Administrator

Administrator

 የአርቲስት ሰብለ ተፈራ( እማማ ጨቤ) የቀብር ስነስርዓት በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን የውጭጉዳይ ሚኒስቴር ዶር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ታዋቂ ግለሰቦች  አድናቂዎቿ በተገኙበት የቀብር ስነስርዓቷ ተፈፀመ፡፡
ለወዳጅ ዘመዶቿ እንዲሁም አድናቂውቾ መፅናናትን እንመኛለን፡፡

Friday, 11 September 2015 10:18

የፀሐፍት ጥግ

  (ስለ ሳንሱር)
ማንኛውንም ዓይነት ሳንሱር አበክሬ እቃወማለሁ፡፡
ዶን ጆንሰን
ባኮሪያ ምንም መንግሥታዊ ሳንሱር የለም፡፡
ቦንግ ጁን-ሆ
ሳንሱር ልክ እንደ ችሮታ ከቤት መጀመር አለበት፡፡ ነገር ግን ከችሮታ በተለየ መልኩ እዚያው ማዎም ይኖርበታል፡፡
ክላሬ ቡዝ ሉሴ
ለዕድገት የመጀመሪያው አስፈላጊ ሁኔታ የሳንሱር መወገድ ነው፡፡
ጆርጅ በርናርድ ሾው
በብዙ የዓለም ክፍሎች ስላለው ሳንሱር እጨነቃለሁ፡፡
ጂማ ዋልስ
ዓለም ዘላለማዊ የሚላቸው መፃህፍት የራሳቸውን ውርደት የሚያጋልጡ ናቸው፡፡
ኦስካር ዋይልድ
ሰውን ዝም ስላሰኘኸው ለወጥከው ማለት አይደለም፡፡
ጆን ሞርሌይ
መፃህፍት ታግደው አይቀሩም ሃሳች ዘብጥያ አይወርዱም፡፡
አልፍሬድ ዊትኔይ ግሪስዎልድ
ምንጊዜም መፃህፍት ሲቃጠሉ ሰዎችም በመጨረሻ መቃጠላቸው አይቀርም፡፡
ሁንሪክ ሄይን
ብዙ ጊዜ ሳንሱር አድራጊው ከመድረሱ በፊት ራሳችንን ሳንሱር እናደርጋለን፡፡
ስፓይክ ሊ-
ማንንም ለማስደሰት ብዬ ራሴን ፈፅሞ ሳንሱር አላደርግም፡፡
ናታሊያ ኪልስ
የሰዎችን ህልም ሳንሱር ማድረግ አትችልም፡፡
ሮቢን ሂችኮክ
ዘፋኙን እንጂ ዘፈኑን መከርቸም አትችልም፡፡
ሃሪ ቤላፎንቴ

      ያለፈው የስራ ዘመናችን መጠነኛ ነበር፡፡ የስራ እንቅስቃሴዎቹ ደህና ናቸው፡፡ ያለፉት አመታት ላይ አጥልቶ የነበረው የስራዎች መጓተት በዚህኛውም ላይ አጥልቶ ነበረ፡፡ በዚህ ምክንያት እንቅስቃሴያችን መጠነኛ ነበር፡፡
በቀጣይ አመት ግን ብሩህ ተስፋ እናያለን፡፡ በኢህአዴግ ጉባኤ ላይ እንደተገለፀው፤የመልካም አስተዳደር ችግር ተቀርፎ፣ ለሀገር ውስጥ ባለሀብቶች የማጠናከሪያ ድጋፍ እየተደረገ ይሄዳል የሚል እምነት አለን፡፡ የሪል እስቴት ግዢና ሽያጭ ህግም ይፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ እሱም በሪል እስቴት ላይ አዎንታዊ አስተዋፅኦ ይኖረው ይሆናል፡፡ በአጠቃላይ መጪው ጊዜ ብሩህ ነው ብሎ ማሰብ ይቻላል፡፡ ለኢትዮጵያ ህዝብም ሰላም፣ ጤናና፣ ፍቅር ይብዛለት!

    ያለፈው ዓመት ጥሩ የሚባሉ ስራዎችን የሰራሁበት ዓመት ነው፡፡ ሁለት ልጓሞቼን (ወርቅ በወርቅና፣ ሄሮሺማን) በቪሲዲ፣በዲቪዲ ለተመልካች ያቀረብኩበት ዓመት ነበር፡፡ የህዳሴውን ዋንጫም ይዘን ኢትዮጵያን የዞርኩበት ዓመት ነው፡፡ ዘመናዊ  ሲኒማ ቤትና የስፖርት ላውንጅ ግንባታም የጀመርኩበት ዓመት ነው፡፡ በብዙ መልኩ ለኔ ስኬታማ ዓመት ነበር፡፡
ቦሌ አካባቢ ያስገነባሁት ሲኒማ ቤት፣በአዲሱ ዓመት ሥራ ይጀምራል፡፡ መደበኛ ስራዎቹ እንደተጠበቁ ሆነው ሌላ አዲስ ፊልም የመስራት እቅድም አለኝ፡፡

