Administrator

Administrator

የጆሊ ጁስ አምራች የሆነው ቴስቲ ፉድስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግ. ኩባንያ፤ በጥራት የስራ አመራር ብቃት ጥራቶችን አሟልቶ አለማቀፉን የISO 9001/2008 ሰርተፊኬት ተሸላሚ መሆኑን የኩባንያው ሃላፊዎች ገለጹባ የተለያዩ የሚበጠበጡ የዱቄት ጣፋጭ መጠጦችንና ቴስቲ ስናክን የሚያመርተው ኩባንያው፤ የአለማቀፉ ጥራት ተሸላሚ መሆኑ፣ ምርቶቹን ወደ አለማቀፍ ገበያ ይዞ እንዲቀርብና ተቀባይነት እንዲያገኝ ይረዳዋል ተብሏል፡፡ ከ8 ዓመት በፊት የተቋቋመው ኩባንያው፤ታዋቂውን የጆሊ ጁስ መጠጥ ጨምሮ የተለያዩ የፍራፍሬ ጣዕም ያላቸውን በውሃ ተበጥብጠው የሚጠጡ ፍሌቨሮች የሚያመርት ሲሆን ደረቅ ቴስቲ ስናክ በማምረትም ከሃገር ውስጥ በተጨማሪ ለውጪ ገበያ እንደሚያቀርብ ተጠቁሟል፡፡  
ኩባንያው ለወደፊት የምርቶቹን የጥራት ደረጃ ጠብቆ በኢትዮጵያ ያለውን የገበያ አድማስ ለማስፋት እንደሚተጋ የስራ ኃላፊዎቹ ገልፀዋል፡፡

ኢትዮጵያ በነፍስ ወከፍ ገቢ ከ213 አገራት 203ኛ ሆናለች
- መንግስት የነፍስ ወከፍ ገቢያችን ከ550-700 ዶላር ደርሷል ይላል
- ሞናኮ በ100 ሺህ ዶላር ስትመራ፣ ማላዊ በ250 ዶላር መጨረሻ ላይ ትገኛለች
           በየአመቱ ሃምሌ ወር መጀመሪያ ላይ የዓለማችንን አገራት ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ይፋ የሚያደርገው የአለም ባንክ፣ ባለፈው የፈረንጆች አመት የኢትዮጵያ አመታዊ የነፍስ ወከፍ ገቢ 550 ዶላር እንደነበር ገለፀ፡፡
የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ፤ አመታዊ የነፍስ ወከፍ ገቢያችን ከ550-700 ዶላር ደርሷል ማለቱ ይታወቃል፡፡የዓለም ባንክ ከትናንት በስቲያ ያወጣው የአለማችን አገራት የኢኮኖሚ ሁኔታ መረጃ እንደሚያሳየው፣ ኢትዮጵያ በአመታዊ የነፍስ ወከፍ ገቢ ከዓለማችን 213 አገራት 203ኛ ደረጃን ይዛለች፡፡
የባንኩ ያለፈው ዓመት የአገራት አመታዊ የነፍስ ወከፍ ገቢ መረጃ እንደሚያሳየው፤ 10 የአለማችን አገራት፣ በ2013 ከነበራቸው የነፍስ ወከፍ ገቢ ጭማሪ ያሳዩ ሲሆን፣ ካላደጉ የአለማችን አገራት መካከል ባንግላዴሽ፣ ኬንያ፣ ማያንማር እና ታጂኪስታን የነፍስ ወከፍ ገቢያቸውን በማሻሻል ወደ አነስተኛ መካከለኛ ገቢ አገራት ሲቀላቀሉ፣ ደቡብ ሱዳን በበኩሏ፤ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ በመቀነሱ ከዝቅተኛ ገቢ አገራት ጋር ተቀላቅላለች ብሏል የአለም ባንክ፡፡ሞንጎሊያና ፓራጓይ በ2013 ከነበሩበት አነስተኛ መካከለኛ ገቢ፣ ዘንድሮ ወደ ከፍተኛ መካከለኛ ገቢ አገራት ተርታ መቀላቀላቸውን የገለጸው የአለም ባንክ፤ አርጀንቲና፣ ሃንጋሪ፣ ሲሸልስና ቬንዙዌላ በበኩላቸው ደረጃቸውን በማሻሻል አምና ከነበሩበት ከፍተኛ መካከለኛ ገቢ ወደ ከፍተኛ ገቢ አገራት ሸጋግረዋል ብሏል፡፡በአመታዊ የነፍስ ወከፍ ገቢ ከአለማችን አገራት ዝቅተኛውን ደረጃ የያዘችው ማላዊ ናት ያለው የአለም ባንክ፤ በ2014 የነፍስ ወከፍ ገቢዋ 250 ዶላር ብቻ የሆነው ማላዊ፣ ባለፉት 24 አመታት
የነፍስ ወከፍ ገቢዋ የጨመረው በ70 ዶላር ብቻ ነው ብሏል፡፡ በአንጻሩ በአመቱ ከፍተኛውን የአለማችን አመታዊ የነፍስ ወከፍ ገቢ ያገኘችው የፈረንሳዩዋ ከተማ ሞናኮ ስትሆን፣ የነፍስ ወከፍ ገቢው ከ100 ሺህ ዶላር በላይ ነው ተብሏል፡፡በአለም ባንክ መስፈርት መሰረት፤ አመታዊ የነፍስ ወከፍ ገቢያቸው ከ12ሺህ ዶላር በላይ የሆኑ፣ ከፍተኛ ገቢ፤ ከ12 ሺ 735 እስከ 4ሺህ 126 ዶላር የሆኑ፣ ከፍተኛ መካከለኛ ገቢ፣ ከ4ሺህ 125
እስከ 1ሺህ 46 ዶላር የሆኑ፣ ዝቅተኛ መካከለኛ ገቢ፤ ከ1ሺህ 45 ዶላር በታች የሆኑ፣ ዝቅተኛ ገቢ
ያላቸው አገራት ተብለው ይመደባሉ፡፡

