Administrator

Administrator

የፍርድ ቤት የእግድ ትእዛዝ በመጣስ፣ በአዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ፣ ልዩ ስሙ የካ አባዶ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የምትገኘውን የቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ያፈረሱ፣ የወረዳ 12 አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚና የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ሓላፊ፣ በ15 ቀን ቀላል እስራት እንዲቀጡ የከተማው ይግባኝ ሰሚ ፍ/ቤት ወሰነ፤ ቤተ ክርስቲያኒቱ እንድትፈርስ የሥር ፍ/ቤት የሰጠው ውሳኔ ግን፣ “ይግባኝ አያስቀርብም” ብሏል፡፡
በይግባኝ ባይ፥ የደብረ ልዕልና ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር እና በመልስ ሰጪ፥ የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ደንብ ማስከበር አገልግሎት ጽ/ቤት መካከል ያለውን የይግባኝ ቅሬታ ሲመረምር መቆየቱን ከትላንት በስቲያው ውሳኔው ያስታወቀው ፍ/ቤቱ፤ መልስ ሰጪዎቹ፥ የወረዳው ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደመላሽ ጎሳ እና የደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ ሓላፊ አቶ ዳዊት ሙሉጌታ፤ የፍ/ቤትን የእግድ ትእዛዝ እያዩ፣ ክርክር የቀረበባትን ቤተ ክርስቲያን ማፍረሳቸው፣ የፍርድ ቤትን ሥራ ማወክ በመኾኑ ጥፋተኛ ኾነው እንደተገኙ ገልጿል፡፡
በይግባኝ ባይ በኩል የቀረቡ አራት ምስክሮች፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ አስተዳዳሪ ሊቀ ካህናት በየነ አሰፋ፥ “የፍ/ቤት የእግድ ትእዛዝ አለ፤ በሕግ አምላክ አታፍርሱ” እያሉ ለተጠቀሱት ሁለት ሓላፊዎች እንዳሳዩዋቸው፤ እነርሱ ግን ለማቆም ፈቃደኛ እንዳልነበሩና በግብረ ኃይል ቤተ ክርስቲያኒቱን እንዳስፈረሱ፣ በበቂ ሁኔታ ማስረዳታቸውን ፍ/ቤቱ በውሳኔው ጠቅሷል፡፡ በመልስ ሰጪዎች የቀረቡ ሁለት ምስክሮች፣ አፍራሽ ግብረ ኃይል ሆነው የማፍረስ ተግባር ያከናወኑና ምስክርነታቸው እርስ በርሱ የሚጋጭ ሆኖ በመገኘቱ፣ “ገለልተኛና ተኣማኒነት ያለው ኾኖ አላገኘነውም፤” ብሏል፡፡
ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ “የጣስነው ሕግ የለም፤ የወሰድነው ርምጃም ተቋሙን ወክለን ነው፤” በሚል የቅጣት ማቅለያ ያቀረቡ ቢኾንም፣ ፍ/ቤቱ፥ “ጥፋተኞችንም ኾነ ሌሎች ግለሰቦችን ያስተምራል፤” በሚል አቶ ደመላሽ ጎሳ እና አቶ ዳዊት ሙሉጌታ፣ ውሳኔው ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በ15 ቀን ቀላል እስራት እንዲቀጡ ወስኗል፤
በሌላ በኩል፣ የሥር ፍ/ቤት፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ይዞታና ግንባታ ሕገ ወጥ ነው፤ በሚል መጋቢት 13 ቀን 2009 ዓ.ም.፣ የሰጠው ውሳኔ፣ የሚነቀፍበት ምክንያት እንዳላገኘበት የይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤቱ ጠቅሶ፤ “መልስ ሰጪን መጥራት ሳያስፈልግ፣ ይግባኙ አያስቀርብም” በማለት መዝገቡን መዝጋቱን በተጨማሪ ትእዛዙ አስታውቋል፡፡ የደብሩ አስተዳደር፣  ለሰበር ሰሚ ይግባኝ እንደሚጠይቅ ተጠቁሟል፡፡

የ2017 ቶታል የአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ  የምድብ ፉክክር 25ኛ ዙር ወዘተ ቢሮ ቅዱስ ጊዮርጊስ በአዲስ አበባ ስታድየም የቱኒዚያውን ኤስፔራንስ የፊታችን ማክሰኞ ያስተናግዳል፡፡ ባለፈው ሳምንት የቀጠለው በምድብ  ማጣርያ የመጀመርያ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሜዳው ውጭ ከደቡብ አፍሪካው ሜመሎዲ ሰንዳውንስ ጋር ተገናኝቶ 0ለ0 አቻ ሲለያይ፤ በምድብ 3  ሌላ የቱኒዚያው ኤስፔራንስ ዴቱኒስ በሜዳው የዲ.ሪ ኮንጎውን ኤኤስ ቪታ አስተናግዶ 3ለ1 አሸንፏል፡፡
ይህ በእንደህ እያለ ባለፈው ሐሙስ ቅዱስ ጊዮርጊስ የ2009 የኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ሻምፒዮናነት ክብሩን ያረጋገጠ ሲሆን ኤስፔራንስም በተመሳሳይ ቀን የቱኒዚያ ሊግ 1 አሸናፊነቱን አግኝቷል፡፡ ስለሆነም የፊታችን ማክሰኞ በአዲስ አበባ ስታድየም የሚደረገው የሁለቱ ክለቦች ፍልሚያ የሻምፒዮኖች ትንቅንቅ ይሆናል፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለፈው ሰሞን ለምድቡ የመጀመርያ ጨዋታ ወደ ደቡብ አፍሪካዋ ከተማ ፕሪቶርያ ያቀናው 18 ተጨዋቾችን በመያዝ ወሳኙን የአጥቂ መስመር ተሰላፊ ሳላዲን ሰኢድ በዚህ ጨዋታ ላይ 1 ቅጣት አለማሰለፉ የግብ እድሎችን እንዳይፈጥር አድርጎታል። ይሁንና ኡጋንዳዊው ግብ ጠባቂ ሮበርት አዶንካራ፤ እንዲሁም የተከላካይ መስመር ተሰላፊዎቹ ደጉ ደበበ እና አስቻለው ታመነ ወሳኝ ሚና ሊጫወቱ የቻሉበት ፍልሚያ ነበር። በፕሪቶርያ በሚገኘው የሜመሎዲ ሰንዳውንስ ስታድዬም በሺዎች የሚቆጠሩ በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ቅዱስ ጊዮርጊስ በህብረት በመደገፍ የፈጠሩትን ድምቀት ሚዲያዎች አድንቀውታል፡፡
የቅዱስ ጊዮርጊሱ አሰልጣኝ ማርቲን ኖይ ከሜመሎዲ ሰንዳውንስ ጋር ከመጫወታቸው በፊት ለካፍ ድረገፅ በሰጡት አስተያየት የምድብ ፉክክሩ ላይ የሚገኙት ሁሉም ክለቦች የአፍሪካ ምርጦች እንደሆነ በመግለፅ ምንም አይነት ጨዋታ ቀላል አይደለም ብለው ነበር፡፡ ክለባቸው ከአምናው ሻምፒዮን ጋር  አቻ ሊወጣ የቻለው በሱፕር ስፖርት ስርጭት ስለሜመሎዲ ሰንዳውንስ ብዙ በማወቃችንና ልዩ ክትትል አድርገን በመዘጋጀታችን ነው ብለዋል፡፡‹‹ ሆላንዳዊ ነኝ፡፡ የጨዋታ ትንተና በዚያ አገር አሰልጣኝነት የተለመደ ነው፡፡ በተለያዩ የግንኙነት መረቦች መረጃዎች እንሰበስባለን፡፡ ያንን በመንተራስ ታክቲክ እነድፋለሁ›› በማለትም ለካፍ ኦንላይን አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ በአፍሪካ እግር ኳስ በአሰልጣኝነት ሲሰሩ 17 ዓመታን ያስቆጠሩት ማርቲ ኖይ በ2012 እኤአ ላይ በኬፕታውኑ ክለብ ሳንቶስ የሰሩበትም ልምድ ስላላቸው በርግጥም ስለደቡብ አፍሪካ ክለቦች እንግዳ አይደሉም፡፡
ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር በተደረገው ጨዋታ በሜመሎዲ ሰንዳውንስ በኩልም ከፍተኛ ግምት የተሰጠው ተጨዋች ኡጋንዳዊው ግብ ጠባቂ ዴኒስ ኦንያንጎ ነበር፡፡ በደቡብ አፍሪካ ሊግ የወሩ ኮከብ ሆኖ ጨዋታውን የተሰለፈው የ31 ዓመቱ ዴኒስ ኦንያንጎ በ2005 እና በ2006 እኤአ ላይ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ መጫወቱ የሁለቱን ክለቦች ግንኙነት ልዩ አድርጎታል፡፡ የኡጋንዳ ብሄራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ ሆኖ የሚያገለግለው ዴኒስ ኦንያንጎ በ2016 እኤአ ላይ አገሩን ከ38 ዓመታት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ ያበቃ፤ ከክለቡ ሜመሎዲ ሰንዳውንስ ጋር በ2016 የአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግና የአፍሪካ ክለቦች ሱፕር ካፕ እንዲሁም የደቡብ አፍሪካ ሊግ ሻምፒዮን በመሆን 3 ዋንጫዎችን የሰበሰበ ነው፡፡ በተጨማሪም በ2016 በአፍሪካ ውስጥ የሚጫወት አፍሪካዊ ኮከብ ተጨዋች ሆኖ በካፍ ሽልማት ያገኘ ነው፡፡ ዴኒስ ኦንያንጎ ከጨዋታው በፊት ለሱፕር ስፖርት በሰጠው አስተያየት ‹‹የቀድሞ ክለቤን የምገጥምበት አጋጣሚ በመፈጠሩ ደስ ብሎኛል፡፡ ስሜታዊ አይደለሁም፤ በፕሮፌሽናልነት የማገለግለው ክለቤን ነው ብሎ ነበር፡፡ የሜመሎዲ ሰንዳውንስ ዋና አሰልጣኝ ደግሞ የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድንን ሲያሰለጥኑ የነበሩት ፒትሶ ሞስማኔ ናቸው፡፡ በ2016 በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን ምርጥ አሰልጣኝ ሆነው ለሽልማት የበቁት ፒትሶ ‹‹ የምንገኘው በሞት ምድብ ነው፡፡ ዘንድሮ የሻምፒዮንስ ሊግ የምድብ ፉክክር የሽልማት ገንዘቡ በማደጉ እና የቴሌቭዥን ስርጭቱ በመስፋቱ ጠንካራ ነው፡፡ የምንገኘው በሞት ምድብ ነው። ሲሉ ይናገራሉ፡፡
ሞሲማኔ ክለባቸው በሜዳው ነጥብ መጣሉ አላስደሰታቸውም፡፡ ክለባቸው ባለፈው የውድድር ዘመን የአህጉሪቱ ሻምፒዮን ለመሆን ሲበቃ በመላው አፍሪካ በመዘዋወር ያደረጋቸው ጨዋታዎች በተጨዋቾቹ ላይ መዳከም መፍጠሩን ምክንያት አድርገውም ጠቅሰዋል። በዘንድሮ የደቡብ አፍሪካ ፕሪሚዬር ሊግ ክለቡ የነበረበት የጨዋታዎች መደራረረብ ተፅዕኖ መፍጠሩንም ያማርራሉ፡፡ ሜመሎዲ ስንዳውንስ የአምና ሻምፒዮናነቱን ለማስጠበቅ ሊከብደው ይቻላል ያሉት አሰልጣኙ በ2ኛ ዙር ጨዋታ፡፡ ወደ ኪንሻሳ በመጓዝ ለምናስመዘግበው ውጤት ከተጨዋቾቼ ቁርጠኝነት እጠብቃለሁ ብለዋል፡፡ ኤኤስቪታ ክለብ በአርቴፊሻል ሜዳ ጨዋታውን በማስተናገድ ብልጫ ሊወስድ ስለሚችል ተጫዋቾቻቸው አዕምሯቸውን ማዘጋጀት እንዳለባቸውም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ከምድቡ የመጀመርያ ጨዋታዎች በኋላ ኤስፔራስን ዴ ቱኒስ በ3 ነጥብ እና በ2 የግብ ክፍያ መሪነቱን ሲይዝ ሜመሎዲ እና ጊዮርጊስ በእኩል 1 ነጥብ ያለምንም ግብ ተከታታይ ደረጃ ላይ ተቀምጠው ኤኤስ ቪታ ያለምንም ነጥብ በመጨረሻ ደረጃ ላይ ነው፡፡
የምድብ ፉክክሩ ሁለተኛ ዙር ጨዋታዎች በሚቀጥለው ሳምንት ሲደረጉ ማክሰኞ ላይ ቅዱስ ጊዮርጊስ በሜዳው የቱኒዚያውን ኤስፔራንስ ዴ ቱኒዝ ሲገጥም፤ የዲ.ሪ ኮንጎው ኤኤስ ቪታ  የአምናውን የሻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊ  ሜሞሎዲ ሰንዳውንስ በኪንሻሳ ከተማ ያስተናግዳል፡፡

 3 ማራቶኒስቶች፤ 20 ሳይንቲስቶች፤ 30 አሯሯጮች ተሳትፈዋል

      የአሜሪካው የስፖርት ትጥቅ አምራች ኩባንያ ናይኪ Breaking2 በሚል ስያሜ በነደፈው ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች ለመግባት  ልዩ ፕሮጀክት የመጀመርያውን ሙከራ ከሁለት ሳምንት በፊት አድርጓል፡፡ በሙከራ ውድድሩ ኬንያዊው ኤሊውድ ኪፕቾጌ ለታቀደው ሰዓት በጣም በመቃረብ ሲሳካለት፤ ኤርትራዊው ዘረሰናይ ታደሰ እና ኢትዮጵያዊው ሌሊሳ ዴሲሳ ግን አልተሳካላቸውም ነበር።
ናይኪ ከ2014 እኤአ ጀምሮ በፕሮጀክቱ ላይ በተለያዩ አቅጣጫዎች ሲሰራ ቢቆይም ስለመጀመርያው የሙከራ ውድድር ለመላው ዓለም  በይፋ በማስታወቅ የሰራው ከ6 ወራት ወዲህ ነበር፡፡
በናይኪ ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች የመግባት Breaking2 ፕሮጀክት  ላይ 3 የዓለማችን ምርጥ ማራቶኒስቶች ተሳትፈዋል፡፡ በማራቶን የኦሎምፒክ ሻምፒዮን የሆነውና የ32 ዓመቱ ኬንያዊ አትሌት  ኤሊውድ ኪፕቾጌ፤ በማራቶን በዓለም ሻምፒዮና የነሐስ ሜዳልያ ያገኘው፣ የቦስተን ማራቶንን ለሁለት ጊዜያት ያሸነፈው የ27 ዓመቱ ኢትዮጵያዊ አትሌት ሌሊሳ ዴሲሳ እና የዓለም የግማሽ ማራቶን ክብረወሰን ባለቤት የሆነው የ35 ዓመቱ ኤርትራዊ አትሌት ዘረሰናይ ታደሰ ናቸው፡፡ ሶስቱ የማራቶን አትሌቶች በናይኪ ፕሮጀክት ስር በመታቀፍ ለመጀመርያው የሙከራ ውድድር ዝግጅት ሲያደርጉ ነበር፡፡ ለፕሮጀክቱ በሰጡት ትኩረትም በትልልቅ የማራቶን ውድድሮች በመሳተፍ የሚያገኟቸውን የሽልማት ገንዘቦች ሌሎች ጥቅማጥቅሞች ትተዋል። ማራቶኒስቶቹ በፕሮጀክቱ ላይ በሚኖራቸው ተሳትፎ የትጥቅ ስፖንሰራቸው ከሆነው ናይኪ በይፋ ያልተገለፁ ክፍያዎችን እንዳገኙ ግን መረጃዎች አውስተዋል፡፡ በተለያዩ የሙያ እና የእውቀት መስኮች ከተሰባሰቡ የዓለማችን ምርጥ የአትሌቲክስ ስፖርት የባለሙያዎች ቡድኖች ጋር ዝግጅቶቻቸውን አድርገዋል። በስፖርት ሳይንስ፤ ስልጠና፤ ህክምና አዳዲስ አሰራሮችን በመመራመር በBreaking2 ፕሮጀክት ላይ የሰሩት  ከ20 በላይ ሳይንቲስቶች ናቸው፡፡ ይህም በፕሮጀክት አይነቱ ግቡ የባለሙያዎች ስብስብ ነው ናይኪ አዳዲስ የመሮጫ ጫማዎች እና ማልያዎችን ከማቅረቡም በላይ፤ በላቀ ደረጃ የሳይንስ፤  ቴክኖሎጂ፤ የአመጋገብ፤ የውሃ እና ሃይል ሰጪ መጠጦችን አዘጋጅቶላቸዋል፡፡ ከ30 በላይ ምርጥ አሯሯጮችን በመመደብም በስፋት ተንቀሳቅሷል። ለዚሁ ሙከራ ተብሎ ዙም ሱፕርፍላይ ኤሊት የተባለ የመሮጫ ጫማን ለሶስቱ አትሌቶች በአዲስ መልክ ናይኪ ያመረተ ሲሆን በውድድሩ ወቅት ሰዓቱንና የአሯሯጭ እና የራጮቹን ፔስ የሚለካ የኤሌክትሪክ መኪናም ነበር፡፡
