Administrator

Administrator

ከዕለታት አንድ ቀን አንድ አባት ክፉኛ ይታመምና የአልጋ ቁራኛ ይሆናል፡፡ ባለቤቱ ቀደም ብሎ ህይወቷ አልፏል፡፡ ያለው አንድ ልጅ ብቻ ነው፡፡ የሚያስታምመውም እሱ ነው፡፡
በሰፈሩ በየምሽቱ የሚመላለስና በረት የሚያጠቃ አንድ ነባር ጅብ አለ፡፡ ሰው ሁሉ ይሄንን ጅብ ለመግደል ብርቱ ጥረት ያደርጋል፡፡ ሆኖም ሊገድለው የሞከረ ሰው ሁሉ በውጤቱ የሚናገረው አንድ ቃል ብቻ ነው፡፡
“እህ አያ እገሌ ያን ጅብ እንዴት አደረግኸው?” ይላል መንደሬው፡፡
አዳኙም፣
“አዬ! አድፍጬ አድፍጬ አመለጠኝ ባክህ!”
እንዲህ እንዲህ እየተባለ ያ ጅብ ግን በየማታው ከየበረቱ አንድ አንድ አህያና አንዳንድ ጊደር እየመነተፈ ጉልበቱ እየጠነከረ መጣ፡፡
ታማሚው አባትና ልጅም የዚሁ ጅብ ሰለባ እየሆኑ፣ ብዙ ከብት ከበረታቸው ተበልቶባቸዋል፡፡
አንድ ቀን አባትዬው ልጁን ጠርቶ፤
“ልጄ ሆይ”
“አቤት አባባ”
“የዚህን የጅብ ነገር አንድ መላ መምታት አለብን”
“ምን ዓይነት መላ አባዬ?”
“ወጥመድ ሰርተን እንይዘዋለን”
“ምን አይነት ወጥመድ?”
“ሄደህ ከመንደር ሙዳ ስጋ ገዝተህ ትመጣለህ”
“እሺ፤ ከዛስ?”
“ያንን ሙዳ ሥጋ በጠመንጃችን አፈ - ሙዝ ላይ ታስረዋለህ”
“እሺ፤ ከዛስ”
“ሙዳውን ያሰርክበትን ገመድ ጫፍ ጠመንጃው ቃታ ላይ ታስረዋለህ”
“ከዛስ?”
“በቃ ያንን ወስደህ በረታችን ፊት ለፊት ታስቀምጥለታለህ፡፡ አጅሬ ሥጋውን አገኘሁ ብሎ ሲጎትት ቃታውን ይስበዋል፡፡ ጥይቱ ባፉ ይገባና ድብን ያደርገዋል”
“እሺ አባዬ ዛሬ ማታ ያልከኝን አደርጋለሁ፤ ይሄ ከተሳካኮ የመንደሩ ህዝብ ነው የሚገላገለው፡፡ ለእኛም ጥሩ ስም ያተርፍልናል፡፡”
ልጅ በቃሉ መሰረት ሥጋውን ገዝቶ፣ ጠመንጃው ላይ አስሮ በረቱ ደጃፍ ላይ አስቀምጦ ይጠባበቅ ጀመር፡፡
ከሰዓታት በኋላ ልጁ ወደ አባቱ ሲሮጥ ይመጣል፡፡
“አባዬ አባዬ፤ ጉድ ሆነናል”
“ምነው? ምን ተፈጠረ” አለ አባት በድንጋጤ፡፡
“አባዬ፤ ጅቡ ጠመንጃውን በሰደፉ በኩል ነክሶ ሥጋውን ከነጠመንጃው ይዞት ሄደ፡፡”
አባትየውም፤
“ወይ ጉድ! እንኳን ጠመንጃ ሰጥተኸው እንዲሁም አልቻልነው!”
*          *          *
እንዲህ ያለ የሠለጠነ ጅብ አያድርስ ነው፡፡ ዛሬ በሀገራችን አያሌ የሰለጠነ ጅብ አለ፡፡ የሰለጠነ ጅብ መኖሩ ብቻ ሳይሆን የጅቦች ማሰልጠኛ ያለ ይመስል በርካታ ጅቦች መኖራቸው የበለጠ አሳሳቢ ያደርገዋል፡፡ ከዚህ እጅግ የከፋው ነገር ደግሞ የጅቦች የተጠላለፈ መረብ፣ በሜዳ ስሙ “ኔትዎርክ” የሚባል መኖሩ ነው፡፡ ጅብ ለማጥመድ የሚሞክሩት ጥቂት ናቸው፡፡ ስለሆነም በመረቡ ተጠልፈው ራሳቸው ይያዛሉ፡፡ የሙስናን ነገር ለመፍታት እጅግ አዳጋች ያደረገው ይሄ ነው፡፡ ከላይ ነገሩን ይከላከላሉ፣ እርምጃ ይወስዳሉ የተባሉት አካላት ጉዳዩ ውስጥ ካሉበት ነገሩ ሁሉ የግብር ይውጣ እንደሚሆን ግልፅ ነው፡፡ “ስለገብስ አታውራ፡፡ ፈረሱ እንዳይሰማ” ሆኗል ችግሩ፡፡ የምናጠምደው ወጥመድ ሁሉ ጠመንጃ የሚያስነጥቀን ከሆነ ገንዘቡ፣ ሀብቱ፣ መሬቱ ወዴት እንደሚሄድ ያለጥርጥር መናገር ይቻላል፡፡ ፈረንጆች who guards the guards ይላሉ፡፡ ተቆጣጣሪዎቹን ማን ይቆጣጠራቸዋል፤ ጠባቂዎቹንስ ማን ሃይ ይላቸዋል፡፡ እንደማለት ነው፡፡ የቢሮክራሲው፣ የሥራ አስፈፃሚውና የነጋዴው ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ዛሬ “ቢዝነስ” የሚባለው ቃል የተራው ዜጋ፣ የተራው ሟች (average mortal) ቋንቋ ሆኗል፡፡ የካፒታሊዝምን ሥርዓት መቀበል፤ “ነፃ ገበያ”፣ “የግል  ሀብት”፣ “የዲሞክራሲ ሥርዓት”፣ “የኢንዱስትሪ መስፋፋት”… እንደምንለው ቃለ-ተውኔት የቀለለ አይደለም፡፡
የካፒታሊዝምን ሥርዓት መቀበል “መሳም ወደሽ ጢም ጠልተሽ” ማሰኘቱ አይቀሬ ነው፡፡ የባህል ወረራው ታላቅ አደጋ ነው፡፡ In God we trust (በእግዚአብሔር እናምናለን) ከሚለው ዶላሩ ላይ ከተፃፈው መራሄ-ቃል ጀምረን (እንዲህ እያልሽ ውቴልሽን ሽጪ ይላሉ ወሎዎች) እስከ ታላላቅ የንግድ መቆጣጠሪያ ኮርፖሬት ኃይሎች ድረስ የተዘረጋ መረብ እንዳለ ማስተዋል አለብን፡፡ በዚህ መረብ ውስጥ የማይጠመደው ጅብ አለ፡፡ በምንም መልኩ ሰው ገለህም ቢሆን፤ ገንዘብ ያዝ የሚለው መርህ አለ፡፡ ከጋሪ እስከ መርከብ ነግደህ አትርፍ (እያጎ እንደሚለው “ገንዝብ ሰብስብ በተቻለ”) የሚለው አለ፡፡ ጉዳዩ ግን የአስርቱ ቃላት ግልባጭ ስብከት፣ ነው፡፡ ማለትም “ሥረቅ”፣ አመንዝር”፣ “የጓደኛህን ሚስት ተመኝ”፣ “ጎረቤትህን እንደራስህ አድርገህ ጥላ” ወዘተ ማለት ነው፡፡ የመንታፊዎች፣ የወሮበሎች፣ የመንገድ ላይ ጉልቤዎች፣ የታጣቂ ሰራቂዎች፣ የቁጭ በሉዎች፣ የምሁራዊ ሌቦች፣ የልማታዊ ቀማኞች፣ የአዛኝ - ቅቤ - አንጓች ዘራፊዎች፣ የረቂቅ አገር - ቦርቧሪዎች፣ የዓለም አቀፍ ጨረታ በዝባዦች፣ የባንክና የኢንሹራንስ መዝባሪዎች ወዘተ መፈልፈያ ነው ካፒታሊዝም፡፡ ታዲያ እነዚህ ፍልፍሎች እንደቃላት መጠሪያቸው የረከሱ አይደሉም፡፡ የክርስትና ስምም፣ የማዕረግ ጥምም፣ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያገኘ ስምም፣ የቢዝነስ ስምም፤ ያላቸው  የተከበሩ  ሥራዎች ናቸው። እንደኛ የተደላደለ ኢኮኖሚ በሌላቸው አገሮች ላይ እንግዲህ በእንቅርት ላይ ጆሮ  ደግፍ፣ በቡሃ ላይ ቆረቆር ማለት ነው፤ ካፒታሊዝም፡፡ ገንዘብና ገንዘብ እንጂ ሌላ ነገር  አታስቡ፡፡ እነሆ አምላካችሁ እሱና እሱ ብቻ ነው! ይላል መጽሐፈ - ንዋይ! ዕውቀት ባልበለፀገበት፣ ሃይማኖት በገንዘብ እየተሸረሸረ ባለበት፣ ባህልና ቅርስ ካንገት በላይ እየታሰበ ባለበት፣ አገም ጠቀም ፖለቲካዊ ኢኮኖሚ የሚያኮራ በሚመስልበት፣ የሚከበሩ በዓላት ሁሉ  የኛም እየመሰሉ በሚታዩበት፣ መሰረታዊ የሚባሉት ቤት፣ ውሃ፣ መብራት እንኳ በቅጡ በማይገኝበት አገር የካፒታሊዝም አባዜ ሲጨመርበት “እንኳን ጠመንጃ ሰጥተኸው እንዲሁም አልቻልነው” የሚያሰኝ ነው፡፡ ከዚህ ይሰውረን!   