 መንግስት ም/ፕሬዚዳንቱ ከአገር የወጡት ለስራ ጉዳይ ነው ብሏል

   የብሩንዲው ፕሬዚዳንት ፔሪ ንኩሩንዚዛ፤ ህገ መንግስቱ ከሚፈቅድላቸው ውጭ በቅርቡ በሚካሄደው የአገሪቱ ምርጫ ለሶስተኛ ዙር ለመወዳደር መወሰናቸውን በመቃወማቸው ከመንግስት አካላት ማስፈራሪያ እየተደረገባቸው እንደሆነ የገለጹት ምክትል ፕሬዚዳንቱ ጌርቪያስ ሩፊኪሪ፣ ለህይወታቸው በመስጋት አገር ጥለው መሰደዳቸውን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
የአገሪቱ መንግስት ቃል አቀባይ በበኩላቸው፤ምክትል ፕሬዚዳንቱ ከአገር የወጡት ለስራ ጉዳይ ነው፤ ምንም አይነት ማስፈራሪያ አልተደረገባቸውም ብለዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ዘንድሮም በምርጫ እንደሚወዳደሩ መግለጻቸውን ተከትሎ፣ በአገሪቱ የተቀሰቀሰው ግጭት እየተባባሰ ነው፤ የህዝቡ ተቃውሞም እንደቀጠለ ነው፤ ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ ጌሪያስ ሩፊኪሪ፣ መንግስት በሌሎች ተቃዋሚዎች ላይ እንደሚያደርገው ሁሉ በእኔ ላይም ዛቻና ማስፈራሪያ እያደረገብኝ ስለሆነ አገሬን ጥዬ ተሰድጃለሁ ብለዋል ከፍራንስ24 የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ፡፡
በቅርቡም የብሩንዲ የህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ፍርድ ቤት ዳኛ እና የምርጫ ኮሚሽን አባልን ጨምሮ ሌሎች የአገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ የፕሬዚዳንት ንኩሩንዚዛን ውሳኔ በመቃወም አገር ጥለው መሰደዳቸውንም ዘገባው አስታውሷል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፤ በመጪው ሐምሌ ወር አጋማሽ ላይ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው የብሩንዲ ምርጫ ሳቢያ የተቀሰቀሰውን ግጭትና የተፈጠረውን ውጥረት ለማርገብ፣ የብሩንዲን ገዢ ፓርቲና ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ለማደራደር እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ ዘገባው ጨምሮ ገልጧል፡፡
የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቶችም ላለፉት ሁለት ወራት በአገሪቱ ፖሊስና በተቃዋሚዎች መካከል በተደረጉ ግጭቶች፣  ከ70 በላይ ዜጎች መሞታቸውንና 500 ያህልም መቁሰላቸውን አስታውቀዋል ብሏል ዘገባው፡፡

