Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 08 October 2011 10:19

ሊያ በ”ብላክጎልድ” ከባንድራስ ጋር ትተውናለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ኢትዮጵያዊቷ ሞዴልና በጎ አድራጊ ሊያ ከበደ “ብላክ ጎልድ” በተሰኘው ፊልም ላይ ከአንቶኒዮ ባንድራስ ጋር እንደምትተውን ተገለፀ፡፡ ከሁለት ሳምንት በኋላ  በኳታር በሚደረግ በ”3ኛው ዶሃ ትሬቤካ” ፊልም ፌስቲቫል ላይ በሚመረቀው “ብላክ ጎልድ” ፊልም ላይ ሊያ ከበደ አይሻ የተባለች ባርያ ገፀ-ባህርይን ወክላ ትጫወታለች፡፡ ፊልሙ 55 ሚሊዮን ዶላር የፈጀ ሲሆን ቀረፃው በቱኒዚያና በኳታር እንደተከናወነ ታውቋል፡፡ ከ80 ዓመት በፊት ስለነበሩ ሁለት የአረብ ኢምሮች ሽኩቻ የሚተርከው “ብላክ ጎልድ”፤ በኳታር ያለውን የሲኒማ ስራ እንቅስቃሴ ያሟሙቃል ያለው ገልፍ ኒውስ፤ አምና “ዴዘርት ፍላወር”  በተሰኘው  ፊልም ላይ መሪ ተዋናይ ሆና የተደነቀችው ሊያ፤ በሙያው ስኬታማ እየሆነች መምጣቷን ገልጿል፡፡

Read 3259 times