• የግብጽና ሱዳን ሚኒስትሮች ልዩ ዝግጅት ለማድረግ መክረዋል
• የሶስቱ አገራት መሪዎች በአ/አ በግድቡ ዙሪያ እንደሚመክሩ ይጠበቃል

    የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በታችኛው የተፋሰሱ አገራት የሚያደርሰውን ተጽዕኖ በማጥናት ላይ የሚገኙት አለማቀፍ አማካሪ ተቋማት፤ በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ውስጥ የቴክኒክ ሃሳቦቻቸውን ያቀርባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅና የግብጽ የመስኖና የውሃ ሃብቶች ሚኒስትር ሆሳም ሞጋዚና የሱዳኑ አቻቸው ሞአታዝ ሙሳም፣ አገራቱ አማካሪዎቹ ለሚያቀርቧቸው ሃሳቦች ማድረግ የሚገባቸውን ልዩ ዝግጅቶች በተመለከተ መምከራቸውን የግብጽ መንግስት የኢንፎርሜሽን አገልግሎት ትናንት ባወጣው መግለጫ አስታወቀ፡፡
ሁለቱ ሚኒስትሮች በቀጣዩ የሁለቱ አገራት የጋራ ከፍተኛ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ ይፈረማል ተብሎ በሚጠበቀው የአገራቱ የውሃ ሃብቶች ትብብር የመግባቢያ ሰነድ ዙሪያ መወያየታቸውን የጠቆመው መረጃው፣ የሁለቱን አገራት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን በሚመለከቱ ሌሎች በርካታ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውንም ገልጧል፡፡ የግብጹ አሃራም ድረገጽ በበኩሉ፤  የግብጽ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ በዛሬው እለት በተጀመረው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ መግባታቸውን ጠቁሞ፣ በግድቡ ዙሪያ ከኢትዮጵና ከሱዳን አቻቸው ጋር ይመክራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዘግቧል፡፡




