የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ሁለንተናዊ አቅም የሚያሻሽሉና ከዚህ ቀደም በኢንዱስትሪው ትኩረት ያልተሰጣቸውን አገልግሎቶች ይዞ ሥራ መጀመሩን እናት ባንክ አስታወቀ፡፡
ባንኩ አገልግሎት የሚጀምርባቸው የመጀመሪያዎቹ ቅርንጫፎች ባንቢስ አካባቢ ከዮርዳኖስ ሆቴል ፊት ለፊት በሚገኘው ዋና መ/ቤቱና ቦሌ መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን አካባቢ መሆኑ ታውቋል፡፡ የባንቢስ አካባቢው ዓቢይ ቅርንጫፍ በእቴጌ ጣይቱ ስም የተሰየመ ሲሆን የቦሌ መድኃኒዓለሙ በንግሥተ ሳባ እንዲሁም የሰንጋ ተራው በወ/ሮ አበበች ጎበና ስም መሰየማቸውን ገልጸዋል፡፡
እናት ባንክ የሴቶችን አቅም በማጐልበትና በመጠቀም በኢንዱስትሪው ፈጣን ዕድገት ለማምጣትና የአገሪቱን ዕድገት ቀጣይ ለማድረግ የበኩሉን ሚና እንደሚወጣ አስታውቋል፡፡