Administrator

Administrator

Saturday, 06 February 2016 11:34

ስምና ማንነት

 ከብዙ መነፋፈቅ በኋላ ካባቴ ታናሽ ወንድም፤ ካቶ አማረ በዳዳ ጋር ተገናኝተን አራት ኪሎ በሚገኘው ሮሚና ምግብ ቤት ምሳ በላን፡፡
አማረ ቢሏችሁ ቀላል ሰው እንዳይመስላችሁ፤ ከስድሳ ስድስት አብዮት ትንሽ ቀደም ብሎ በዩንቨርሲቲ ኮሌጅ በታሪክ ትምህርት ዘርፍ በዲግሪ ተመርቋል፡፡ በአብዮት ማግስት ዓመት በኢህአፓ አባልነት ተመልምሎ፣ በዚሁ ጦስ ተይዞ ዓለምበቃኝ አምስት ዓመት ታስሯል፡፡ እነ ማርታ ኩምሳ፣ ጌታቸው ኩምሳና ገነት ዘውዴ አብሮ ታሳሪዎቹ ነበሩ። ደራሲ ግርማይ አብርሃ በእሥር ቤት ማስታወሻው ላይ እንደጠቀሰው፤ አማረ በእሥር ቤት ቆይታው እሥረኞችን በነጻ የማስተማር አገልግሎት ከሚሰጡ ታራሚዎች አንዱ ነበር፡፡
እስከቅርብ ጊዜ ድረስ የኢትዮጵያ ቤተሰብ መምርያ ያዲሳባ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ ሆኖ ሲሠራ ቆይቷል፡፡ አዲሳባ ዩኒቨርሲቲ በምማርበት ወቅት የሻይ መጠጫ የሚቆርጥልኝ አማረ ነበር፡፡
አባቴና አማረ ያንድ አባት ያንድ እናት ቢሆኑም በመልክና በእጣ ፈንታ የተለያዩ ነበሩ፡፡ አባቴ የቀይ ዳማ ሲሆን አማረ ክስል ያለ ጥቁር ነው፡፡ ወንድማማቾቹ የሚጋሩት አንድ ምልክት ቢኖር፣ ከጥቁር ጸጉራቸው ማኽል እንደባትሪ ቦግ ብሎ የሚታየው ሽበታቸው ነበር፡፡ ከአማረ በተቃራኒ አባቴ ለፖለቲካ ያለው ስሜት በጣም የቀዘቀዘ ነው፡፡ አማረ የቢሮ ሰው ሲሆን፣ አባቴ የተፈጥሮ ሰው ነው። ከትምህርት ቤት ውጭ ያለውን ጊዜውን ያሳለፈው ከልጆቹ የማያንስ ፍቅርና ጊዜ ለሚሰጣቸው የጓሮ አትክልቱ ነበር ማለት ይቻላል፡፡
በድህረ ምሳ ጨዋታ ላይ የዘመዳ-ዝማድ ጉዳይ ስናነሳ ስንጥል ቆይተን ልንሰነባት ስንል፣
“እስቲ ያባቴን የትውልድ ሐረግ ጻፍና ስጠኝ” አልኩት፡፡
“ምን አሳሰበህ” አለኝ በዋዛ፡፡
“እንዴት አያሳስበኝ፤ አባታዊነትን የሚያጋንን ማኅበረሰብ አባል ነኝ፡፡ አንድ ሰው ፍቅሩን ለመግለጽ “እንዲያው ምናባቴ ላርግህ” በሚልበት፤ ጠላቱ ክፉ እንደገጠመው ሲሰማ፣ “የታባቱ” ብሎ፣ በሚፈነጥዝበት ግራ ሲገባው፤ “ምናባቱ” እያለ በሚያጉተመትምበት ሀገር ውስጥ የምኖር ነኝ። አባት የነገሮች ሁሉ መስፈርያ ሆኖ የሚቀርብበት ማኅበረሰብ ውስጥ ስለአባቴ ማንነት ለማወቅ ብጥር ምን ይገርማል?”
በግርምት ለጥቂት ጊዜ አተኩሮ ሲያየኝ ከቆየ በኋላ ወደ መኪናው ውስጥ ይዞኝ ገባ፡፡ ከዚያ ከመኪና እረኛዋ (ከፓርኪንግ ሠራተኛዋ) እስክርቢቶ ተውሶ፣ በቢጫ ማስታወሻ ደብተሩ ውስጥ አንድ ቅጠል ገንጥሎ የሚከተለውን ጻፈልኝ፤
በዕውቀቱ ሥዩም - በዳዳ - ደስታ - ወየሳ
“ይሄው ነው?”
“እኔ የማውቀው እስከዚህ ድረስ ያለውን ነው፤ ሌላውን ደሞ የሁላችን ታላቅ የሆነችውን አበራሽን ጠይቃት”
ትንሽ አሰብ አድርጌ፤
“አባታችን አባቱ በዳዳ ተብሎ እንደሚጠራ ነፍስ ስናውቅ ጀምሮ ይነግረን ነበር፡፡ ግን በመሰለ ለምን እንደሚጠራ ጠይቀነው አናውቅም፡፡ ለምንድነው አባታችን በመሰለ የሚጠራው?  
አማረ ማብራራት ጀመረ፡፡
ምንጭ፡- (ከበዕውቀቱ ሥዩም
“ከአሜን ባሻገር”
አዲስ መፅሐፍ የተቀነጨበ፤ 2008 ዓ.ም)

