Administrator

Administrator

 እናት የማስታወቂያ ድርጅት ከጀመርን የባህል ማዕከል (ጎተ) ጋር በመተባበር ነገ ከቀኑ 8፡00 በወመዘክር አዳራሽ ‹‹መስቀል አደባባይ›› በተሰኘው የግጥም መድበል ላይ ውይይት ያካሄዳል፡፡ መድበሉ የተለያዩ ወጣት ገጣሚያን የግጥም ሥራዎች ስብስብ ነው ተብሏል፡፡ ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ መሆናቸውን የጠቆመው የውይይት አዘጋጁ፤ ፍላጎት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ ጋብዟል፡፡

 “ስደት የሚለው ቃል በእርስዎ ምን ትርጉም አለው? አንድ ቀን እሰደዳለሁ ብለው ያስባሉ?” በሚሉና ሌሎች
ስለስደት የተነሱ ጥያቄዎች ላይ በዓለም ያሉ ከ40 በላይ ደራሲያንና ምሁራን የሰጧቸው መልሶች የተካተቱበት
የፖስተር ኤግዚቢሽን፣ ነገ በጀርመን የባህል ማዕከል (ጎተ) ከረፋዱ 4 ሰዓት ጀምሮ ይከፈታል፡፡
   በመክፈቻው ሥነ-ስርዓት ላይ ደራሲያን፣ ምሁራን፣ በስደት ላይ የሚሰሩ ድርጅቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የሚታደሙ ሲሆን ታዋቂው ደራሲ፣ ሀያሲና ጋዜጠኛ ዓለማየሁ ገላጋይና ደራሲ ሰዓዳ መሀመድ፤ “ስደት በኢትዮጵያ የስነ-ፅሁፍ ስራዎች ውስጥ እንዴት ይታያል” በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሁፎች እንደሚያቀርቡና ውይይት እንደሚደረግባቸው የጀርመን የባህል ማዕከል፣ የመረጃና የቤተ መፅሀፍት አገልግሎት ኃላፊ፣ አቶ ዮናስ ታረቀኝ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡

