“ፓናሮማ አክቲቪቲ 3”የተባለው ሆረር ፊልም ባለፈው ሳምንት በሰሜን አሜሪካና በመላው ዓለም ለእይታ የበቃ ሲሆን ከበጀቱ 16 እጥፍ የሚልቅ ከፍተኛ ገቢ አስገባ፡፡ ፊልሙ በመጀመርያ ሳምንት ገቢው በሰሜን አሜሪካ ብቻ 80 ሚሊዮን ዶላር በመድረሱ በሆረር ፊልሞች ታሪክ አዲስ የገቢ ሪኮርድ ማስመዝገብ መቻሉን ቦክስ ኦፊስ ሞጆ አመልክቷል፡፡ በፓራማውንት ፒክቸርስ በ3 ሚሊዮን ዶላር በጀት የተሰራው ‹ፓናሮማ አክቲቪቲ 3” በሳይንሳዊ ልቦለድ ላይ ያተኮረ አስፈሪ ፊልም ነው፡፡ ከ18 ዓመት በፊት የተሰራው “ፓናሮማ አክቲቪቲ” ክፍል 1 እና ሁለተኛው ክፍል 3 ሚሊዮን ዶላር ወጥቶባቸው በመላው ዓለም 371 ሚሊዮን ዶላር አስገብተዋል፡፡