በፕሮጀክቱ ስኬታማነት የስፖርቱን የወደፊት እድገት ለማነሳሳትና ለፕላኔታችን ምርጥ አትሌቶች መነቃቃትን የመፍጠር ዓላማን ያነገበው ናይኪ፤ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በፕሮጀክቱ በሚያደርጉት እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ ሚሊዮኖችን የሚያነሳሳ ውጤት  ይመዘገባል በሚል ተስፋ ነበረው፡፡
በBreaking2 የሙከራ ውድድሩን ፕሮጀክት ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች ለመግባት ናይኪ የመጀመርያ የሙከራ ውድድሩን ያደረገው በጣሊያኗ ከተማ  በሚገኘው  አውቶድሮሞ ናዚዮናሌ ሞንዛ በተባለ ዝግ ስታድዬም ነበር፡፡ የፎርሙላ ዋን የመኪና ሽቅድምድም መወዳደርያ ትራክ ላይ ነበር የአንድ ዙር መሙ ርዝማኔ 100 ሜትር የሆነው የስታድዬሙ ትራክ በመጠምዘዣዎቹ ምቹነት እና አካባቢ ተስማሚ የአየር ሁኔታ በናይኪ ተመራጭ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ በማራቶን የምንግዜም ፈጣን ሰዓቶች ደረጃ ሶስተኛ ሆኖ የተቀመጠውን 2፡03፡05 በ2016 እኤአ ላይ በለንደን ማራቶን ሲያሸንፍ ያስመዘገበውና የኦሎምፒክ ሻምፒዮኑ ኤሊውድ ኪፕቾጌ በፕሮጀክቱ የመጀመርያ ሙከራ ከባዱን ፈተና በአስደናቂ ብቃት በመወጣት ልዩ መነቃቃትን ፈጥሯል፡፡ የማራቶኑን ርቀት ሲጨርስ የገባበት ሰዓት 2፡00፡25 ነበር፡፡ ከ2 ሰዓት በታች ለመግባት  በ26 ሰከንዶች በመዘግየቱ አልተሳካለትም ፤ ይሁን እንጅ የመኪና መወዳደደርያ ትራኩን የ100 ሜትር መም 422 ጊዜ ሲዞር እያንዳንዱን ዙር በ17 ሰከንዶች መሸፈኑ ለብዙዎች የገረመ ብቃት ነበር፡፡ የዓለም ማራቶን ሪከርድ በ2014 የኬንያው ዴኒስ ኪሜቶ በበርሊን ማራቶን በ2፡02፡57 የተመዘገበው እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በናይኪ ፕሮጀክት የተሳተፈው ኪፕቾጌ የገባበት ሰዓት ይህን የዓለም የማራቶን ሪከርድን በ2 ደቂቃ ከ32 ሰከንዶች ቢያሻሽልም በክብረወሰንነት ግን የሚመዘገብ አይደለም፡፡ የመጀመርያው ምክንያት የመወዳደርያው ትራክ በአይኤኤኤፍ እውቅና ያገኘ ባለመሆኑ ሲሆን በውድድሩ ላይ የተመደቡ አሯሯጮች እየተቀያየሩ መስራታቸው ሌላው ነው ፡፡ ኪፕቾጌ ከውድድሩ በኋላ ያስመዘገበውን ሰዓት ታሪካዊ ክስተት ብሎታል፡፡ በአጠቃላይ ግን  የናይኪ ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች የመግባት ሙከራ የመላው ዓለምን ትኩረት የሚስብ ትልቅ ክስተት ሲሆን የዓለም ሚዲያዎች አውስተዋል፡፡ ከኤሊውድ ኪፕቾጌ ሌላ መብቃቱን ዘረሰናይ ታደሰ እና ሌሊሳ ዴሲሳ በተመሳሳይ ፕሮጀክት ታቅፈው እየሰሩ ቢሆንም አልሆነላቸውም፡፡ የዓለም ግማሽ ማራቶን ሪከርድ ባለቤት የሆነው የኤርትራው ዘረሰናይ  በ2፡06፡51 ሲጨርስ የኢትዮጵያ ሌሊሳ ደሲሳ ደግሞ በ2፡14፡10 ርቀቱን ሸፍኗል፡፡
ለታሪካዊው የማራቶን ከፍተኛ ውጤት በተለያዩ ፕሮጀክቶች ቅድሚያ ግምት የሚያገኙት ከሁለቱ የምስራቅ አፍሪካ አገራት ኬንያና ኢትዮጵያ የሚወጡ ማራቶኒስቶች ናቸው፡፡ በተለይ ደግሞ በኢትዮጵያ በቆጂ በምትባለዋ የክልል ከተማ እንዲሁም በኬንያ ኤልዶሬት እና ኢቴን በተባሉት ከተማዎች እንደሚገኙ የብዙዎች እምነት ነው፡፡ በእነዚህ የምስራቅ አፍሪካ የገጠር ከተሞች በማራቶን ፈጣን ሰዓቶችን የሚያመዘግቡ እና ትልልቅ ውድድሮችን የሚያሸንፉ ሯጮች በብዛት እንደሚገኙ የሚታወቅ ነው፡፡ በየከተሞቹ ያሉት መልክዓምድራዊ ሁኔታዎች፤ የድህነት ኑሮ፤ የስኬታማ ማራቶን ሯጮች መብዛት፤ ባህላዊ የአመጋገብ ስርዓቶች ለማራቶን ስኬታቸው ተጠቃሽ ምክንያቶች ናቸው፡፡
ከዚህ አንፃር በናይኪ Breaking 2 ፕሮጀክት ኤሊውድ ኮፕቾጌ ያስመዘገበው ውጤት ግምቱን ወደ ኬኒያ አትሌቶች እንዲያጋድል አድርጎታል፡፡ ኢትዮጵያዊው ሌሊሣ ዴሢሣ የገባበት ሰዓት ከምርጥ ማራቶኒስቶች አማካይ ሰዓት የራቀ መሆኑ የኢትዮጵያን አትሌቲክስ የሚያስቆም ነው፡፡  
ናይኪ በመጀመርያ የሙከራ ውድድሩ ከ2 ሰዓት በታች የመግባት እቅዱን ማሳካት ባይችልም በማርኬቲንግ እንቅስቃሴዎቹ ተሳክቶለታል፡፡ በተለይ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎች ያገኘው ትኩረት የስፖርት ትጥቅ አምራቹን ብራንድ ያሳደገ ነበር፡፡ ስለBreaking2 የሚለው የፕሮጀክቱ በሚሊዮኖች እየተጠቀሰ በመላው ዓለም በትልቅ የአትሌቲክስ ስፖርት ዘጋቢ ድረገፆች፤ መፅሄቶች፤ ጋዜጠኞች እንዲሁም በማህበራዊ ሚዲያዎች ተዋውቋል፡፡ ናይኪ በዚህ ፕሮጀክት ላለፉት 3 ዓመታት ሲሰራ ለማስታወቂያ የመደበው በጀት ከ800 ሚሊዮን ዶላር በላይ ነው፡፡ ብራንድዎች የተባለ ተቋም ይፋ ባደረገው መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎች ስለሙከራው ከ600ሺ ጊዜ በላይ መጠቀሱን 400ሺ ጊዜ #Breaking2 የሚለው ቃል መፃፉን አስታውቋል፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ በአትሌቲክስ ዙርያ ትንታኔ የሚሰሩ ድረገፆች እና ኤክስፐርቶቻቸውም አድናቆት ሰጥተውታል፡፡ በላይቭ ስትሪሚንግ በኢንተርኔት ድረገፅ ውድድሩ ባገኘው ስርጭት በ2 ቀናት 5 ሚሊዮን ተመልካች ማግኘት ችሏል፡፡ እነ ኪፕቾጌ የሮጡበት ቫፖርፍላይ ኤሊት የተሰኘው የናይኪ የጫማ ምርት በ250 ዶላር የሚሸጥ ሲሆን የሙከራ ውድደሩ የምርቱን ገበያ አሟሙቆታል፡፡
