Saturday, 09 February 2013 12:41

“የጠፋችውን ከተማ ኅሰሳ” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የ”አዲስ ነገር” ጋዜጣ መስራች እና ምክትል ዋና አዘጋጅ የነበረው ግርማ ተስፋው የገጠማቸው ግጥሞች የተካተቱበት “የጠፋችውን ከተማ ኅሰሳ” የግጥም መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ ገጣሚው በአራት የአለማችን ከተሞች ላይ ተመስርቶ የፃፋቸውን 69 ግጥሞች በአራት ክፍሎች ያቀረበ ሲሆን የመፅሐፉ ዋጋም 25 ብር ነው፡፡
ግርማ ተስፋው “አዲስ ነገር” ጋዜጣ ከተዘጋ በኋላ በ”አዲስ ነገር ኦንላይን” እና በኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጦች ላይ ፅሁፎቹ የታተሙ ሲሆን እ.ኤ.አ በ2011-12 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ የናይት (Knight) ጆርናሊዝም ፌሎ ነበር፡፡

Read 3874 times