ አባላት ይገኙበታል፡፡ መፅሐፉ በ70 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 3300 times