Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 15 October 2011 12:20

“ሁለት ለአንድ” ተመረቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ሽፈራው መኮንን ጽፎት መስፍን ጣፋ ያዘጋጀው “ሁለት ለአንድ” የፍቅር ኮሜዲ ፊልም ከትናንት ወዲያ በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ትያትርና ባህል አዳራሽ ተመረቀ፡፡ 100 ደቂቃ በሚፈጀው ለማጠናቀቅ 15 ወራት በወሰደው ፊልም ላይ ሊዲያ ጥበቡ፣ ጀንበር አሰፋ፣ ወንድወሰን ብርሃኑ (ዶክሌ)፣ ሳምሶን ግርማ፣ ፀጋ ንጉሴ እና ሌሎች ተውነውበታል፡፡ ሁለት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ጓደኛማቾች አንዲት ሴት አፍቅረው የግላቸው ለማድረግ የሚያደርጉትን ፉክክር የሚያሳየውን ፊልም ያቀረበው ኢትዮ ቪዥን ኢንተርቴይመንት ነው፡፡ በምርቃቱ መጨረሻ ለፊልሙ ባለሙያዎችና ደጋፊዎች ከተሰጠው የምስክር ወረቀትና የአበባ ስጦታ በተጨማሪ ለሁለት ባለሙያዎች የክሪስታል ዋንጫና ሽልማት የተደረገ ሲሆን ሁለቱም ከፍቅረኞቻቸው ጋር በኩሩፍቱ ሪዞርት ለአንድ ቀን በነፃ እንዲዝናኑ የተበረከተላቸውን ስጦታ ከክብር እንግዳው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትያትር ጥበባት ተባባሪ ፕሮፌሰር በላይነህ አቡኔ ተቀብለዋል፡፡

Read 3280 times