 በፓኪስታን በተከሰተው ከመጠን ያለፈ የሙቀት አደጋ ከሰባት መቶ በላይ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን ሲኤንኤን ከዋና ከተማዋ ካራቺ የዘገበ ሲሆን የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ናዋዝ ሸሪፍ የአስቸኳይ የአደጋ ጊዜ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
ሙቀቱ በድንገት የመታት የመጀመሪያዋ ከተማ፣ ከፓኪስታን በደቡባዊ አቅጣጫ የምትገኘዋን የሲንድ ግዛትን ነበር፤ ባለፈው ሳምንት ማገባደጃ ላይ፡፡ ወሩ በእስልምና ሀይማኖት ተከታዮች ዘንድ የሮመዳን ፆም  የተያዘበት እንደመሆኑ አደጋው እጥፍ ድርብ ችግሮችን እንዳስከተለ ዘገባዎች ይጠቁማሉ፡፡  ህይወታቸውን በሙቀቱ ያጡት ሰለባዎች ቁጥር የአስከሬን ማቆያዎች ከሚቀበሉት በላይ በመሆኑ ሆስፒታሎች በሬሳ ተጨናንቀው በዜና ማሰራጫዎች ታይተዋል፡፡  እስከ ትላንት በስቲያ ድረስ ወደ 750 የፓኪስታን ዜጎች ሲሞቱ፣ ከሺ በላይ የሚገመቱት ደግሞ ከሙቀቱ ጋር በተያያዘ እንደ ሀይለኛ ትኩሳትና የሰውነት ፈሳሽ ድርቀት (Dehydration) መሰል የጤና ቀውሶች ተጠቅተው፣ አስከፊ ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የሙቀቱ አደጋ ከፍተኛ የህይወት መጥፋት ያስከተለው በሀገሪቱ ትልቅ በምትባለው የካራፒ ከተማ ሲሆን ወደ ስድስት መቶ ነዋሪዎችም ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡
ከአደጋው ጋር በተያያዘ በተከሰተ የትራፊክ መጨናነቅ ሳቢያ ነዋሪዎች  የሟች ዘመዶቻቸውን አስከሬን ወደ ቀብር ቦታ ለማድረስ መቸገራቸውን ገልፀዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በሀይል እጥረት ምክኒያት እየተዛባ ይዳረስ የነበረው የውሀ አቅርቦት ጊዜያዊ መፍትሄዎች እንዳይወሰዱ አድርጓል። አንዳንድ ነዋሪዎች የተከሰተውን ሙቀት በውሀ ለማብረድ ቢፍጨረጨሩም  … በከተማው ያሉ የውሀ መስመሮች በመሰባበራቸው መፍትሄ ሊሆኑዋቸው አልቻሉም፡፡ የፓኪስታን ክልል አስተዳዳሪ ከዌም አሊ ሻህ፤ የሙቀቱ አደጋ ጋብ እስከሚልበት ጊዜ ድረስ ትምህርት ቤቶችና የመንግስት መስሪያ ቤቶች ተዘግተው እንዲቆዩ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል፡፡ አስተዳዳሪው ለተቀጠፉት ነፍሶች ተጠያቂው መንግስት እንደሆነም ሲገልጹ፤ “ሀይል ማሰራጫ መስመሮች እንዲታደሱ አስቀድመን ብንወተውትም፣ የሚመለከታቸው ባለሥልጣናት ምላሽ ባለመስጠታቸው አደጋው ከመጠን ያለፈ ጥፋት አድርሷል” በማለት ቅሬታቸውን አሰምተዋል፡፡

