የዛሬ ሳምንት ምሽት በጀርመን ባህል ተቋም ቀርቦ የነበረው ኪነጥበባዊ ዝግጅት በሕዝብ ጥያቄ ዛሬ ከቀኑ 11፡30 በኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር በድጋሚ ሊቀርብ እንደሆነ ተገለፀ፡፡ ፋቡላ የጥበባት ማህበር ከዘለስ የባህል ቡድን ጋር በሚያቀርቡት ዝግጅት፤ ወጣት ታዋቂ ገጣምያንና ሰዓሊያን ሥራዎቻቸውን በሙዚቃ ታጅበው እንደሚያቀርቡ የዝግጅቱ አስተባባሪ ኬር ማስታወቂያና ፕሮሞሽን ገልጿል፡፡ ለዝግጅቱ ኬር አድቨርታይዚንግ፣ ጐተ ኢንስቲትዩት፣ ጃፋር መፃሕፍት መደብር፣ ፕሮቴክ ፕሪንቲንግና አድቨርታይዚንግ እና ማርክ ማተሚያ ቤት ድጋፍ አድርገዋል፡፡