Administrator

Administrator

“The power of Negative Thinking” የተሰኘው የስነልቦና መጽሐፍ “የአሉታዊ አስተሳሰብ ልዩ ሃይል” በሚል ርዕስ በአሸናፊ ሰብስቤና በእሩቅነህ አደመ ወደ አማርኛ ተተርጉሞ ለገበያ ቀረበ፡፡
“ለህይወት ወይም ለመኖር ከውስጥህም ሆነ ከውጭ ወይም ለሁለቱም ምንም ዓይነት ዋስትና ሳትሰጥ ስትቀር መኖር ወይም ህይወት በራሱ በመከራ፣ በስቃይ፣ በሀዘን፣ በፍርሃትና ባልተጠበቁ ክስተቶች የተሞላች ትሆናለች” ይላል - መፅሃፉ። በ183 ገፆች የተቀነበበው ይሄው መጽሐፍ፤ በ11 ምዕራፎች ተከፋፍሏል፡፡ “የአሉታዊ አስተሳሰብ ልዩ ሃይል” በ50 ብር ከ65 እየተሸጠ ነው፡፡

 የኢትዮጵያ ሴት ደራሲያን ማህበር ከኢትዮጵያ ባህል ማዕከል ጋር በመተባበር ባህላዊ ህክምናንና አገር በቀል ዕውቀቶችን በተመለከተ የተለያዩ መፃሕፍት የፃፉትን ደራሲ በቀለች ቶላን የሚዘክር ፕሮግራም ባለፈው ረቡዕ በኢትዮጵያ ባህል ማዕከል አዳራሽ ያካሄደ ሲሆን በስራዎቻቸው ላይ የመነሻ ጽሑፍ ቀርቦም ውይይት ተካሂዷል፡፡
ደራሲ በቀለች ቶላ የሴት ደራሲያን ማህበር አባል እንደሆኑ ታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ሴት ደራሲያን ማህበር ከኢትዮጵያባህል ማዕከል ጋር በመተባበር ባህላዊ ህክምናንና አገርበቀል ዕውቀቶችን በተመለከተ የተለያዩ መፃሕፍትየፃፉትን ደራሲ በቀለች ቶላን የሚዘክር ፕሮግራምባለፈው ረቡዕ በኢትዮጵያ ባህል ማዕከል አዳራሽ ያካሄደ ሲሆን በስራዎቻቸው ላይ የመነሻ ጽሑፍ ቀርቦም ውይይት ተካሂዷል፡፡ደራሲ በቀለች ቶላ የሴት ደራሲያን ማህበር አባል
እንደሆኑ ታውቋል፡፡

