Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

በ2003 ዓ.ም ከግል ህይወቴ ስጀምር የመኖሪያ ቤቴ ጉዳይ ነው የሚመጣው፡፡ ወይ ቤቱ ይታደስ ወይ ተተኪ ሌላ ቤት ይሰጠኛል የሚል ተስፋ ነበረኝ፡፡ በ2003 ክረምት ቤቱ እየፈረሰ ነው፤ አሁን ያለሁበት አንዱ ክፍል እስከ መኝታ ቤቴ ድረስ ያፈሳል፤ ሌሊት ሳልተኛ ነው የማድረው፡፡ በግሌ ያጣሁት ይሄን ነው፡፡ በፖለቲካው ዘርፍ በድርጅቶቻችን በኩል አንዳንድ ነገሮችን ብንሰራም የሚፈለገውን ያህል አልተንቀሳቀስንም፡፡ በውስጥ መደራጀትና መገማገም ቢኖርም ከህዝብ ጋር ለመወያየትና ለመከራከር እድል አላገኘንም፡፡

አቶ ተስፋዬ ታሪኩ፤ የመኢአድ ዋና ፀሐፊ
4.5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ህዝብ ተጨማሪ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልገው በመንግስት ቢነገርም፤ ቁጥሩ ይህ ብቻ ነው የሚል እምነት የለኝም፡፡ አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ በብልሹ የኢኮኖሚ ፖሊሲ፣ በሙስናና በአላስፈላጊ ወጪዎች ለችግር ተዳርጓል፡፡ ተጨማሪ የምግብ እርዳታ የሚባለው መጀመሪያ ምን ተገኝቶ፣ ምን ተበልቶ ነው? አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ የእለት ጉርስ አጥቶ፤ በሃገሪቱ ታሪክ እጅግ የከፋ ድህነት ላይ ደርሷል፡፡

አቶ ተመስገን ዘውዴ፤ የአንድነት የፋይናንስ ጉዳይ ኃላፊ
ዜጎች ለረሃብ የሚጋለጡት፣ በአጋጣሚና በአንድ ሌሊት በተፈጠረ ችግር ሰበብ አይደለም፡፡ ባለፈው ዓመት የተከሰተው ርሃብ ከዘንድሮው ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ ዘላቂ መፍትሔ ሊያገኝ የሚገባው ነገር ነው፡፡ ድርቅን ለመቋቋምና ወገኖቻችን በረሃብ አደጋ ላይ እንዳይወድቁ ለማድረግ መንግስት ዘላቂ መፍትሔ የማመቻቸት ኃላፊነት አለበት፡፡ ያለፈው ዓመት ሁለት ሚሊዮን ህዝብ ተጨማሪ የምግብ እርዳታ እንደ¸ÃSfLgW ተነግሮ ነበር፡፡ ዘንድሮ ቁጥሩ ጨምሯል፤ ወደ 4.5 ሚሊዮን፡፡ ከዚህም በተጨማሪ 8 ሚሊዮን ህዝብ በሴፍቲ ኔት እርዳታ እየታቀፈ እንደሆነ ተነግሮናል፡፡ ዘላቂ መፍትሄ ያስፈልጋል፡፡

አቶ ሙሼ የኢዴፓ ሊቀመንበር
ድርቅ የተፈጥሮ ጉዳይ ነው፤ ይሁን እንጂ ድርቅ በተከሰተበት አገር ሁሉ ረሃብ ይፈጠራል ማለት አይደለም፡፡ በቂ ክትትልና ዝግጅት ቢኖር ኖሮ፤ ድርቅ የዜጎችን ህይወት እንዳይፈታተን ማድረግ ይቻላል፡፡ በአገራችን ግን፤ በድርቅ ምክንያት ብዙ ወገኖቻችን የረሃብ ተጠቂ ሆነዋል፡፡ መንግስት ከመናገሩ በፊት፤ ከተለያዩ የውጭ መገናኛ ብዙሃን ድርቅና ረሃብ እንደተከሰተ ስንሰማ ቆይተናል፡፡ ይህም፤ በመንግስት በኩል ትኩረት ሳይሰጠው እንደቆየ የሚያሳይ ነው፡፡ የችግሩ ምንነት ቀድሞ እንዲታወቅ በማድረግ፤ ችግር ሳይባባስ መፍታት ይገባ ነበር፡፡

የአሜሪካኑ የጠፈር ምርምር ተቋም ናሳ መረጃዎችን እየሰበሰበ በማቀበል በዘርፉ የሚደረገውን የምርምር ሥራ እንዲያግዝ ከወራቶች በፊት ወደ ዓለም አቀፉ የህዋ ጣቢያ ልኮት የነበረውን ሮቦት ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲነሳ ማድረጉን አሶሺየትድ ፕሬስ ዘገበ፡፡ የስነ ፈለክ ተመራማሪዎችን የሚያግዝ ልዩ ሮቦት እንደሆነ የተነገረለት ..ሮቦናውት.. ምድር ላይ ከሚገኘው የመቆጣጠሪያ ማዕከል በተላለፉለት ተእዛዝ መሠረት ሲስተሙ እንዲበራ ከተደረገ በኋላ ስላለበት ሁኔታ አንዳንድ መልእክቶችን እንደላከ የተገለ ሲሆን ነገሩ በሮቦት ቴክኖሎጂው ዘርፍ የታየ ትልቅ ስኬት ነውም ተብሏል፡፡ እንደ ዓይን የሚያገለግሉት እና መረጃዎችን የሚቃርምባቸው ካሜራዎች ያሉት ይህ ጠፈርተኛ ሮቦት ወደ ምድር ከላካቸው መረጃዎች መካከል ደግሞ በህዋ ጣቢያው ላይ የሚገኘውን የአሜሪካን ቤተ-ሙከራ የሚያሳይ ምስል እንደሚገኝበት ለማወቅ ተችሏል፡፡