ማራቶን ከ2 ሰዓት በታች ለመግባት እንደሚቻል በማቀድ በፕሮጀክት ደረጃ የሚንቀሳቀሰው ናይኪ ብቻ አይደለም፡፡   ስኮትላንዳዊው ፕሮፌሰር ያኒስ ፒስተሊደስ በsub2hr ፕሮጀክታቸው ከጀርመኑ የትጥቅ አምራች ኩባንያ አዲዳስ ጋር በመንቀሳቀስ ፈርቀዳጅ ሆነው ይጠቀሳሉ፡፡ ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች መግባትን አስመልክቶ በርካታ በአትሌቲክስ ላይ በሚያተኩር ዘገባቸው በሚታወቁ መፅሄቶች፤ ድረገፆች እና የመረጃ ሚዲያዎች በየጊዜው ትንታኔዎች መቅረባቸውን ቀጥለዋል፡፡ በአጀንዳው ላይ በማተኮር የተፃፉ ታዋቂ መጽሐፍትም አሉ፡፡ በተለይ በኤድ ሲዛር የተፃፈውን “The quest to Run Impossible Marathon መጥቀስ ይቻላል፡፡  
ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች ለመግባት በርካታ ወሳኝ ሁኔታዎችን እና አስተዋጽኦዎች ይኖራሉ፡፡ 1፡59፡59 ሰዓትን በማራቶን ለማስመዝገብ 1 ማይል ርቀትን በ4 ደቂቃ ከ34 ሰኮንዶች መሸፈን ግድ ይሆናል፡፡ ከወቅታዊ ሪከርድ በየማይሉ በ7 ሰኮንዶች በፈጠነ አሯሯጥ ነው። የስፖርቱ  ሳይንቲስቶች የማራቶን ርቀትን በሰው ልጅ የተፈጥሮ ብቃት ለመሸፈን የሚቻልበት የመጨረሻው የሪከርድ ሰዓት ወሰኑ 1፡57፡57 እንደሆነ የሚገልፁ ሲሆን ይህም ማራቶን ከ2 ሰዓት በታች ለመግባት እንደሚቻል የሚያመለክት ነው፡፡  
ስፖይክ የተባለና ከዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌደሬሽኖች ማህበር ጋር የሚሰራ ድረገፅ በአንድ ወቅት  በሰራው ዘገባ ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች ለመግባት የሚያስፈልጉ 13 ወሳኝ ሁኔታዎችን ዘርዝሯል፡፡ ከሪኮርዱ 5 ደቂቃዎች ባለፉት 20 ዓመታት መቀነሳቸው፤ አሁን ከተያዘው ሪኮርድ ከ2 ሰዓት በታች ለመግባት የሚቀሩት ከ3 ያነሱ ደቂቃዎች መሆናቸው፤ ከ2 ሰዓት 05 ደቂቃዎች በታች የሚገቡ አትሌቶች ከ30 በላይ ማለፋቸው፤ በማራቶን የፈጣን ሰዓቶች ደረጃ በየዓመቱ እስከ 30ኛ ደረጃ አዳዲስ አትሌቶች በብዛት መግባታቸው፤ በመጀመሪያ ማራቶናቸው ከ2፡04 በታች የሚገቡ አትሌቶች መገኘታቸው፣ በትራክ ከፍተኛ ልምድ ያካበቱ አትሌቶች ወደ ማራቶን በመግባት ስለሚሳካላቸው የሚሉት ይጠቀሳሉ፡፡ በአትሌቲክስ ስፖርት አሰለጣጠን በሳይንሳዊና ቴክኖሎጂ የምርምር ተግባራት የተጋዙ ፕሮጀክቶችንም በትኩረት መስራትን ወሳኝ እንደሆነ የሚገልፁ አሉ፡፡
የሰው ልጅ በሚችለው ብቃት ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች ለመግባት  የስልጠና ሳይንስ እና ቴክኖሎጂም ለውጥ የሚፈጥሩም ናቸው፡፡ ከ40 አመት በፊት የነበረው ስልጠና አሁን በከፍተኛ ደረጃ በምርምሮች ማደጉ እንደ አጋዥ ምክንያት ሊጠቀስ የሚችል ነው።  በአዲዳስ፤ በናይኪ እና በፑማ የትጥቅ አምራች ኩባንያዎች የሚቀርቡ የመሮጫ ማልያዎችና ጫማዎችም የሚኖራቸው አስተዋፅኦ ቀላል አይደለም። በማራቶን ውድድሮች የሚመደቡ አሯሯጮች ልዩ ብቃት እና በማራቶን ውድድሮች ዳጎስ ያሉ ሽልማቶች፤ የስፖንሰርሺፕ እና የቦነስ ክፍያዎች ከፍተኛ ገቢ መገኘቱ ሌሎቹ አስተዋፅኦዎች ናቸው፡፡
በመላው ዓለም ከሚካሄዱና የሪከርድ ሰዓት ህጋዊ ከሚሆንባቸው ትልልቅ  ውድድሮች መካከል ከ2 ሰዓት በታች ለመግባት ዋና እጩዎች የሚባሉት በበርሊን እና ለንደን ከተሞች  የሚዘጋጁት ማራቶኖች ነበሩ፡፡ ናይኪ የመጀመርያ ሙከራን በመኪና ውድድር ትራክ ላይ ማድረጉ ብዙዎችን አላስደሰተም፡፡
ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች መግባት በተለያዩ ጥናቶች እና ትንታኔዎች እስከ 2028፤ 2035 ወይም 2041 እኤአ ላይ እንደሚሳካ ይገመታል፡፡ በናይኪ Breaking2 ፕሮጀክት በ2017 ለማሳካት ታቅዶ አልሆነም፡፡ ስኮትላንዳዊው ፕሮፌሰር ያኒስ ፒስታሊደስ በበኩላቸው ከአዲዳስ ጋር በሚሰሩበት በsub2hr ፕሮጀክታቸው እስከ 2019 እኤአ የሚገኝ ውጤት ነው በሚል ስራቸውን ቀጥለዋል፡፡

አንዲት ሴት ስታረግዝ በተለይም የእንግዴ ልጅ ከሚባለው ጋር በተያያዘ አዳዲስ ሆርሞኖች ስለሚመረቱ በሁሉም የሰውነትዋ ክፍሎች ላይ አዳዲስ ለውጦች ይታያሉ። ዶ/ር ድልአየሁ በቀለ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ መምህርና የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት ለዚህ እትም እንደገለጹት ለእርጉዝ ሴት የአካል ለውጥ ምክንያት የሚሆኑ ብዙ ነገሮች አሉ። እርጉዝ ኤት የሰውነትዋ ክብደት ይጨምራል። ይህ የሰውነት ክብደት መጨመር ደግሞ የሚፈለግና የሚጠበቅ ሲሆን አንዲት ሴት በአንድ የእርግዝና ወቅት ከ9-16 ኪሎ ትጨምራለች።ይህ ኪሎ ከሚጨምርበት ምክንያትም ዋናዋናዎቹ፡-
የሚያድገው ልጅ ጽንስ መኖሩ፣
እንግዴ ልጅ ፣
የሽርት ውሀ ፣
የራስዋ ደም መጠን መጨመር ቀይ የደም ሴል መጠን ፣የውሀው መጠን
የኩላሊት መጠን መጨመር ፣የሚያመርተው የሽንት መጠን መጨመር፣
የተለያዩ የሰውነት ክፍሎች ማደግየጡት መጨመር፣
የማህጸን ማደግ ማህጸን ከእርግዝና በፊት ከ70 እስከ 100 ግራም ሲሆን ልክ እርግዝናው ዘጠኝ ወር ሲደርስ አንድ ኪሎ ይደርሳል።ይህም ማለት ከአስር አጥፍ በላይ ክብደቱ ይጨምራል።
ከዚህ በተጨማሪም በአይን በቀላሉ የሚታዩ የሰውነት ለውጦች ይኖራሉ። ለምሳሌም በቆዳ ላይ መጥቆር ፣በሆድ መካከል የሚታይ ጥቁረት በሆድ ፣በታፋ እና በጭን አካባቢ የሚታዩ ሸንተረር መሰል ነገሮች ይታያሉ። ሁሉም እርጉዝ እናቶች ላይ ባይሆንም 80 % የሚሆኑት ላይ የእግር ማበጥ ይታያል። ብዙ ሴቶች የእግር ማበጥን እንደችግር ሊያዩት ይችላሉ። ነገር ግን ፊትና እጅ አብረው የሚያብጡ ካልሆነ በስተቀር ብቻውን እንደችግር ሊታይ አይገባውም። የእጅ እና ፊት እብጠት ከታከለ ግን ከደም ግፊት ጋር በተያያዘ ወይንም ሌላ ችግር ሊሆን ስለሚችል ስጋት ሊኖር ገባል።