Saturday, 27 June 2015 09:41

የኪነት ጥግ

• ቤተሰባችን በጣም ድሃ ስለነበር እኔን
የወለደችኝ ጐረቤታችን ናት፡፡
ሊ ትሬቪኖ
• የአይጦች ውድድር ችግሩ…ብታሸንፍ እንኳ
ያው አይጥ ነህ፡፡
ሊሊቶምሊን
• በውሃ ላይ ብራመድ ኖሮ፣ ሰዎች መዋኘት
አይችልም ይሉኝ ነበር፡፡
ጆን ተርነር
• ስለእኔ የማነበውን አምኜ ብቀበል ኖሮ እኔም
ደፋርነቴን እጠላው ነበር፡፡
ዛሳ ዛሳ ጋቦር
• እውነቱ ምንድነው…በ30 ዓመታት ውስጥ
30 ፊልሞችን ሰርቻለሁ፡፡ ለ30 ዓመታትም
ሌሎችም ተጨማሪ ፊልሞችን ባለመስራቴ
ስተች ኖሬአለሁ፡፡
ደስቲን ሆፍማን
• በውብ ነገሮች መከበብ በመፈለጌ ሰዎች
“እማ ዝራው ናት!” ይሉኛል፡፡ ግን እስቲ
ንገሩኝ ማነው በዝባዝንኬ (ነገሮች) መከበብ
የሚፈልገው?
ኢሜልዳ ማርቆስ
• የዜና ዕረፍቴ ዘገባ በእጅጉ ተጋንኗል፡፡
ማርክ ትዌይን (ዜና ዕረፍቱ በጋዜጣ መዘገቡን
ሲሰማ የመለሰው
• ሥራዬን ስለወደዳችሁት የእናንተ ዕዳ አለብኝ
ማለት አይደለም፡፡
ቦብ ዳይላን
• ሆሊውድ ለመሳሳም 50ሺ ዶላር፣ ለነፍስህ
50 ሳንቲም የሚከፍሉህ ሥፍራ ነው፡፡
ማርሊን ሞንሮ
• በትያትር ዓለም የሚቆጨኝ ፊት ለፊት
ተቀምጬ ራሴን ለመመልከት አለመቻሌ
ብቻ ነው፡፡
ጆን ባሪሞር
• አንዳንዴ በጣም ጣፋጭ ከመሆኔ የተነሳ
እኔም ራሴ ሁኔታውን መቆጣጠር ይሳነኛል፡፡
ጁሊ አንድሪውስ
• ወሲብ እግዚአብሔር በሰዎች ላይ የፈጠረው
ቀልድ ነው፡፡
ቤቲ ዴቪስ
• በመድረክ ላይ ከ25ሺ ሰዎች ጋር ፍቅር
እሰራለሁ፡፡ ከዚያም ብቻዬን ወደ ቤቴ
እሄዳለሁ፡፡
ጃኒስ ጆፕሊን
• በኦሎምፒክ ሁለተኛ መውጣት ብር
ያስገኝልሃል፡፡ በፖለቲካ ሁለተኛ መውጣት
መረሳትን ያጐናፅፍሃል፡፡
ሪቻርድ ኤ.ም ኒክሰን

Saturday, 27 June 2015 09:40

የፍቅር ጥግ

• ባል የቤተሰቡ ራስ ሲሆን ሚስት ደግሞ
ራስን የሚያሽከረክረው አንገት ናት፡፡
ያልታወቀ ፀሐፊ
• ራስሽን ከመሆን የሚያደናቅፍ ግንኙነትን
አሜን ብለሽ አትቀበይ፡፡
ኦፕራ ዊንፍሬይ
• ወንዶች ሴቶችን የሚያገቡት ጨርሶ
አይለወጡም በሚል ተስፋ ነው፡፡ ሴቶች
ወንዶችን የሚያገቡት ይለወጣሉ በሚል
ተስፋ ነው፡፡ ሁለቱም ግን ማዘናቸው
አይቀርም፡፡
አልበርት አነስታይን
• በካሜራ ፊት ለበርካታ ጊዜያት ባልና ሚስት
ሆናችሁ ከተጫወታችሁ በኋላ ከካሜራ
ውጭ ባልና ሚስት ቀላል ነው፡፡
ኤሚ ያስቤክ
• ትዳር ወንድ ልጅ ሚስቱ እንደምትፈልገው
እንዲያደርግ ከሚፈቅዱ ጥቂት ተቋማት
አንዱ ነው፡፡
ሚልተን በርሌ
• ግሩም ትዳር የሚባለው እንከን የለሽ ጥንዶች
ሲገናኙ አይደለም፤ ፍፁም ያልሆኑ ጥንዶች
ከእነልዩነታቸው መኖርን ሲያጣጥሙ ነው፡፡
ዴቭ ሜዩሬር
• እውነታህ ከህልምህ የተሻለ ሆኖ እንቅልፍ
መተኛት ሲያቅትህ፣ ያኔ ፍቅር እንደያዘህ
ትገነዘባለህ፡፡
ዶ/ር ሴዩስ
• በትዳር ውስጥ ደስታን ማግኘት ሙሉ
በሙሉ የዕድል ጉዳይ ነው፡፡
Pride & Prejudice
• ሚስትህ እንድታዳምጥህ ከፈለግህ ከሌላ
ሴት ጋር አውራ፡፡ ያኔ ሁሉነገሯ ጆሮ
ይሆናል፡፡
ሲግመንድ ፍሩድ
• ቦርሳዬን ስመለከት ባዶ ሆነብኝ፡፡ ኪሶቼንም
ብፈትሽ ባዶ ሆኑብኝ፡፡ ልቤን ስመለከት ግን
አንቺን አገኘሁሽ፡፡ ያን ጊዜ ነበር ሃብታም
መሆኔን የተገነዘብኩት፡፡
ያልታወቀ ፀሐፊ
• ፍቅር አ ንድ ረ ዥም ጣ ፋጭ ህ ልም ሲ ሆን
ትዳር ከእንቅልፍ የመቀስቀሻ ደወል ነው፡፡
ምንጩ ያልታወቀ
• ስኬታማ ወንድ የሚባለው ሚስቱ ማጥፋት
ከምትችለው በላይ ገንዘብ የሚሰራ ሲሆን
ስኬታማ ሴት እንደዚያ ዓይነቱን ወንድ
ማግኘት የቻለች ናት፡፡
ላና ተርነር
• ትዳር ልክ ወደ ጦርነት እንደመሄድ ያለ
ጀብዱ ነው፡፡
ጂ. ኬ. ቼስቴርቶን
• ፍቅር፤ በትዳር ሊድን የሚችል ጊዜያዊ
እብደት ነው፡፡
አምብሮሴ ቢርስ
• ለደስተኛ የትዳር ህይወት ወንዶች ሁለት
ነገሮችን ልብ ማለት አለባቸው፡- ሲያጠፉ
በፍጥነት መናዘዝን ፣ ትክክል ሲሆኑ ዝም