Saturday, 06 February 2016 11:31

የኪነት ጥግ

(ስለ እግር ኳስ)
በእግር ኳስ ደስ የሚለው ነገር፣ ነገሮች በሰከንድ ውስጥ ሊቀየሩ ይችላሉ፡፡
ዲዲየር ድሮግባ
ከእግር ኳስ ውጭ ህይወቴ ከንቱ ነው፡፡
ክርስቲያኖ ሮናልዶ
ራሴን እንደ እግር ኳስ ተጫዋች ብቻ አልመለከትም፤ እንደ አዝናኝና ተምሳሌት እንጂ።
ካም ኒውተን
ለነገሩ እግር ኳስ ጨዋታ ነው ወይስ ሃይማኖት?
ጆሴ ሞሪኖ
የእግር ኳስ ቲፎዞ ነኝ፣ የስፖርት ቲፎዞ ነኝ፣ የውድድር ቲፎዞ ነኝ፡፡
ማቲው ማክኮናግሄይ
ብራዚል የምትበላው፣ የምትተኛውና የምትጠጣው እግር ኳስ ነው፡፡ የምትኖረው እግር ኳስን ነው!
ፔሌ
በህይወቴ የተማርኳቸውን የግብረ ገብነት እሴቶች የተማርኩት በእግር ኳስ ውስጥ ነው፡፡
አርሴን ቬንገር
እግር ኳስ ስህተት የመስራት ጨዋታ ነው፡፡ ጥቂት ስህተቶችን የሰራው ወገን ያሸንፋል፡፡
ጆሃን ክሩዩፍ
ዳንስ ጥበብ እንደሆነው ሁሉ የእግር ኳስም ጥበብ ነው - ነገር ግን በቅጡ ሲከናወን ብቻ ነው ጥበብ የሚሆነው፡፡
አርሴን ቬንገር
አንዳንድ ሰዎች እግር ኳስ የህይወትና የሞት ጉዳይ ይመስላቸዋል፡፡ እኔ ግን ከዚያም የጠነከረ መሆኑን አረጋግጥላችኋለሁ፡፡
ቢል ሻንክሊ
የመጀመሪያ ሴሚስተር ውጤቴ ሲወጣ እናትና አባቴ እግር ኳስ እንደማልጫወት ነገሩኝ፡፡
ጆ ቢዴን
እግር ኳስ ቅድመ ሁኔታ የሌለው ፍቅር ነው።
ቶም ብራዲ
ሚሊዬነር ለመሆን ፈፅሞ አልሜ አላውቅም - የእግር ኳስ ተጫዋች ለመሆን ነበር ያለምኩት፡፡
ቪክቶር ክሩዝ
መላ ህይወቴን እግር ኳስ ለመጫወት መስዋዕት አድርጌአለሁ፡፡
ብሪያን ቦስዎርዝ

