Administrator

Administrator

  ደብረዘይት፣ አዴ ወረዳ እና ሻሸመኔ የብሾፍቱ ማህበራዊ ተጠያቂነት ማጠቃለያ
ባለፈው የደብረዘይት/ብሾፍቱ ጉዞዬን ጀምሬ ነበር፡፡ ላጠቃልለውና ወደ አጄ ጉዞዬ እቀጥላለሁ፡፡
ስለናንተ ጉዳይ (ስለማህበራዊ ተጠያቂነት) የጋዜጣችን አንባቢ ያውቅ ዘንድ ቀለል አድርጌ ልጽፍ ነው፡፡
አገልግሎት ሰጪዎችና አገልግሎት ተቀባዮች ናቸው መልስ የሰጡኝ፡፡ ማህበራዊ ተጠያቂነት በብሾፍቱ ምን ይመስል ነበር? ከዚያስ በኋላ ውጤቱ ምን ሆነ?
የት/ቤትን ችግሮች በተመለከተ ሙሉ በሙሉ ባይሆንም
የክፍል ጥበቶች ነበሩ፤ተሠርተው በነፃነት ይማራሉ
መፀዳጃ ቤቶች አዲስ መሠራት ብቻ ሳይሆን የወንድና የሴት ተብለው ተከፍለው እየተገለገሉባቸው ነው፡፡
ሜዳው አፈር ነበረ፤ አሸዋ ተደፍቶበታል፡
በአንድ ጠረጴዛ ላይ ለ5 ለ6 የሚማሩት አሁን ለ3 እንዲማሩ ተደርጓል
አንድ መጽሐፍ ለ3 ለ2 ያልነበረውን፣ አሁን መጽሐፍ ለአንድ ተማሪ እንዲያገኝ ጥረት ተደርጓል - ይህ የሆነው በህብረተሰቡ ድጋፍ ሲሆን፤ ይህም የእየሩሳሌም ህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት (ጄክዶ) አካባቢውን ለቅቆ ቢሄድ ህብረተሰቡ በዘላቂነት ሊረከብ እንደሚችል ይጠቁማል፡፡
ኤችአይቪ ፖዘቲቭ የሆኑ ስለመድሃኒቱ አጠቃቀም በጥንካሬያቸው የሚያሳምኑ የሳክ አባላት ይፋ ገለፃ እንዲያደርጉ ተደርጓል (ግን ይቀረዋል)
በውሃ በኩል አራት ችግርተኛ ቀበሌ ተለይቶ ተመርጦ ነው መፍትሔ ፍለጋ የተገባው! ት/ቤቶችም እንደዚያው!
ከአራቱ ቀበሌዎች ሁለት ሁለት መቶ ሰዎች እንዲሳተፉ ነው የተደረገው!
የመንግስት ስታንዳርድን መርምረዋል፡፡ እንዲጣጣሙ ለማድረግ ስኮር - ካርድ የምትባል መመዝገቢያ አለች፡፡ ውጤት ከ5 ይታረማል፡፡ የሁሉም ቀበሌ ስዕል ይገኛል፤ ለምሳሌ ካራ ሁራ 1.5 ሚሊዮን ብር ተመድቦ፣ 4 ባለ 8 መማሪያ ክፍል ሁለት ብሎኮች ተሠርቷል፡፡ ስታንዳርድ ጠረጴዛ ቀርቦልናል፡፡ (የሽንት ቤት ስታንዳርድም በቪዲዮ በተቀረፀው መሠረት መፍትሔ አገኘን - በህብረተሰቡና በሊንክ ኢትዮጵያ) እንደችግር የማህበረሰባዊ ተጠያቂነት ግንዛቤ አልነበረም፡፡ ችግሩን አምቆ ይይዝ ነበር፡፡
ለት/ቤቱ አባላት ብቻ ሳይሆን ለመንግሥትም ጠቀሜታ ያለው ነገር ተካሂዷል፡፡ የየክፍሉን ችግር ሁለቱም ወገኖች ተማምነው ለውጥ ስላዩበት! ተማሪዎች ረባሾችን ያጋልጣሉ! የመማር ማስተማር ሂደት በግልጽ የሚያምኑበት ሆኗል፡፡ ተማሪዎች የፈለጉትን ይጠይቃሉ!