በቀድሞ አጠራር በሲዳሞ ክ/ሀገር በቡሌ ወረዳ የተወለዱት ደራሲና ጋዜጠኛ ሽፈራው መንገሻ ባደረባቸው ህመም በአገር ውስጥና በውጭ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ባለፈው ሰኔ 12 በ75 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩ ሲሆን በነጋታው የቀብር ሥነስርዓታቸው በቅዱስ ዮሴፍ ቤ/ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡
ለረዥም ዓመታት በተለያዩ የመንግስት መ/ቤቶች ያገለገሉት አቶ ሽፈራው፤ በማስታወቂያ ሚ/ር ፕሬስ መምሪያ የሳምንታዊው “የዛሬይቱ ኢትዮጵያ” ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ በመሆን ለብዙ ጊዜያት ማገልገላቸው ተገልጿል፡፡
ደራሲና ጋዜጠኛው የተለያዩ መፃህፍትን ለንባብ ያበቁ ሲሆን ከእነሱም መካከል ታሪክ ጠቀሶቹ “ህግ ያልገዛውን ነፃነት ሃይል ይገዛዋል” እና “የኢትዮጵያ የታሪክ ጉዞ እስከቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ ዘመነ መንግስት” የሚሉት ይገኙባቸዋል፡፡
“የኦሾዊት ምስጢር” የተሰኘው የትርጉም ሥራና የፊልም ባለሙያው የበቀለ ወያ ታሪክ የሆነው “የትውልድ አርአያ”ም ከሚታወቁባቸው ሥራዎቻቸው መካከል ይጠቀሳሉ፡፡ ደራሲና ጋዜጠኛ ሽፈራው መንገሻ የ3 ልጆች አባት ነበሩ፡፡

Saturday, 27 June 2015 09:27

የግጥም ጥግ

ችጋር
አላፊ፣ አግዳሚው - ወጪና ወራጁ
የሰልፍ ተክተልታይ - ወደ ‘ሚሻው ሂያጁ
ነውና ምሳሌው፡-
እሾህ ለአጣሪው -ወንጀል ለፈራጁ፡-
ምስለተሰንካዮች - የሚግበሰበሱ
እንደ ምንጭ ሲፈልቁ - እንደ ‘ኋ ሲፈሱ
ቀለብ ሰፋሪያቸው ከቶ ማነው እሱ?
ሸክሎች ተሰብስበው አፈር እየላሱ፡፡
አንድስ‘ንኳ
በመስቀል ውዥንብር - በቁርባን ቱማታ
በመሃይም ቦታ፡-
የባልቴቶች ጌታ፡-
በግዝት ቅብጥርጥር፡-
በፍታት ድንግርግር፡-
ሚስጥረ ሥላሴ፤
ግዕዝ ወቅዳሴ፡-
በሰንበቴ ጉርሻ፤
በሙት ዓመት ቁርሻ
ባለትልቅ ድርሻ፡-
ከበሮ አስደግፈው አነጣጥረው በልክ፤
ወረብ አስተማሯት ውሽማዬን ብልክ
በመቋሚያ ሽብርክ፤ ቅዳሴ የ’ንብርክ፡፡
በካሣሁን ወ/ዮሐንስ
ከአማርኛ የግጥም መድብል የተወሰደ

