የአዲስ አበባ ዋንጫው ዛሬ ሲቀጥል በ8 ሰዓት ደደቢት ከመብራት፣ በ10 ሰዓት ቡና ከባንክ ይጋጠማሉ ጊዮርጊስና መከላከያ ደግሞ ነገ በ10 ሰዓት ይገናኛሉ፡፡ የፊታችን ሰኞ በ9 ሰዓት መብራት ከቡና ፣ ባንክ ከደደቢት ጋር ተገናኝተው የምድብ 1 ጨዋታ ሲጠናቀቅ ማክሰኞ እለት ደግሞ በምድብ 2 መድን ከጊዮርጊስ ጋር ተገናኝተው የምድብ ትንቅንቁ ያበቃል፡፡ በምድብ 1 ባንክ፣ ቡና፣ መብራት፣ደደቢት ሲደለደሉ ጊዮርጊስ፣ መከላካያና መድን በምድብ 2 ይገኛሉ፡፡ በአዲስ አበባ ዋንጫ ስፖንሰሮች 600ሺ የደገፉ ሲሆን ለሻምፒዮኑ 30 ሺ ብር፤ ለ2ኛ 20ሺ እንዲሁም ለ3ኛ ደረጃ 10ሺ ብር የሚበረከት ይሆናል፡፡
ግማሽ ፍፃሜው ሐሙስ ሲቀጥል በ9 ሰዓት የምድብ ሀ 1ኛ ከምድብ ለ 2ተኛ እንዲሁም በ11 ሰዓት የምድብ ሀ 2ተኛ ከምድብ ለ1ኛ ጋር ተገናኝተው ለዋንጫ ያለፉት ክለቦች የሚታወቁ ይሆናል፡፡