-    የኩሪፍቱ ሪዞርት ቅርንጫቾች 9 ደርሰዋል
-    3 አዳዲስ ቅርንጫቾች በመገንባት ላይ ናቸው
-    በጅቡቲም በ150 ሚ. ብር ሪዞርት እየተሰራ ነው
በዓለም ላይ ያሉ ታዋቂ ሆቴሎች፣ ኤርፖርቶችና ከቀረጥ ነፃ (ዲዩቲ ፍሪ) ሱቆች፣ በዓለም የተሰራጩ የኢትዮጵያውያን ሬስቶራንቶች፣ … በኢትዮጵያውያን ቪሌጅ ውስጥ ኮርነር ወይም መደብር ሊኖራቸው ይችላል፡፡
ሀሳቡ የተጠነሰሰው ከ6 ዓመት በፊት ነው፡፡ ኢትዮጵያን ቪሌጅ፣ የኢትዮጵያ ቻምፒዮን (ምርጥ) ምርቶች የሚሸጡበት ማዕከል ነው፡፡ ምርቶቹን መሸጥ ብቻ ሳይሆን የምርት ሂደታቸውም  የሚታይበት ሥፍራ ነው፡፡ ጥጥ ሲፈተል፣ ሲደወር፣ ሲሸመን…፤ብረት ሲግል፣ ሲቀጠቀጥ፣ ሲቀልጥ … ፤የሸክላ ሥራው፣ አፈሩ ሲነፋ፣ ሲቦካ፣ ሲሰራ፣ በእሳት ሲቃጠል … በመጨረሻም የሁሉም ምርቶች የሚቀርብበት ማዕከል ነው - ኢትዮጵያን ቪሌጅ፡፡
የኢትዮጵያ ባህላዊ ጭቃዎች አሰራር ለትውልድና ለልጅ ልጆቻችን የምናስተላልፍበት፣ የባህል ማዕከል ሆኖ የውጭ አገር ሰዎችና (ቱሪስቶች) ትልልቅ ማርኬተሮች ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ፣ የአገራችንን ባህላዊ የወግ ዕቃዎችና የሚፈልጉትን ዓይነት ምርቶች ከአንድ ስፍራ የሚገዙበት የኤክስፖርት ማርኬት ለመጀመሪያ ጊዜ “የራሳችን ምርት ማዕከል” ሰፈር ወይም መንደር የምንለው የገበያና የማሳያ ቦታ በቢሾፍቱ (ኩሪፍቱ) በ74 ካ.ሜ ቦታ ላይ እየተገነባ ነው፡፡
በባልትና የተካኑ ታዋቂ አምራቾች፣ በአሁኑ ወቅት ምርቶቻቸውን ወደ ውጭ እየላኩ ያሉ ታላላቅ ኩባንያዎች ከእኛ ጋር ለመሥራት ተመዝግበው የግንባታው ስራ እየተካሄደ ነው፡፡ በያዝነው የፈረንጆች ዓመት የተለያዩ የኢትዮጵያ ምርጥ (ሻምፒዮን) ምርቶችን ሱቅ እየከፈትን፣ የኢትዮጵያን የቱሪዝም፣ የባህልና የኤክስፖርት ማዕከል፣ አዲሲቱን ኢትዮጵያ በግልጽ ለዓለም ማሳየት እንጀምራለን፡፡ የሚገነቡት ሱቆች ብቻ አይደሉም፤200 ያህል የኮንፈረንስና የቱሪስቶች ማረፊያ ክፍሎች ስለሚሰሩ ወጪው 400 ሚሊዮን ብር ይሆናል፡፡
በሪዞርት ደረጃም በኢትዮጵያ ትልቁን ስፍራ ይይዛል ብዬ አስባለሁ፡፡ አሁን 100 ክፍሎች አሉን፡፡ 200 ክፍሎች ሲጨመሩ 300 ክፍሎች ይኖሩናል፡፡ በአንድ ጊዜ 300 ያህል ሰዎች እናስተናግዳለን ማለት ነው፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ በርካታ የኮንፈረንስ ክፍሎች ይኖሩናል፡፡ አሁን 1,000 ሰዎች መያዝ የሚችል አዳራሽ አለን፡፡ አዲሶቹ ሲጨመሩ ደግ ከ1,500 - 2,000 ሰዎች የሚያስተናግድ አዳራሽና ፋሲሊቲ ይኖረናል፡፡ በዚህ ሁኔታ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ በዓይነቱም፣ በትልቅነቱም፣ በስፋቱም የመጀመሪያው ይሆናል ----- በማለት የኩሪፍቱ ሪዞርት ባለቤትና ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ታዲዎስ ጌታቸው በለጠ፣ በግንባታ ላይ ስላለው አዲሱ የኢትዮጵያ ቪሌጅ ገልጸዋል፡፡
አቶ ታዲዎስ አርሲ ውስጥ በትንሽ መንደር ተወልደው፣ ደሴና አዲስ አበባ ነው ያደጉት፡፡ በ1973 ዓ.ም ወደ ሱዳን ገብተው፣ ለ3 ዓመት ከቆዩ በኋላ በስደተኝነት አሜሪካ ገቡ፡፡ እዚያም ከጓደኞቻቸው ጋር በመሆን የራሳቸው ፀጉር ቤት፣ የራሳቸው ሬስቶራንት ከፍተው ይሰሩ ነበር፡፡ ክለቦችንም ፕሮሞት በማድረግ ሰርተዋል፡፡ በዚህ ዓይነት እየሰሩ ድርጅቶቹ ወደ ሁለት አድገው ነበር፡፡
ከ20 ዓመት የአሜሪካ ቆይታ በኋላ፣ በ1994 ዓ.ም በአገራቸው ኢንቨስት ለማድረግ ጓደኞቻቸውን ጥለው ወደ ኢትዮጵያ ተመለሱ፡፡ በመጀመሪያ በቦሌ መንገድ የሚገኘውን ቦስተን ህንፃ በ37 ሚ. ብር ገንብተው በቦስተን ስፓ ጀመሩ፡፡ ቦስተን ስፓ የአዲስ አበባና የአካባቢዋ ሴቶች ለሰርግና ለልዩ ዝግጅቶች የሚዋቡበት ምርጥ ስፓ ነው፡፡ በመቀጠልም በቢሾፍቱ ኩሪፍቱ ሪዞርት ተከፈተ፡፡ የሪዞርቱ ሥራ እያደገና እየሰፋ ሄዶ፣ ባህርዳር ኩሪፍቱ፣ አዳማ ኩሪፍቱ፣ ዝዋይ ኩሪፍቱ፣ … እያለ የኩሪፍቱ ቅርንጫፎች ብዛት 9 ደርሷል፡፡ አቶ ታዲዎስ በዚህ ብቻ አልረኩም፡፡ ሌሎች አዳዲስ ሪዞርቶች በቡራዩ ------------------፣ በጅቡቲ እያስገነቡ ነው፡፡
ኩሪፍቱ ሪዞርት ኢትዮጵያ ውስጥ ተወልዶና አድጎ ወደ ውጭ የወጣ የመጀመሪያው ሪዞርት ነው፡፡ ጂቡቲ የተመረጠችበት የራሷ ምክንያቶች አሏት፡፡ ሁለቱም አገሮች የቱሪዝም ደጋፊ ከመሆናቸውም በላይ ጂቡቲ በዕድገት እንቅስቃሴ ከኢትዮጵያ ጋር ለመስራት ፍላጎት አላት፡፡ ሁለተኛው ምክንያት ጂቡቲ፣ ኢትዮጵያ የሌላትን ሰማያዊ ውሃ፣ ነጭ የባህር ዳርቻ አሸዋ፣ በርካታ የባህር ምግቦች፣ … ስላላት ነው፡፡ ሦስተኛው ምክንያት ደግሞ ከኢትዮጵያ ከ40 ወይም 45 ደቂቃ የአውሮፕላን በረራ በኋላ የሚደረስባት መሆኗ ነው ያስመረጣት፡፡
ሌሎች ምክንያቶችም አሉ፡፡ የጂቡቲ ወደብ ከምስራቅ አፍሪካ ለየት ያለና በጣም ውብ ነው፡፡ ከዚህም በላይ 250 ሺህ ካ.ሜ ሰው ሰራሽ ደን አሉት፡፡ ኢትዮጵያውያን የጫጉላ ሽርሽርና ክብረ በዓላቸውን ጂቡቲ እየሄዱ እንደሚያሳልፉ ይታወቃል፡፡ ስለዚህ የራሳቸው የሆነ የተሻለ ምርጫ ቢያገኙ በጣም ይደሰታሉ በማለት ኩሪፍቱ ቁጥር 2 በጅቡቲ እየተሰራ መሆኑን አቶ ታዲዎስ ገልጸዋል፡፡
የመጀመሪያው ምዕራፍ የጂቡቲ ኩሪፍቱ ፕሮጀክት 150 ሚሊዮን ብር ወይም 7 ሚሊዮን ዶላር ይፈጃል፡፡ ሪዞርቱ እየተስፋፋ ሲሄድ ወጪው ምን ያህል ሊሆን እንደሚችል መናገር ይከብደኛል ይላሉ አቶ ጌታቸው፡፡ ነገር ግን ይህ ሪዞርት፣ ለኢትዮጵያውያን አንድ መውጪያ አማራጭና መዝናኛ እንደሚሆን በእርግጠኝነት ተናግረዋል፡፡
በቱሪዝም በኩል ኢትዮጵያ በሰሜን ያላት እሴቶች፡- ላሊበላ፣ አክሱም፣ ጎንደር፣ ባህርዳር እንዲሁም በደቡብ ያሉ ሰፊ የሆኑ ሞዛይክ ባህላችንን እናስተዋውቅበታለን፡፡ ጂቡቲ ደግሞ ሰማያዊ ውሃዋን፣ የባህር ዳርቻዋን፣ የባህር ምግቦቿን፣ ሻርኮቿን፣ … በማስተዋወቅ ሁለቱም አገሮች ይጠቀሙበታል፡፡
ጂቡቲ በዓለም የሌለ ልዩ የሆነ የአሳ ነባሪ ጉብኝት፣ እንደጨው ባህር በአፍሪካ ዝቅተኛ ሥፍራ ላካሰን የተባለ ንፁህ የጨው ቦታ፣ የተፈጥሮ የሆኑ የተለያዩ የባህር ውስጥ እንስሳት (አኳሪየም) አሏት፡፡ እነዚህን ነገሮች አንድ ላይ ሲቀናጁ ጂቡቲ የመጣ ቱሪስት ወደ ኢትዮጵያ ጎራ ብሎ ይጎበኛል፡፡ እዚህ የመጣ ጎብኚ ደግሞ ወደ ጅቡቲ ሄዶ ያላትን የተፈጥሮ ሀብት ያያል፡፡ በዚህ አይነት ሁለቱ አገሮች ዓለም አቀፍ እውቅና አግኝተው ቱሪዝማቸውን ያሳድጋሉ፡፡    
የጅቡቲው ኩሪፍቱ ግንባታው የተጀመረ ሲሆን በመጀመሪያው ምዕራፍ 64 ክፍሎች ይኖሩታል፡፡ የተለያዩ አገራት ሬስቶራንቶች፣ ስፓ፣ የተለያዩ የውሃ ላይ መዝናኛዎች፣ የዶልፊንና የሻርኮች ትርዒት፣ የተለያዩ የተፈጥሮ የውሃ ውስጥ እንስሳት መመልከቻ ጀልባዎች፣ … ለየት ባለ መልኩ የኢትዮጵያና የዓለም ቱሪስቶች ይስተናገዱበታል፡፡
ኩሪፍቱ ዕድገቱ እየተስፋፋ፣ ቅርንጫፎቹ እየበረከቱ ነው፡፡ እነዚህን ሁሉ ቅርንጫፎች በአንድ ዓይነት አስተዳደር ማናጅመንት መምራት የጥራት ደረጃው ተመሳሳይ የሆነ አገልግሎት መስጠት … ሊከብድ ይችላል፡፡ አቶ ታዲዎስ እነዚህን ጉዳዮች እንዴት ተወጥተዋቸው ይሆን?
እኛ ስንጀምርም ኢትዮጵያዊ ሆኖ ወደ ሌሎች አፍሪካ አገሮች ሊሻገር የሚችል፣ ኢትዮጵያዊ ዲዛይን ያለው፣ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች የሰሩትና የሚመሩት (ካስፈለገ አፍሪካውያን የሚመሩትና የሚያስተዳድሩት) የኢትዮጵያንና የአፍሪካን ሬነሳስ ለዓለም ህዝብ የምናስተዋውቅበት ኮርፖሬት ማኔጅመንት አለን፡፡ እያንዳንዱ ቅርንጫፍ ደግሞ፣ የየራሱ አመራር አለው፡፡ ሰራተኞቻችንን የምንቀጥረው አሰልጥነንና ፈትነን ነው፡፡ ከጊዜው አሰራር ጋር እንዲተዋወቁና እንዲላመዱ የሥራ ላይ ሥልጠና ይሰጣቸዋል፡፡
ስለዚህ መቶ ቅርንጫፎች ቢኖሩንም አሰራርና ማኔጅመንታችን አንድና ተመሳሳይ ነው፡፡ ኩሪፍቱ በኢትዮጵያ ውስጥ በብራንድ ደረጃ እያደገና እየሰፋ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ሰራተኞቻችንም ከጊዜ ወደ ጊዜ በአገልግሎት አሰጣጣቸው ልምድና ክህሎታቸውን እያገለበቱ ስለሆነ እኛ ኢትዮጵያውያን ለዓለም ህዝብ ጥራት ያለው አገልግሎት እንሰጣለን በሚል ኩራት ይቀጥላሉ ብዬ አምናለሁ ብለዋል፡፡
 ኩሪፍቱ በየቦታው ቅርንጫፎቹን የሚከፍተው በትርፍ ቢንበሸበሽ ነው ወይስ ትርፉን መልሶ ኢንቨስት እያደረገ ነው? ጥያቄውን ለባለቤቱ አቀረብኩ፡፡ “የበለፀገችና ያደገች፣ የተለወጠች ኢትዮጵያን የማየት ዓላማና ፅናት ነው እንጂ በትርፍ ተንበሽብሸን አይደለም” አሉ፤ፍርጥም ብለው፡፡
እኛ የምናገኘውን ትርፍ ሁሉ ድንጋይና ሲሚንቶ ላይ ነው የምናውለው፡፡ እዚህ ደረጃ መድረስ የቻልነው በዓላማና በቁርጠኝነት፣ በማደግና በመለወጥ ላይ ያለችውን አገራችንን በምንችለው አቅም እንደግፍ ብለን፣ ፍላጎታችንን እየገታንና በየፕሮጀክቱ ከተባባሪ አካላት ጋር ጠንክረን በመስራት ነው በማለት አስረድተዋል፡፡
 
