Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 08 October 2011 10:10

ኮሜድያን ክበበው ገዳ ይቅርታ ጠየቀ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ከ8 ዓመት በፊት የተሰራ የኮሜዲ ስራው እንደ አዲስ ስራ መውጣቱን የገለፀው ኮሜድያን ክበበው ገዳ፤ ሕዝቡ በእኔ ላይ ያለውን እምነት የሚሸረሽር ስለሆነ ሕዝቡን ይቅርታ እጠይቃለሁ አለ፡፡ ረቡዕ ጧት በሐርመኒ ሆቴል በሀበአብ ሚዲያና ኢንተርቴይመንት አማካይነት ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ ከ8 ዓመት በፊት በ45 ሺህ ብር የሸጥኩት ለዚያን ጊዜ የሚሆን ኮሜዲ ያኔ መውጣት ሲገባው አሁን መውጣቱ በአዲሱ ስራዬ ላይ ተጽዕኖ አሳድሯል ያለው ኮሜዲያኑ፣ አዲሱ ስራም በዚሁ ምክንያት አልወጣም ኤሌክትራ ሙዚቃ ቤት እኔን ሳያማክር በ1995 ዓ.ም. የገዛውን ስራዬን ለመሸጥ ሲነሳና አዲሱን ስራዬን ለመጠቀም ሲወስን በተመልካቹ ዘንድ ከሚፈጥረው ስሜትና ትርጉም አንጻር ሊጠነቀቅና እኔንም ሊያማክር፣ ቢያንስ ሊያሳውቀኝ ይገባ ነበር ብሏል፡፡ “ኤሌክትራ ቢያማክረኝ በአሮጌው ምትክ አሁን የስራዬን እድገት የሚገልጽ አዲስ ስራ እሰጠው ነበር” ሲል ተናግሯል፡፡ እስከ መቼ በኮሜዲያንነት እንደሚቀጥል የተጠየቀው ኮሜዲያን ክበበው ገዳ፤ ዕድሜ ልኩን ኮሜዲያን ሆኖ መቆየት እንደማይፈልግ ተናግሯል፡፡

Read 5774 times