Saturday, 27 June 2015 09:24

የፀሐፍት ጥግ

ረመዳን ወደ ገፅ 19 ዞሯል
• የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ድረገጽን ባለፈው ዓመት በአጠቃላይ ከ80
ሚሊዮን በላይ ተመልካቾች ጎብኝተውታል፡፡
• ዘንድሮ ከጥር ወር እስከ መጋቢት አጋማሽ ባሉት ጊዜያት ብቻ ከ20
ሚሊዮን በላይ ጎብኚዎች የተመለከቱት ሲሆን በየወሩ በአማካይ
ከ6 ሚሊዮን በላይ ተመልካቾች አሉት፡፡
• እስካሁን የተጠቀሱት መረጃዎች የአገር ውስጥ ጎብኚዎችን ብቻ
የሚመለከቱ ሲሆን በተመሳሳይ ሁኔታ በአሜሪካ፣ በአውሮፓ፣
በአረብ አገራትና በሌሎች ዓለማትም በርካታ ሚሊዮን
ኢትዮጵያውያን የሚጎበኙት ተወዳጅ ድረ-ገጽ ነው!
• ሦስት ዓለም አቀፍ ተቋማት በኢትዮጵያ የሚገኙ የዜና ድረ-ገጾችን
በተለያዩ መስፈርቶች አወዳድረው፣ የአዲስ አድማስ ድረ-ገጽን
ከቀዳሚዎቹ ሦስት ድረገጾች አንዱ መሆኑን መስክረውለታል፡፡
• በአሁኑ ሰዓት ትላልቅ የሪል እስቴት ኩባንያዎች፣ዓለም አቀፍ
የሞባይል ስልክ አምራቾች፣ታዋቂ የለስላሳ መጠጥ ፋብሪካዎችና
ሌሎችም---- በድረ ገጻችን ላይ እያስተዋወቁ ይገኛሉ፡፡
እርስዎስ? ለእርስዎም ቦታ አለን!!
ድረ ገጻችንን ይጎብኙት፡ www.addisadmass.news.com
ለተጨማሪ መረጃ፡- 0911-936787
ድርጅትዎን፣ ምርትዎንና አገልግሎትዎን
በርካታ ሚሊዮኖች በሚጎበኙት
ድረ-ገጻችን ያስተዋውቁ!
• አርታኢ እና አሳታሚ በሚሉት መጠሪያዎች
መካከል ያለውን ልዩነት ለማወቅ ከፈለግህ:-
አርታኢ ረቂቅ ጽሑፎችን የሚመርጥ ሲሆን
አሳታሚ አርታኢዎችን የሚመርጥ ነው፡፡
ማክስ ሹስተር
• መጽሐፍ በኪስ ውስጥ እንደሚይዙት
የአትክልት ሥፍራ ነው፡፡
የአረቦች አባባል
• ሥነፅሁፍን በራሱ እንደ ግብ አልቆጥረውም።
አንድ ነገር የማስተላለፊያ መንገድ ነው፡፡
ኢሳቤል አሌንዴ
• ፍፅምናን ብጠብቅ ኖሮ አንዲትም ቃል
ባልፃፍኩ ነበር፡፡
ማርጋሬት አትውድ
• ረቂቅ ሃሳብ ማስፈር፣ ጥናት ማድረግ፣
ስለምትሰራው ነገር ከሰዎች ጋር ማውራት
- ከእነዚህ ውስጥ አንዳቸውም ከመፃፍ
አይመደቡም፡፡ መፃፍ መፃፍ ነው፡፡
ኢ. ኤል ዶክቶሮው
• ለመኖር ታሪኮችን መተረክ አለብህ፡፡
ዩምቤርቶ ኢኮ
• ስድስቱ የመፃፍ ወርቃማ ህጐች፡- ማንበብ፣
ማንበብ፣ ማንበብ እና መፃፍ፣ መፃፍ፣ …
መፃፍ ናቸው፡፡
ኧርነስት ጌይንስ
• ፀሐፊነት በቋንቋ መስከርን ይጠይቃል፡፡
ጂም ሃሪሰን
• ለወጣት ፀሐፍት ምክር መለገስ ቢኖርብኝ፣
ስለ ጽሑፍ ወይም ስለራሳቸው የሚያወሩ
ፀሐፊዎችን አትስሟቸው እላቸዋለሁ፡፡
ሊሊያን ሄልማን
• በኪነጥበብ ቁጥብነት ሁልጊዜ ውበት ነው፡፡
ሔነሪ ጄምስ
• ማንነትህን እስክታውቅ ድረስ መፃፍ
አትችልም፡፡
ሳልማን ሩሽዲ
• በጥያቄ እጀምራለሁ፡፡ ከዚያም መልስ
ለመስጠት እሞክራለሁ፡፡
ሜሪ ሊ ሴትል
• ባልሆነ ቦታ ኮማ መደንቀር ያስጠላኛል፡፡
ዋልት ዊትማን
• ስለራስህ እውነቱን ካልተናገርክ ስለሌሎች
ሰዎች እውነቱን ልትናገር አትችልም፡፡
ቨርጂኒያ ውልፍ
• በውስጥህ ያለ ያልተነገረ ታሪክን ከመሸከም
የበለጠ ትልቅ ስቃይ የለም፡፡
ማያ አንጄሎ