አንዲት እናት ከእርግዝና በፊት የነበራት ክብደት በእርግዝና ወቅት ይጨምራል። ከወሊድ በሁዋላ ደግሞ በተወሰኑ ሳምንታት ውስጥ ሌላ አይነት ክብደት ይመዘገባል። ይም ሂደት የታወቀ ነው። ነገር ግን በምን መንገድ ነው ከእርግዝና በፊት ወደነበረችበት ክብደት መመለስ የምትችለው? ተብሎ ሲጠየቅ ብዙ ምላሾች ይኖሩታል። አንዲት ሴት ወፈርፈር ብላ ስትታይ ወልደሽ ነው እንዴ? የሚለው ጥያቄም የተለመደ ነው። ስለዚህ አንዲት ሴት ከእርግዝናና ከወሊድ በሁዋላ የነበረውን ክብደትዋን ቀድሞ ወደነበረበት ወፍራም ካልነበረች እንዴት ልትመልሰው ትችላለች ሲባል ከአመጋገብና ከአኑዋኑዋርዋ ጋር የተገናኘ ይሆናል። ብለዋል ዶ/ር ድልአየሁ በቀለ።
ምግብን አለማስወገድ፡-
አንዳንድ እናቶች በእርግዝና ጊዜ የተከሰተውን ክብደት ለማስወገድ ሲሉ (diet) ምግብን ወደማስወገድ ደረጃ የሚደርሱ አሉ። ይህ ግን ስህተት ነው። አንዲት እናት በወለደቸበት ወቅት ልትመግበው ጡትዋን ልታጠባው የሚገባው ልጅ አላት። በዚህ ላይ ሌሎች የእናትነት ጭን ቀቶች ተደራርበው ምግብን ከማስወገድ ጋር ከፍ ያለ ጉዳት ሊያደርሱባት ይችላሉ። ከሚደር ሱት ችግሮች መካከልም ጭርሱንም ውፍረትን እንዲመጣ ማድረግ አንዱ ነው። ስለዚህም ምግብን ማቆም ሳይሆን ምግብን አመጣጥኖ መውሰድ ብልህነት ይሆናል። ለምሳሌም አትክ ልትና ፍራፍሬ ፣ቅጠላቅጠል ወይንም የእህል ዘሮች እንደ ስንዴ ገብስ የመሳሰሉ በቆሎ መልክ የሚዘጋጁ ምግቦችን መጠቀም ጠቃሚ ይሆናል።
ከፍተኛ ንጥረ ነገር ያላቸውን ምግቦች መመገብ፡-
የወለደች ሴት ከፍተኛ ንጥረ ነገር ያላቸውን እና ቀለል ያለ ፕሮቲን እና ቅባት ያላቸውን ምግቦች መመገብም አለባት።ለምሳሌም የ ኦሜጋ 3 ውጤት ባለቤቶች ከሆኑት እንደ አሳ ሰርዲን ቱና ከዚህም በተጨማሪ ወተት ፣እርጎ፣ የተፈጨ ስጋ፣ የዶሮ ስጋ እንዲሁም ባቄላ ነክ ነገሮችን በፕሮግራም በምግብ ውስጥ አካቶ መውሰድ ይጠቅማል። ከላይ የተጠቀሱትና መሰል ምግቦችን ከፍተኛ ቅባት የሌላቸውና ከፍተኛ ንጥረ ነገር ያላቸው በመሆናቸው ጠቀሜ ታቸው ለእናትየውም ጡት ለሚጠባው ልጅም ነው።
ጡት ማትባት፡-
ጡት ማጥባት ሌላው ክብደትን ለመቀነስ የሚረዳ ዘዴ መሆኑን አንዳንድ ጥናቶች ያስረዳሉ። አንዳንድ ጥናቶች ደግሞ ጡት ማጥባትና ክብደት ምንም አይገናኙም ይላሉ። ዋናው ነገር ጡት ማጥባት ለልጆች እጅግ ጠቃሚ በመሆኑ ወላጆች ይህን እንዲፈጽሙ ይደገፋል።ስለዚህም እናቶች በጡት ማጥባት ወቅት ጥሩ ወተት እንዲኖራቸው በሚል ለክብደት የሚዳርግ ምግብ ከመመገብ ተወግደው ቅባትነት የሌላቸውን ምግቦች ማለትም ከላይ እንደተጠቀሰው የእህል ዘር ቅጠላ ቅጠል እና ፍራፍሬዎች እንደ እንጆሪ ብርቱካን የመሳሰሉትን መጠኑ ሳይበዛ እንቁላል ጭምር መመገብ ፣ቡናማ መልክ ያለው ሩዝ የመሳሰሉትን ቢመገቡ ይመከራል።
ውሀ መጠጣት፡-
ሌላው ክብደትን ለመቆጣጠር የሚያስችለው ዘዴ ውሀ መጠጣት ነው። ውሀ በደንብ መጠጣት ረሀብን አስወግዶ ብዙ ምግብ ከመውሰድም ሊያስቆም ስለሚችል ጠቃሚ ነው። በተያያዥም አንዳንድ ሕመሞችን ለማስወገድ ፣በሰውነት ውስጥ የሚፈጠሩ መርዛማ ነገሮችንም ለማስወገድ ስለሚረዳ በተጨማሪም ምግብን ለመፍጨት ስለሚያፋጥን ውሀ በቀን ቢያንስ እስከ ሁለት ሊትር መጠጣት ይመከራል። በቂ ውሀ ጠጥቻለሁ? ወይንስ አልጠጣሁም ? የሚለውን ለማወቅ አንዲት እናት የሽንትዋ ቀለም ውሀማ መሆኑን ወይንም በየ3 እና 4 ሰአት መሽናትዋን መከታተል አለባት።
የሰውነት እንቅስቃሴ ማድረግ፡-
የሰውነት እንቅስቃሴ ወይንም እስፖርት መስራት ክብደትን ለመቆጣጠር አንዱ መንገድ ነው። የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ የእናትየውን ክብደት ከመቀነሱም በላይ በእናትየውም ሆነ አዲስ በተወለደው ልጅ ላይ ሊኖር የሚችለውን ጭንቀት ያስወግዳል። ከዚህም በተጨማሪ የእንቅልፍ ሁኔታን ያስተካክላል። በእርግጥ አንዲት እናት ልጅ በወለደች በጥቂት ቀን ውስጥ ወደ እስፖርት ማዘውተሪያ መሄድ ላይጠበቅባት ይችላል። ነገር ግን በየቀኑ ልጅዋን ይዛ በቤት ውስጥ ወይንም በግቢው ውስጥ እርምጃ ወይንም ሶምሶማ በማድረግ መጀመር ትችላለች። በሳምንት ጊዜ ውስጥ የተለያዩ የሰውነት እንቅስቃሴዎችን እስለ 150 ደቂቃዎች በመመደብ መፈጸም ተገቢ ነው። ከተቻለም ለወላድ እናቶች ፕሮግራም ወዳላቸው የእስፖርት ቤቶች በመሄድ እንቅስቃሴውን ማድረግም ይመከራል። አንዲት እናት የእስፖርት እንቅስቃሴ ከማድረ ግዋ በፊት በተለይም የቀዶ ሕክምና ተጠቃሚ ከሆነች ከሐኪምዋ ጋር መመካከር ይጠበቅ ባታል።
ጥሩ እንቅልፍ፡-
አዲስ ልጅ መወለዱን ተከትሎ በሚመጡ የተለያዩ ኃላፊነቶችና ግዴታዎች ምክንያት ልጅ ከመወለዱ በፊት እንደነበረው በቀን የስምንት ሰአት እንቅልፍ መተኛት ሊከብድ ይችላል።ነገር ግን አንዲት እናት ጥሩ እንቅልፍ ካላገኘች በወሊድ ምክንያት የመጣ ውፍረትን እንዳይቀንስ በማድረግ ረገድ እንደ አንድ ትልቅ እንቅፋት ሊቆጠር ይችላል። አንድ ጥናት እንደሚያሳየው ከ5 ሰአት በታች የሚተኙ እናቶች በቀን 8 ሰአት ከሚተኙት ጋር ሲነጻጸር ውፍረታቸውን መቀነስ እንደሚከብዳቸው ይገልጻል። ሙሉ ስምንት ሰአቱን በቀጥታ መተኛት እንኩዋን ባይቻል በተገኘው አጋጣሚ አጫጭር እንቅልፍ በመተኛት እረፍት በማድረግ ማካካስ እንደሚገባ ጥና ቶች ይመክራሉ።
በአጠቃላይም ልጅ ባረገዙ ጊዜ የሚከሰተውን ውፍረት ከወሊድ በሁዋላ ቀድሞ ወደነበሩበት ለመመለስ የህክምና ባለሙያዎችንና በተለይም የምግብ ስርአት አማካሪዎችን ማማከር ጠቀሜታው የጎላ ነው። የህክምና ባለሙያዎቹ በምን ያህል ጊዜ ምን ያህል ክብደት መቀነስ እንደሚገባና ምን አይነት እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባ አስፈላጊውን ምክር ይለግሳሉ። የምግብ ስርአት አማካሪዎቹ ደግሞ ክብደትን ለመቀነስ ሲባል ምግብን ከመውሰድ መታቀብ ወይንም ( diet ) ውስጥ መግባት ትክክል አለመሆኑንና ይልቁንም በደንብ የተመጣጠነ የምግብ አይነትን መጠቀም ለእናትየውም ለተወለደው ልጅ ጡት አመጋገብም እንደሚረዳ ይመክራሉ። ምናልባት ከምግብ ሰአት ውጭ ባሉ ጊዜያት ረሀብ ቢሰማ በረሀብ ጊዜ ሊወሰዱ የሚችሉ በቤት ውስጥ የሚዘጋጁ በቀላሉ የሚዘጋጁ ምግቦችን መመገብ ጠቃሚ ነው። ለምሳሌም በሀገራችን ከተለያዩ የእህል ዘሮች የሚዘጋጁ ቆሎዎችን መጥቀስ ይቻላል። ባጠቃላይም አንዲት እናት በእርግዝና ጊዜ የጨመረው ክብደትዋ ምን ያህል ነው? የሚለውን ሐኪምዋ አይቶ ይህ በአጭር ጊዜ ሊስተካከል ይገባዋል ወይንም በተወሰነ ጊዜ ማለትም እስከ 2 ወር ድረስ መቀነስ ይቻላል የሚለውን ማማከር ይችላል። ነገር ግን ክብደቱ ከእርግዝናም በፊት የነበረ ከሆነ ያንን ወደትክክለኛው የሰውነት አቋም ለማድረስ ከአመት በላይም ሊፈጅ ስለሚችል በትእግስት እርምጃ መውሰድ ከወላድዋ ይጠበቃል። እናቶች ምናልባትም ለተጨማሪ እርግዝና የሚዘጋጁ ከሆኑ አስቀድመው የሰውነት ክብደታቸውን ማስተካከል ይጠበቅባቸዋል።