 “ችግራቸው የቅርፅና የይዘት ነው”
(ደራሲ ኃይሉ ፀጋዬ)
የቴሌቪዥን ድራማዎች አልበዙም? መበራከታቸው በጥበቡ ላይ የሚያሳድረው አዎንታዊና አሉታዊ ተፅእኖ ይኖራል?
 እኔ በግሌ የቲቪ ድራማዎች በዝተዋል ብዬ አላምንም፡፡ እዚህ ጎረቤት ኬንያ፣ በቀን 4 ተከታታይ ድራማ ይታያል፡፡ በMBC 2 አረብ ሳት፣ ቀንና ሌሊት ፊልም ነው የሚታየው፡፡ በሳምንት አንድ ድራማ ብቻ ይታይ ከነበረበት ጊዜ አንጻር ካየነው ጥሩ ነው፡፡ አዎንታዊ ጎኑ  በዋናነት፣ሰዎች አማራጭ የሚያዩት ነገር እንዲኖራቸው ማድረጉ ነው፡፡ አንድ ድራማ ብቻ በነበረ ወቅት ምርጫ የለም፤ መጥፎም ሆነ ጥሩ ያንኑ ማየት ብቻ ነው፡፡ ሌላው ለተከታታይ ድራማ እድገት በጎ አስተዋፅኦ ይኖረዋል፡፡ እንግዲህ ብዛት ይቀድማል፤ጥራት የሚመጣው ዘግይቶ ነው፡፡ አሉታዊ ጎኑ ብዙ ሲሆኑ ተመሳሳይነትና ተደጋጋሚነት ይኖራቸዋል፤ በዚህም ተመልካቹን የማሰልቸት ነገር ሊፈጠር ይችላል፡፡  
የቲቪ ድራማዎች አጠቃላይ ይዘታቸው ምን ይመስላል?
እንግዲህ እንደነገርኩሽ በዙ ሲባል ያስቀኛል፡፡ የሚታየው ነገር ጥራት ቢኖረው እኮ ችግር የለውም፡፡ አሁን ትልቁ ችግር የቅርፅና የይዘት ነው፡፡ በድራማዎቹ ምንድን ነው እየተላለፈ ያለው መልእክት? ጥልቀትና ብስለት አለው ወይ? ግልብ ነገር መስራት የትም አያደርስም፡፡ እና በይዘትም በቅርፅም ገና ብዙ ይቀረናል፡፡ በእርግጥ አንዳንድ  የተሻሉ ስራዎች ይኖራሉ፡፡  
በድራማዎቹ መካከል --- ተወዳጅ ለመሆን እርስ በርስ የመፎካከር ነገር ይታያል?
 ገና አልተጀመረም፤ፉክክር የሚጀምረው ጥራት ሲመጣ ነው፡፡ ምናልባትም በቀጣዮቹ አምስትና አስር ዓመታት አሪፍ ስራዎችን ልናይ እንችላለን፡፡ ጥሩ የድራማ አፃፃፍና ምርጥ ፕሮዳክሽኖች ይመጣሉ፡፡   
አንዳንድ ድራማዎች በስፖንሰርሺፕ ገንዘብ ለማግኘት ብቻ ታልመው ስለሚሰሩ ደረጃቸው የወረደ ነው የሚሉ ትችቶች ይሰነዘራሉ፡፡ አንተ ምን ትላለህ? …
በአሁን ሰዓት የቴሌቪዥን ድራማ ገንዘብ ያስገኛል የሚል አስተሳሰብ ያላቸው ፕሮዲዩሰሮች ተበራክተዋል። ያለአቅማቸው የማይችሉትን እየጎረሱ ነው፡፡ ለገንዘብ መስራት ሃጢያት አይደለም፡፡ ግን ብቃት ያስፈልጋል። ገንዘብ ላይ ያተኮረ፣ ስምና ዝናን ያማከለ ስራ እየተሰራ ነው ያለው፡፡ ብቃት የሌላቸው ዳይሬክተሮችና ፕሮዱዩሰሮች ይገጥሙሻል፡፡ እነዚህ ጥራት እያደገ ሲመጣ ከጨዋታ ውጭ ይሆናሉ፡፡
“አንዳንድ የቲቪ ድራማዎች አይመጥኑም”
(ረዳት ፕሮፌሰር ሙሉጌታ ጀዋሬ)
የቴሌቪዥን ድራማዎች አልበዙም? መበራከታቸው በጥበቡ ላይ የሚያሳድረው አዎንታዊና አሉታዊ ተፅእኖ ይኖራል?
አዎንታዊ ጎኑ ሁልጊዜ ከብዛት ጥራት ይገኛል፡፡ ሰዎች ከጥንካሬ ብቻ ሳይሆን ከድክመትም ይማራሉ፡፡ ብዙ ጠንካሮች እድል ባላገኙበት ሁኔታ ከሆነ ነው አስቸጋሪ የሚሆነው፡፡ የቴሌቪዥን ድራማ ገና ብዙ ሊሰራበት የሚገባ ዘርፍ ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓት ለልጆችና አዋቂዎች ተመሳሳይ ነገር ነው የሚቀርብላቸው፡፡ ለሁሉም አንድ ነው፡፡ እንደዚህ ያልጠራና ሁሉን ያላማከለ፣---- አቅጣጫ የሌለው ሲሆን ብዥታ ይፈጥራል፡፡
የቲቪ ድራማዎች አጠቃላይ ይዘታቸው ምን ይመስላል?
ምናልባት የኢቢሲ ኤዲቶሪያል ፖሊሲን መሰረት ተደርጎ ስለሚሰራ ይሆናል፡፡ የቲቪ ድራማዎች ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና መሰል ጉዳዮችን እንዲፈትሹ ይፈለጋል፡፡ ነገር ግን  በሳይኮሎጂ ህብረተሰቡን የማከምና ፆታዊ፣ማህበራዊና ሌሎች ጉዳዮችን መዳሰስ ይቻላል።  አንዳንዴ በድራማዎች መካከል መመሳሰል ሊከሰት ይችላል፡፡ ሆኖም አተያያቸውና የትኩረት አቅጣጫቸውም ሊመሳሰል አይችልም፡፡ አንዳንድ ችግሮች ይታያሉ፡፡ ለምሳሌ አንዳንድ ድራማዎች ብቃታቸው ታይቶ ነው አየር ላይ የሚቀርቡት? የሚያሰኙ ናቸው፡፡ በተለይ የተወሰኑት በህዝብ አይን፣ ጊዜ፣ አእምሮና ባህል ላይ እንደ መቀለድ የሚቆጠሩ ናቸው ማለት ይቻላል፡፡ በጭራሽ ለቲቪ ድራማ የማይመጥን ሥራ እያየን ነው፡፡ ምስሉ ያብረቀረቀ ሁሉ ያምራል ማለት አይደለም፡፡ አሁን በሚሄድበት ሃዲድ ምን ያህል ይጓዛል የሚለው ያጠያይቃል፡፡
ከብዛታቸው አንፃር የቲቪ ድራማዎች ያለባቸው ተግዳሮት ምንድን ነው?
ሰው ለምሳሌ እያየሁ ያለሁት “መለከት” ነው “ዋዜማ” ሊል ይችላል፡፡ ሎጎውን እስኪመለከት ድረስ ኢቢኤስ ነው ኢቢሲ በሚል መደነጋገርም ይፈጠራል፡፡ ይህን የሚያመጣው የገፀ ባህሪያት መመሳሰል ነው፡፡ ደግነቱ የኛ ተመልካች ቶሎ የሚሰለች አይደለም፡፡ በጊዜ ሂደት ግን አዲስ ነገር መፈለጉ አይቀርም፤ካላገኘ የተሰራውን ባለመመልከት፣ በመዝጋት መቅጣት ይጀምራል። አማራጮች ሲያገኝ ወደ ማወዳደር ይገባል፡፡ ሰው እስኪሰለች ድረስ መጠበቅ ግን አይገባም፡፡ ድራማዎችና በጥራትና በሚመጥን መልኩ መስራት አለባቸው፡፡
አንዳንድ ድራማዎች በስፖንሰርሺፕ ገንዘብ ለማግኘት ብቻ ታልመው ስለሚሰሩ ደረጃቸው የወረደ ነው የሚሉ ትችቶች ይሰነዘራሉ፡፡ አንተ ምን ትላለህ? …
የፊልሙ አካሄድ ወደ ቲቪ ድራማም እየመጣ ነው። ሰዎች ከፍለው ማፃፍ እየጀመሩ ነው፡፡ መኪናቸውን ሸጠው ወደዚህ ሥራ የሚገቡ አሉ፡፡ ታዲያ የተፃፈ ሁሉ ይታያል ማለት አይደለም፡፡ ገምጋሚው አካል ደረጃቸውን በጥራት ፈትሾ ማሳለፍ አለበት፡፡ ጥሩ ድራማ ከቀረበ እኮ የግዜ ጉዳይ ካልሆነ በቀር ነጋዴው በሰልፍ ይመጣል፡፡
አሁን ባለው ሁኔታ ከቀጠለ ግን ትውልዱ ለአደጋ ይጋለጣል፡፡ ልጆቻችን በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አገራዊ ጉዳዮችን ለነሱ በሚመጥን መንገድ ተሰርቶ ማየት ካልቻሉ ልንለያይ ነው፡፡ እኔና ልጆቼ በጋራ ተቀምጠን የምናየው ፕሮግራም መሰራት አለበት፡፡ አሁን የእኔ ልጅ ሳይማር አረብኛ ይናገራል፡፡ በአገሩ ቴሌቪዥን ቋንቋና ባህሉን ማሳደግ ሲገባው፣ የአረብ ቻናል በማየት አረብኛ ችሏል፡፡ ስለዚህ ሁሉንም የሚመጥኑና ሁሉንም ያማከሉ፣ የጠሩ ስራዎች ሊቀርቡ ይገባል፡፡   
“ድራማ ለፅድቅ ልስራው የምትይው አይደለም;
(የፊልም ዳይሬክተር፤ ተስፋዬ ማሞ)
የቴሌቪዥን ድራማዎች አልበዙም? መበራከታቸው በጥበቡ ላይ የሚያሳድረው አዎንታዊና አሉታዊ ተፅእኖ ይኖራል?
መብዛታቸው አዎንታዊ እንጂ አሉታዊ ተፅእኖ የለውም፡፡ መብዛት ችግር የለውም፡፡ ዋናው የበዙት ምን አይነቶቹ ናቸው የሚለው ነው፡፡ በተረፈ ብዙ መሆናቸው ውድድርና የእርስ በርስ ፉክክርን ያበረታታል፡፡
የቲቪ ድራማዎች አጠቃላይ ይዘታቸው ምን ይመስላል?
 የተጠና ነገር ሳይኖር በጅምላ መፈረጅ ይከብዳል። ግን የሚያስገርመው---- ስንት ዓመት ድራማ ስንሰራ ኖረን፣ገና ጀማሪ ስለሆንን፣ ሁሉም ይሞክር አይነት እየተባለ ነው፡፡ ይሄ “ጀማሪ ነኝ፣ ጀማሪ ነኝ” መቼ እንደሚቆም እግዜር ይወቀው፡፡ ብዙ ጊዜ ከድራማው ይልቅ ዝነኛ ሰዎችን፣ ታዋቂ ፊቶችን ---- ለማካተት ነው ትኩረት የሚሰጠው፡፡
ከብዛታቸው አንፃር የቲቪ ድራማዎች ያለባቸው ተግዳሮት ምንድን ነው?
ለምሳሌ በኢቢሲ እሁድ የመዝናኛ ፕሮግራም ላይ ሁለት ድራማ አይጠፋም፡፡ ድራማ ሲባል ለምን ረቡዕና እሁድ ብቻ እንደሚታሰብ አይገባኝም፡፡ በሌሎች ቀናት ለምን አይበተንም፡፡ በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት ሲሆን ተመልካች ሳይወድ በግድ አንዱን ብቻ መርጦ እንዲመለከት ያደርገዋል፡፡ ወደፊት ቻናል እየበዛ ሲመጣ ደግሞ ውድድሩ በነሱ መካከል ይሆናል፡፡ ያኔ እኛም የተሻለ ነገር እናያለን፡፡
አንዳንድ ድራማዎች በስፖንሰርሺፕ ገንዘብ ለማግኘት ብቻ ታልመው ስለሚሰሩ ደረጃቸው የወረደ ነው የሚሉ ትችቶች ይሰነዘራሉ፡፡ አንተ ምን ትላለህ? …
 እንደሱ ብሎ መነሳት ይከብዳል፡፡ ለምሳሌ ገመናን ብናይ፣ገንዘብ የመሰብሰብ ሳይሆን በሙያ የማትረፍ አላማ ነበረው፡፡ ሰው ለሰውም እሱን ተከትሎ ስለመጣ፣ ከገመና የተሻለ ነገር ለማቅረብ በውድድር ስሜት በመሰራቱ፣ ጥሩ ነገር ለማየት ችለናል፡፡ አሁን አሁን  ሲጀመር ጥሩ ይሆንና በኋላ ጥድፊያ! በእርግጥ ድራማ ከፍተኛ ወጪ ያለው ስራ ነው፡፡ ለፅድቅ ልስራው የምትይው አይደለም፡፡ ግን እንደ ፊልሙ እየሆነ መጥቷል፤ ገንዘብ ስላለ ብቻ የሚገባበት፡፡
ገንዘብ ይዞ መምጣቱ ባልከፋ፤ግን የወጣውን ገንዘብ  ለመመለስ ሥራው ተወዳጅ መሆን አለበት፤ ያለበለዚያ ባለገንዘቡም ተመልካቹም አያተርፉበትም፡፡ እናም በተቻለ አቅም በባለሙያዎችና በጥራት መስራት ያስፈልጋል፡፡
*   *   *
“አማራጭ ከሌለሽ ያለውን ታያለሽ;
 “መብዛታቸው ጥሩ ነው ብዬ ነው የማስበው!አሁን አማራጭ ስላለ የምትፈልጊውን ታያለሽ፡፡ `ለምሳሌ ”በቀደሙት ሳእታት ኢቲቪ ላይ Up”ßእሮብና እሁድ ነው ያለው፡፡ አማራጭ ከሌለሽ ያለውን ጠብቀሽ ታያለሽ፡፡ አሁን ላይ በእኩል ሰዓት ለምሳሌ እሮብን ብታይ ኢቢኤስ ላይም አለ፣ ኢቢሲ ላይም አለ፡፡ የመረጥሽውን መከታተል ትችያለሽ፡፡;
(ወጣት ቤተል:ሔም ባህሩ)
“የሚንዛዙ ድራማዎች አሉ”
 “መብዛታቸው መልካም ቢሆንም እየተንዛዙ ያሉ ድራማዎች ደግሞ አሉ፡፡ ለምሳሉ አንድ ሂደት ለማሳየት ረጅም ሰዓት የመውሰድ ነገር አለ፡፡ ያ ደግሞ ጥራቱን ያጓድላል ብዬ አምናለሁ፡፡ ለተመልካችም ያሰለቻል። ሌላው ለምሳሌ ኢቢኤስና ኢቢሲ በተመሳሳይ ሰዓት ድራማ ያሳያሉ፡፡ ይሄ ለማንም ጥሩ አይደለም፤ተናበው ቢሰሩ ይመረጣል”
 (አካሉ ጴጥሮስ)
“መብዛታቸው ምርጫ ሰጥቶኛል”
“የተለያዩ የቴሌቭዥን ጣቢያዎች ተከፍተዋል፡፡ ይህ ጥሩ ነው፡፡ በነሱ አማካኝነትም በርካታ ድራማዎች ይታያሉ፡፡
ምን ያህል ጥሩ ናቸው፣ አይደሉም የሚለውን ሙያዊ ትንታኔ ለመስጠት ይከብደኛል፡፡ ባለኝ እውቀትና እይታ ግን አብዛኞቹ ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ትኩረታቸው ፍቅር ላይ ነው፤ መጨረሻቸውም ፍቅር ነው፡፡ ልክ ፊልም ላይ እንደምናየው /አሁን የተወሰኑ መሻሻሎች ቢኖሩም/ ሁሉም ፍቅር ላይ ነው፡፡ ሌሎች በፊልም፣ በድራማ፣ ትልቅ ደረጃ ላይ የደረሱ አገሮችን ሥራዎች ቨማየት፣ የአገራችንን የድራማ፣ ፊልምና ቲያትር እድገት ራሳችን ማሻሻል መቀየር እንችላለን፡፡ ተመሳሳይ ናቸው፤- የፍቅር ታሪኩ አመጣጡና ድንበሩ ይለያይ እንጂ ከመፋቀር አይዘልም፡፡ መሻሻል አለበት እላለሁ፡፡ ሆኖም መብዛታቸው ምርጫ ሰጥቶኛል፤ በምመርጠው ቴሌቪዝን የፈለግሁትን ለማየት ችያለሁ”
(ሄለን አይችሉም)  
“እኔ መብዛታቸው ጥሩ ነው እላለሁ፡፡ ድሮ ትዝ የሚለኝ ፣ድራማ ሲኖር ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ˜አንድ ብቻ ስለሆነ፤ ማታ እኮ እንትን ይታያል እል ነበር፡፡ አሁን ግን የመረጥኩትን ማየት አያለሁ፡፡”
(ትእግስት ወገኔ)