 --- መሣሪያዎቻቸውንና ልብሶቻቸውን በሲቪሎች የተነጠቁ ብዙዎች ተራፊዎች የለበሱት ቡቱቶ ነበር፣ ጥቂቶቹም እርቃናቸውን ነበሩ። አንዳንዶቹ ደግሞ ተሰልበዋል፤ከመሀላቸው አንዱ እሱን በኃይል ለመቆጣጠር ስምንት ሰዎች እንዳስፈለጉ ሲፎክር ነበር፡፡ ‹‹እጆቼ ደህና ናቸው›› ሲል ጮኸ፡፡ ‹‹ስድን ሁሉንም አቢሲኒያውያን መፍጀት እፈልጋለሁ…››
በዮሐንስ ዘመን የንጉሣዊ ግዛቱ ዋና ከተማ የነበረችው መቀሌ የተወሰነ ትኩረት ያላት ከተማ ነበረች፡፡ በ1895 የታህሳሥ ወር አብዛኛውን ጣልያኖቹ መከላከያዎችን ገነቡ። አንድ ቤተክርስቲያን የጥይት ማከማቻ ሆነ፡፡ የጣልያን ወታደሮችና አስካሪ ምልምሎቻቸው ዋና መከላከያቸው የሚሆነውን 230 ጫማ ርዝመት ያለውን ግምብ ሲገነቡ፣ ጣልያንኛ ዘፈኖችን ይዘፍኑ ነበር፡፡ ግንቦቹ ሲጠናቀቁም ግዙፍ ሆኑ፡፡ የኢትዮጵያን ቀላል መሣሪያዎች ከላይ በኩል ስድስት ጫማ፣ ከስር ደግሞ አስራ ስድስት ጫማ ውፍረት ያለውን ግምብ ለመደርመስ አስቸጋሪ ይሆንባቸዋል፡፡
የተከላካዮች ተስፋ የኢትዮጵያ ጦር አዛዦች በሰው ብዛት ምሽጉን ለመስበር እግረኛ ወታደሮችን በማከታተል ይልካሉ የሚል ነበር፡፡ የኢትዮጵያ የእግረኛ ጦር ጥቃት የጣልያን መድፎች ሥራቸውን እንዲሠሩ ያደርጓቸዋል፡፡ ጣልያኖቹ ለዚህ ዓይነት ፍልሚያ የተዘጋጁት በጥንቃቄ ነበር፡፡ ለአጥቂዎቹ ሽፋን ሊሆኑ የሚችሉና ለጣልያን መድፍ የእይታ መስመር የሚከልሉ ምሽጉ አካባቢ የነበሩ ጎጆዎችን አፈረሱ፡፡ ከምሽጉ ውጪም የመከላከያ ክልል በሽቦ አጠሩ፡፡ ከደቡብ በኩል ወደ ምሽጉ ዋና መዳረሻ፣ ግራና ቀኝ ኢንጂነሮች ጥልቅ ምሽጎች ቆፈሩ፡፡ እነዚህ አሥር ጫማ ጥልቀት ያላቸው ምሽጎች ስር በየሁለት ጫማ ርቀት አንድ፣ አንድ ሜትር የሚረዝሙ ሹል እንጨቶች ቀበሩ፡፡ ከደቡብ አቅጣጫ ወደ ምሽጉ የሚንደረደሩ የኢትዮጵያ ወታደሮች ሹል እንጨት የተሰካባቸው ምሽጎች አልፎ ለመሄድ ወደ መንገዱ መውጣት ይኖርባቸዋል፡፡ እንዲህ ሲያደርጉም ለጣልያን ተኩስ ምቹና ሰብሰብ ያሉ ኢላማዎች ይሆናሉ፡፡
ተርፈው ወደ ምሽጉ ግምቦች የሚጠጉ ወታደሮች፣ተጨማሪ አደጋዎች ይገጥሟቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ወታደሮች የሚዋጉት ባዶ እግራቸውን ነበር፡፡ ስለሆነም ጣልያኖቹ የጠርሙስና የሸክላ ስብርባሪዎችን በመንገዱ ላይ በተኑ። ኢትዮጵያውያኑ አደጋዎቹን አልፈው ከሄዱም ለጣልያን አልሞ ተኳሾች ይጋለጣሉ፡፡
አንድ ምሽግ ራሱን የቻለ ተቋም ነው፡፡ ሆኖም አብዛኛውን ጊዜ እንዲህ አይሆንም፡፡ ታህሣሥ ዘጠኝ አንድ ቡድን ለሰዎቹ ምግብ፣ ለእንስሶቹ መኖ ፍለጋ ምሽጉን ለቆ ወጣ፡፡ የቡድኑ አባላት በፍለጋቸው የተገነዘቡት ነገር አብዛኛው የአካባቢው ህብረተሰብ መሰወሩን ነው፡፡ ይህ የወታደሮቹን ሥራ ይበልጥ አስቸጋሪ አደረገው፡፡ የአካባቢ ገበሬዎችን እቃዎቻቸውን እንዲለዋወጡ፣ እንዲሸጡ ከማሳመን ይልቅ ወታደሮቹ ገበሬዎቹ ምግባቸውንና የከብት መኖውን የት እንደ ደበቁ ለማሰስ ተገደዱ፡፡
እነኚህ የምግብ ፍለጋ ተልዕኮዎች ቀጠሉ፡፡ የእንቅስቃሴው ክልል መስፋት ነበረበት፡፡ ውሎ አድሮ እነኚህ የምግብ ፍለጋ እንቅስቃሴዎች ከምሽጉ በስድስት ማይል ርቀት ተለጠጡ፡፡ ሌሎች የመጥፎ ገድ ምልክቶችም ነበሩ፡፡ ከሰሜኑ ጋር ያለው ግንኙነት የማያስተማምን ሆኗል፡፡ ከአምባ አላጌ በኋላ የአካባቢው ህብረተሰብ አምርሯል፡፡ በቀን የሚጓጓዙ መልእክተኞች እንቅፋቶች ገጠሟቸው፡፡ ማለፍ የሚችለው በሌሊት የሚጓጓዝ ደብዳቤ ብቻ ሆነ፡፡
በየቀኑ በሚሰጣቸው የወይን ጠጅ፤ የቡናና የመጠጥ ራሽን ሳቢያ የጣልያኖች መንፈስ የተነቃቃ ነበር፡፡ ለአውሮፓውያን ወታደሮች በተጨማሪ ሲጋሮችና ትምባሆ ይሰጧዋል፡፡ ወታደሮቹ በጭንቀትና በመጠጥ በመገፋፋት ኢትዮጵያውያኑን እንዴት እንደሚፈጇቸው ጉራ ይቸረችራሉ። ‹‹አቢሲኒያዎች! የገሃነምን መንገድ እንድታገኙ እንረዳችኋለን!›› ሲል አንዱ ጮኸ፡፡ ማታ ማታ አውሮፓውያን መኮንኖች ተሰብስበው እየጠጡ ይጮኹ ነበር፡፡
‹‹የቺያንቲ ፋሽኮዎች፣ የባርቤራ ጠርሙሶች በጠረጴዛ ስር ተንከባለሉ›› ሲል አንድ መኮንን ያስታውሳል፡፡ ‹‹ረጅም ዕድሜ ለጣልያን! ረጅም ዕድሜ ለንጉሥ ኡምቤርቶ! ረጅም ዕድሜ ለሜጀር ጋሊያኖ! ረጅም ዕድሜ ለሜጀር ቶዜሊ!›› እያሉ ይጮሁ ነበር፡፡ ሜጀር ቶዜሊ ለጄኔራል ባራቲዮሪ በቃላት የተዋበ ዘገባ ላከ፡፡ ‹‹ሞራል እስከ ጫፍ ተሰቅሏል፡፡››
ታህሳስ 19 ይህ ሁሉ መንፈስ በአስደናቂ ሁኔታ ተለወጠ፡፡ ጠዋት አራት ሰዓት አካባቢ በደቡብ ምሥራቅ በሸለቆው ዳርቻ፣ ከፍታው ወደሜዳው በሚያዘቀዝቅበት አካባቢ ከፍተኛ የአቧራ ደመና ተነሳ፡፡ መሠረቱ በእግርና በፈረስ የሚተም ግዙፍ የጦር ክፍል ቅርፅም ያዘ፡፡ የራስ መኮንን ጦር ከአምባ አላጌ ድሉ እየተመለሰ ነበር፡፡
(በሬይሞንድ ጆናስ ከተጻፈውና በኤፍሬም እንዳለ ከተተረጎመው “የአድዋ ጦርነት”
መጽሐፍ የተቀነጨበ፤ 2009)

Thursday, 09 March 2017 07:50

“ሆድ ይፍጀው... ብዬ”