     ሰሞኑን ይፋ የተደረገው የአመቱ የብሉምበርግ አለማቀፍ የጤና ሁኔታ አመላካች ሪፖርት፣ ጣሊያንን ከዓለማችን አገራት እጅግ ጤናማዋ በሚል በአንደኛ ደረጃ ላይ ማስቀመጡን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል፡፡
በ163 የዓለማችን አገራት ላይ የተሰራው የጤና ሁኔታ አመላካች ጥናት ሪፖርት፣ ጣሊያን በተለያዩ የጤና መስፈርቶች መሰረት ከአለማችን አገራት በአንደኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን የገለጸ ሲሆን በአገሪቱ አማካይ ዕድሜ ከፍተኛ መሆኑን፣ የጤና ተቋማትና ባለሙያዎች አቅርቦትም ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱንና ጤናማ አመጋገብ መኖሩን አስታውቋል፡፡
በዘንድሮው የብሉምበርግ የዓለማችን አገራት የጤና ሁኔታ ሪፖርት መሰረት፣ በጤናማነት ከጣሊያን በመቀጠል በቅደም ተከተላቸው እስከ አምስተኛ ደረጃን የያዙት አገራት አይስላንድ፣ ስዊዘርላንድ፣ ሲንጋፖርና አውስትራሊያ መሆናቸውንም  ዘገባው ገልጧል፡፡

የቢዮንሴ እና የጄይ ዚ ሃብት 1.16 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል
     በቅርቡ መንታ ልጆችን ወልደው ለመሳም እየተዘጋጁ የሚገኙት አሜሪካውያኑ ድምጻውያን ቢዮንሴ ኖውልስ እና የትዳር አጋሯ ጄይ ዚ ከሚሊየነርነት ወደ ቢሊየነርነት መሸጋገራቸውን የዘገበው ፎርብስ መጽሄት፣ የጥንዶቹ የጋራ ሃብት 1.16 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን አስታውቋል፡፡
የጄይ ዚ የተጣራ ሃብት 810 ሚሊዮን ዶላር መድረሱንና የባለቤቱ ቢዮንሴ ሃብት በበኩሉ 350 ሚሊዮን ዶላር መሆኑን የጠቆመው ፎርብስ፤ ጥንዶቹ ወደ ቢሊየነርነት ያሸጋገራቸውን አብዛኛውን ሃብት ያፈሩት በሮክ ኔሽን እና በሌሎች የጄይ ዚ ትርፋማ ኩባንያዎች አማካይነት እንደሆነም ገልጧል፡፡
በትዳር ቆይታቸው የአምስት አመት ሴት ልጅ ያፈሩት ጥንዶቹ፣ በታዋቂው ታይዳል ኩባንያ ውስጥ ጠቀም ያለ የሃብት ድርሻ እንዳላቸው የጠቆመው ፎርብስ መጽሄት፤ ጄይ ዚ ባለፈው ሳምንት ላይቭ ኔሽን ከተባለው ታዋቂ ኩባንያ ጋር ለ10 አመታት የሚቆይና 200 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት አዲስ ውል መፈጸሙንም አስታውሷል፡፡

ፌስቡክ ታዋቂው የማህበራዊ ድረ ገጽ ዋትሳፕን የራሱ ለማድረግ ካከናወነው ግዢ ጋር በተያያዘ ለአውሮፓ ህብረት የተሳሳተ መረጃ ሰጥቷል በሚል በህብረቱ የንግድ ውድድር ተቆጣጣሪ አካላት 95 ሚሊዮን ፓውንድ ቅጣት እንደተጣለበት ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡
ፌስቡክ ከሶስት አመታት በፊት ዋትሳፕን በ19 ቢሊዮን ዶላር በመግዛት የራሱ ባደረገበት ወቅት የሁለቱን ማህበራዊ ድረገጾች ተጠቃሚዎች ኣካውንቶች ግንኙነት በተመለከተ ለህብረቱ ከሰጣቸው መረጃዎች ጋር በሚቃረን መልኩ ሲሰራ መገኘቱ በመረጋገጡ ቅጣቱ እንደተጣለበት ዘገባው ገልጧል፡፡
ፌስቡክ የራሱንና የዋትሳፕ ተጠቃሚዎችን አካውንቶች የግዢ ውሉ ላይ ከተጠቀሰው ውጭ ከስልክ ቁጥራቸው ጋር አስተሳስሮ አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱ ስህተት መሆኑን በማመን፣ ድርጊቱ ሆን ተብሎ የተፈጸመ አይደለም ሲል ቅጣቱ መተላለፉን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ አስተባብሏል፡፡
ኩባንያው ድርጊቱን ሆን ብዬ አልፈጸምኩም ብሎ ያስተባብል እንጂ የተጣለበትን ከፍተኛ የገንዘብ ቅጣት በመቃወም ይግባኝ ይጠይቅ አይጠይቅ በግልጽ ያስታወቀው ነገር እንደሌለም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

  ባለፉት 2 አመታት ብቻ 170 ሺህ ያህል የተለያዩ አገራት ዜግነት ያላቸው ህጻናት ስደተኞች ወደ አውሮፓ አገራት በመግባት ጥገኝነት መጠየቃቸውንና በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በአለም ዙሪያ ያለ ወላጅ ወይም ረዳት ብቻቸውን የተሰደዱ ህጻናት ቁጥር ከ300 ሺህ በላይ መድረሱን ዩኒሴፍ አስታውቋል፡፡
ድርጅቱ ባለፈው ረቡዕ ባወጣው መግለጫ እንዳለው፤ የአለማችን ህጻናት ስደተኞች ቁጥር በአምስት እጥፍ ያህል ያደገ ሲሆን፣ እየተባባሰ በመጣው ደጋፊና ረዳት የሌላቸው ብቸኛ ህጻናት ስደተኞች ላይ የሚሳተፉ ህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች  በርካቶቹን ለባርነትና ለሴተኛ አዳሪነት እየዳረጉ ይገኛሉ፡፡
ባለፈው አመትና በዘንድሮው የፈረንጆች አመት የመጀመሪያ ወራት በጀልባ ተሳፍረው ወደ ጣሊያን ከገቡት ህጻናት ስደተኞች መካከል 92 በመቶ የሚሆኑት ብቻቸውን የተጓዙ ወይም ወላጅ ዘመዶቻቸውን በስደት ጉዞ ላይ ያጡ እንደሆኑና አብዛኞቹም የኤርትራ፣ ጋምቢያ፣ ናይጀሪያ፣ ግብጽ እና ጊኒ ዜግነት ያላቸው እንደሆኑ ዩኒሴፍ አስታውቋል፡፡
90 ሺህ ያህል የአፍሪካ ቀንድ አገራት ህጻናት በአገራቸው ውስጥና በአካባቢው አገራት ከተቀሰቀሱ የእርስ በእርስ ግጭቶች ለመሸሽ በአገር ውስጥ እና ከአገር ውጭ ብቻቸውን ለመሰደድ እንደተገደዱም ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
በተያያዘ ዜናም፣ በደቡብ ሱዳን የቀጠለውን የእርስ በእርስ ግጭት በመሸሽ በየቀኑ 100 ያህል የአገሪቱ ህጻናት ብቻቸውን ድንበር አቋርጠው ወደ ኡጋንዳ እንደሚሰደዱ ወርልድ ቪዥን የተባለው አለማቀፍ ተቋም ማስታወቁን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