የታዋቂው ገጣሚና ደራሲ በእውቀቱ ስዩም “ከአሜን ባሻገር” የተሰኘ አዲስ መፅሃፍ የመጀመሪያው 20ሺ ቅጂ በግማሽ ቀን ውስጥ ተሸጦ ማለቁን ምንጮች ለአዲስ አድማስ ገለፁ፡፡
ባለፈው ሰኞ ጠዋት ገበያ ላይ የዋለው መፅሀፉ፤ ከሰዓት በኋላ ተሸጦ እንዳለቀ ታውቋል፡፡ ሁለተኛው ህትመት ከአስር ቀናት በኋላ በድጋሚ በገበያ ላይ ይውላል ተብሏል፡፡
የአንድ መፅሃፍ መደብር ባለቤት ለአዲስ አድማስ እንደተናገረው፤ “እስከዛሬ ከሸጥኳቸው መፃህፍት በአንድ ቀን ያለቀ አልገጠመኝም፡፡ ይሄ የመጀመሪያው ነው፡፡” ብሏል፡፡
ሌላው ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የመፅሃፍ አከፋፋይ በበኩሉ፤ “ብዙ የመፃህፍት ሽያጭ እንቅስቃሴ በሌለበት በዚህ ወቅት በአጭር ጊዜ ተሸጦ ያለቀው “ከአሜን ባሻገር” የመፃህፍትን ገበያ አነቃቅቷል፡፡ እስካሁን ታትሞ በወጣ በግማሽ ቀን ውስጥ ተሸጦ ያለቀ መፅሃፍ አላየሁም፡፡ በህዝቡ ውስጥ የተለየ ስሜት የፈጠረና ሁሉም ነጋዴ የያዘው መፅሃፍ ነው፡፡” ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል። ሌሎች መፃህፍት የራሳቸው አንባቢ አላቸው፤ ይሄኛው ግን ወጣት አዛውንት ሳይል በሁሉም የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ሰዎች የጠየቁትና የገዙት መፅሃፍ ነው፡፡” ሲልም አክሏል አከፋፋዩ፡፡
“ይህች መጽሐፍ ጉዞ ቀመስ፣ ፖለቲካ ቀመስና ታሪክ ቀመስ መጣጥፎችን ይዛለች” በሚል ደራሲው በመግቢያው የገለፀው ይኸው መጽሐፍ፤ በ70 ብር ነው ለገበያ የቀረበው፡፡
የመፅሃፉ ደራሲ በዕውቀቱ ስዩም በአሜሪካ ሃዋርድ ዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን በመከታተል ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡   