“የአቶ አንዳርጋቸው አያያዝ የአገራቱን ግንኙነት አደጋ ላይ የሚጥል ነው”
- የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍሊፕ ሃሞንድ

   የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፊሊፕ ሃሞንድ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በኢትዮጵያ በእስር ላይ የሚገኙት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የሚገኙበት ሁኔታና አያያዛቸው፣ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት አደጋ ላይ የሚጥል ነው ሲሉ ለኢትዮጵያ መንግስት ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን ዘ ጋርዲያን ዘገበ፡፡
አቶ አንዳርጋቸው የቆንስላ ድጋፍ ማግኘት በማይችሉበት ወይም ይግባኝ የመጠየቅ መብት ባላገኙበት ሁኔታ በግልጽ በማይታወቅ ስፍራ ከሰው ተነጥለው ለብቻቸው መታሰራቸውን ያወገዙት ውጭ ጉዳይ ሚነስትሩ፣ የኢትዮጵያ መንግስት በግለሰቡ ጉዳይ ላይ አፋጣኝ ማሻሻል እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፊሊፕ ሃሞንድ ባለፈው ረቡዕ ከኢትዮጵያው አቻቸው ከዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ጋር በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ ዙሪያ በስልክ ባደረጉት ውይይት፣ ግለሰቡ እስሩን በህግ ለመቃዎም ዕድል ባላገኙበት ሁኔታ ከሰው ተነጥለው ላለፈው አንድ አመት በእስር ላይ መቆየታቸው ያሳስበኛል ብለዋል፡፡
አቶ አንዳርጋቸውን በየጊዜው ለመጎብኘት የምንችልበት ሁኔታ እንዲመቻችልን ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም፣ የኢትዮጵያ መንግስት ቃል ከመግባት ባሻገር ተገቢ ምላሽ ሊሰጠን አለመቻሉ አሳዝኖኛል ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፣ የኢትዮጵያ መንግስት በተደጋጋሚ ላቀረብነው ጥያቄ ምላሽ አለመስጠቱ ተቀባይነት የለውም፣ በግለሰቡ ጉዳይ ዙሪያ ይህ ነው የሚባል መሻሻል አለመታየቱም ትልቅ ስፍራ የምንሰጠውን የሁለቱ አገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት አደጋ ላይ የሚጥል ነው ሲሉ ለዶ/ር ቴዎድሮስ መናገራቸውንም ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ለአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እና ለቤተሰባቸው የሚያደርገውን
የቆንስላ ድጋፍ ለወደፊትም እንደሚቀጥል ሃሞንድ ተናግረዋል፡፡የአቶ አንዳርጋቸው ጠበቃ ቤን ኩፐር በበኩላቸው፤ የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ግለሰቡ ከሰው ተነጥለው መታሰራቸውንና መጎብኘት እንዳለባቸው በማረጋገጥ እስሩን መቃወሙ አስደስቶናል፣ ይሄም ሆኖ የእንግሊዝ መንግስት አቶ አንዳርጋቸው ከእስር ተለቀው ወደ እንግሊዝ በመመለስ ከቤተሰቦቻቸው ጋር የሚገናኙበትን ሁኔታ እንዲያመቻችልን እንጠይቃለን ማለታቸውንም ዘገባው ጠቁሟል፡፡ የተመድ የስቃይ ጉዳዮች ምርመራ ልዩ ባለሙያ ጁዋን ሜንዴዝ በበኩላቸው፤ የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌን አያያዝ በተመለከተ ምርመራ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ
ለሁለቱም አገራት መንግስታት ማስታወቃቸውን ጋዜጣው ጠቁሟል፡፡