   እኔ በልጅነቴ ነበር አክስቴ ወደምትኖርበት ውጭ ሀገር ሄጄ የሰው ቤት ስራ እንድሰራ ሁኔታዎች የተመቻቹልኝ። የዚህም ምክንያት በትዳር አለም ስኖር ሁለት ልጆችን ከወለድሁ በሁዋላ ባለቤ በመሞቱ ነበር። በሁዋላም ወደውጭ ሀገር ሄጄ ስራዬን በመስራት ላይ እንዳለሁ የአሰሪዬ ዘመድ የሆነ ሀብታም ለትዳር እፈልጋታለሁ በማለቱ ተዳርኩለት። በዚህ ሁኔታ እንዳለን ታሪኬን አጫወትኩት። ልጆቼን ወስጄም እንዳስተምራቸው ፈቀደልኝ። በደስታ ወደምኖርበት ሀገር ወስጄ ሁለቱንም ትምህርት ቤት አስገባሁዋቸው። ሲውል ሲያድርም ልጆቹ አደጉ። አማረባቸው። በተለይም ሴትዋ በጣም ውብ ሆነች። ሰው ማንን ይመስላል ሲባል ኑሮውን ...ተብሎ የለ? ነገር ግን ሁኔታዎች መልካቸውን እየቀየሩ መምጣታቸው አልቀረም። ባለቤ ልጄን አስገድዶ ደፈራት። እኔም ኡኡ የአገር ያለህ አልል...ያለሁት እሰው ሀገር...ማን ሰሚ ይኖረኛል? እንዲሁ እዬዬ እያልኩ ያገናኙንን ሰዎች ሽምግልና ብልክበት...እኔ ልጅ እፈልጋለሁ። እስዋ ደግሞ አልወልድልህም ብላኛለች...ስለዚህ ...በቃ ...እክሳለሁ...አለ። እኔም ለጊዜው ልጄን ይዤ ወደሐገር ቤት መጣሁ። እውነትም ጸንሳ ኖሮአልና ምንም ማድረግ አልቻልኩም። በ17/አመት እድሜዋ የተደፈረችውን ልጄን የጸነሰችውን ልጅም በሰላም ተገላግላ እንድታሳድግ በሚል ተለመንኩና... የተሰጠኝን ካሳ ተቀብዬ ...ሆድ ይፍጀው...ብዬ እንደገና ልጄን ለባሌ በሕግ አፈራርሜ ዳርኩለት። እሱዋም በመጀመሪያው ወንድ ልጅ ከዚያም ሴት ልጅዋን ወልዳ ትዳር ከተባለ ትዳርዋን ይዛ ቁጭ ብላለች። አኔም ከሀያ አመት በላይ ከኖርኩባት ሀገር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ትቼ ወደሀገር ቤት ተመልሻለሁ። አያሳዝንም?
 ወ/ሮ ፈትለወርቅ ከአዲስ አበባ።
አለምአቀፉ (Behavioral social and movement sciences ) በ2014 አንድ ጥናት አውጥቶአል። ይህ ጥናት እንደሚገልጸውም አስገድዶ መድፈር በአሁኑ ወቅት አለም አቀፍ ችግር እንደሆነ ነው። እንዲያውም ጥናቱ እንደሚገልጸው ካለጥርጥር በአለማችን እየተካሄዱ ካሉ ጦርነቶች እንደአ ንዱ ሊቆጠር ይችላል። ምንም እንኩዋን በሴቶች መብት ላይ አመታትን ያስቆጠረ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረኮችና ንቃተ ሕሊናን የሚያዳብሩ ስራዎች ቢሰሩም ዛሬም ሴቶችንና ልጃገረዶችን የመድፈር ሁኔታ በመቀጠሉ እንደ አንዱ የስነዋልዶ ጤና ችግር መንስኤ ሆኖ ከማስቸገሩም በላይ ምናልባትም ከህብረተሰቡ ማግኘት የሚገባውን የመከላከል ስራም አላገኘም ማለት ይቻላል ይላል ጥናቱ። በእርግጥ አስገድዶ መድፈር ከቦታ ቦታ እና እንደየህብረተሰቡ የኑሮ ልምድ እና እንደየሀገራቱ የህግ አተረጉዋጎም የተለያየ ትርጉም የሚሰጠው ነው። በአጠቃላይ ግን አስገድዶ መድፈር ወንድ በሴት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት የከፋ ሆኖ ቢታይም ሴቶችም አልፎ አልፎ በወንዶች ላይ የሚፈጽሙት ሆኖ ይስተዋላል። ወደጥናቱ ዝርዝር ስንገባ በመጀመሪያ የአስገድዶ መድፈር ሁኔታ እና የደፋሪዎች ማንነት ይቀድማል።
የአስገድዶ መድፈር እና የደፋሪዎች አይነት
Zanni(2009) ዛኒ የተባለች ተመራማሪ ለአለም የጤና ድርጅት ባቀረበችው ምርምር እንደገለጸ ችው ጥቃት አድራሾች በተለያዩ ቡድኖች ይከፈላሉ ትላለች።
Stranger Rape - በማይተዋወቁ ሰዎች መካከል የሚደርስ የጾታዊ ጥቃት አይነት ነው። ይህም ማለት ጥቃት አድራሹም ሆነ ጥቃት የሚፈጸምበት ሰው ቀደም ሲል ምንም አይነት ትውውቅ የሌላቸውና በአጋጣሚ የሚፈጸም ነገር መሆኑን ነው።
Acquaintance rape - ጥቃት አድራሹ እና ጥቃት የሚፈጸምበት ሰው አስቀድሞውኑ ትውውቅ ያላቸውና ያንን መሰረት በማድረግም የሚፈጸም ነው። ይህ ትውውቅም ምናልባትም በቀድሞው ጊዜ እጮኛነት ወይንም የፍቅር ግንኙነት የነበራቸው እንዲሁም የግብረስጋ ግንኙነት አድርገው የሚያውቁ ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ።
Partner rape - አብረው በሚኖሩ ሰዎች መካከል የሚፈጸም ነው። ሁለቱ ሰዎች አብረውየኖሩት በባልና ሚስትነት ሊሆን ይችላል። ወይንም በዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ወይንም በስራ አጋጣሚ በአንድ ጣሪያ ስር የሚኖሩ ሊሆኑ ይችላሉ። በኑሮ አጋጣሚም በቤት ውስጥ በዘመዳሞች መካከል የሚፈጠር አስገድዶ መድፈር ሊሆን ይችላል።