ህዝብ አገልግሎት ሰጪዎችን ለሚጠይቅበት የካራ ሆራ ት/ቤት ምሳሌ ነው፡፡
Citizens report card እና የህብረተሰቡ ሃሳብ መስጫ ካርድ ተጠቅመዋል፡፡ መሞራረድ በመሟገት ጠቅሞናል፡፡
በ150 ብር የተሠራ ፕሮጄክት ነበር፤ በዐይናችን ሄደን አይተናል፡፡ ውሃ ልማት አይደለም፤ እኛ ነን ተሟጋቾች - ቴክኒካል ጉዳይ፣ የጥራት ጉዳይ፣ የኮንስትራክተሮችና የዕቃው ጥራት፣---- ሳቢያ እንዳለ ፓምፑ 400 ሜትር ሰመጠ፡፡ ሌላ ጄኔሬተር ተገዝቷል፡፡ ችግር along the line ነው አልተፈታም፡፡ ማህበራዊ ተጠያቂነት አጋዥ ነው፤ብቻችንን ወደላይ ስንጮህ አጋር አላገኘንምና! ትክክለኛ ኤክስፐርት እንደሌለ ነው የሚታየው! የክትትል ጥራት ማነስ!
የፍሳሽ መኪና ዕጥረት ነበር በከፍተኛ ወጪ ተገዝቷል!
በወር አንድ ጊዜ በህብረተሰቡ የጽዳት ዘመቻ ይካሄዳል
በእኛና በት/ቢሮ መካከል ትልቅ መቀራረብ አለ!
የህዝቡ አማካሪ ምክር ቤት ፀሐፊ እንዳሉት - 1ኛና ሁለተኛ ፌዝ አባል - “የመንግስት የ5 ዓመት ዕቅድ እንደስታንዳርድ ተቆጥሯል፤ በግሩፕ አስበን ያልተሳኩትን እንደ ችግር ወስደን ነው፡፡ ከንቲባው ቃል ገቡ - ዕቅድና በጀት ተፈቀደ - የገንዳ ማጠራቀሚያና የቆሻሻ ማንሻ መኪና ዕጥፍ ሆኑ!
ፊት የተገዛው ፓምፕ ለሙቅ አይሆንም ነበር፤ ህዝቡ አልረካንም ብሏል
በት/ቤት ግቢ ያሉ ቤቶች ማካካሻ ቦታና ቤት ተሠርቶላቸው ለቀዋል! ኮንዶምኒየም የገቡ አሉ!
ለመላው ኢትዮጵያ ምሳሌ እየሆነ ነው፤ ከሶማሊያና ከኬንያ ጭምር መጥተው ጐብኝተዋል! መተሃራ ምንጃር አካባቢ ልምድ ከካራ ሆራ ት/ቤት አግኝተናል ብለዋል ከዝቅተኛ ወደ ከፍተኛ ስለሄደ!
አንገብጋቢው ነገር ላይ ስላለሁ ሁሌ እንዳነባሁ ነው፤ ውሃ የለም፤ ወልደው መታጠቢያ፣ ለአስከሬን ማጠቢያ እንኳን! (ቀበሌ 08)
3 ቀን ብቻ የመጠጥ ውሃ አገኘን! ደሞ የፈላ ውሃ ብቻ ለቀቁብን ይላሉ፤ባልቴቷ ተወካይ! ይሁን አቀዝቅዘን እንጠጣ አልን፤ከ2 ቀን በኋላ ቀጥ አለ!
ወዴት እንሂድ፤ ከዚህ በላይ አቤት የት አለ፤ ከንቲባው በተቀመጡበት ተናገርን!
“የጠገበ ሰው የተራበን ሰው ነገር አያቅም! በ6 ወር ዝናብ ከዘነበ ድንገት አጠራቅመን ነው የምንታጠበው፤እነሱ ግን ፀድተው ይወጣሉ! አብሲት የምንጥለው የምናቦካው በዝናብ ውሃ ነው፤ ለአሁን ክረምት!
ግን አሁን በቦቲ ይመጣል፤ ለዛ ሁሉ ህዝብ እንዴት ያዳርሳል? እሱም ህዝቡ ቀይ አሸዋ አልብሶ ነው ----- መናገሩን በውሃ ጉዳይ ላይ አቁሜያለሁ - ጉድጓድ ውሃ ገባ አሉ፣ ሞተር ገብቷል ውስጡ ተባለ - ሄደን ውሃ ልማት መጠየቃችን አልቀረም - እኮ! ከአሜሪካን አገር ሰው አምጥተን አሉ፤ ትልቁ አገር አሜሪካን ነው አሉ እንግዲህ አቅቶት ሄደ (ሳቅ) ሌላ ማን ሊያወጣው ነው ታዲያ?
እኔ መሀይም ነኝ አላቅም፤ አፍርሰውት ቢያወጡት ሰብረው! አልወጣም አይል፡፡
ህዝቡ ከማልቀስ ውጪ አደለም፤ አንድ በርሜል 100 ብር ነው!
ትምህርትስ አልተሻሻለም?