Saturday, 06 February 2016 11:11

የስኬት ጥግ

- ስኬት ምስጢር የለውም፡፡ የዝግጅት፣ ተግቶ
የመስራትና ከውድቀት የመማር ውጤት ነው፡፡
ኮሊን ፖል
- ከገንዘብ በቀር ምንም የማይፈጥር ቢዝነስ ደካማ
ቢዝነስ ነው፡፡
ሔነሪ ፎርድ
- አንተ አንድ ግሩም ሃሳብ ካለህ ሰዎች ሌላ 20
ያቀርቡልሃል፡፡
ሜሪ ቮን ኢብነር - ኢሼንባች
- ታላላቅ ኩባንያዎች የሚገነቡት በታላላቅ
ምርቶች ላይ ነው፡፡
ኢሎን ሙስክ
- መሸጥ የማይችል ከሆነ ፈጠራ አይደለም፡፡
ዴቪድ ኦጊልቪ
- ሌሎች ሰዎች ሲሸጡ እኔ እገዛለሁ፡፡
ጄ.ፓል ጌቲ
- ገንዘብ መስራት ቀላል ነው፡፡ በጣም የሚከብደው
ልዩነት መፍጠር ነው፡፡
ቶም ብሮካው
- ሁሉም ዘላቂ ቢዝነሶች የሚገነቡት በወዳጅነት
ላይ ነው፡፡
አልፍሬድ ኤ. ሞንታፔርት
- ቢዝነስ በራሱ ኃይል ነው፡፡
ጋሬት ጋሬት
- የሥራ ኃላፊ የውደሳ ጭብጨባዎችን አይሰማም።
አልቪን ዳርክ
- ስኬታማ ለመሆን ልብህን ቢዝነስህ ውስጥ፣
ቢዝነስህን ልብህ ውስጥ ማድረግ አለብህ፡፡
ቶማስ ጄ. ዋትሶን