በአሁኑ ወቅት ካፒታላችሁ ምን ያህል ነው? አልኳቸው
አቶ ታዲዎስ ዝም ብለው መስራት እንጂ ካፒታላቸው ምን ያህል እንደሆነ አያውቁም፡፡ “በእውነት ነው የምልህ፣ ምን ያህል እንደሆነ አላወቀውም፡፡ አሁን እየበዛ ስለመጣ ቁጭ ብለንም ካልኩሌት አድርገነው አናውቅም ዕድገታችን ግን በግልፅ የሚታይ ነው፡፡ በቀጣይ እንመጣበታለን ብዬ አስባለሁ፡፡
አቶ ታዲዎስ ሲጀምሩ ራዕይ ነበራቸው፡፡ ራዕዩም ከአፍሪካ 100 ምርጥ ሪዞርቶች አንዱ መሆን የሚል ነበር፡፡ አሁን ያን ሕልማቸውን ምን ያህል እያሳኩ ይሆን? ይደረስበታል ብዬ አምናለሁ፡፡ ባለፉት 13 ዓመታት ባደረግነው ጠንካራ የቡድን ሥራ እዚህ ደረጃ ላይ ደርሰናል፡፡ ከዚህ በኋላ ያለው ሥራ ይከብደናል ብዬ ስለማላምን፣ በአፍሪካ በመጀመሪያ ተርታ ከሚሰለፉ ሪዞርቶች አንዱ፣ የኢትዮጵያን ስም የሚያስጠናራ ተወዳዳሪ የሚሆን ሪዞርት ይሆናል ብየየ አምናለሁ፡፡
ኩሪፍቱ፣ እንደሚገመተው ውድ አይደለም፡፡ የውጭ አተር ዜጎችና ዲያስፖራዎች ቢኖሩም አብዛኞቹ ደንበኞች ኢትዮጵውያን እንደሆኑ ባለቤቱ ይናገራል፡፡ “ዝም ብሎ የሚመጣ ነገር የለም፡፡ እኛ በዓለም አቀፍ ደረጃ ፕሮሞት እናደርጋለን፡፡ “ኩሪፍቱ” የሚለው የብራንድ ስማችንም “ሂልተን፣ ሸራተን፣ …” እንደሚለው እየተለመደና እየታወቀ ስለሆነ ሥራችን በቋሚነትና በተከታታይነት እያደገ ነው የመጣው፡፡
እንደማንኛውም ሆቴል እንደየጊዜው የሚለዋወት ዋጋ አለን በእኛ ክረምት ሰኔ፣ ሐምሌና ነሐሴ የሚመጣ ቱሪስት የለም፡፡ በእነዚህ ሦስት ወራት ጎረቤት አገሮች ጂቡቲ፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ኩዌት ሌሎቹንም አገሮች የምናግባበት የተለየ ፓኬጆች አሉን፡፡ በዚያን ጊዜ ከተለያየ የዓለም ክፍሎች ልጆቻቸውን ይዘው የሚመጡ ኢትዮጵያውያን እናቶች አሉ፡፡ ጊዜውን እያየን ስለምንሰራና ፕሮሞት ስለምናደርግ አልጋችን ይያዛል፡፡
ኩሪፍቱ በአሁኑ ጊዜ ለ2000 ቋሚና ጊዜያዊ ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል፡፡ የኢትዮጵያውያኒ ቪለ፤ጅ ሥራ ሲጀምር 1,000 ወጣት ሴቶች ይቀጠራሉ፡፡ በመጪው ዓመት መጨረሻ በኩሪፍቱ ሪዞርት የሚሰሩ ዜጎች ቁጥር 3, 000 ይደርሳል ብለዋል፡፡  