ትምርቱ ግን ጥሩ ነው ፤ግን ሲማር ውሃ ያስፈልገዋላ መቼም!
ከላይ የተጠቀሰው የድፍን ብሾፍቱ ችግር አይደለም፤ መንግሥት ከአቅሙ በላይ ቢሆንበት ነው እንጂ!
ሰው ራሱ ተጠያቂ መሆኑን አውቋል፤ ችግሩንም ይፋ መናገር እንዳለበት ተገንዝቧል፤ ትልቅ ለውጥ አለ!
አየር ኃይልና አሻም አፍሪካ አግዘውናል
091307 ቀበሌ የበጀት ተወካይ እህማልድ ታላቅ አስተዋጽኦ ትልቅ ድርጅት ነው - የራሳችንን ችግር በራሳችን እንድናወጣ - እሾክን በሾክ! አንድ ዐይናችን ነው! 26 ሴክተር መ/ቤቶች ከነ ከንቲባው ከነአባላቱ ጭምር ከጄክዶ ጋር ተሰብስበው፤ ተወያይተው የማተ ኮሚቴ እንደ አገር ብልጽግና ታዳጊ ሆኖ ከሥር እየተመካከረ በቡና፣ በዕድር፣ በቀብር፣ በውይይት ላይ በቀበሌ ሰብሳቢዎች ላይ - ነገሬ ብሎ እንዲያስብ አድርጓል - በከተማ ልማት ዕቅድም ህዝቡ ከታች እንዲመክርበት በጐጥ አድርጓል - እኔ አውቅልሃለሁ እንዲቀር ጥሯል፡፡
እንደ ችግሩና እንደተጠቃሚው ብዛት እንዲሆን አድርጓል
በጀት ይለጠፋል፤ ህዝቡ ሃሳብ እንዲሰጥ
50 50 በጀት ከመንግሥት ጋር እንዲሠራ ደረጃ ላይ ደርሷል
የተራ ሆራ የልጅ ሃ/ማ ነው
   ለግል መኖሪያ ያሠሩት ነው!
ግልጋሎት ሰጪው የመንግሥት አካል የህዝቡን ጥያቄ እየተቀበለ ነው! ትልቁ ነገር ለመላው ኢትዮጵያ የሚሆን እየተፈጠረ ነው!
ባቦ ጋያ ህፃናት መዋያ ተጀምሯል፤ እኛ ራሳችን በጐ ተፅዕኖ መፍጠር አለብን፤ መጨቃጨቅ መካሰስ መቃወም ሳይሆን! ጀምረነዋል - በትዕግሥት!!
መጽሐፍ ስቶር ይገባል፤ይሠራጭ አይሠራጭ የሚከታተል የለም! አሁን ያ ተለውጧል!
የማህ/ተጠዋና ሥልጣን የማቀጣጠል ሥራ ነው!
በኤችአይቪ ዙሪያ ቤት እስከመስራትና እስከቁጠባ ተሠማርቷል - ጄክዶ!
የአካል ጉዳተኞች ላይ ትኩረት አድርጐ እርዳታ ያጠናክር! የመንግስት ባጀት ሲመደብ
ወጣት ላይ ይሠራ ፤ለመተካካት!
አገልግሎት ሰጪው ቆልፎ እንዳይይዝ ከፖለቲካ ጋር አይቆላለፍ awareness ይሰጥ! መልካም አስተዳደር ይታሰብበት!