Saturday, 06 February 2016 11:13

የዘላለም ጥግ

- እውነተኛ እጣ ፈንታችን ፍቅር ነው፡
፡ የህይወትን ትርጉም ለብቻችን ፈልገን
አናገኘውም - ከሌሎች ጋር ሆነን እንጂ፡፡
ቶማስ ሜርቶን
- እጣ ፈንታህ ቅርፅ የሚይዘው ውሳኔዎችን
በምታሳልፍባቸው በምትወሰንበት ቅፅበቶች
ነው፡፡
ቶኒ ሮቢንስ
- እያንዳንዱ ሰው የራሱን እጣ ፈንታ የመወሰን
መብት አለው፡፡
ቦብ ማርሊ
- እጣ ፈንታ የዕድል ጉዳይ አይደለም፡፡ የምርጫ
ጉዳይ ነው፡፡ ቁጭ ብለን የምንጠብቀው ነገር
አይደለም፤ የምናሳካው እንጂ፡፡
ዊሊያም ጄኒንግስ ብርያን
- ሰዎች እጣ ፈንታን አይቀርፁትም፡፡ ዕጣ ፈንታ
ለጊዜው የሚሆን ሰው ይፈጥራል፡፡
ፊደል ካስትሮ
- የአንተ እጣፈንታ የእኔ እጣፈንታ ነው፡፡ የአንተ
ደስታ የእኔ ደስታ ነው፡፡
አይስሎም ካሪሞቭ
- ሁላችንም ከእጣ ፈንታችን ጋር የታሰርን ነን፤
ራሳችንን ነፃ የምናወጣበት መንገድ የለም፡፡
ሪታ ሃይዎርዝ
- ሁሉም ሰው የየራሱ እጣ ፈንታ ፈጣሪ መሆን
አለበት፡፡
ማርቲን ዴላኒ
- እጣ ፈንታህን ተቆጣጠር፤ ያለበለዚያ ሌላ
ሰው ይቆጣጠረዋል፡፡
ጃክ ዌልሽ
- በእጣፈንታ፣ በእግዚአብሔር ጣልቃገብነትና
ተግቶ በመስራት አምናለሁ፡፡
ካትሪና ካይፍ
- ሁሌም ዲ ሞክራሲ ፍ ፁም እ ንዳልሆነ
ለማስረዳት ከመሞከር ወደ ኋላ ብዬ
አላውቅም፡፡ ነገር ግን ዕጣ ፈንታህን ለመቅረፅ
ዕድል ይሰጥሃል፡፡
ኤዩንግ ሳን ሱ ኬዩ
- ሁልጊዜ የሰውን ልጅ ለመብረር የሚያስችለው
ማሽን መስራት እጣ ፈንታዬ ነው አስብ ነበር፡፡
ሊኦናርዶ ዳቬንቺ
- የምትንቀውን ሥራ እየሰራህ እጣ ፈንታህን
እውን አታደርግም፡፡
ጆን ሲ. ማክስዌል
- ታሪካችን እጣ ፈንታችን አይደለም፡፡
አላን ኮኸን፡፡

አቤል በ6፣ ጀስቲን ቢበር በ5 ዘርፎች ታጭተዋል

   ትውልደ ኢትዮጵያዊው የአር ኤንድ ቢ ሙዚቃ አቀንቃኝ አቤል ተስፋዬ ወይም ዘ ዊክንድ እና ታዋቂው ድምጻዊ ጀስቲን ቢበር የካናዳውያን የግራሚ ሽልማት ተብሎ በሚታወቀው የዘንድሮው የጁኖ የሙዚቃ ሽልማት በበርካታ ዘርፎች በመታጨት መሪነቱን መያዛቸውን ፎርብስ መጽሄት ዘገበ፡፡
የ25 አመቱ ኢትዮ-ካናዳዊ ድምጻዊ አቤል ተስፋዬ በዘንድሮው 45ኛው የጁኖ አመታዊ ሽልማት በስድስት ዘርፎች መታጨቱን የገለጸው ዘገባው፣ አምናም በአመቱ ምርጥ አርቲስት እና በአመቱ የአር ኤንድ ቢ ሶል ሪከርዲንግ ዘርፎች ተሸላሚ እንደነበር አስታውሷል፡፡
አቤል በዘንድሮው የጁኖ ሽልማት በዕጩነት ከቀረበባቸው ስድስት ዘርፎች፣ የአድናቂዎች ምርጫ፣ የአመቱ ምርጥ አልበምና የአመቱ ምርጥ የዘፈን ደራሲ... ይገኙባቸዋል ተብሏል፡፡
ጀስቲን ቢበርና ሌላው ታዋቂ ካናዳዊ ድምጻዊ ድሬክም በ2016 የጁኖ አለማቀፍ የሙዚቃ ሽልማት በአምስት ዘርፎች ለሽልማት መታጨታቸውን ያመለከተው ዘገባው፣ የሽልማት ስነስርዓቱ በመጪው ሚያዝያ ወር መጀመሪያ ላይ በካልጋሪ እንደሚካሄድም አክሎ ገልጿል፡፡