 በያዝነው የፈረንጆች አመት በርካታ ሰራተኞችን ቀጥረው እያሰሩ ከሚገኙ የዓለማችን ተቋማትና ድርጅቶች መካከል፣ 3.2 ሚሊዮን ሰራተኞችን የሚያስተዳድረው የአሜሪካ መከላከያ ሚንስቴር ፔንታገን በሠራተኞች ብዛት መሪነቱን መያዙን ፎርብስ መጽሄት ዘገበ፡፡
የአለም የኢኮኖሚ ፎረም ሰሞኑን ይፋ ያደረገውን የጥናት ውጤት ጠቅሶ ፎርብስ ባለፈው ማክሰኞ እንዳስነበበው፣ የቻይና ህዝቦች የነጻነት ጦር 2.3 ሚሊዮን ሰራተኞችን በመያዝ በሁለተኝነት ሲከተል፣ ታዋቂው አለማቀፍ የሸቀጣሸቀጥ ሱፕርማርኬት  ዎልማርት በ2.1 ሚሊዮን ሰራተኞች ሶስተኛውን ደረጃ ይዟል፡፡ በአመቱ በርካታ ሰራተኞችን በስሩ ቀጥሮ በማስተዳደር ከአለማችን አራተኛውን ደረጃ የያዘው ደግሞ 1.9 ሚሊዮን ሰራተኞች ያሉት ታዋቂው የምግብ አምራች ኩባንያ ማክዶናልድ ነው፡፡
የእንግሊዝ ብሄራዊ የጤና አገልግሎት ድርጅት በ1፣7 ሚሊዮን ሰራተኞች አምስተኛ ደረጃን እንደያዘ የገለጸው ዘገባው፣ የቻይና ብሄራዊ የነዳጅ ኮርፖሬሽን በ1.6 ሚሊዮን፣ የቻይናው ስቴት ግሪድ ኮርፖሬሽን በ1.5 ሚሊዮን፣ የህንድ ምድር ባቡር ኩባንያ በ1.4 ሚሊዮን፣ የህንድ የጦር ሃይል በ1.3 ሚሊዮን እንዲሁም ሆን ሃይ ፕሪሲዥን የተባለው ኩባንያ በ1.2 ሚሊዮን ሰራተኞች እስከ አስረኛ ደረጃ ይዘዋል ብሏል፡፡