እነዚሁ የአገሪቱ ህጻናት ያለምግብና መጠጥ እንዲሁም ደጋፊ ወላጅ ዘመድ ድንበር አቋርጠው ለቀናት በአስቸጋሪ ሁኔታ እንደሚጓዙና ለተለያዩ የከፉ ችግሮች እየተጋለጡ እንደሚገኙም ዘገባው ገልጧል፡፡

 ከሶስት አመታት በፊት የተቀሰቀሰው አስከፊ የኢቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ 49 ዜጎቿን ለህልፈተ ህይወት በዳረገባት ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አንዳንድ አካባቢዎች ሰሞኑን የኢቦላ ቫይረስ ዳግም መቀስቀሱንና ይህም አገሪቱን ለከፋ ስጋት እንደዳረጋት የአለም የጤና ድርጅት አስታውቋል፡፡
ከሰሞኑ በአገሪቱ ሰሜን ምስራቃዊ አካባቢ በተቀሰቀሰው የኢቦላ ቫይረስ የተጠቁ ሁለት ሰዎች መገኘታቸውን፣ ሶስት ሰዎች መሞታቸውንና ሌሎች 18 ሰዎችም በቫይረሱ ሳይያዙ እንዳልቀሩ በመጠርጠሩ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኙ ድርጅቱ አስታውቋል፡፡
በቫይረሱ ከተጠቁ ሰዎች ጋር ንክኪ አላቸው የተባሉ ከ400 በላይ ሰዎችን በአፋጣኝ ወደ ህክምና ካፕም ማስገባትን ጨምሮ፣ በአገሪቱ ኢቦላ ዳግም በወረርሽኝ መልክ እንዳይከሰት በመጪዎቹ ስድስት ወራት የተለያዩ ስራዎች እንደሚከናወኑ የዘገበው አሶሼትድ ፕሬስ፣ ለዚህም 10 ሚሊዮን ዶላር ያህል ያስፈልጋል መባሉን ገልጧል፡፡
ቫይረሱ ከታወቀበት እ.ኤ.አ ከ1976 አንስቶ ለሰባት ጊዜያት በወረርሽኝ መልክ በተከሰተባት ኮንጎ ሰሞኑን በአዲስ መልክ የተቀሰቀሰውን የኢቦላ ቫይረስ ስርጭት ለመግታት ችግሩ በተከሰተባቸው አካባቢዎች የህክምና ማዕከል ማቋቋምን ጨምሮ ሌሎች ርብርቦች እየተደረጉ እንደሚገኙም አስረድቷል፡፡

   ጊፍት ሪል ኢስቴት በሲኤምሲ አካባቢ ከሚሰራቸው የመኖሪያ መንደሮች አንዱ የሆነውንና ከ850 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበትን የመንደር ሁለት ቤቶች ግንባታ ሙሉ በሙሉ አጠናቅቆ የዛሬ ሳምንት ለነዋሪዎች አስረከበ፡፡
ባለፈው ሳምንት ግንቦት 5 ቀን 2009 መሪ ሎቄ አካባቢ በሚገኘው የመንደር ሁለት ግቢ ውስጥ በተከናወነው የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ በተለያየ ዲዛይን የተሰሩ 350 ቪላዎች፣ ሮው ሃውስ፣ ታውን ሃውስና አፓርትመንቶች ለነዋሪዎች የተላለፉ ሲሆን በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ጥሪ የተደረገላቸው ታዋቂ ሰዎችና የንግዱ ማኅበረሰብ አባላት ተገኝተዋል፡፡
የመንደር አንድ ግንባታን ሙሉ በሙሉ አጠናቅቆ ባለፈው ዓመት ለነዋሪዎች ያስተላለፈው ጊፍት ሪል ኢስቴት፣ በዘርፉ ከተሰማሩ ግንባር ቀደም ተቋማት አንዱ ሲሆን በሊዝ በተረከበው 16.3 ሄክታር መሬት ላይ የሚገነቡ 1500 ቪላ፣ ታውን ሃውስ፣ ሮው ሃውስና አፓርትመንት ቤቶች ግንባታ ጠቅላላ ኢንቨስትመንት 2 ቢሊዮን ብር እንደሚጠጋ የሪል ኢስቴቱ መሥራችና ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ገብረየሱስ ኢጋታ ገልጸዋል፡፡
እነዚህ የሦስት መንደር ልማት ፕሮጀክቶች ከ1500 በላይ ቤተሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ታውን ሃውስ፣ ሮሃ ሃውስና ቪላ ቤቶች፣ 44 ብሎክ አፓርትመንቶች፣ 12ና ከዚያም በላይ ፎቅ ያላቸው የንግድ ሕንፃዎችን የሚያካትቱ እንደሆኑ፣ ከ1,500 ለሚበልጡ ዜጎች ጊዜያዊና ቋሚ የሥራ ዕድል መፍጠሩን ማኔጂንግ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡
በሚገነባቸው ቤቶች ጥራት በደንበኞች ዘንድ ምስጉን የሆነው ጊፍት ሪል ኢስቴት፤ በገባው ቃል ባለማስረከብ ይወቀሳል፡፡ የዚህንም ችግር አቶ ገብረየሱስ ሲናገሩ፤ ‹‹የመኖሪያ መንደሮች ግንባታ አልጋ በአልጋ አልነበረም፤ እጅግ ፈታኝና የድርጅቱን ሕልውና አደጋ ላይ የጣሉ፣ ደንበኞችንም ለስጋት የዳረጉ ክስተቶች አስተናግደናል። በተዋረድ በሚገኙ የአስተዳደር መዋቅሮች ውስጥ የነበሩ አንዳንድ ግለሰቦች በፈጠሩት ውስብስብ ችግሮች ድርጅቱ ለዓመታት አስተዳደራዊ አገልግሎት እንዳያገኝ ተከልክሎ ቆይቷል፡፡ ይህ እርምጃ በብዙ መልኩ ድርጅቱን ቢጎዳውም፣ ከደንበኞች ጋር የገባነውን ቃል ለማክበር ጥረት ስናደርግ ቆይተናል›› ብለዋል፡፡
ደንበኞች እስካሁን ለጠበቁት ጊዜ በቂ ማካካሽ ባይሆንም ድርጅቱ እንደ ምስጋና መግለጫ ይሆነው ዘንድ 14 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ በውል ላይ ከሰፈረው ውጪ በLTZ መሠራት የነበረባቸውን ታውን ሃውስና አፓርትመንት ቤቶች ሙሉ በሙሉ በአሉሚኒየም መቀየሩን፣ የውስጥ ለውስጥ መንገዶችን ሙሉ በሙሉ በአስፋልት መቀየሩን፣ ለነዋሪዎች ምቾትና ለግቢው ውበት ባለፏፏቴና በአረንጓዴ ዕፅዋት ያማረ መናፈሻ ማዘጋጀታቸውን ማኔጂንግ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡
ጊፍት ሪል ኢስቴት ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ከመውጣት አኳያ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ለገቢ ማሰባሰቢያ የሚውል መኖሪያ ቤት በመስጠት፣ ለቀይ መስቀል ማኅበርም በተመሳሳይ መኖሪያ ቤት በመስጠትና በማንኛውም ሀገራዊ የልማት ተግባር ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ አቶ ገብረየሱስ ኢጋታ ተናግረዋል፡፡
ጊፍት ሪል ኢስቴት ብቻ ሳይሆን፣ በርካታ በተመሳሳይ የሥራ ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶች፣ “እናስረክባለን” ባሉት ጊዜ ኃላፊነታቸውን ያለመወጣት ችግር አለባቸው፡፡ ሁለትና ሦስት ዓመት የመቆየት ችግር የተለመደ ነው፡፡ ፍ/ቤት ደጃፍም የረገጡም አሉ፡፡
ጊፍት ሪል ኢስቴት፣ “አስረክባለሁ” ባለው ጊዜ ባለማስረከብ፣ “ዘግይቷል” የሚለው ቃል አይገልጸውም። ምክንያቱም ሰባትና ዘጠኝ ዓመት የጠበቁ ደንበኞች ስላሉ ነው፡፡ ከሁለተኛው መንደር ቤት የተረከቡ ሰዎች ምን ይላሉ?