ከዕለታት አንድ ቀን በአንድ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ወደጎረቤት አካባቢ ያለችን አንዲትን ለአቅመ - ሔዋን የደረሰች ኮረዳ ለወንድ ልጃቸው ፈለጓትና ሽማግሌዎች ወደልጅቷ ቤተሰቦች ተላኩ።
ሽማግሌዎቹ የልጅቱ ቤተሰቦች ዘንድ ሲደርሱ፣ ቤት ገብተው ቆሙ፡፡ የልጅቱ ቤተሰቦችና ዘመድ - አዝማድ ሁሉ በአንድ ተርታ ተሰድረዋል፡፡
አባት፤
“እህስ፤ ምን አግር ጣላችሁ ጎበዝ?”
ከሽማግሌዎቹ አንዱ፤
“ምን የመሰለ ለአቅመ - አዳም የደረሰ ጎበዝ ወንድ ልጅ አለን፡፡ ልጃችሁን ለልጃችን ትሰጡን ዘንድ ይኸው ከወዲያኛው አምባ መጥተናል” ሲሉ መለሱ፡፡
አባት፤
እንደዚህ ከሆነማ፣ እኛ እምቢ የምንልበት ምንም ምክንያት አይኖርም፡፡ ግን አንድ ቅድመ - ሁኔታ ማሟላት አለባችሁ”
“ምን?”
የልጅቷ ወላጆችም፤ “እንግዲያው በጥሞና አዳምጡን፡፡ ልጃችንን የምንሰጣችሁ ሃምሳ ሰው ይዛችሁ መጥታችሁ 1ኛ/ ሃምሳ በግ ቀርቦላችሁ የምትበሉ ከሆነ
         2ኛ/ ሃምሳ ጋን ጠላ የምትጠጡ ከሆነ
     3ኛ/ መላ የሚያውቅ ሰው፣ ግን መላጣ ያልሆነ ሰው ይዛችሁ ከመጣችሁ  ነው፤” አሉ
 የወንዱ ልጅ ወገኖች፤
“ሀሳቡን እንቀበላለን፡፡ ያላችሁትን 50 ሰው ይዘን እንመጣለን” ሲሉ ሀሳቡን መቀበላቸውን አረጋገጡ።
“እንግዲህ ከቆረጣችሁ የዛሬ 15 ቀን ኑ” አሉና ቀጠሯቸው፡፡
በቀጠሮው ቀን ሽማግሌዎቹ 50 ሆነው መጡ፡፡ 50 በጎች ቀረቡላቸው፡፡ እንዳጋጣሚ ይዘውት የመጡት መላ አዋቂ ሰው መላጣ ነው፡፡ “እንዴት እናድርግ መላጣ አይግባብን ብለዋል?” ብለው ጠየቁት፡፡
“ጥምጥም አምጡ፡፡ ቄስ ሆኜ እገባለሁ፡፡ ቄስ አይግባ አላሉ!” አለ፡፡
“የቀረቡትን በጎች እንዴት እንብላቸው?” አሉት፡፡
“አንድ በአንድ እየተረከባችሁ ለ50 ሰው ጥሬውን መቀራመት ነው” አላቸው፡፡
መላ አዋቂው እንዳለው አንድ አንድ በግ እየተቀበሉ ከጋኖቹ ጠላ እየቀዱ እያማጉ ጥብስቅ አድርገው በሉና ጠላውን ግጥም አድርገው ጠጡ፡፡
የሙሽሪት ቤተሰቦች አይሆንም ያሉት ነገር ሆነና ተሸነፉ፡፡ የግዳቸውን ልጃቸውን ለማስረከብ ተስማሙ፡፡ የወንድ ወገን “ሃይ ሎጋ!” አለ፡፡ ከዚያን ጊዜ ወዲህ በሴት ወገን በኩል ለወንድ ወገን አካባቢ ሰዎች ስም ወጣላቸው፡፡ ለምን ቢሉ፣ ልብ ብሎ ላያቸው ጥሬውን ሲበሉ ነው የታዩት፡፡ ቢጠብሱት ኖሮ ቅባቱ ይዘጋቸው ነበር፡፡ ይሄን ተመርኩዞ፤
“አይጠብሴ” የሚል የቅፅል ስም ወጣላቸው፡፡
*          *         *
ሌሎችን አሸንፍበታለሁ ያልነው ዘዴ አንዳንዴ መሸነፊያችን ሊሆን ይችላል፡፡ በርካታ ህዝብ ዘክሮ መክሮ የሚያመጣው ብልሃት አይታወቅም፡፡ ዋናው ነገር የሚዘክር የሚመክረውን ህዝብ መሰባሰብ፣ መምረጥና ማደራጀት መቻል ነው፡፡ ይህ ባልሆነበት ሁኔታ የተበታተነ የህዝብ ሐተታ እንጂ የሰከነ ዕምነት ማፍራት አንችልም፡፡ የአስተሳሰብ አንድነት የዛሬ የሀገር ጥሪ ነው!
በጋራ አስቦ፣ በጋራ ተስማምቶ የጋራ ዓላማ መያዝ እጅግ ከባድ ተልዕኮ ነው፡፡ ለዚህ ሁሉ ጠጣት ሰናይ ተግባር ስም የሚያስጠራ ምግባር ያስፈልጋል፡፡ ፀሐፍት፤ “ያለጥርጥር መልካም ሥራህ ካንተ ቀድሞ ይታወቃል፡፡ ክብርን ያመለካተ ከሆነ አንተ ወደ መድረኩ ትርዒት ሳትደርስ በፊት ብዙው ሥራህ ተከናውኖ ጠበቀህ ማለት ነው፡፡ አንዲት ቃል ሳትተነፍስ ጉዳይህ አለቀ” ይላሉ፡፡
ስለመልካምም ሆነ እኩይ ምግባር የማሳወቅ ታላቅ ኃላፊነት ያለባቸው ጋዜጠኞች ናቸው፡፡ ምንም ዋጋ ያስከፍላቸው የፈጠጠውን እውነት መራቅ የለባቸውም፡፡ በእርግጥ መንግሥትም ይህን ሀቅ ተገንዝቦ ሊያግዛቸው እንጂ ሊያስፈራራቸው አይገባም፡፡ እንደ ሙስና ያሉት መያዣ መጨበጫ ያጡ ድርጊቶች በሁሎች ርብርብ የሚጋለጡ መሆናቸውን አለመርሳት ነው፡፡
በሀገራችን የሚታየውን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ስናይ ኃምሌት ይከሰታል፡-
“…ኋላ ምን ሊታየኝ ኖሯል፣ ጊዜ ከፈተነው ሌላ
ምድር ዕፅዋት ብቻ አታበቅል፣ ያለሾህ ያላሜከላ
ወይንም የተፈጥሮ መልክ፣ ሲካበት ሞልቶ ድርጅቶ ብቻውን አደለም ከቶ
ግን እንደዚሁ እንደ ህንፃ፣ ላዩ በሰም አንፀባርቆ
አካባቢው በጌጥ ደምቆ
መሰረቱ ግን በግድፈት፣ በአገም ጠቀም ተደባብቆ
በመሀንዲስ ጥበብ ጉድለት፣ ወይ ባጉል መራቀቅ ዘፍቆ
ከስህተቱም፣ ከጥራቱም፣ ተቻችሎ፣ አለ ተጣብቆ”
ህንፃው ብቻውን ባዶ ነው፡፡ መሰረቱ የተዛባ ነው፡፡ መሀንዲሱ ስራውን በአገም - ጠቀም ሰርቶ አሳቡን ከወሰደ ቆይቷል፡፡ አካባቢያችን ጌጥ ብቻ ነው! እሾህና አሜከላ ዙሪያችንን ከቦናል፡፡ ይሄ የሀገራችን ሀቅ ነው፡፡ ማማር ያለበት መንገድ፣ ህንፃው፣ ሪል ኢስቴቱ ብቻ አይደለም፡፡ ዋናውና ዋነኛው የህዝባችን ኑሮ ነው፡፡ ተመችቶኛል፣ ደልቶኛል ማለት ያበት ነዋሪው ህዝብ ነው! በግፍ ተበልቻለሁ፣ ተመዝብሬአለሁ ማለትም ያለበት ነዋሪው ህዝብ ነው፡፡ በሹመት ስም፣ በሀገር ሰላም ስም፣ በትራንስፎርሜሽን ስም፣ በኢንቬስተሮች ማበረታታት ስም፣ ዘራፊዎችን በማሳደድ ስም፣ … የሚካሄዱ ምዝበራዎችን አውቆ፣ ነቅቶ፣ ከሥር መሰረቱ አብጠልጥሎ ተረድቶ፣ ማጋለጥና ዕውነቱን ይፋ ማድረግም የነዋሪው ህዝብ ደንታ ነው፡፡ በፋይናንስ፣ በገቢ አሰባሰብና የመሬት ቁጥጥር ጉዳይ ላይ ህዝብ የመናገር መብት ሊኖረው ይገባል!! የመክሰስ መብቱን ሊጠቀም ይገባል!
በሥልጣን ብልግናም ይገለጥ፣ በመሬት ዘረፋም ይገለጥ፣ በታክስ ማጭበርበርም ይገለጥ፣ በኮንስትራክሽን ግዢም ይገለጥ፣ በሚዲያ ኢንዱስትሪ ሀሳዊ - ስብከትም ይገለጥ፣ የቦርድ አባልነትን ተገን በማድረግም ይገለጥ፣ በሙልሙል ቢሮክራት መልክም ይገለጥ … “ከጅብ ጅማት የተሰራ ክራር ቅኝቱ ልብላው ልብላው ነው” በሚለው ተረት በሚገባ የሚንፀባረቅ ነው፡፡ ይህንን ልብ ለማለት ልብ ይስጠን!!