 በናይጄሪያ መንግሥት ከፍተኛ ተከፋይ እንደሆኑ የሚነገርላቸው የህግ አውጪ ባለሙያዎች (ሴናተሮች) የገዛ ራሳቸውን ደመወዝ ለመቀነስ የሚደነግግ ህግ ለማፅደቅ ሀሳብ እንዳቀረቡ ሮይተርስ ዘገበ፡፡
ናይጄሪያ የህግ አውጪ ሆነው የሚሰሩ 469 የከፍተኛ ፍትህ አባላት አሏት፡፡ እነዚህ ህግ አውጪዎች በዓመት የሚቀበሉት የደመወዝና ጥቅማ ጥቅም በጀት በሀገሩ ላይ ያሉት 36 ክልሎች በአመት ከሚመደብላቸው ገንዘብ የበለጠ እንደሆነ ማወቅ ተችሏል፡፡ እነዚህ ክልሎች በአማካይ እያንዳንዳቸው ከሚሊዮን ነዋሪዎች በላይ የሚያስተዳድሩ ናቸው፡፡  
 ለአስር አመታት ያህል በተለይም ከአለፉት አራት አመታት ጀምሮ የናይጄሪያ ኢኮኖሚ ባሽቆለቆለው የዓለም አቀፍ ነዳጅ ገበያ መንስኤነት አጣብቂኝ ውስጥ መግባቱን ሮይተርስ ጠቁሟል፡፡ የናይጄሪያ መንግስት የሚተዳደረው ነዳጅ ተሸጦ ከሚገኘው ቀረጥ በመሆኑ፣ ከወደቀው የዓለም ነዳጅ ዋጋ ጋር የመንግስት የበጀት አቅምም ላሽቋል፡፡ በዚህም ምክኒያት በሌጎስ የሚገኝ ገለልተኛ ተቋም ቡድን የነዋሪዎቹን የገንዘብ አወጣጥ በቅርብ ሆኖ እየገመገመ ይገኛል፡፡
የዚሁ ተቋም መስራች የሆነው ኦሊሲዮን አጓበንዴ፤ ከሌላው መንግስታዊ ተከፋይ በተለየ ሁኔታ ገንዘብ የሚያገኙትን የፍትህ ስርዓት ባለሙያዎች፣ የህዝብ አገልጋይ መሆን ሲገባቸው ከመጠን ያለፈ የመንግስት በጀት ተጠቃሚ መሆናቸውን በመጠቆም አቤቱታ ያሰማል፡፡
ባለፈው ሳምንት በሌጎስ የወጣው ዴይሊ ሪፖርት፤ እያንዳንዱ የሴኔት አባል በዓመት ለልብስ መግዣ እንዲሆነው 105 ዶላር እንደሚሰጠው ዘግቧል፡፡ ባለፈው ሚያዚያ አዲሱን የፕሬዚዳንት ወንበር የተረከቡት ሞሀመድ ቦሀሪ፤ በሀገሪቱ ላይ የተንሰራፋውን የአባካኝነት ባህል እንደሚለውጡ ቃል መግባታቸው ይታወሳል፡፡ የሀገሪቱ ብሔራዊ ምክር ቤት አባላትም ከፕሬዚዳንቱ ጋር ሆነው ለመስራት በከፊል ተስማምተዋል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የህግ አውጪ ባለሙያዎቹም የፕሬዚዳንቱን አቋም በመደገፍ የሚከፈላቸውን ወርሀዊ ደሞዝ ዝቅ ለማድረግ ሀሳብ ማቅረብ ጀምረዋል፡፡ ከሀሳብ አቅራቢዎቹ መካከል የኮጂ ክልል ተወካይ በሰጠው አስተያየት፤ “በመንግስት ወጪ የተትረፈረፈ ህይወት ከእንግዲህ ልንመራ አንችልም” ሲል ተደምጧል፡፡ “የናይጄሪያ ህዝብ ይኼንን የደመወዝ አከፋፈል በአንድ ድምፅ ማውገዝ ይኖርበታል” ብሏል፡፡
በ2013 (እ.ኤ.አ) የአንድ በዝቅተኛ እርከን ላይ የሚገኝ ሴናተር (ህግ አውጪ) ዓመታዊ ገቢ 13,000 ዶላር ነበር። ግን በዚህ ደመወዙ ላይ ለመኖሪያ ቤት፣ ለቤት ቁሳቁስ እና መሰል ጥቅማጥቅሞች ከሚፈቀድለት ተጨማሪ ገቢ ጋር ተዳምሮ ወደ 115,000 ዶላር በዓመት እንደሚያገኝ የናይጄሪያ ጋዜጦች ጽፈዋል፡፡  
ከ2013 በኋላ ተጨማሪ ጥቅማ ጥቅሞች ተፈቅደውላቸዋል፡፡ ለምሳሌ፤ የውሎ አበል 930 ዶላር በእየለቱ፣ እንደዚሁም በየአራት ወሩ ደግሞ 38, 000 ዶላር --- በአመታዊው ደሞዝ ላይ ተጨማሪ መውሰድ ይችላሉ፡፡  
ከእነዚህ የህግ ባለሙያዎች የተጋነነ ደመወዝ ጋር የሀገሩ ዝቅተኛ የገቢ መጠን ሲነፃፀር በጣም ማስደንገጡ አልቀረም፡፡ የሀገሩ ዝቅተኛ ተከፋይ 18,000 ኒራ ወይንም 90 ዶላር በወር ነው የሚያገኘው፡፡
በናይጄሪያ ያለ ሴናተር በአሜሪካ በዝቅተኛ እርከን የሚከፈል ሴናተር ከሚያገኘው ገቢ ጋር ሲነፃፀር … በመካከላቸው ጥቂት ልዩነት ብቻ እንዳላቸው መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ እንደ ናይጄሪያ አይነት 75 በመቶ የመንግስት በጀት ከዘይት ቀረጥ ላይ በሚተማመን ሀገር፤ የዓለም የነዳጅ ገበያ ሲያሽቆለቁል… እንደ ቀድሞው ተንደላቀው ህይወታቸውን የሚመሩ ባለስልጣናት በአንፃራዊ ሁኔታ መለወጥ እንዳለበት የሚያመለክት ነው፡፡ 

“The power of Negative Thinking” የተሰኘው የስነልቦና መጽሐፍ “የአሉታዊ አስተሳሰብ ልዩ ሃይል” በሚል ርዕስ በአሸናፊ ሰብስቤና በእሩቅነህ አደመ ወደ አማርኛ ተተርጉሞ ለገበያ ቀረበ፡፡
“ለህይወት ወይም ለመኖር ከውስጥህም ሆነ ከውጭ ወይም ለሁለቱም ምንም ዓይነት ዋስትና ሳትሰጥ ስትቀር መኖር ወይም ህይወት በራሱ በመከራ፣ በስቃይ፣ በሀዘን፣ በፍርሃትና ባልተጠበቁ ክስተቶች የተሞላች ትሆናለች” ይላል - መፅሃፉ። በ183 ገፆች የተቀነበበው ይሄው መጽሐፍ፤ በ11 ምዕራፎች ተከፋፍሏል፡፡ “የአሉታዊ አስተሳሰብ ልዩ ሃይል” በ50 ብር ከ65 እየተሸጠ ነው፡፡