 ህጋዊ መታወቂያ ወይም የጉዞ ሰነድ አልያዙም ተብሏል
- የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአ/አ ስንነሳ ህጋዊ ሰነድ ነበራቸው ብሏል

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአየርላንድ ርዕሰ መዲና ደብሊን በኩል ወደ አሜሪካ ሎሳንጀለስ የጀመረውን አዲስ በረራ ለማስመረቅ ባለፈው ቅዳሜ ከአዲስ አበባ በመነሳት ባደረገው ጉዞ፣ ተሳታፊ የነበሩ 7 ኢትዮጵያውያን መንገደኞች፣ አውሮፕላኑ ደብሊን አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ሲያርፍ ወደ ኢሚግሬሽን ክፍሉ አምርተው ጥገኝነት መጠየቃቸውን አይሪሽ ኢንዲፔንደንት ትናንት ዘገበ፡፡ሁለት ህጻናትን ጨምሮ ጥገኝነት የጠየቁት 7 መንገደኞች በአየር ማረፊያ ጣቢያው ሲደርሱ ምንም አይነት መታወቂያ ወይም የጉዞ ሰነዶችን አልያዙም ነበር ያለው ዘገባው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቃል አቀባይ ግን፣ በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች በሙሉ ከአዲስ አበባ ሲነሱ ህጋዊ ሰነዶችን ይዘው ነበር፣ ስለ ጥገኝነት ጠያቂዎቹ የግል ጉዳይ ግን አስተያየት መስጠት አንፈልግም ብለዋል፡፡
አየር መንገዱ ላለፉት ከ40 በላይ አመታት ወደ አውሮፓ አገራት በረራ ሲያደርግ መቆየቱን ያስታወሱት ቃል አቀባይዋ፣ የምናጓጉዘው የተሟላ ህጋዊ የጉዞ ሰነድና ተገቢ ቪዛ ያላቸውን መንገደኞች ብቻ ነው ሲሉ መናገራቸውንም ዘገባው ገልጧል፡፡አንድ የአገሪቱ የህግ ክፍል ቃል አቀባይም የተለያዩ አገራት መንገደኞች በደብሊን አየር ማረፊያ ጣቢያ ሲደርሱ ጥገኝነት መጠየቃቸው የተለመደ የዘወትር ክስተት ነው፣ ባለፈው አመት ብቻ 221 መንገደኞች ለትራንዚት አርፈው ጥገኝነት ጠይቀዋል ብለዋል፡፡