***
ቀጥሎ የተጓዝኩት ወደ ሻሸመኔ ሲሆን ከዚያ 30 ኪ.ሜ ገደማ ወደቀኝ ተገብቶ አጄ ወረዳ ይደረሳል፡፡
የአጄ የማህበራዊ ተጠያቂነት ኮሚቴ መርምሮ አዎንታዊ ውጤት ማምጣቱን ሲናገር፣ የሳክ የትምህርት ኮሚቴ ሊመንበር አቶ መርዕድ ዋናው ጉዳይ አገልግሎት ሰጪውና አገልግሎት ተቀባይ የግንዛቤ ለውጥ ማምጣታቸው ነው፤ የችግሩን ባለቤት ማስገኘትና ለውጥ ማስከተል ሲሆን በዚህ ረገድ ተጨባጭ ውጤት ታይቷል፤ ድፍረት ታይቷል፤ ትምህርት፣ ውሃና ንፅህና ላይ ነው ውጤቱ የተመዘገበው፡፡ ሽንት ቤት ለሌለው ሽንት ቤት ተሠርቷል፡፡ ህዝብ ይገባኛል ያለውን መንግሥት ይገባል ብሎ ፈጽሟል፡፡ ይጠፋ የነበረውም ውሃ መጥፋት የለበትም ተብሎ የኦሮሚያ የውሃ መ/ቤት፣ ወደ አንድ ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ትልቅ ጄኔሬተር ተገዝቶ፣ የውሃም የመብራትም ችግር እንዳይኖር ሆኗል፡፡ ሻወር አልነበረም ኖረ፡፡ ልብስ ማጠቢያ ኖረ፡፡ ሃሳብ በዐይን ተተግብሮ ታየ፡፡ አቶ አማን ደግሞ ስለ ገጽ ለገጽ ምን ዕውነታ አለ ብያቸው፣ ዋናው ነገር አገልግሎት ሰጪና ተቀባይ አጠገብ ላጠገብ ተቀምጠው በድፍረት መናገራችን ነው! ብለዋል፡፡ የዛሬ ሁለት ዓመት በተወያየነው መሠረት፤ በግለሰብ ደረጃ ሽንት ቤት የሌለው እንዲኖረው፣ በማህበረሰብ ደረጃም የህዝብ ሽንት ቤት እንዲሠራ ተደርጓል፡፡ ሥራ ባግባቡ ባለቤት አግኝቶ፣ መሬት ላይ የሚታይ ለውጥ ተገኝቷል፡፡
እንዳገር ሽማግሌ ይሄን አይቻለሁ፡፡ እጅ መታጠቢያም ተሠርቷል፡፡ በጽዳት በኩልም ደረቅ ቆሻሻ አንድ ቦታ ተሰብስቦ እንዲቃጠል፣ እርጥቡ ጉድጓድ እንዲገባ ተደርጓል፡፡ በውሃ በኩል ቦኖ ተደርጓል፡፡ ተማሪዎች፣ ወላጆች፣ መምህራን እና ህብረተሰብ ተገኝተዋል፡፡ የሴክተር ቢሮዎችም የልምድ ልውውጥም ተካሂዷል፡፡ የሴቶች ኃላፊም፣ ሴቶች እንዲሳተፉ በጽዳቱም፣ በውሃውም በትምህርቱም ተደርጓል፡፡
ያለው ችግር የውሃው ኃይል ማጣት ነው፡፡ ጫካው ተመናምኗል፡፡ ለመተካት እየተሞከረ ነው፡፡ ግንዛቤ መጨበጥ፣ ችግር ማጤን፣ ማቀድ መበጀትና ውጤት ማምጣት ነው ተግባራዊ ሂደቱ! “ራሳችሁ ላይ ያለው ለውጥ ምንድን ነው? ብዬ ለጠየኳቸውም፤“ስልጠና ማግኘታችንና ችግርን በድፍረት ማንም ፊት መናገር መቻላችንን ተረድተናል፣ በፊት እንፈራ ነበር” ብለዋል አባላቱ! የስዊድን ልማት ድርጅትና ዓለም ባንክ ከእየሩሳሌም ድርጅት ጋር የሠሩ ሲሆን፤ ከመጠየቅ መጠየቅ (ጠ ይጠብቃል) እንደሚከብድም አስምረውበታል፡፡
ከዚህ በኋላ ወደ ግብርና ቢሮ አመራሁ፤ እዚያው ያለውን ስብሰባ ለማየት ነው! 

  ከእለታት አንድ ቀን አንድ ሽማግሌ ሹም የተቋሙን ሠራተኛ ሁሉ የሚያጣላ፣ የሚያጋጭና የሚበጠብጥ ወሬ እያወራ ሰውን እያተራመሰ አስቸገረ፡፡ ሰው ተሰበሰበና መምከር ጀመረ፡፡
አንደኛው - “ይሄ ሰው የባለቤቱ ዘመድ ነው፡፡ ለዚህ ነው እንደልቡ የፈለገውን እያወራ ዘራፍ የሚልብን!” አለ፡፡
ሁለተኛው - “ታዲያ ባለቤቱም ቢሆኑ‘ኮ ውሸት አይፈቅዱም!”
ሦስተኛው - “እሱን እንኳ እሳቸው ካልተናገሩ ማንም አያውቅም”
ይሄ ሙግት እየተካሄደ ሳለ ባለቤትየው መጡ፡፡
“ምንድን ነው የሚያጯጩሃችሁ?” አለ፡፡
ከተሰበሰቡት መካከል አንዱ፤
“ጌታዬ ይሄ የርስዎ ልጅ በጣም አስቸገረን”
“ምንድ አድርጐ?”
“እየዋሸን”
“ታዲያ ውሸት ለእናንተ አዲስ ነው እንዴ? ታገሱታ!”
“እንዴት ጌታዬ፤ እሱኮ ውሸት አያልቀበትም”
“እንዴት አያልቅበትም?”
“በጣሊያን ጊዜ የሰማውን ውሸት እስከዛሬ ስለሚያስታውስ ነዋ!!”
