ፊልሙ በቤት ሰራተኛነት በሚሰሩ 6 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ህይወት ላይ እንደሚያተኩር የገለፀችው ራሄል፤ በበቤይሩት ለአስር ዓመት ስትሰራ የታዘበችውን በፊልሟ ውስጥ ማካተቷን ተናግራለች፡፡ ፊልሙ በተለይ በሊባኖስ በቤት ሰራተኞች ህይወት ዙሪያ በይፋ ስለማይገለፁ አሳሳቢ ጉዳዮችም እንደሚያሳይ ገልፃለች፡፡
በአዲስ አበባ በፈረንሳይ ለጋሲዮን ተወልዳ ያደገችው ራሄል፤ “ቤይሩት” የተባለውን የፊልም ስክሪፕት ለማዘጋጀት ዘጠኝ ዓመት እንደወሰደባት፣ ቀረፃውንም በሁለት ዓመት እንዳጠናቀቀች ለ “ታድያስ” ተናግራለች፡፡