Gang Rape - ሌላው አስገድዶ መድፈር የመፈጸም ሁኔታ የተወሰኑ ወንዶች በቡድን ሆነው የሚፈጽሙት ነው። ይሄም ሰዎቹ ለምንድነው እንዲህ ያለ ጥቃት የሚፈጽሙት ተብሎ ሲጠየቅ በልጅነት ዘመናቸው ወይንም ደጉም በሁዋላ በህብረት ወንጀል መፈጸ ምን እያዳበሩ የመጡ መሆናቸውን ነው መረጃዎች የሚጠቁሙት። በአባቢ፣ በዘር ወይንም በትምህርት ቤት በመሳሰሉት እነእገሌ እኮ ኃይለኞች ወይንም ጎበዞች ናቸው ተዋጊዎች ናቸው የሚል አይነት መገለጫን እያዳበሩ የመጡ ሰዎች ናቸው አስገድዶ መድፈር ወንጀልን የሚፈጽሙት። እንደዚህ ያለው ወንጀል በተለያዩ የአፍሪ አገሮችና በሌሎችም የሚታይ ነው። አንዱ ሌላውን ከመዋጋት ይልቅ የተቃራኒውን ወገን አስገድዶ በመድፈር ሃይልን መወጣት ይበልጥ የሚያስደስትበት ሁኔታ ይታያል።
የተለያዩ መረጃዎች እንደሚገልጹት አልኮሆል ወይንም ሱስ አስያዥ እጽን መጠቀም አንዱ ለአስገድዶ መድፈር የሚዳርግ ነገር ነው። ሰዎች በተፈጥሮ ህብረተሰቡ የሰጠውን ሁኔታ ተቀብሎ በማደግ ያልሆነ ነገር ውስጥ እንዳይገቡ የሚመልሳቸው በጭንቅላት ውስጥ የሚገኝ ተፈጥሮአዊ ነገር አለ። ያ ተፈጥሮአዊ ነገር ድርጊትን ለመፈጸም በሚፈለግበት ጊዜ ይሄ ትክ ክል አይደለም ይሄ ትክክል ነው የሚል ከመጥፎ ነገር የሚከላከለ ነው። አልኮሆል ወይንም ሱስ አስያዥ ንጥረ ነገር ግን ይህንን ጥሩና መጥፎ ነገር አመላካች የሆነውን ነገር በማደብዘዝ ይገታዋል። ስለሆነም ይህንን ነገር ማድረግ የለብኝም ያስቀጣኛል ወይንም ሰው እጎዳለሁ ወይ ንም ህብረተሰቡ ይህንን ድርጊት ያወግዘዋል ብሎ ለመተው ከመሞከር ይልቅ እንዲያውም ድርጊቱን ለመፈጸም የሚገፋፋ የሚያደፋፍር ነገር ይፈጠራል።
ወንድ ሴትን የሚደፍረው ብዙ ጊዜ የስርአተ ጾታ ክፍፍል ልዩነቱ ወይንም ጀንደር ከሚለው ሁኔታ ጋር ይያያዛል። ሴት እንዲህ ነች ወንድ ደግሞ እንዲህ ነው የሚለውን ህብረተሰቡ የሚያምንበትና ተግባራዊ እያደረገው ለው ጋር በተያያዘ አስገድዶ መድፈሩ ብዙ ጊዜ ይፈጸማል። ምክንያቱም ህብረተሰቡ ለወንድ ልጅ ኃይል ወይንም አቅም እንዳለው እየነገረ ስለሚያሳድገው ወንዱ በተፈጥሮው ገኘው ጥንሬ ባሻገር በአስተሳሰብም ኃይል እንዲኖረው ያደርገዋል።ከዚህም በተለየም በልጅነታቸው የመደፈር ወይንም የመገለል እንዲሁም የተለያዩ ጥቃቶች የደረሰባቸው ከሆነ አስገድዶ መድፈርን እንደ እልህ መወጫ ይጠቀሙበታል። አንድ ወንድ እንደዚህ ያለ ጉዳት እየደረሰበት ያደገ ከሆነና እሱም ጥቃቱን መፈጸሙ በሳይንሳዊው መንገድ ሲተረጎም አእምሮው በሚያድግበት ሰአት የተለያዩ ኢንዛይሞች ማለትም ነርቭ ከነርቭ የሚገናኝበት መልእክት የማስተላለፊያ ኬሚሎች በደም ውስጥ እየቀነሰ ይመጣል። አእምሮው እያደገ ሲመጣ ደሙ ግን እየቀነሰ መምጣቱ በሚያድጉበት ሰአት ላይ ይህንን ወሲባዊ ጥቃትም ሆነ ማንኛውንም ወንጀል እንደሰው መግደል የመሳሰሉትን ጨምሮ የመፈጸም እድላቸው የሰፋ ይሆናል። ብዙ ጊዜ አስገድዶ መድፈር የሚፈጽሙ ሰዎች ከአንድ ሰው ጋር ወይንም ከተለያዩ ሰዎች ጋር ጥሩ አይነት ግንኙነት መመስረት የማይችሉ ናቸው። ይህ እንግዲህ ከአስተዳደግ ወይንም ከተለያዩ የህይወት አጋጣሚዎች ሊሆን ይችላል። በተረጋጋ ሁኔታ ከሰዎች ጋር መኖር ልተቻለ ወይንም ህብረተሰቡ የሚጠብቀውን ደረጃ ማሟላት ልተቻለ እንደመሸሻ የሚቆጠረው የአስገድዶ መድፈር ወንጀልን የመሳሰሉ ሊሆኑ ይችላሉ።
 ዶ/ር ዳዊት ደሳለኝ
 የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት
Alexis (2009) እንደምትገልጸው የወሲብ ጥቃት አድራሾች ወይንም አስገድደው ደፋሪዎች በሶስት ይከፈላሉ።
Power rapist :- ጉልበት የማሳየት ወይንም እኔ ከእገሌ እበልጣለሁ ስለዚህም ማሳየት አለብኝ ከሚል የተሳሳተ አስተሳሰብ የሚመነጭ ሲሆን የሚረኩትም ጾታዊ ግንኙነት በማድረጋቸው ሳይሆን የበላይነትን በማሳየታቸው ነው።
Opportunist rapists:- የሚባሉት ደግሞ የሚፈልጉዋትን ሴት ለረጅም ጊዜ ሲከታተሉ ቆይተው ሁኔታዎች ሲፈቅዱ የወሲብ ጥቃት የሚያደርሱ ናቸው።
Entitlement rapists :- የሚባሉት ደግሞ ሴትዋ ፈለገችም አልፈለገችም ወሲባዊ ግንኙነት ማድረግ የወንድ ልጅ መብቱ ነው ብለው የሚያስቡ ናቸው።
“አስገድዶ መድፈርን የሚፈጽሙት ወንዶች የግብረስጋ ግንኙነትን ፈልገው ሳይሆን ኃይልን ለመግለጽ የሚያደርጉ ሲሆን በዚሁ አጋጣሚ ግን አንዳንድ ጊዜ ሴቶች ተገደው እየተደፈሩ ሳሉ ወደ ወሲባዊ ስሜት የሚገቡበት ሁኔታ መኖሩም ተረጋግጦአል።
ሴቶቹ በዚህ ስሜት ምክንያት ማለትም ተገድጄ እየተደፈርኩ ግን ደስተኛ ሆንኩ በሚል ብዙ ጊዜ እራሳቸውን ያማርራሉ። ነገር ግን እንዲህ ያለው ነገር የሚከሰተው ስሜቱ ከተፈጥሮ ቁጥጥር ውጭ በመሆኑ ነው። ይሄ ሁሉም ተገደው የሚደፈሩ ሴቶች ላይ የሚኖር ሳይሆን አንዳንድ ሴቶች ላይ የሚፈጠር ነው። ወንዶቹም አስገድደው በሚደፍሩበት ጊዜ ኃይላቸውን አሳይተው ይተዋሉ እንጂ የዘር ፈሳሽ እስኪለቁ ድረስ ወሲባዊ ግንኙነቱን እያደረጉ አይቆዩም።”
ዶ/ር ዳዊት ደሳለኝ
የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት

  የሞ ኢብራሂም የ5 ሚ. ዶላር ሽልማት፣ ብቁ መሪ በመታጣቱ ለ5 አመታት አልተሰጠም

    የላቀ የአመራር ብቃት ላሳዩ ውጤታማ የአፍሪካ አገራት የቀድሞ መሪዎች በየአመቱ የ5 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት የሚያበረክተው ታዋቂው ሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን፤ ዘንድሮም እንደ አምናው ሁሉ ለሽልማት የሚመጥንና መስፈርቱን የሚያሟላ መሪ አለማግኘቱን አስታወቀ፡፡
አምና ባካሄደው ውድድር መስፈርቱን የሚያሟላ መሪ በማጣቱ ሽልማቱን ሳይሰጥ የቀረው ፋውንዴሽኑ፤ ዘንድሮም ከአህጉሪቱ የቀድሞ መሪዎች መካከል ለሽልማት ብቁ የሆነ ሰው ባለማግኘቱ ለ2016 ያዘጋጀውን ሽልማት ለማንም ሳይሰጥ ለማለፍ መወሰኑን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
ተቋሙ ሽልማቱን መስጠት ከጀመረበት እ.ኤ.አ ከ2006 ጀምሮ ባሉት አመታት፣ ያወጣውን መስፈርት የሚያሟላ ብቁ መሪ በማጣቱ ሳቢያ የዘንድሮውን ሽልማት ጨምሮ ለአምስት ጊዜያት በተመሳሳይ ሁኔታ አመታዊ ሽልማቱን ሳይሰጥ መቅረቱን ያስታወሰው ዘገባው፤ ከዚህ ቀደም መስፈርቱን በአግባቡ አሟልተው የተቋሙን ሽልማት ለመቀበል ከበቁ የአፍሪካ አገራት የቀድሞ መሪዎች መካከል የሞዛምቢኩ ጆኣኪም ቺሳኖ እና የቦትስዋናው ፌስቱስ ሞጋኤ እንደሚገኙበትም አክሎ ገልጧል፡፡
የቀድሞ የአፍሪካ አገራት መሪዎች ከሚገመገሙባቸውና ለሽልማት ከሚበቁባቸው የተለያዩ የተቋሙ መስፈርቶች መካከል በዲሞክራሲያዊ መንገድ ተመርጦ ስልጣን መያዝ፣ በህግ ከተቀመጠው የስልጣን ዘመን ገደብ በላይ አለመግዛትና የተለየ የአመራር ብቃት ማሳየት የሚሉት እንደሚገኙበት ተነግሯል፡፡ ዲሞክራሲያዊ አመራርን የማስረጽና ውጤታማ የቀድሞ የአፍሪካ አገራት መሪዎችን የማበረታታት አላማ ያለው ተቋሙ፤ በቴሌኮም ዘርፍ አለማቀፋዊ ስኬትን ባስመዘገቡት ታዋቂው ሱዳናዊ ሞ ኢብራሂም ተቋቁሞ አመታዊ ሽልማት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡

በየቀኑ ዩቲዩብ ላይ የሚጫኑ ቪዲዮዎች ርዝማኔ 65 አመታት ያህል ነው
    በታዋቂው ድረገጽ ዩቲዩብ አማካይነት ለእይታ የቀረቡ የተለያየ አይነት ይዘት ያላቸው ቪዲዮዎች በአንድ ቀን ውስጥ ብቻ ከ 1 ቢሊዮን ሰዓታት በላይ በአለም ዙሪያ በሚገኙ የድረገጹ ተጠቃሚዎች እንደሚታዩ ተዘገበ፡፡
   በዩቲዩብ የሚታዩ ቪዲዮዎች ብዛት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ እንደሚገኝ የዘገበው ዎልስትሪት ጆርናል፤ የድረገጹ ቪዲዮዎች በአንድ ቀን ውስጥ የሚታዩበት ሰዓት ባለፉት አምስት አመታት በአስር እጥፍ ያህል ማደጉን ጠቁሟል፡፡  ወደ ዩቲዩብ ድረገጽ የሚጫኑ ቪዲዮዎች ቁጥርም እጅግ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ሲሆን በየቀኑ በድረገጹ ላይ የሚጫኑ ቪዲዮዎች አጠቃላይ የሚፈጁት ጊዜ እርዝማኔ 65 አመታት ያህል እንደሚደርስም ኩባንያው አስታውቋል፡፡   እ.ኤ.አ በ2005 ስራ የጀመረው ዩቲዩብ፣ በመላው አለም በሚገኙ የቪዲዮ ተመልካቾች ተቀዳሚ ምርጫ መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፤ ድረገጹ ገቢም በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን አክሎ ገልጧል፡፡

 ኦባማ እና ሚሼል አዳዲስ መጽሃፍትን ለማሳተም ከ65 ሚ. ዶላር በላይ ይከፈላቸዋል
    የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦማባ በዘንድሮው የፈረንሳይ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ እንዲወዳደሩ የሚጠይቅ የድጋፍ ፊርማ የማሰባሰብ ዘመቻ በድረገጽ አማካይነት መጀመሩንና እስካሁን ድረስም ከ42 ሺህ በላይ ሰዎች ሃሳቡን በመደገፍ ፊርማቸውን ማስፈራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
የዘመቻው አስተባባሪዎች ኦባማ በመጪው ግንቦት ወር  በሚካሄደው የፈረንሳይ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ እንዲወዳደሩ የድጋፍ ፊርማ ማሰባሰብ የጀመሩት፣ ሃሳባቸው ህጋዊ ተቀባይነት እንደማያገኝ ቢያውቁም፣ ለምርጫው በዕጩነት የቀረቡት የአገሪቱ ዜጎች ይህ ነው የሚባል ብቃት የሌላቸው መሆናቸውን ለማስመስከር በማሰብ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በሳምንቱ መግቢያ  ላይ በተጀመረውና ለቀናት በዘለቀው የፊርማ ማሰባሰብ ዘመቻ፣ ከ42 ሺህ በላይ ሰዎች ድጋፋቸውን መግለጻቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ አስተባባሪዎቹ 1 ሚሊዮን ያህል ለማድረስ አቅደው በስፋት እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙና በፓሪስ ጎዳናዎች ላይ ኦባማ 2017 የሚል መፈክር የተጻፈባቸው ፖስተሮች በስፋት መሰራጨታቸውን አመልክቷል፡፡
ኦባማ ለፈረንሳይ ፕሬዚዳንትነት እንዲወዳደሩ የሚጠይቀው የድጋፍ ድምጽ ከሚሊዮን አልፎ ቢሊዮንና ትሪሊዮን ፊርማዎችን ቢያሰባስብም፣ የአገሪቱ ህግ የውጭ ዜግነት ያለው ሰው ለፕሬዚዳንትነት መወዳደር እንደማይችል የሚደነግግ በመሆኑ ከንቱ ድካም ሆኖ እንደሚቀር ዘገባው አስረድቷል፡፡
በሌላ በኩል፣ ባራክ ኦባማ እና ባለቤታቸው ሚሼል ኦባማ፤ ሁለት አዳዲስ መጽሃፍቶቻቸውን ለንባብ የሚያበቁበትንና ከ65 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ እንደሚያገኙበት የተነገረለትን የህትመት ስምምነት ውል መፈጸማቸው ባለፈው ማክሰኞ ተዘግቧል፡፡
ኦባማ በዋይት ሃውስ የነበራቸውን የስምንት አመታት ቆይታ የሚዳስሱበትን፣ ሚሼል ደግሞ አነቃቂ ይዘት ያለው ነው የተባለውን መጽሃፍት ለንባብ ለማብቃት ከታዋቂው አሳታሚ ኩባንያ ፔንጉዊን ራንደም ሃውስ ጋር በድምሩ ከ65 ሚሊዮን ዶላር በላይ ስምምነት መፈጸማቸውን የዘገበው አሶሼትድ ፕሬስ፤ የመጽሃፍቱ ርዕሶችም ሆነ ለገበያ የሚበቁበት ጊዜ ይፋ አለመደረጉን ጠቁሟል።
ኦባማ እና ሚሼል ከአሳታሚው ኩባንያ ከሚከፈላቸው ገንዘብ ዳጎስ ያለውን ለበጎ አድራጎት ስራ ለማዋል ማቀዳቸውን ያስታወቀው ዘገባው፤ መጽሃፍቶቹን ለማሳተም በርካታ አሳታሚ ኩባንያዎች መወዳደራቸውንና  ፔንጉዊን ራንደም ሃውስ የተጠቀሰውን ገንዘብ በማቅረብ ውድድሩን ማሸነፉንና ይህ ዋጋ በአሜሪካ ፕሬዚዳንቶች የማስታወሻ መጽሃፍ ክፍያ ታሪክ ከፍተኛው መሆኑን አመልክቷል፡፡
የስልጣን ዘመናቸው ማብቃቱን ተከትሎ ለንባብ ባበቋቸው መጽሃፍት ከፍተኛውን ክፍያ በማግኘት ቀዳሚነቱን ይዘው የቆዩት የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ቢል ክሊንተን መሆናቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ ክሊንተን በ2004 ለንባብ ላበቁት ማይ ላይፍ የተሰኘ መጽሃፍ ከአሳታሚያቸው የተከፈላቸው ገንዘብ 15 ሚሊዮን ዶላር እንደነበርም  ጠቅሷል፡፡
ኦባማ ከዚህ ቀደም ለንባብ ያበቋቸው ድሪምስ ፍሮም ማይ ፋዘር እና ዘ ኦዳሲቲ ኦፍ ሆፕ የተሰኙ ሁለት መጽሃፍት በሚሊዮኖች ቅጂ መቸብቸባቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ የሚሼል ኦባማ ብቸኛ መጽሃፍ ደግሞ በ2012 ያሳተሙት አሜሪካን ግሮውን የተባለ በምግብ ዝግጅትና በተክሎች እንክብካቤ ዙሪያ የሚያጠነጥን መጽሃፍ መሆኑን አስረድቷል፡፡