“ያ ከሆነማ ከዛሬ ጀምሮ ተሰናብቶላችኋል!” አሉ ባለቤቱ!
***
ውሸት ሁሌም ውሸት ነው! የጣሊያን ጊዜ ውሸትና የዛሬ ውሸት ብሎ ልዩነት መፍጠር የለም! ዕውነት ያልሆነ ሁሉ ውሸት ነው ብሎ ማመን እንጂ ለውሸት ጊዜ መለየትም ሆነ፣ ቦቃ መለየት የትም አያደርስም! ማናቸውም አሉታዊ ነገር ያለው ውሸት ነው፡፡ ውሸትን ለማራመድ ሥልጣን ተጠቀምን ማለት ሹመት ለውሸት ተግባር ዋለ ማለት ነው!
“ደንጊያና ቅል ተላግቶ
ዜጋና ሹም ተጣልቶ”
አይሆንም፤ የሚለውን አባባል፤ የማንሽር ከሆነ፣ አዲስ ሹመት አዲስ ሽረት እንደማለት ነው፡፡ የጊዜ ጉዳይ ነውና!
“ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል”ን ምን ያህል ረስተናል?
ሙስናን ተገላግለነዋል ወይ? የጣሊያን ጊዜን ውሸት ተፋትተናል ወይ? መልካም አስተዳደር ዜማ ነው ተግባር ነው? ፍትሕ እዚያው ፍርድ ቤት ነው ወይስ እኛ ውስጥ አለ? ስለ አንደኛውና ስለ ሁለተኛው ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ስንቶቻችን በዕውን እናውቃለን?
ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች መከፈላቸው መቼም ሳይጠና እንዳልሆነ እንገምታለን፡፡ ለጠቅላይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት በርካታ አማካሪ ሲሾም (ሲመራ) ያለጥናት እንዳልሆነ እንዳልገመትን ሁሉ “ጠርጥር ጉድ አለ በሰኔ” የሚለውም ሆነ፤ “የፊት ወዳጅሽን በምን ሸኘሽው?”
    በሻሽ፡፡
ለምን?
የኋለኛው እንዳይሸሽ!”
የሚለው፤ እንደጊዜው የሚፈረጁ ናቸው!!
“ግፋው እንጂ አታርቀው” የሚለውም ያው ነው!” እዚህ ቦታ ያልረባ እዚያ ይገባ!” ማለትም ያጠያይቃል፡፡ “ጉልቻ ቢቀያየር ወጥ አያጣፍጥም!” የሚለው፤ የኃይለሥላሴ ዘመን ሲያበቃና እንዳልካቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ሲሆን የተሰነዘረ መፈክር ዛሬም ቢነሳ አያስቀይምም!
ዋናው ጉዳይ፤ “ወገናዊነትን ሳይሆን ሙያችንን እንሥራበት” የሚለው ነው፡፡
አፈረስነው ያልነው ኢዲሞክራሲያዊነት፣ ኢፍትሐዊነትና ሙስና፤ መልሶ እኛኑ የሚያፈርሰን ታሪክን ከደገምን ነው፡፡ “የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳ” የሚለው ተረት የማይረሳንን ያህል፤
“የተወጋ በቅቶት ቢረኛ፣ የወጋ ምን እንቅልፍ አለው፤
የጅምሩን ካልጨረሰው!” የሚለውንም የማንዘነጋ መሆን አለብን!
ሀገርን በሀቀኛ ተግባር እንሞላ ዘንድ ከሆነ የተሾምነው፤ ሹመት በመቀባት ሳይሆን፣ በመመኘትም ሳይሆን፣ ለሀገር አሳቢ በመሆን ብቻ ተገኘ ማለት ነው!