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፡- የነዋሪዎች ኮሚቴ ሊቀመንበር ነው፡፡ የቤት ርክክቡ በጣም ዘግይቷል። በመኻል  የቤት ባለቤቶች ኮሚቴ ተቋቁሞ ከድርጅቱ ጋር ብዙ ክርክሮች ተደርገዋል፡፡ በመጨረሻ የጠቅላይ ሚ/ር ጽ/ቤት፣ የአዲስ አበባ መስተዳደር ጽ/ቤትና የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ተጨምሮበት በተሰጠው አመራር፣ የቤቱን ግንባታ በትብብር በመሥራት በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ እንዲያልቅ ስምምነት ላይ ተደርሶ፣ ይኸው እንግዲህ ባለፈው አንድ ዓመት በተደረገው ርብርብ የቤቱ ግንባታ አልቆ ልንረካከብ ችለናል፡፡
ችግሩ ምንድን ነው? የተባለ እንደሆነ፣ እኛ ቤት ለመረከብ ውል የገባነው በ18 ወር ነው፡፡ የፈጀው ግን 7 ዓመት ነው፡፡ ይታይህ፣ ይህንን መዘግየት አይገልጸውም። ያ አይደለም የሰዎቹ ጥያቄ፡፡ እሺ ዘገየ፤ መቼ ነው የሚያልቀው? የሚለው ጥያቄ ቁርጥ ያለ መልስ የለውም። ከ20 ዓመት በላይ ነው በሉንና ቁርጣችንን አውቀን ሌላ አማራጭ እንፈልግ። ወይም ከ20 ቀን በኋላ በሉንና ደስ ይበለን እያለ ነበር ሲወተውት የነበረው፡፡ በአንድ ዓመት ውስጥ ማለቅ አለበት ተብሎ እኛም ችግሮችን አብረን ሆንን እየፈታን ለመረከብ በቃን፡፡
የእኔ ቤት ታውን ሃውስ የሚባለው ስለሆነ ብዙም ችግር አልነበረውም፡፡ ነገር ግን የሌሎች ካላለቀ ምንም ትርጉም የለውም፡፡ ናይጄሪያውያን የሚሉት አንድ አባባል አለ፡- “ልጅን ለማሳደግ መንደር ያስፈልጋል” ይላሉ፡፡ የመንደሩ ቤቶች ካላለቁ የእኔ ቤት ብቻ ቢያልቅ ዋጋ ያለውም፡፡ ስለዚህ የእኛ ክርክር ሁሉም ቤቶች ይለቁ የሚል ነበር፡፡ ይኸው ዛሬ ሁሉም ቤቶች አልቀው ለመረከብ በቃን፡፡ ጥቂት ነገሮች ቢቀሩም ወደ መኖሪያነት ተቀይሯል፡፡ ውሃና መብራት ገብቶልናል፤ ዘጠና ከመቶ ተጠናቋል፡፡
ትልቁ ችግር የነበረው ዋጋው ነው፡፡ መጀመሪያው ከ7 ዓመት በፊት የነበረው ዋጋ፣ የእኛ ቤቶች ከ800 እስከ 1.2 ሚሊዮን ብር ነበር፡፡ በ1997 የዛሬ 12 ዓመት ማለት ነው፡፡ ያኔ የቀን ሠራተኛ ዋጋ 30 ብር ነበር፡፡ ዛሬ 140 ብር ሆኗል፡፡ ሌላ ሌላውም እንደዚሁ ጨምሯል፡፡ በተለይ ችግር የተፈጠረው ‹‹በየትኛው ዋጋ ነው የምንከፍለው?›› የሚል ነው። በተለይ ከፍለው የጨረሱት፡፡ ‹‹በዛሬ ዋጋ ክፈሉ›› ሲባሉ ‹‹እናንተ ባዘገያችሁት ለምንድነው በዛሬ ዋጋ የምንከፍለው?›› ይሉ ነበር፡፡ ችግሮች በሽምግልና በድርድር እየተፈቱ ዛሬ ጥሩ ቀን ላይ ደርሰናል፤ በማለት ገልዷል፡፡ አቶ አዲስ ሚካኤል፤ ‹‹ብዙ ሪል ኢስቴቶች ላይ ያሉ ችግሮች ጊፍት ሪል እስቴትም ላይ ይታያሉ። ዋናው ነገር በብዙ ችግሮች ውስጥ አልፎ እዚህ መድረሱ በጣም ደስ ይላል፡፡ እኔ ከዛሬ 8 ዓመት በፊት በ1.7 ሚሊየን ብር የገዛሁት ቤት ተጎራባች ወይም ታወን ሃውስ  የሚባለውን ነው፡፡ የጊፍት ሪል እስቴት ትልቁ ቁምነገሩ ቤቶችን በጥራት መሥራቱ ነው፡፡ እናም ከሌሎቹ ሪል ኢስቴቶች ጊፍትን መርጠን ቤት እንድንገዛ ያደረገን የጥራቱ አሠራር ነው፡፡
አሁን ሁሉም ነገር በሰላም አልቆ፣ ውሃና መብራት ገብቶላቸው ተረክበን እየኖርንበት ነው፡፡ የቤቶቹ ግንባታ የዘገየበት ብዙ ምክንያቶች አሉ፡፡ የቦታ ማለትም የወሰን ማስከበር፤ የባለሙያ፣… ችግር ነበረበት፡፡ ገዥዎችም ላይ በወቅቱ ያለመክፈል ችግር ይኖራል፡፡ በመጨረሻ ሁሉ ችግር አልፎ እዚህ መድረሱ በጣም ደስ ይላል፡፡›› ብለዋል።
ወ/ሮ ስርጉት ተክሉ፣ የሦስት ልጆች እናት ናቸው፤ ‹‹የተመዘገብኩት ከ7 ዓመት በፊት ሲሆን ቤቱን የተረከብኩት ደግሞ ካቻምና በ2007  ዓ.ም ነው፡፡ በፊት በመዘግየቱ ተከፍተን ነበር፡፡
አሁን ግን ቤቱን ተረክበን ገብተንበት ስናየው ቤቱን ሰርቶ (አቁሞ) እንዲያስረክበንና የውስጥ ዲዛይን እኛ በፈለግነው መንገድ እንድንጨርሰው ነበር፡፡
በውላችን መሠረት ቤቱን አስረከበን፤ እኛም በፈለግነው መሰረት የውስጥ ዲዛይኑን ጨርሰን ገባንበት። ምንም ቅር አላለንም፤ በዚህና በቤቱ ጥራት በጣም ደስተኞች ነን፡፡
የእኔ ቤት 370 ካሬ ላይ ያረፈ ቪላ ነው፡፡ 7 መኝታ ክፍሎችና፣ 2 ሳሎንና 2 ወጥ ቤት አለው፡፡ ውስጥ ዲዛይኑና ፊኒሽንጉ በራሴ በመሆኑ ሙሉውን አልከፈልኩም፡፡
ሁለት ሚሊዮን ብር ያህል ከፍያለሁ፡፡ በፊት ግንባታው በመዘግየቱ የተነሳ ብከፋም፤ አሁን ከገባሁበት በኋላ ግን ደስተኛ ነኝ፡፡ አየሩንም፣ ጎረቤቶቼንም፣ ጊፍትንም ወድጃቸዋለሁ። በጣም በደስታ ከልጆቼና ከባለቤቴ ጋር እየኖርኩ ነው፡፡›› ብለዋል፡፡