የብላክቤሪ ሞባይል ስልክ አምራች ..ሪሰርች ኢን ሞሽን.. (Research in Motion/RIM) በቅርቡ የራሱን የሙዚቃ አቅርቦት ለተጠቃሚዎቹ ማድረስ ሊጀምር እንደሆነ ዴሊሜል አስታወቀ፡፡ ..ብላክቤሪ ሜሴንጀር.. ወይም በአጭሩ “BBM” በመባል የሚታወቀውን የሞባይል ኔትዎርኩን ሲያሻሽል የቆየው ኩባንያው እንደ አፕል እና ጉግል አንድሮይድ (ኦፐሬቴንግ ሲስተም) ካሉ ተቀናቃኞቹ እኩል ለመራመድ የሚያስችሉትን አንዳንድ ማሻሻያዎች በማድረግ ላይ የሚገኝ ሲሆን አዲስ ለሚጀምረው የሙዚቃ ስትሪሜንግ አገልግሎትም እንደ ሶኒ ሚዩዚክ እና ዋርነር ሚውዚክ ግሩፕ ካሉ ታላላቅ የሙዚቃ እንዱስትሪዎች ጋር ድርድር እያደረገ እንደሆነ ታውቋል፡፡

ስራችንን የሚያቀላጥፍልን የኮምፒዩተር ቴክኖሎጂ በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ
ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ አገራት ከቴክኖሎጂው ጋር አብረው በመራመድ በራሳቸው ፊደል ለመጻፍ የሚችሉበትን የኮምፒዩተር ሶፍትዌር ማበጀት ከጀመሩ ቆየት ብለዋል፡፡ በአገራችንም እንደ ..ፓወር ግዕዝ.. እና ቪዥዋል ግዕዝ.. ያሉ የአማርኛ መጻፊያ ሶፍትዌሮች ተሰርተው በስፋት ጥቅም ላይ የዋሉ ሲሆን የአገርኛ ቁጥሮች መጻፊያ እና የቃላት ወይም የፊደላት መጠን ማስተካከያዎችም አሉ፡፡ በቃላት አጻጻፍ ዙሪያ የሚታዩ የፊደላት ግድፈቶችን ለማስተካከል የሚያግዘን የቃላት ማረሚያ ግን ይጐድለናል፡፡

በዓለማችን የተንቀሳቃሽ ስልክ ስርጭት በ2016 እ.ኤ.አ መቶ በመቶ እንደሚደርስና የሞባይል ስልክ አገልግሎት ማግኘት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን እንደሚችል ተገለ፡፡ ..ሰንዴይ ሞርኒንግ ሄራልድ.. ጋዜጣ ያወጣው ዘገባ እንደ የተንቀሳቃሽ ስልክ ስርጭት ሽፋን ከአምስት አመት በኋላ በዓለም አቀፍ ደረጃ መቶ በመቶ የሚሆን ሲሆይ ይሄም ማለት እያንዳንዱ ሰውም የሞባይል ተጠቃሚ ይሆናል እንደማለት ነው፡፡

ብዙ ወላጆች የልጆቻቸውን ነገረ ስራ ለማየትና ለመቆጣጠር እንደ ..ፌስቡክ.. ያሉ የማህበራዊ ግንኙነት ማቀላጠፊያ ድረ-ገጾችን እንደሚጠቀሙ በቅርቡ የተደረገ ጥናት አመለከተ፡፡ በየትኛውም የዓለማችን ክፍል ከሚገኝ ሰው ጋር በኢንተርኔት በቀጥታ ጓደኝነት መመስረትና መወያየት በሚቻልበት በዚህ የዲጅታል ዘመን የልጆች ማህበራዊ ትስስር በመኖሪያ ቤት አካባቢ እና በትምህርት ቤት ውስጥ ብቻ የማይወሰን ሲሆን አብዛኛዎቹ አፍላ ወጣቶች የማህበራዊ ግንኙነት በሚደረግባቸው የኢንተርኔት መድረኮች ውስጥ እጅግ በጣም በርካታ ጓደኞች እንዳሏቸው ይነገራል፡፡

Sunday, 24 July 2011 07:39

|3D´ ሞባይል ስልክ መጣ

ምስሎችን በእውኑ እንደምናያቸው አድርገው የሚያሳዩን 3D´ ቴሌቪዥኖች ተሰርተው ለመጀመሪያ ጊዜ ገበያ ላይ ከወጡ ከአንድ ዓመት በኋላ ..ኤልጂ.. የመጀመሪያውን3D´ ሞባይል ስልክ ይዞ ብቅ ብሏል፡፡ ነገሮችን ልክ በውኑ እንደምናያቸው ከሦስት አቅጣጫ መመልከት የምንችልብት 3D´ ቴሌቪዥን ሲነሳ ምስሉን ለመመልከት ማድረግ ያለብን መነጽር እንዳለ ይታወቃል፡፡