ሙስናን በተመለከተ አንዲት ገጠመኝ ጠቅሰን እንደምድም፡፡ ሰውዬው መንገድ ላይ ተኝቶ ቁስሉን ዝንብ ወሮታል፡፡ ሌላ መንገደኛ መጥቶ “እሽ!” ብሎ ዝምቦቹን አባረረለት፡፡
ያ ቁስለኛም፤
“ምነው ወዳጄ ጠግበው የተኙትን ዝንቦች አባረህ አዲሶቹን ጋበዝክብኝ!” አለው፡፡

     በቅርቡ በሳዑዲ አረቢያ በሃጂ ስነስርአት ወቅት በተፈጠረ መጨናነቅ ህይወታቸውን ያጡ ኢትዮጵያውያን ቁጥር 47 መድረሱን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ገልጿል፡፡
ባለፈው መስከረም 13 ቀን 2008 በሳዑዲ አረቢያ ሚና አካባቢ በደረሰ አደጋ ከ1ሺህ በላይ የተለያዩ ሀገር የሃይማኖታዊ ስነ ስርአቱ ተሳታፊዎች ህይወታቸውን ባጡበት ወቅት ኢትዮጵያውያን ላይ አደጋ ስለመድረሱ ወዲያው ማወቅ ያልተቻለ ሲሆን ከቀናት በኋላ 2 ኢትዮጵያን ህይወታቸው ማለፉ ተዘግቦ እንደነበርና ኋላም የሟቾች ቁጥር ወደ 31 ማደጉ ይታወቃል፡፡ ከትናንት በስቲያ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ቁጥሩ 47 መድረሱንና ተጐድተው ሆስፒታል ገብተው ከነበሩት 26 ኢትዮጵያውያን 24 ተሽሏቸው ከሆስፒታል ሲወጡ፣ 2ቱ ተኝተው ህክምና እየተከታተሉ መሆኑ ታውቋል፡፡
ለሃጅ ስነስርአት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ሄደው የነበሩ ከ1ሺህ 100 በላይ አማኞች መመለሳቸውንም ምክር ቤቱ አስታውቋል፡፡ በዘንድሮ የሃጂ ስነስርአት ላይ 10ሺ ኢትዮጵያውያን መሣተፋቸውም ታውቋል፡፡

 ኤርትራ ዝቅተኛ የኢንተርኔት ተጠቃሚ በመሆን አለምን ትመራለች
   በኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚ የሆነው ከአጠቃላዩ ህዝብ 1.7 በመቶ የሚሆነው ብቻ ነው መባሉን የአሜሪካው የቢዝነስ መጽሄት ፎርቹን ዘገበ፡፡ኢንተርኔት ላይቭ ስታትስ የተባለው አለማቀፍ ተቋም ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ እጅግ ዝቅተኛ የኢንተርኔት አገልግሎት አቅርቦት ካላቸው አስር የአለማችን አገራት መካከል ስምንቱ በአፍሪካ አህጉር እንደሚገኙና ኢትዮጵያም አንዷ እንደሆነች በጥናት ተረጋግጧል፡፡በኢንተርኔት አገልግሎት አቅርቦት ዝቅተኛነት ከአለማችን ቀዳሚውን ስፍራ የምትይዘው ኤርትራ መሆኗን የጠቆመው ዘገባው፣ ከአገሪቱ ህዝብ የአገልግሎት ተጠቃሚ የሆነው 0.91 በመቶ ብቻ መሆኑን ገልጧል፡፡ከአውስትራሊያ በስተሰሜን የምትገኘው ቲሞር ሌሴቴ ደሴት በ1 በመቶ፣ ማይንማር በ1.16 በመቶ፣ ብሩንዲ በ1.39 በመቶ እንዲሁም ሴራሊዮን በ1.49 በመቶ በኢንተርኔት አቅርቦት ዝቅተኛነት እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል ተብሏል፡፡  ሶማሊያ በ1.51 በመቶ፣ ኒጀር በ1.61 በመቶ፣ ኢትዮጵያና ጊኒ በ1.7 በመቶ እንዲሁም ኮንጎ በ1.92 በመቶ እንደሚከተሉም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

ኢትዮጵያ አምና ወደዚያው ከላከችው ስጋ 58.8 ሚ ዶላር አግኝታለች
     የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የኢትዮጵያ የስጋ ምርት ወደ ግዛቷ እንዳይገባ ከአንድ ሳምንት በፊት ጥላው የነበረችውን ማዕቀብ ማንሳቷን ተርኪሽ ዊክሊ ድረገጽ ትናንት ዘገበ፡፡
ከሳምንት በፊት ከኢትዮጵያ ሰባት ስጋ ላኪ ኩባንያዎች ወደ አገሪቱ ከገባው 36 ቶን የበግ ስጋ ጋር በተያያዘ የተፈጠረውን ችግር ተከትሎ አገሪቱ የኢትዮጵያ የስጋ ምርት ወደ ግዛቷ እንዳይገባ ገደብ ጥላ እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ ከሚመለከታቸው የኢትዮጵያ መንግስት አካላት ጋር በመነጋገር ችግሩን መፍታት መቻሉን ገልጧል፡፡
