Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

ለቤተሰቡ አራተኛ ልጅ ሲሆን በ1961 ዓ.ም በእንቁላል ፋብሪካ አካባቢ ነው የተወለደው፡፡ በምህንድስና በዲፕሎም ተመርቋል፡፡ በአቢሲኒያ ሥነ ጥበብ ትምህርት ቤት ስዕል ተምሯል፡፡ ምህንድስናና ስዕሉን ጨምሮ ፈረንሳይኛ ቋንቋ በማስተማር ራሱን ያስተዳድራል፡፡ ከወዳደቁ ነገሮች የሰራቸው በመቶ የሚቆጠሩ የፈጠራ  አሉት፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን አግራሞትን የሚፈጥሩ የተለያዩ ነገሮችን ሰብስቧል፡፡ የአዲስ አድማሱ ፀሃፊ ብርሃኑ ሰሙ የዚህ ታሪክ ባለቤት ከሆነው አቶ በዕደ በቀለ ጋር አዲሱ ገበያ በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ቆይታ
የወላጆችህ ሙያ ምንድነው?

አንደኛ የወጣ የአይዶል ተወዳዳሪ - ፈረሱ በራሱ ችሎታ ከመጀመሪያውም ይተማመን ነበር፡፡ ላቡን አንጠፍጥፎ ነው የዳንስ ብቃቱን ያዳበረው፡፡ በአይዶል የዳንስ ውድድሩ አንደኛ ወጥቶ 35ሺ ብር ሲሸለም በሰላሳ ሁለት ጥርሱ ሳቀ፡፡ ፈነጠዘ፡፡ ሆድ የባሰው፤ እሱ አንደኛ የወጣው ፈረስ እያለ ሁለተኛ የወጡት በክልላቸው የተሸለሙትን የገንዘብ መጠን ሲመለከት ነው፡፡ ለምን ተሸለሙ ብሎ መመቅኘቱ ግን አልነበረም፡፡

ጓድ ሌ ጓድ ሌኒን ኒን
George Gordon, Lord Byron
“If I should meet thee after long years,
How would I greet thee? In silence and tears” Lord Byron
የተከበራችሁ አንባብያን
ባለ ቅኔው George Gordon እንደ ፀሐፊ Romanticism የሚባለውን የስነጽሑፍ ዘርፍ የሚወክል፣ ሲሆን እንደ ግለሰብ ደግሞ በውርስ የመሳፍንት ዘር ስለሆኑ Lord Byron ይባላሉ፡፡

በራስ ተፈሪ መኮንን የተመሩት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት በ1916 ዓ.ም አውሮፓን በጐበኙበት አጋጣሚ በፈረንሳይ የተካሄደውን 8ተኛውን የኦሎምፒክ ውድድር የመመልከት እድል አግኝተው ነበር፡፡ ከ32 አመታት በኋላ በ1948 ዓ.ም በተካሄደው የሜልቦርን ኦሎምፒክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈችው ኢትዮጵያ በስፖርቱ አደባባይ ስምና የድል ታሪኳ ትጠራ ጀመረ፡፡በዚህ አላቆመም፡፡ በ1952 ዓ.ም በሮም ኦሎምፒክ ላይ የሚሳተፉ ስፖርተኞችን ለመምረጥ በአገር ውስጥ የተካሄዱት ፉክክሮች ተመልካቾችንና የጋዜጦችን ትኩረት የሚስቡ ነበሩ - በተለይ የቦክስ ግጥሚያዎች፡፡

የፓርቲዎች ፉክክር፣ የተቃውሞ ሰልፍ፤ የነፃ ፕሬስ እድገት፤ የዜጎች ነፃ ውይይት ተረት ሆነዋል?
ባለፉት አመታት ነፃነት እየጠበበ፣ የመንግስት አላስፈላጊ የቁጥጥር አይነቶች እየተበራከቱ፤ የሚያሳርፉት ጫና እየከረረ መምጣቱ፤ በእውን ኑሯችን ምን እንደሚመስልና ምን  እንደሚል ማወቅ ይከብዳል? ሁሌም ከፖለቲካው ድባብ ጋር የሚፈካውንና የሚጠወልገውን ኢኮኖሚ በማየትም፤ የነፃነት መጥበብን መገንዘብ ይቻላል፡፡
ለነገሩማ፤ ነፃነት ሰፋ  እያለ ሲሄድ፤ ነቃ ከሚለው ኢኮኖሚ ጋር ተዳምሮ ምን እንደሚመስልም ከነጣእሙ... በትንሹም ቢሆን አንዳንዶቻችን እናውቀዋለን፡፡ ለአጭር ጊዜ ቢሆንም፤ የኋላ ኋላ መጨረሻው ባያምርም በእውን አይተነዋል - ያኔ ከአምስት አመታት በፊት፡፡ የ1997 አም ምርጫ ማለቴ አይደለም፡፡