      የፓኪስታን አለማቀፍ አየር መንገድ ባለፈው ጥር ወር ላይ ከካራቺ ወደ ሳኡዲ አረቢያዋ ከተማ መዲና ባደረገው በረራ፣ መጫን ከሚገባው የመንገደኛ ቁጥር በላይ 7 ትርፍ መንገደኛ መጫኑን እንዳመነ ኒውስ 18 ድረ-ገጽ ዘግቧል፡፡  የአየር መንገዱ ሰራተኞች ጥር 20 ቀን በረራውን ባደረገውና 409 ሰዎችን የማሳፈር አቅም ባለው ቦይንግ 777 አውሮፕላን ውስጥ ተጨማሪ 7 መንገደኞችን በማሳፈር፣ ለአደጋ የሚያጋልጥ ጉዞ እንዲደረግ በመፍቀዳቸው በህግ እንደሚጠየቁና አየር መንገዱ ምርመራ እያደረገ እንደሚገኝም ዘገባው ገልጧል፡፡
  በትርፍ የተጫኑት መንገደኞች ረጅም ሰዓታት የሚፈጀውን ጉዞ ያለምንም መቀመጫ፣ ቆመው እንደጨረሱት የአገሪቱ ጋዜጦች ቢዘግቡም፣ አየር መንገዱ ግን ይህን ማስተባበሉንና በረራው ያለምንም ችግር እንደተጠናቀቀ ማስታወቁን ድረ ገጹ ጠቁሟል።  አውሮፕላኖች መጫን ከሚገባቸው የመንገደኛ ቁጥር በላይ እንዲጭኑ መፍቀድ፣ የኦክስጂን አቅርቦት ካለመኖር፣ ከመተፋፈግና ከተያያዥ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ አውሮፕላኑንና ተሳፋሪዎቹን ለከፋ አደጋ እንደሚያጋልጥና በአቪየሽን ህግ መሰረት ከፍተኛ ቅጣት እንደሚያስጥልም ዘገባው አስታውቋል፡፡

   የቀጣይ 6 አመታት የፕሮግራም ስትራቴጂውን ይፋ አድርጓል
     በኢትዮጵያ በውሃ፣ የአካባቢ ንጽህና እና የስነ ጤና አጠባበቅ ላይ ትኩረት አድርጎ በመስራት ብቸኛው መንግስታዊ ያልሆነ አለማቀፍ ድርጅት የሆነው ዎተርኤይድ ኢትዮጵያ፤ ባለፉት ስድስት አመታት በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ባከናወናቸው ተግባራት 1.3 ሚሊዮን ያህል ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረጉን ያስታወቀ ሲሆን ከ2016 እስከ 2021 ባሉት ቀጣይ አመታት የተጠናከረ ስራ ለማከናወን የሚያስችለውን አዲስ የፕሮግራም ስትራቴጂ ባለፈው ማክሰኞ ይፋ አድርጓል፡፡
ለስድስት አመታት በዘለቀውና ዘንድሮ በተጠናቀቀው የፕሮግራም ስትራቴጂ ዘመን ከአጋር አገር በቀል ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት በአገሪቱ አምስት ክልሎች የሚገኙ ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን የውሃ፣ የአካባቢ ንጽህናና የስነ ጤና አጠባበቅ አገልግሎቶች ተጠቃሚ ማድረጉን የገለጸው ዎተርኤይድ ኢትዮጵያ፤ በቀጣይም አገልግሎቶቹን በስፋት ለማዳረስ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ለማከናወን ማቀዱን አስታውቋል፡፡
የውሃ፣ የመስኖና የኤሌክትሪክ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬነሽ መኩሪያ በካፒታል ሆቴል በተከናወነው የድርጅቱ የፕሮግራም ስትራቴጂ ማስተዋወቂያ ስነስርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር፣ የውሃ፣ የአካባቢ ንጽህናና የስነ ጤና አጠባበቅ አገልግሎቶችን እ.ኤ.አ እስከ 2030 በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ለሁሉም ዜጎች በተሟላ መልኩ ለማዳረስ የተያዘውን አገራዊ እቅድ በማሳካት ረገድ ዎተርኤይድ ኢትዮጵያ የራሱን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ በሚሊኒየሙ የልማት ግቦች ውስጥ የተካተተውን የውሃ አቅርቦት ግብ ማሳካት ችላለች ያሉት ወ/ሮ ፍሬነሽ፤ የአካባቢ ንጽህና ግብን ለማሳካት በተደረገው ጥረት መልካም ውጤት ቢመዘገብም፣ ግቡን ለማሳካት ተጨማሪ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ በመጥቀስ፣ ለዚህ ደግሞ ዎተር ኤይድን ጨምሮ በመስኩ የሚሰሩ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት የሚያደርጉት የተቀናጀ ርብርብ ወሳኝ መሆኑን አስምረውበታል፡፡
በሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ የውሃ፣ የአካባቢ ንጽህናና የስነ ጤና አጠባበቅ አገልግሎቶችን አጠቃላይ አቅርቦት ፍትሃዊና ዘላቂ በሆነ መልኩ ለማሟላት ግብ ተቀምጦ እየተሰራ እንደሚገኝ የጠቆሙት ወ/ሮ ፍሬነሽ፤ ለዕቅዱ መሳካት ባለድርሻ አካላት ከመንግስት ጎን እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የዎተርኤይድ ኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተር ቤተልሄም መንግስቱ በበኩላቸው፤ ባለፉት 20 አመታት በአገሪቱ የውሃ፣ የአካባቢ ንጽህናና የስነ ጤና አጠባበቅ አገልግሎቶችን አጠቃላይ አቅርቦት ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት ጉልህ ውጤቶች መመዝገባቸውን አስታውሰው፣ ዎተርኤይድ ኢትዮጵያም በመስኩ የተመዘገቡ ውጤቶችን በተቀናጀ አሰራር የበለጠ በማሳደግና የተቀመጡ ግቦችን በማሳካት ረገድ የራሱን አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችለውን የቀጣይ አመታት የፕሮግራም ስትራቴጂ መቅረጹን ገልጸዋል፡፡
ድርጅቱ በቀጣይም በመስኩ የሚታዩ አንዳንድ ችግሮችን በመቅረፍ፣የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ፣ የዘላቂ ልማት ግቦችንና በሴክተሩ የተቀመጠውን የ”ዋን ዋሽ” ብሄራዊ ፕሮግራም ግቦችን ለማሳካት በመንግስት እየተደረገ ያለውን ጥረት እንደሚያግዝም አስረድተዋል፡፡
የዎተርኤይድ ኢትዮጵያ አገልግሎቶችን በፍትሃዊና በዘላቂነት ለማዳረስ የሚያስችሉ የስርዓት ቀረጻ ስራዎችን እንዲሁም በብሄራዊ፣ በክልላዊና በወረዳ ደረጃ በመስኩ ለተሰማሩ ባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ድጋፎችን ማድረግ ከጀመረ 30 አመታትን ያህል ያስቆጠረ ሲሆን አለማቀፉ ዎተርኤይድም በ37 የተለያዩ የአለማችን አገራት ሰፋፊ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡

Tuesday, 07 March 2017 00:00

የፀሐፍት ጥግ

· ዘፈን ያው ዘፈን ነው፡፡ ግን አንዳንድ ዘፈኖች አሉ … አንዳንድ ዘፈኖች በጣም ግሩምናቸው፡፡ የቢትልስ “yesterday” የሚለው ዘፈን ዓይነት፡፡ እስቲ ግጥሙን አዳምጡት፡፡
   ቹክ ቤሪ
· የድሮ የዘፈን ግጥሞቼን ብመለከታቸው በቁጣ የተሞሉ ነው የሚመስሉት፤ ግን ባዶ ናቸው፡፡ በህይወቴ ውስጥ ባዶነት ነበረ፡፡
   ቢሊ ጆ አርምስትሮንግ
· በሙዚቃዬና በዘፈን ግጥሞቼ፣ የሰዎችን ህይወት ለመንካት እፈልጋለሁ፡፡
   ሮሚዮ ሳንቶስ
· ብዙ ልዋሽ እችላለሁ፤ በዘፈን ግጥሞቼ ውስጥ ግን ፈፅሞ ውሸት የለም፡፡
   ኮርትኔይ ላቭ
· ብዙ ጊዜ የዘፈን ግጥሞች ሀዘንና ትካዜ ይበዛቸዋል፡፡
   ዊል ቻምፒዮን
· የዘፈን ግጥሞችን እንዳብራራ ልትጠይቁኝ አትችሉም፤ ምክንያቱም አላደርገውም፡፡
   ሎዩ ሪድ
· የዘፈን ግጥሞችን የምንሰራው በከፍተኛ ጥንቃቄ ነ ው፤ ማ ንንም ማ ስቀየም አንፈልግም፡፡
   ቢል ሃሌይ
· የማስታወሻ ደብተር ይዤ የዘፈን ግጥሞች ለመፃፍ የምቀመጥ ዓይነት ሰው አይደለሁም፡፡
   ጄምስ ቪንሴንት ማክሞሮው
· ከ11 እስከ 15 ዓመት ባለው ዕድሜዬ ያደመጥኳቸውን ዘፈኖች ግጥም ብቻ ነው የማውቀው፡፡
   ኤልዛቤት ባንክስ
· ሁልጊዜ እንደፃፍኩ ነው፤ ተንቀሳቃሽ ስልኬ በሃሳቦች ጢም ብሎ የተሞላ ነው - በዜማዎች፣ በግጥሞችና የመሳሰሉት፡፡
   ኤሊዛ ዱሊትል
· ለእኔ ሙዚቃ መስራት ከቀላል ዜማ ይጀምራል፤ ከዚያ በኋላ ግጥም ይከተላል፡፡
   ሊዮን ብሪጅስ
· የራፕ ሙዚቃ ድንቅ ነው፤ ውብ፡፡ ችግሩ ያለው ከግጥሞቹ ነው፡፡ ግጥሞቹን ከሚፅፋቸው ሰው - ያ ነው ችግሩ፡፡
   ኢማኑኤል ጃል
· እንደሚመስለኝ አንድ ዘፈን ውብ ግጥሞች እስካሉት ድረስ በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡
   ጁሊ አንድሪውስ
· የዘፈን ግጥሞቼ የራሴ ወይም የጓደኞቼ የህይወት ተሞክሮ ትናንሽ ታሪኮች ናቸው፡፡
   ሳዴ አዱ
· በዙሪያዬ ጊታር መኖር አለበት፡፡ ሻወር ውስጥ ሆኜ እዘፍናለሁ፡፡ በመኖሪያ ቤት አካባቢ እዘፍናለሁ፡፡ ሙዚቃው በሁለተኛ ደረጃ የሚመጣ ነው፡፡ ቅድምያ የሚሰጠው ለግጥሙ ነው፡፡
   ኢሚሎዩ ሃሪስ