 የኢትዮጵያ ሴት ደራሲያን ማህበር ከኢትዮጵያ ባህል ማዕከል ጋር በመተባበር ባህላዊ ህክምናንና አገር በቀል ዕውቀቶችን በተመለከተ የተለያዩ መፃሕፍት የፃፉትን ደራሲ በቀለች ቶላን የሚዘክር ፕሮግራም ባለፈው ረቡዕ በኢትዮጵያ ባህል ማዕከል አዳራሽ ያካሄደ ሲሆን በስራዎቻቸው ላይ የመነሻ ጽሑፍ ቀርቦም ውይይት ተካሂዷል፡፡
ደራሲ በቀለች ቶላ የሴት ደራሲያን ማህበር አባል እንደሆኑ ታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ሴት ደራሲያን ማህበር ከኢትዮጵያባህል ማዕከል ጋር በመተባበር ባህላዊ ህክምናንና አገርበቀል ዕውቀቶችን በተመለከተ የተለያዩ መፃሕፍትየፃፉትን ደራሲ በቀለች ቶላን የሚዘክር ፕሮግራምባለፈው ረቡዕ በኢትዮጵያ ባህል ማዕከል አዳራሽ ያካሄደ ሲሆን በስራዎቻቸው ላይ የመነሻ ጽሑፍ ቀርቦም ውይይት ተካሂዷል፡፡ደራሲ በቀለች ቶላ የሴት ደራሲያን ማህበር አባል
እንደሆኑ ታውቋል፡፡

Saturday, 27 June 2015 09:41

የኪነት ጥግ

• ቤተሰባችን በጣም ድሃ ስለነበር እኔን
የወለደችኝ ጐረቤታችን ናት፡፡
ሊ ትሬቪኖ
• የአይጦች ውድድር ችግሩ…ብታሸንፍ እንኳ
ያው አይጥ ነህ፡፡
ሊሊቶምሊን
• በውሃ ላይ ብራመድ ኖሮ፣ ሰዎች መዋኘት
አይችልም ይሉኝ ነበር፡፡
ጆን ተርነር
• ስለእኔ የማነበውን አምኜ ብቀበል ኖሮ እኔም
ደፋርነቴን እጠላው ነበር፡፡
ዛሳ ዛሳ ጋቦር
• እውነቱ ምንድነው…በ30 ዓመታት ውስጥ
30 ፊልሞችን ሰርቻለሁ፡፡ ለ30 ዓመታትም
ሌሎችም ተጨማሪ ፊልሞችን ባለመስራቴ
ስተች ኖሬአለሁ፡፡
ደስቲን ሆፍማን
• በውብ ነገሮች መከበብ በመፈለጌ ሰዎች
“እማ ዝራው ናት!” ይሉኛል፡፡ ግን እስቲ
ንገሩኝ ማነው በዝባዝንኬ (ነገሮች) መከበብ
የሚፈልገው?
ኢሜልዳ ማርቆስ
• የዜና ዕረፍቴ ዘገባ በእጅጉ ተጋንኗል፡፡
ማርክ ትዌይን (ዜና ዕረፍቱ በጋዜጣ መዘገቡን
ሲሰማ የመለሰው
• ሥራዬን ስለወደዳችሁት የእናንተ ዕዳ አለብኝ
ማለት አይደለም፡፡
ቦብ ዳይላን
• ሆሊውድ ለመሳሳም 50ሺ ዶላር፣ ለነፍስህ
50 ሳንቲም የሚከፍሉህ ሥፍራ ነው፡፡
ማርሊን ሞንሮ
• በትያትር ዓለም የሚቆጨኝ ፊት ለፊት
ተቀምጬ ራሴን ለመመልከት አለመቻሌ
ብቻ ነው፡፡
ጆን ባሪሞር
• አንዳንዴ በጣም ጣፋጭ ከመሆኔ የተነሳ
እኔም ራሴ ሁኔታውን መቆጣጠር ይሳነኛል፡፡
ጁሊ አንድሪውስ
• ወሲብ እግዚአብሔር በሰዎች ላይ የፈጠረው
ቀልድ ነው፡፡
ቤቲ ዴቪስ
• በመድረክ ላይ ከ25ሺ ሰዎች ጋር ፍቅር
እሰራለሁ፡፡ ከዚያም ብቻዬን ወደ ቤቴ
እሄዳለሁ፡፡
ጃኒስ ጆፕሊን
• በኦሎምፒክ ሁለተኛ መውጣት ብር
ያስገኝልሃል፡፡ በፖለቲካ ሁለተኛ መውጣት
መረሳትን ያጐናፅፍሃል፡፡
ሪቻርድ ኤ.ም ኒክሰን