    የገጣሚ ኤፍሬም ስዩም “ኑ ግድግዳ እናፍርስ” የተሰኘ አዲስ የግጥም መድብል የፊታችን ረቡዕ ከቀኑ 11፡30 ሰዓት ጀምሮ በዋቢሸበሌ ሆቴል ይመረቃል፡፡ በእለቱ ገጣሚውን ጨምሮ ሌሎች እውቅ ገጣሚያን ግጥሞቻቸውን በሙዚቃ ታጅበው የሚያቀርቡ ሲሆን ግጥሞቹን ሰዓሊያን በቀጥታ ወደ ስዕል እየቀየሩ ታዳሚውን እንደሚያዝናኑ ተገልጿል፡፡
መፅሐፉ፤ በማህበራዊ፣ በውበት፣ በፍቅር በፍልስፍና ዙሪያ የሚያጠነጥኑ 61 ግጥሞችን ያካተተ ሲሆን ግጥሞቹ በእውቁ ሀያሲ አብደላ ዕዝራ ትንታኔ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ በ150 ገፆች የተቀነበበው መፅሀፉ፤ በ45 ብር ከ65 ሳንቲም ለገበያ ቀርቧል፡፡ ገጣሚው ከዚህ ቀደም “ፍቅር እዚህ ቦታ ፈገግ ብሎ ነበር”፣ “የብርሀን ክንፎች” “ሶሊያና” (በሲዲ)፣ “ተዋነይ”፣ “የይሁዳ ድልድይ” እና ከሌሎች ገጣሚያን ጋር “ግጥም በመሰንቆ” የተሰኙ የግጥም ስራዎችን ለአንባቢ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡

ትውልደ ኢትዮጵያዊው የፖፕ ሙዚቃ አቀንቃኝ አቤል ተስፋዬ /ዘ ዊኪንድ/፤ “ኧርንድ ኢት” በተባለው የፊልም ማጀቢያ ሙዚቃው፣ለዘንድሮው የኦስካር ሽልማት መታጨቱ ተዘገበ፡፡

“ፊፍቲ ሼድስ ኦፍ ግሬይ” ለተባለው ፊልም በማጀቢያ ሙዚቃነት የተሰራው “ኧርንድ ኢት”፣ በኦስካር ሽልማት የምርጥ ወጥ ሙዚቃ ዘርፍ መታጨቱን ዘ ካናዲያን ፕሬስ ዘግቧል፡፡

በዘርፉ ለሽልማት ከታጩት አምስት ሙዚቃዎች መካከል በታዋቂዋ ድምጻዊት ሌዲ ጋጋ የተቀነቀነውና “ዘ ሃንቲንግ ግራውንድ” ለተባለው ፊልም በማጀቢያነት የተሰራው “ቲል ኢት ሃፕንስ ቱ ዩ” ይገኝበታል፡፡  
የዘንድሮው የኦስካር ሽልማት ስነስርዓት በመጪው የካቲት መጨረሻ እንደሚካሄድና የመድረክ መሪውም ታዋቂው የሆሊውድ ተዋናይ ክሪስ ሮክ እንደሚሆን የተነገረ ሲሆን በኤቢሲ ቴሌቪዥን በቀጥታ ይተላለፋል ተብሏል፡፡

Saturday, 23 January 2016 13:43

የህፃናት ጥግ

(ስለ ፍቅር ተጠይቀው የተናገሩት)
-    “እሱን ማሰብ ራሴን ያሳምመኛል፡፡ እኔ ገና ህፃን ነኝ፡፡ የዚህን ዓይነት ችግር አልፈልግም፡፡”
ኮኒ (የ7 ዓመት ህፃን)
-    “የመዋዕለ ህፃናት ትምህርቴን ስጨርስ ለራሴ ሚስት እፈልጋለሁ፡፡”
ቶም (የ5 ዓመት ህፃን)
-    “በቀስት ወይም በሆነ ነገር መወጋት ያለብህ ይመስለኛል፤ የቀረው እንኳን ያን ያህል ስቃይ ያለው አይመስልም፡፡”
ማኑኤል (የ8 ዓመት ህፃን)
-    “በፍቅር መያዝ ስፔሊንግ እንደመማር ከሆነ ልገባበት አልፈልግም፡፡ በጣም ረዥመ ጊዜ ይወስዳል፡፡”
ግሌን (የ7 ዓመት ህፃን)
-    “ወደ ፍቅር ለመግባት አልጣደፍም፡፡ 4ኛ ክፍል በጣም ከብዶኛል፡፡”
ሬጂና (የ10 ዓመት ህፃን)
-    “አንድ ወንድና አንድ ሴት በሽታና ህመምን በአንድ ላይ ለማሳለፍ ቃል የሚገቡበት ነው፡፡”
ማርሎን (የ10 ዓመት ህፃን)
-    “ፍቅር ጅል ነው … ቢሆንም ግን አልፎ አልፎ እሞክረው ይሆናል፡፡”
ፍሎይድ (የ9 ዓመት ህፃን)
-    “አለመግባባት ይመረጣል … ምክንያቱም እኔ የሽንት ጨርቅ (ዲያፐር) መቀየር አልፈልግም፡፡ በእርግጥ ካገባሁ እንድ መላ እዘይዳለሁ፡፡ እናቴ ጋ እደውልና መጥተሸ ቡና ጠጪ ብዬ የሽንት ጨርቅ አስለውጣታለሁ፡፡”
ክሪስቲን (የ101 ዓመት ህፃን)
-    “አብዛኞቹ ወንዶች አዕምሮ-ቢስ ናቸው፤ ስለዚህ አዕምሮ ያላቸውን ለማግኘት ከአንድ ጊዜ በላይ መሞከር ይኖርባችሁ ይሆናል፡፡”
ኤንኪ (የ10 ዓመት ህፃን)
-    “አንድ ሰው ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሳም ይወድቃል፤ ቢያንስ ለአንድ ሰዓትም ከወደቀበት አይነሳም፡፡”
ዌንዲ (የ8 ዓመት ህፃን)
-    “እናትህ ከሆነች በማንኛውም ጊዜ ልትስማት ትችላለህ፡፡ አዲስ ሰው ከሆነ ግን ፈቃድ መጠየቅ ይኖርብሃል፡፡
ሮጀር (የ6 ዓመት ህፃን)
-    “መስቲካዋን ለመስረቅ እየሞከረ ነው፡፡”
(የ6 ዓመት ህፃን (ጥንዶች ሲሳሳሙ አይቶ የተናገረው)