ይህን ተከትሎም የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የኢትዮጵያ የስጋ ምርት ወደ ግዛቷ እንዳይገባ የጣለችውን ማዕቀብ ማንሳቷንና አገሪቱ ያሳለፈችው ውሳኔ በዘርፉ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያንን እንዳስደሰተ ዘገባው አስረድቷል፡፡
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የኢትዮጵያን የስጋ ምርት በስፋት በመግዛት ቀዳሚዋ አገር እንደሆነችና ኢትዮጵያ ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ከምትልከው የምግብ ኤክስፖርት ምርት በአመት በአማካይ 30 ሚሊዮን ዶላር ገቢ እንደምታገኝም ገልጧል፡፡
ኢትዮጵያ ባለፈው አመት ወደ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ከላከችው 11.692 ቶን የስጋ ምርት 58.8 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷንም ዘገባው አክሎ አስታውሷል፡፡

  •         የገቢ አሰባሰቡ የአስተዳደር ጉባኤ አባላቱን አወቃቅሷል
  •         ከዕድሳት ዕጦት የሕንጻው ደኅንነት አደጋ ላይ ወድቋል

   በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት፣ ለተለያዩ አገልግሎቶች ከአከራያቸው የሕንጻው ክፍሎች ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ የኪራይ ክፍያ አለመሰብሰቡ ተገለጸ፤ ተከራዮች ውዝፍ ዕዳቸውን ከነመቀጫው አጠናቀው እንዲከፍሉ ጽ/ቤቱ አስጠነቀቀ፡፡
የሀገረ ስብከቱን ሕንጻ ለቢሮ፣ ለሕክምና እና ለሱቅ አገልግሎቶች ከተከራዩ ስድስት ተከራዮች ያልተሰበሰበው አጠቃላይ ክፍያ ብር 675 ሺሕ 244 ከ31 ሳንቲም ያህል እንደኾነ ጽ/ቤቱ ባለፈው ዓመት ነሐሴ ከጻፈው የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ማስጠንቀቂያው ከደረሳቸው  መካከል፣ ከሰኔ ወር 2005 ዓ.ም. ወዲህ ኪራያቸውን ሳይከፍሉ የቆዩና እስከ 360 ሺሕ ብር ከፍተኛ ውዝፍ ያለባቸው ተከራዮች እንደሚገኙበት ታውቋል፡፡ተከራዮች ደብዳቤው በደረሳቸው በሦስት ቀናት ውስጥ ውዝፍ ዕዳቸውን ከነመቀጫው ከፍለው ለጽ/ቤቱ ካላሳወቁ፣ ቢሮዎቻቸውና ሱቆቻቸው እንደሚታሸጉ የተሰጠው ማስጠንቀቂያም የሚገባውን ያህል ተግባራዊ ሳይሆን ከወር በላይ ማስቆጠሩ ተገልጧል፡፡
ኪራዩ በወቅቱ ቢሰበሰብ፣ ገንዘቡ በወቅቱ የነበረውን ዋጋ ያህል ቤተ ክርስቲያኒቱን ተጠቃሚ ያደርግ እንደነበር የሚገልጹ የሀገረ ስብከቱ ምንጮች፣ የፋይናንስና በጀት ዋና ክፍሉን ቀዳሚ ተጠያቂ አድርገዋል፡፡
ዋና ክፍሉ ከኪራዩ የሚሰበሰበውንና የቀረውን ገቢ በየጊዜው ለአስተዳደር ጉባኤው በሪፖርት በማሳወቅ፣ ክፍያው እንዳይወዘፍ ማድረግ የሚገባው ቢሆንም አለማቅረቡ ድክመቱን እንደሚያሳይ ምንጮቹ አስረድተዋል፡፡
በከፍተኛ የክፍያ ዕዳ ከሚታወቁ ተከራዮች መካከል ከአንዳንድ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ጋር ግንኙነት ያላቸው እንደሚገኙበት ምንጮቹ ጠቁመው፤ አጀንዳው በአስተዳደር ጉባኤው ስብሰባ ላይ ቀርቦ በታየበት ወቅትም “የገቢ አሰባሰቡ በዝምድና የተሸፋፈነ ነው” በሚል ሓላፊዎቹን እርስ በርስ አወቃቅሶ እንደነበር ተናግረዋል፡፡
በ2001 ዓ.ም. በወቅቱ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል አስተዳደር፣ በከፍተኛ ወጪ ተሠርቶና በቀድሞው ፓትርያርክ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ሕንጻ፣ ባለቤት አልባ እስኪሰኝ ድረስ እያፈሰሰ እንደሚገኝና አስቸኳይ ዕድሳት ካልተደረገለትም ደኅንነቱን አስጊ እንደሚያደርገው ምንጮቹ ይገልጻሉ::