በአመት 82ሺ ኢትዮጵያውያን የመን ገብተዋል። 11ሺ ያህሉ ሴቶች ናቸው።
20ሺ የመናዊያን በጦርነት ወደ ጂቡቲ፣ ሶማሊያና ኢትዮጵያ ተሰደዋል።

    ለሥራ ወደ አረብ አገራት መጓዝ የተከለከለው፣ ጉዳት ይደርስባቸዋል በሚል ነበር። በእርግጥም በየጊዜው፣ ለአደጋ የሚጋለጡ ስደተኛ ኢትዮጵያውያን ጥቂት አይደሉም። ነገር ግን፣ እገዳው፣ በጎ ውጤት አላስገኘም። አደጋንና ጉዳትን ከመቀነስ ይልቅ እንዲባባስ አድርጓል።
አይኦኤም ሰሞኑን ባሰራጨው መረጃ እንደጠቆመው፤ እስከ ጥር ወር ድረስ፣ ወደ የመን ለመግባት ከተጓዙት ስደተኞች መካከል 340 ያህሉ ህይወታቸውን አጥተዋል፤ ደብዛቸው ጠፍቷል። አብዛኞቹ ደግሞ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ናቸው - 280 ያህሉ። በህጋዊ ምዝገባ ወደ አረብ አገራት መሄድ፣ የዛሬ ሁለት አመት ከመታገዱ በፊት፣ እንዲህ አይነት እልቂት አይከሰትም ነበር።
ይህም ብቻ አይደለም። ቀደም ሲል፣ አብዛኞቹ ሴቶች ወደ አረብ አገራት የሚሄዱት በህጋዊ ምዝገባ በአውሮፕላን በረራ እንጂ፣ በአደገኛ የባህር ጉዞ ወደ አደገኛዋ አገር ወደ የመን የመሄድ ብዙም ፍላጎት አልነበራቸውም። አሁን ግን፣ በህጋዊ ምዝገባ የመሄድ እድል በእገዳ ስለተዘጋ፣ አማራጭ በማጣት፤ በየመን በኩል የሚጓዙ ሴቶች ቁጥር ጨምሯል - 11ሺ።
የዛሬ አራት አምስት ዓመት፣ ወደ አረብ አገራት የሄዱ ኢትዮጵያውያን ላይ ሲደርስ የነበረው ጉዳት ቀላል አይደለም። የሚያስቆጭ የሚያንገበግብ ነው። ነገር ግን፣ ያንን ጉዳት ለመቀነስ በትጋት ከመስራት ይልቅ፣ ጉዞዎቹን ማገድ አቋራጭ መፍትሄ ሆኗል። ተቆርቋሪነትም ይመስላል። ተቆርቋሪነት ግን አይደለም። ጭካኔ ነው - የአምስት የአስር ሰዎች መሞት የሚቆረቁረው ሰው፤ መቶ፣ ሁለት መቶ፣ ሰዎችን ለሞት የሚዳርግ እገዳ ማወጅ።

- በፊናቸው ጠቅላላ ጉባኤ እናካሂዳለን ብለዋል
- አንዱ ሌላውን “ከሃላፊነት አግጃለሁ” ሲሉ ወስነዋል

   የመኢአድ ላዕላይ ምክር ቤት፤ የፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሃሪን የከሰሰ ሲሆን፤ ፍ/ቤት አቶ አበባውን ለጊዜው በማገድ፣ የክስ መልስ እንዲያዘጋጁ የአንድ ወር ቀጠሮ ሰጠ፡፡  
ለአመታት ከተለያዩ ውዝግቦች እፎይታ ያላገኘው መኢአድ፣ ዘንድሮም የፓርቲው ፕሬዚዳንትና የምክትላቸው በተቀናቃኝ ጐራ የተሰለፉበት የተካረረ ውዝግብ ገጥሞታል፡፡
መኢአድ፤ መጋቢት 24 ቀን ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ ወስኗል ቢባልም፤ የፓርቲው  ም/ሬዚዳንት ተቃውመዋል፡፡ አቶ አበባው ከአመራር እንዲታገዱ ስለተወሰነ ጉባኤውን የመጥራት ስልጣን የላቸውም ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ አቶ አንድሪያስ ኤሮ፤ እኛ በስድስት ወር ጠቅላላ ጉባኤ እናካሂዳለን ብለዋል፡፡
በአቶ እንድሪያስ ኤሮ አስተባባሪነት፤ ከ50 በመቶ በላይ የፓርቲው ላዕላይ ም/ቤት አባላት ተሰብስበው፤ አቶ አበባው መሃሪን ከፕሬዚዳንትነት አግደዋል፡፡ ክስም አቅርበዋል፡፡
አቶ አበባው በበኩላቸው ሌላ ስብሰባ በማካሄድ፤ የአቶ እንድሪያስን ቡድን አግጃለሁ ብለዋል፡፡ በፊናቸው ክስ እንደሚያቀርቡ በመጥቀስ፡፡