Saturday, 23 January 2016 13:42

የፀሐፍት ጥግ

ልጄ ሂሳብና ፍልስፍና የመማር ነፃነት እንዲኖረው እኔ ፖለቲካና ጦርነትን ማጥናት አለብኝ፡፡
ጆን አዳምስ
-    የህብረተሰብ ደስተኛነት የመንግስት ማክተሚያ ነው፡፡
ጆን አዳምስ
-    ፍርሃት የአብዛኞቹ መንግስታት መሰረት ነው፡፡
ጆን አዳምስ
-    አንድን ነገር ካልወደድከው ለውጠው፡፡ ልትለውጠው ካልቻልክ አመለካከትህን ለውጥ፡፡
ማያ አንጄሎ

Saturday, 23 January 2016 13:41

የዘላለም ጥግ

(ስለ ትምህረት)
-    ትምህርት ሥልጣኔን የማስተላለፊያ መንገድ ነው፡፡
ዊል ዱራንት
-      ልቡናን ሳያስተምሩ አዕምሮን ማስተማር ፈፅሞ ትምህርት አይባልም፡፡
አሪስቶትል
-    ትምህርት ዓለምን ለመወለጥ ልትጠቀሙበት የምትችሉት እጅግ ሃያል መሳሪያ ነው፡፤
ኔልሰን ማንዴላ
-    አስተማሪዎች በሩን ይከፍታሉ፤
የቻይናውያን አባባል
-     የመማር ፍቅር አዳብሩ፡፡ ያኔ ፈፅሞ ማደግ አታቆሙም፡፡
አንቶኒ ጄ.ዲ'አንጄሎ
-    አስተማሪዎች ፈተና መስጠት እስከቀጠሉ ድረስ ሁልጊዜም በትምሀርት ቤቶች ውስጥ ፀሎት መኖሩ አይቀርም፡፡
ምንጩ ያልታወቀ
-    በመማር ታስተምራለችሁ፤ በማስተማር ትረዳላችሁ፡፡
የላቲኖች አባባል
-    የራሳችን መንተድ ሳናበራ የሌሎችን መንገድ ለማብራት ችቦ ልንይዝ አንችልም፡፡
ቤን ስዊትላንድ
-    ምንም ነገር ለማስተማር ብትፈልግ ቅልብጭ አድርገው፡፡
ሆራስ
-    የትምህርት ዘጠኝ አስረኛው ማበረታታት ነው፡፡
አናቶሌ ፍራንስ
-    የዘመናዊ የትምህርት ባለሙያ ተግባር ደኖችን ማጥፋት ሳይሆን በረሃን በመስኖ ማልማት ነው፡፡
ሲ.ኤስ.ሌዊስ
-    እንዴት እንደሚታሰብ የሚያውቁ አስተማሪዎችን አይፈልጉም፡፡
ማሃትማ ጋንዲ
-    የሚያደምጠው ካገኘ ሁሉም ሰው አስተማሪ ነው፡፡
ዶሪስ ሮበርትስ
-    ምርጥ አስተማሪየችሁ ለመጨረሻ ጊዜ የሰራችሁ ስህተት ነው፡፡
ራልፍ ናዴር



Saturday, 23 January 2016 13:39

የኪነት ጥግ

(ስለ ዳንስ)
-    በዳንስ ወለል ላይ አሸርን የምረታው ይመስለኛል፡፡
ክሪስ ብራውን
-    ከስድስት ወንድሞቼ ጋርነው ያደግሁት፡፡ ዳንስን የተማርኩት እንደዚያ ነው - የመታጠቢያ ቤት ወረፋ እየጠበቅሁ፡፡
ቦብ ሆፕ
-    ከፍሰቱ ጋር እፈሳለሁ፡፡ ለእኔ ምንም ዓይነት ሙዚቃ ብታጫውቱልኝ እደንሳለሁ፡፡
ጋኤል ጋርሽያ ቤርናል
-    ዕልድ የዳንስ ወለሉ ላይ ከወጡት ጋር ትደንሳለች፡፡
ኤች. ጃክሰን በራውን ጄአር
-    ዛሬ ህፃናቱ በፊታቸው መደነስ የሚች የመስላቸዋል፡፡
ጓንገር ሮጀርስ
-    ጀስቲን ቢበር የፀጉር ቁርጤን ሰረቀኝ፡፡ አክል ሮዝ ደግሞ ዳንሴን!
ዴቪ ጆንስ
-    ዴኒስ ሎው በእንቁላል ቅርፎቶች ላይ መደነስ ይችላል፡፡
ቢል ሸንክሊ
-    የምትኖረው መደነስ እስከቻልክ ድረስ ነው፡፡
ሩዶልፍ ኑሩዬቭ
-    በደብን መደነስ ባትችል ማንም ደንታ የሚሰጠው የለም፡፡ ዝም ብለህ ተነስተህ ደንስ፡፡
ዴቭ ባሪ
-    ሚስቶች፤ በበቂ ሁኔታ ደንሰናል ብለው የማያስቡ ሰዎ ናቸው፡፡
ግሮሾ ማርክስ
-    መዝፈን፣ መደነስ ወይም መተወን አልችልም፤ የቶክ ሾው አዘጋ ከመሆን ውጭ ሌላ ምን ልሆን እችል ነበር፡፡
ዴቪድ ሌተርማን
-    ሰዎች ውበትን ለማየት ይመጣሉ፤ እኔም የሚሹትን ለመስጠት እደንሳለሁ፡፡
ጁዲት ጃሚሶን
-    ዳንስ ስህተት አልባ እቅጩነት ሊኖረው ይገባል፡፡
አሪሌ ዶምባስሌ

