Sunday, 03 March 2013 00:00

ለ4 ዓመታት ዚንክን ለማቅረብ የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በተቅማጥ በሽታ ህይወታቸው የሚያልፈውን በ10ሺዎች የሚቆጠሩ ህፃናትን ከሞት ለመታደግ የሚያስችለውን ዚንክ የተባለ ንጥረ ነገር ለቀጣዮቹ አራት ዓመታት ለማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ማይክሮ ኒውትሬንት የተባለውና በካናዳ መንግስት የሚደገፈው ድርጅት ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋር ሰሞኑን ተፈራረመ፡፡
ባለፈው ሣምንት በሒልተን ሆቴል በተካሄደው በዚሁ የስምምነት ፊርማ ላይ እንደተገለፀው ድርጅቱ ለቀጣዮቹ 4 አመታት የ Zinc ንጥረ ነገሮችን በመድሃኒት መልክ የተቅማጥ በሽታ በስፋት በሚታይባቸው አካባቢዎችና በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች ያሰራጫል፡፡
ዚንክ በተቅማጥ ህመም ሣቢያ ህይወታቸው የሚያልፈውን ሰዎች በተለይም ህፃናትን ሞት በእጅጉ ለመቀነስ ከማስቻሉም በላይ የአዕምሮና የሰውነት ቅልጥፍና በመጨመር ጤናማ ማህበረሰብ እንዲኖር ትልቅ አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡
ማይክሮ ኒውትሬንት ኢንሼትቭ የተባለውና በእናቶችና ህፃናት ሥነ ምግብና ጤና ላይ አተኩሮ የሚሰራው ድርጅት ከጤና ጥበቃ ሚኒስትር መ/ቤት ጋር ባደረገው ስምምነት መሠረት ዚንክን ወደ አገር ውስጥ በማስገባት በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች እንዲሰራጭ ያደርጋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ በየዓመቱ ከ27ሺ በላይ ህፃናት በተቅማጥ በሽታ ይሞታሉ፡፡

Read 3498 times