የቀድሞው የአሜሪካን አይዶል ዳኛና የሙዚቃ ፕሮዲውሰር ሲሞን ኮዌል ..ሌዲ ጋጋ ትደብራለች ማለቱን ዴይሊ ሚረር ዘገበ፡፡ ..ዘ ኤክስ ፋክተር.. በተባለ ፕሮግራሙ ስኬታማ እየሆነ የመጣው የ51 ዓመቱ ሲሞን ኮዌል፤ ሌዲ ጋጋ የዓለማችን ደባሪ ዘፋኝ ብሎ በተቸበት ንግግሩ ኬቲ ፔሪና ቢዮንሴም አይመቹኝም ሲል አጣጥሏል፡፡ ሲሞን ኮዌል የፖፕ ንግስቶቹን እውቀት የሌላቸው ብሏዋቸል፡፡

በቢልቦርድ የምርጥ አልበሞች ደረጃ ሰንጠረዥን ከለቀቀ ሁለት ሳምንቱ የሆነው የሌዲ አንትቤለም ..ኦውን ዘ ናይት.. አዲስ አልበም በምርጥ 200 አልበሞች ደረጃ መሪነቱን እንደያዘ ተገለፀ፡፡ በዓለም ዙሪያ 10 ሚሊዮን ቅጂ በመቸብቸብ የዓመቱን ከፍተኛ የአልበም ሽያጭ ያስመዘገበው የአዴሌ ..21.. አልበም ሁለተኛ ሲሆን ሰሞኑን 29 ዓመቱን የያዘው ሊል ዋይኔ የሰራው ..ዘ ካርተር 5.. ሦስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

ስለ ዋጋ ንረትና ስለ ኑሮ ውድነት ስናወራ ስንት አመታችን? መሬት በራሷ ዛቢያ እየተሽከረከረችና ፀሃይን እየዞረች፤ እኛም በዋጋ ንረት እንዝርት እየሾርን፤ በኑሮ ውድነት ምህዋር እየዞረብን አመታት ተቆጠሩ፡፡ ቢሆንም ግን፤ ልንለምደው የቻልን አልመሰለኝም፡፡ ነጋ ጠባ፤  ቅሬታና ስሞታ፤ ተቃውሞና አቤቱታ፤ ምክርና ውትወታ ... በአይነት በአይነቱ መደጋገማችንን ቀጥለናል - ክረምት ከበጋ የማይቋረጥ መዝሙር ሆኗል ማለት ይቻላል፡፡ አንዳንዴም፤ በጣም ከመደጋገሙ የተነሳ የመዝሙሩ ዜማ እየፈዘዘ ወደ አስቀያሚ እንጉርጉሮነት ይቀየርብናል፡፡ ባስ ሲልም ኡኡታ ሊመስል ምንም አይቀረውም፡፡

ሰነዶቼ ተሰርቀው በዊኪሊክስ ተሰራጩብኝ - የአሜሪካ መንግስት
ሰነዶቹ እውነተኛ ሰነድ መሆናቸው ያጠራጥራል - የኢቲቪ የህትመት ዳሰሳ
ኢቲቪ ከዊኪሊክስ ጋር ፀብ ለመግጠም ሲንደረደር ያየነው በሰሞኑ የህትመት ዳሰሳ ፕሮግራሙ ነው፡፡ ከፀቡ ጋር አብሮ ሲነሳ የነበረው ጉዳይ፤ ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ስለ ሱዳን መንግስትና ስለ ፕሬዚዳንት አልበሽር ..እንዲህና እንዲያ.. ተናግረዋል የሚል ሰነድ በዊኪሊክስ ዌብሳይት የመለቀቁ ጉዳይ ነው፡፡ በአሜሪካ ኤምባሲ ተዘጋጅቶ ለኤምባሲው ..የበላይ አካል.. (ማለትም ለአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት) የተላከው ሰነድ ምን ይላል? የሱዳን መንግስትን ወይም ፕሬዚዳንት አልበሽርን ከስልጣን አስወግዱ በማለት ጠ/ሚ መለስ ለአሜሪካ ባለስልጣናት ተናግረዋል ይላል ሰነዱ፡፡

ነገ በሚካሄደው 38ኛው የበርሊን ማራቶን የ38 ዓመቱ አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ  በማራቶን የመጀመሪያውን የሪኮርድ ሃትሪክ ሊሰራ እንደሚችል ተጠበቀ፡፡  ሰሞኑን በማራቶን ሪከርዷ ላይ ማስተካከያ የተደረገባት ፓውላ ራድክሊፍ ለመጀመርያ ግዜ በበርሊን ማራቶን ትሳተፋለች፡፡ ሁለቱ የዓለም የማራቶን ሪኮርድ ባለቤቶች ከ40ሺ በላይ ተወዳዳሪዎች በሚሮጡበት የበርሊን ማራቶን ተሳታፊ መሆናቸው ለውድድሩ ያለውን ዓለም አቀፍ ትኩረት ጨምሮታል፡፡ አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ በበርሊን ማራቶን ሲሳተፍ ዘንድሮ ለ5ኛ ጊዜ ሲሆን አስቀድሞ በተሳተፈባቸው ውድድሮች አራቱንም ከማሸነፉም በላይ ሁለቱን ያሸነፈው ለ2 ጊዜያት የማራቶን አዲስ ሪኮርዶችን አስመዝግቦ መሆኑ ይታወሳል፡፡