   ወ/ሮ ዘሃራ ኑረዲን በህይወት የተለያ ምእራች በአስቸጋሮ ሁኔታ ያለፉ ሴት ናቸው፡፡ ወ/ሮዋን የላዳ ሹፌር በመሆን ሁለት ልጆቻቸውን በብቸኝነት የሚያስተዳድሩ እናት ናቸው፡፡ ያለፉበትን የህይወት ውጣ ውረድና ስኬቴ ያሉትን የታክሲ ማሽከርከር ህይወት ለአዲስ አድማሷ ጋዜጠኛ ማህሉት ኪዳነወልድ በአጭሩ አውግተዋል፡፡
እስኪ ስለ አስተዳደግዎ ያጫውቱኝ?
የተወለድኩት አዲስ አበባ አባ ኮራን ሰፈር፣ ልዩ ስሙ ሐግቤስ አካባቢ ነው፡፡ ለቤተሰቦቼ አራተኛ ልጅ ነኝ፡፡ አሁን ሁለቱ በህይወት ስለሌሉ ሁለተኛ ልጅ ሆኛለሁ፡፡ በአጠቃላይ ግን 12 ነበርን፡፡ እናትና አባቴ ከዝቅተኛው የህብረተሰብ ክፍል የሚመደቡ ነበሩ፤በእርግጥ ወደ መጨረሻ አካባቢ  በእናቴ ጥረት ነገሮች ተቀይረዋል፡፡  
የትምህርት ሁኔታስ?
ከ8ኛ ክፍል ነው ያቋረጥኩት፡፡ እንደነገርኩሽ ወላጆቼ ኑሮአቸው ጥሩ አልነበረም፤እናም እነሱን ለመርዳት በማሰብ ትምህርቴን አቋርጬ አረብ አገር ሄድኩኝ፡፡ ለ3 ዓመት ስሰራ ከቆየሁ በኋላ እዛው የነበረ ኢትዮጵያዊ አጨኝና ትዳር ተጀመረ፡፡ ሆኖም ትዳሬ ስኬታማ አልነበረም፤ እኔ የማደላው ለቤተሰቦቼ ነው፡፡ ሃሳቤ ሁሉ የእነሱን ህይወት መቀየር ነበር፡፡ እሱ ደግሞ ለቤተሰቤ ትኩረት መስጠቴን አልወደደውም፡፡ ይባስ ብሎም እንደ እህት ከምወዳት ጓደኛዬ ጋር ግንኙነት ጀመረ፡፡ አሁን እንደውም ተጋብተዋል፡፡ ያንን መቋቋም አልቻልኩም፡፡ የአንድ ዓመት ልጄን ይዤ ወደ አገሬ፣ወደ እናቴ ቤት ተመለስኩ፡፡
ከአረብ አገር ስትመጪ የቋጠርሽው ጥሪት ነበረሽ?
በጭራሽ ቤሳቤስቲ አልነበረኝም፡፡ እዚያ የኖርኩት ለቤተሰቤ ነው፡፡ በዚያ ላይ ልጅ ነበር፡፡ ንብረት ከተባለ የራሴ የጣትና የአንገት ወርቅ ብቻ ነው የነበረኝ፡፡
ታዲያ አዲስ አበባ እንዴት ተቀበለችሽ?
እሱ ነበር ከባዱ፡፡ እናቴ ጠንካራ ሴት ናት፤ጥንካሬን አውርሳኛለች፡፡ ያልሰራችው ነገር የለም፡፡ እንጀራ ጋግራ አከፋፍላለች፡፡ ሹራብ ሰርታ ሸጣለች፡፡ ከመጣሁ በኋላ ለተወሰነ ጊዜ መረጋጋት አልቻልኩም፤እኔም ከነልጄ እሷ ቤት ነው የገባነው፡፡ ትንሽ ቆይቼ ግን የቤት ደላልነት ሥራ ጀመርኩ፡፡
የቤት ደላልነት ለሴት አልተለመደም፡፡ ወደዚያ ለመግባት ያነሳሳሽ የተለየ ምክንያት ነበር? ሥራውስ አልከበደሽም?
ውይ ---- በጣም ከምነግርሽ በላይ አድካሚ ነው፡፡ አንዳንዱ ሰው ሊከራይ ሳይሆን ሊገዛ ነው የሚመስልሽ፡፡ እኔን ወደ ስራው እንድገባ ያበረታቱኝ አብረውኝ የተማሩ ሁለት ልጆች ሙያው ላይ ስለነበሩ ነው፡፡ እነሱ ያግዙኝ ነበር፡፡ የሰዎች ስሜትና ፍላጎት የተለያየ ነው፡፡ ቤት እየዞርሽ አሳይተሽ የማይፈልግም ይኖራል፡፡ አንዳንዴ አከራዮቹ እራሳቸው መንገድ ላይ ያገኙሽና በዚህን ያህል ብር የሚከራይ ቤት አለ ይሉሽና፣ ተከራዩ ደግሞ ስፋቱን ስንት ነው፣ ግድግዳው በሩ --- ይልሻል፡፡
በስራው የገጠመሽ ገጠመኝ ከአከራይ ወይ ከተከራይ
ብዙ ነገር ይገጥምሻል፤ ቀብድ ሰጥቶ የሚቀር አለ፡፡ በመሃል ካልገባሁ ብሎ የሚያስጨንቅ አለ፡፡ ጥሩው ነገር ግን ሴት ስለሆንኩ ነው መሰለኝ ሰዎች እኔን በጣም ያምኑኝ ነበር፤ የምላቸውን ይሰሙኛል፡፡  
 የድለላውን ሥራ እንዴት ተውሽው?
ድካሙን አልቻልኩም፡፡ ኩላሊቴን አመመኝ፡፡ ግን አሁን አሁን ሳስበው ድካሙን ችዬ ብቆይ ኖሮ ያዋጣኝ ነበር እላለሁ (ሳ---ቅ--)
ከዚያስ ምን መስራት ጀመርሽ ?
ለትንሽ ጊዜ የምኖርበት የቀበሌ ቤት ጥግ ላይ ውሃና ለስላሳ መሸጥ ጀምሬ ነበር፡፡ እሱም አልተሳካም፡፡ በመሃል በእናቴ እርዳታ 2ኛ መንጃ ፍቃድ አወጣሁ፡፡ ሆኖም እጅ የምፈታበት መኪና አላገኘሁም፡፡ በመሃል ትዳርም ሞክሬ ነበር፤ከሁለት ዓመት በላይ አልዘለቀም፡፡ ግን ከሁለቱም ትዳሬ ሁለት የሚያማምሩ ሴት ልጆችን አፍርቼበታለሁ፡፡  
የልጆቹ አባቶች ይረዱሻል?
በጭራሽ አንድ ቀንም አይተዋቸው አያውቁም፡፡ አሁን ሁለቱም ሌላ ሚስት አግብተዋል፡፡ ነፍሷን ይማረውና ልጆቼን በማሳደግ በኩል ብኩን እናቴ ሁሉ ነገሬ ነበረች፡፡
ባወጣሽው 2ኛ መንጃ ፍቃድ ሰራሽበት ?