 የታሪክ ፀሐፊ ጋዜጠኛና ዲፕሎማቱ አምባሳደር ዘውዴ ረታ ባለፈው ረቡዕ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡ አምባሳደር ዘውዴ ረታ በተለይ “የኤርትራ ጉዳይ”፣ “የተፈሪ መኮንን ረጅም የስልጣን ጉዞ” እና “የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት” የሚሉ የታሪክ መፅሃፍትን ፅፈዋል፡፡
በአዲስ አበባ ኦርማ ጋራዥ አካባቢ ነሐሴ 7 ቀን 1927 ዓ.ም የተወለዱት አምባሳደር ዘውዴ፤ እንግሊዝ ሎንደን ከተማ ዕረፍት ላይ እንዳሉ በድንገት በገጠማቸው ህመም ህይወታቸው ማለፉ ታውቋል፡፡አምባሳደር ዘውዴ በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት በሬድዮ በቤተ መንግሥት ዜና አቅራቢነት የሰሩ ሲሆን፣ በቱኒዚያና በሌሎች ሀገሮች በአምባሳደርነትና በሌሎች የመንግሥት ኃላፊነቶች ላይም ሰርተዋል፡፡አምባሳደር ዘውዴ ረታ በቅርቡ በኤግዚቢሽን ማዕከል በተዘጋጀው “ንባብ ለህይወት” የመፅሃፍ አውደ ርዕይና ሸያጭ ላይ “የአመቱ የንባብ ለህይወት” የወርቅ ብዕር ተሸላሚ የነበሩ ሲሆን “የ2006 የበጐ ሰው” ተሸላሚም ነበሩ፡፡

  ፊልሞች ደህንነታቸው ተጠብቆ ለተመልካች ለማድረስ የሚያስችልና የፊልም ስርቆቶችን ያስቀራል የተባለ አዲስ ቴክኖሎጂ ስራ ላይ ዋለ፡፡
አቢስውድ በተባለ ድርጅት ስራ ላይ የዋለው  አዲስ ቴክኖሎጂ፤ ፊልሞች በአንድ ጊዜ ከአንድ የማሰራጫ ስፍራ ወደተለያዩ ሲኒማ ቤቶች እንዲሰራጩ የሚያደርግና የፊልሙን ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ የሚጠብቅ ነው፡፡
 ድርጅቱ በፊልሞች ላይ የራሱን የይለፍ ኮድ በማድረግ ፊልሞች ያለ ባለቤቱ ፈቃድ እንዳይታዩ ቴክኖሎጂው ይከላከላል ተብሏል፡፡ድርጅቱ ከፊልም ስራዎች ተቀብሎ በየሲኒማ ቤቱ እንዲታዩ ለሚያደርጋቸው ሲኒማዎች ሁሉ ዋስትና የሚሰጥ ሲሆን ፊልሞቹ በምንም መንገድ ያለባለቤቱ ፈቃድ ለተመልካች ቢደርሱ ተጠያቂ የሚሆንበትን አሰራር ተግባራዊ የሚያደርግ ነው፡፡
 ድርጅቱ ፊልሞች በክልል ከተሞችም በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት እንዲታዩ ለማድረግ የሚችል ሲሆን በቀጣይ ከአገር ውጭ ፊልሞች የሚታዩበትን አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ እቅድ እንዳለው ተገልጿል፡፡

 “መርካቶ ሰፈሬ” በሚለው የመጀመሪያ አልበሙ ተወዳጅነትን ያተረፈው ድምፃዊው አብዱ ኪያር፤ “ጥቁር አንበሳ” በሚል ስያሜ አራትኛ አልበሙን ሰሞኑን ለአድማጭ አድርሷል፡፡ የአልበሙን መጠሪያ ጨምሮ 11 ዘፈኖች የተካተቱበት የሙዚቃ አልበሙ፤ በአሸብር ማሞ የተቀናበረ ሲሆን ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ዜማ ስቱዲዮ ውስጥ እንደታተመ በአልበሙ ሽፋን ላይ ተገልጿል፡፡ በግጥምና በዜማ ድምፃዊውን ጨምሮ በርካታ ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን ታዋቂው ሙዚቀኛ ፈለቀ ሀይሉ በሳክስፎን አጅቦታል፡፡ ዘፈኖቹ በፍቅር፣ በአንድነት፣ በትውስታና ሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚያጠነጥኑም ለማወቅ ተችሏል፡፡

 ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ ከኢትዮጵስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር፣ ነገ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በብሔራዊ ቤተ መፃሕፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ በ “አንቀፅ 39” መጽሐፍ ላይ ውይይት እንደሚያካሂድ ገለፀ፡፡ የመጽሐፉ ደራሲ አቶ ውብሸት ሙላት፤ ለውይይቱ መነሻ ሃሳብ እንደሚያቀርቡ የጠቆመው ሚዩዚክ ሜይዴይ፤ የመጽሐፍት አፍቃሪያን በውይይቱ ላይ እንዲታደሙ ጋብዟል፡፡