እናቴ አንድ ቀን የሆነ ዱቄት ፋብሪካ ወሰደችኝና መንጃ ፍቃዴን ኮፒ አድርጌ ለባለቤቱ ሰጠሁት፡፡ መጀመሪያ ሴት በመሆኔ ደስ ብሎት፣ አንቺ የልጆቼ ሹፌር ትሆኛሽ፤ ጎበዝ ልጅ ነሽ፤በርቺ አለኝ፡፡ በኋላ ቢሮ ቀጥሮኝ ፈተና ሲፈትነኝ ግን እጄን ስላልፈታሁ ትንሽ አቃተኝ፡፡ እሱም ለልጆቹ ስላጨኝ ፈራ፡፡ በቃ ትንሽ ጊዜ እጅ እስክትፈቺ ብሎ የዱቄት ፋብሪካው የስምሪት ክፍል ኃላፊ አደረገኝ፡፡ እኔ ግን ህልሜ መንዳት ነበር፡፡ የሚገርምሽ በልጅነቴ እቤት ውስጥ ወደፊት የአንበሳ አውቶቡስ ሹፌር ነው የምሆነው ስል እናቴ ትናደድ ነበር፡፡ አንቺ ከልጆቼ ፈጣን ነሽ፡፡ ትልቅ ተስፋ ያለኝ ባንቺ ነው፤እንደዚህ አትበይ ትለኝ ነበር፡፡ በስምሪት ሰራተኝነቱ ብዙም አልገፋሁም፤ ደሞዜም ከ500 ብር የማይበልጥ ነበር፡፡
በዚህ መሃል 3ኛ መንጃ ፍቃድ አወጣሁ፡፡ ግን ስራ ማግኘት ቀላል አልነበረም፡፡ ያልሞከርኩበትና ማመልከቻ ያላስገባሁበት መስሪያ ቤት የለም፡፡ ግማሹ ሴት መሆኔን ሲያይ ቦታ የለም ይለኛል፡፡ እንደ በፊቱ እንዳልቸገርም የሰፈራችንን የታክሲ ሹፌሮች እየለመንኩ እጄን በደንብ ፈታሁ፡፡ በዚህ መሀል እናትና አባቴ ተከታትለው ሞቱ፡፡ ልጆቼን ይዤ የምገባበት አጣሁ፡፡ የቀበሌውም ቤት ብዙ ታሪክ አለው፤ ብቻ ተወሰደ፡፡ ግን ሁልጊዜ የምፅናናበት እናቴ ከእኔ ስምንት እጥፍ ችግሮችን ተቋቁማ ያሰበችበት መድረሷ ነበር፡፡ በኋላ ላይ እኔም የላዳ ታክሲ ሹፌር ሆንኩ፡፡
 የላዳ ሹፌርነት አልፈተነሽም ? ሴት በመሆንሽ የሰው አቀባበል እንዴት ነበር?
 አዲስ አበባ ውስጥ ያለነው ሴት ላዳ ሹፌሮች ሁለት ወይ ሦስት ብንሆን ነው፡፡ ያው ሰው በተለያ አይነት መንገድ ነው የሚቀበልሽ እንዳመጣጡ መቀበል ነው፡፡ አንዳንዴ በተለይ ከመሸ አፏጭተው አስቁመው ሴት መሆኔን ሲያዩ ደንግጠው ጥለውኝ የሚሄዱም አሉ፡፡
በታክሲ ሹፌርነት ህይወትሽ በበጎነት የምትጠቅሻቸው ገጠመኞች ይኖሩሻል ብዬ እገምታለሁ----
ሰው በጣም ያዝናል፡፡ እንደምታይው ትንሽ ወፍራም ነኝ፡፡ ቀን ቀን ከሙቀቱ ጋር ላቤ በጣም ይወርዳል፡፡ እንደውም አንዱ ተሳፋሪ፣ አባይ መገደብ የነበረበት ከአንቺ ነው ብሎ ቀልዶብኛል፡፡ እናም ከተነጋገረው ክፍያ በላይ ጨምሮ የሚሰጥሽ ብዙ መልካም ሰው አለ፡፡ ያው እንዴት ስራውን ጀመርሽ ምናምን እያለ የሚያደርቅሽም አይጠፋም፡፡  
መጥፎ የምትያቸው ገጠመኞችሽ?
ውይ እነሱ ብዙ ናቸው፡፡ ብዙ ችግሮች አይቻለሁ፤አሁን አሁን ሥራ ካልጠፋ አላመሽም፡፡ በፊት ግን ለሊትም እሰራ ነበር፡፡ ያው ገቢ ማስገባት አለብሽ፤የቤት ኪራይም አለ፡፡ የልጆች ቀለብ ምናምን --- ወጪዎች ስላሉ አመሽ ነበር፡፡ ታዲያ ሰክሮ የሚሳደብ ብዙ ነው፡፡ አንዱ ጉራንጉር ሰፈር ውስጥ ካላስገባሽኝ ሂሳብ አልከፍል ብሎ፣በፖሊስ ኃይል ያመለጥኩበት ግዜም አለ፡፡ ከኋላ ጭነሽው ድንገት ተነስቶ የሚደበድብም አለ፡፡ ሰክሮ ብር ሳይዝ ገብቶ ቦታው ሲደርስ አልከፍልም የሚልም ያጋጥማል፡፡ ብዙ አላስፈላጊና ጭንቅላት የሚነኩ ቃላቶችን የሚናገርሽም አለ፡፡ በተለይ እኔ ሙስሊም እንደመሆኔ፣ሙስሊም ደንበኞቼ ስራሽ ከእምነት ጋር አይሄድም፣በሚል ይቃወሙኛል፡፡ ከብዙ ወንዶች ጋር ስለሚያገናኝሽ አቁሚ የሚሉኝም አሉ፡፡ እንደውም አንድ ደንበኛዬ፤ባለፈው “ይሄን ስራ ከአሁን ጀምሮ አቁሚ” ሲለኝ፤ “ነገ ተቸግሬ አስር ብር ስጠኝ ብልህ፣እግር አለሽ ሰርተሽ ብይ ነው የምትለኝ፤በዚህ አልጠራጠርም፡፡ በዲናችንም የሚያስጠላው የሰው እጅ ማየት ነው” በማለት መልሼለታለሁ፡፡ ለእኔ ስራዬ ኑሮዬን አሸንፎልኛል፤እዚህ ጋ ለመድረስ ያልፈነቀልኩት ድንጋይ የለም፡፡ የታክሲ ስራ ለእኔ ትልቁ ስኬቴ ነው፡፡ ህልሜን ነው የሞላሁት፡፡ በእኔ አእምሮ ጥሩ ስራ ነው፡፡ የሰው ፊት ከማየት ገላግሎኛል፡፡ የአበራና የተሰማ ሀሳብ ለኔ ዳቦ አይሆንም፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ብዙ መልካም ሰው አለ፤ወርጄ ጎማ ስቀይር የሚያየኝ ሹፌር ሁሉ ካላገዝኩሽ ይላል፡፡ አንዳንድ ደንበኞችም፤“ትንሽ ትንሽ ብር የሚያዋጣልሽ ፈልጊና ደህና መኪና ግዢ፤እኛም እናግዝሻለን” ይሉኛል፡፡
ላዳዋ ያንቺ ናት ወይስ ተቀጥረሽ ነው የምትሰሪው?
አሁን አይደለችም፤ግን ትሆናለች፡፡ አሁን የያዝኳት ላዳ አሮጌ ብትሆንም፣ ጥረቴን ያየ አንድ መልካም ሰው ሰርቼ እንድከፍለው የሰጠኝ ነው፡፡ አሁን ግማሽ ያህሉን ከፍያለሁ፤ስጨርስ ስሙን ያዞርልኛል፡፡
ወደፊት ስንገናኝ ከአንቺ ምን ልጠብቅ?
በየቦታው የማያቆመኝን የራሴን ላዳ ታክሲ ይዤ! (…ሳ…ቅ….) ያኔ አንቺንም እሸኝሻለሁ  (ሳ…ቅ…)