   አንጋፋዋ ድምፃዊት አስቴር አወቀና ማዲንጎ አፈወርቅ ለአዲስ ዓመት ዋዜማ ዛሬ ምሽት  በጊዮን ሆቴል የሙዚቃ ኮንሰርት ያቀርባሉ፡፡ ከቀኑ 10፡30 ላይ የኮንሰርቱ መግቢያ በሮች እንደሚከፈቱ አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡
የዝግጅቱ አስተባባሪ አቶ እዩኤል ልዑልሰገድ ለአዲስ አድማስ እንደተናገሩት፤በኮንሰርቱ ላይ ድንገተኛ (surprise) እንግዳ የሚኖር ሲሆን እንግዳው 2 ወይም 3 ዘፈኖችን ያቀነቅናል፡፡ አስቴር በዋዜማው ኮንሰርት 25 ዘፈኖችን የምታቀርብ ሲሆን ማዲንጎ 8 ወይም 9 ዘፈኖችን እንደሚያቀርብ ተገልጿል፡፡
የ2008 አዲስ ዓመትን ለመቀበል ከሌሊቱ 6 ሰዓት ላይ የርችት ተኩስ ሥነስርዓት ይካሄዳል ተብሏል፡፡ የVIP አቀማመጡ ከመድረኩ ፊት ለፊት መደረጉን የገለፁት አዘጋጆቹ፤ቲኬቶቹ ኤሌክትሮኒክ ስለሆኑ ግፍያ አይኖርም ብለዋል፡፡  

 የዘመን መለወጫ በዓልን ምክንያት በማድረግ የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ከፖሊስ ኦርኬስትራ የሙዚቃ ባንድ ጋር በመተባበር በነገው ዕለት ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ ልዩ የዓውዳመት የመዝናኛ ፕሮግራም ማዘጋጀቷን አስታውቋል፡፡ በእለቱ አጫጭር ድራማዎችን ጨምሮ ዘመናዊና ባህላዊ ዘፈኖች ከነውዝዋዜያቸው ይቀርባሉ፡፡ ፕሮግራሙን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እስከ 11፡30 በ30 ብር መግቢያ መታደም እንደሚቻል አዘጋጆች ተናግረዋል፡፡

 “የአባባ ተስፋዬ ተረቶች የስዕል አውደ ርዕይ” ባለፈው ማክሰኞ በብሔራዊ ቴአትር አርት ጋለሪ ተከፍቶ ለ4 ቀናት ክፍት ሆኖ የቆየ ሲሆን በዛሬው ዕለት ይጠናቀቃል፡፡ አውደ ርዕዩን መርቀው የከፈቱት አባባ ተስፋዬ፤በኔክስት ጄነሬሽን የበጎ አድራጎት ማህበር ህፃናትና ወጣቶች የተዘጋጀላቸው በሙካሽ የተጌጠ ካባ ተበርክቶላቸዋል፡፡ “በዓለም ላይ ብዙ አገራትን አይቻለሁ፤ሰርቶ ለመኖር እንደ ኢትዮጵያ የተመቸ አገር አላየሁም” ያሉት አባባ ተስፋዬ፤“አገራችሁንም ሥራንም ውደዱ፤እኔ አርቲስት ሆኜ እየሰራሁ  ሻሸመኔ ላይ በግብርና ሥራም ተሰማርቼ ነበር፡፡ ከግብርናው ባገኘሁት ትርፍም የራሴን ቤት ሰርቻለሁ፤መኪናም ገዝቻለሁ” በማለት የሥራን ጥቅም አስረድተዋል፡፡
በመክፈቻው ላይ ንግግር ያደረገው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በበኩሉ፤“እኛ ዛሬ ላይ የደረስነው በቀደመው ትውልድ ታግዘንና ተረድተን ነው፡፡ ይህንን ውለታ ታሳቢ በማድረግ አባባ ተስፋዬን የሚዘክር መድረክ መሰናዳቱ መስፋፋትና መቀጠል አለበት” ብሏል፡፡
በአባባ ተስፋዬ ሳህሉ መኖሪያ ቤት ይዞታ ላይ ሊሰራ የታቀደው ቴአትር ቤትና የባህል ማዕከል ጋለሪ ህንጻ ዲዛይን በዕለቱ ቀርቦም ገለፃ ተሰጥቶበታል፡፡

 በብሩክ ከድር የተዘጋጀው “የአረቦች ፀደይ” የተሰኘ መፅሃፍ በትላንትናው ዕለት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ፣ የፕሮፌሰር እሸቱ ጮሌ መታሰቢያ አዳራሽ ተመርቋል፡፡
መፅሀፉ እ.ኤ.አ ከ2010 ጀምሮ በመካከለኛው ምስራቅ የተከሰተውና እስካሁንም ሙሉ በሙሉ ያልተጠናቀቀው ንቅናቄ ያስከተለውን ዘርፈ ብዙ ምስቅልቅልና ሁለንተናዊ ገፅታውን ይዳስሳል፡፡
በ253 ገፆች በተቀነበበው “የአረቦች ፀደይ” መፅሃፍ ላይ አጭር ውይይት እንደተካሄደም ታውቋል፡፡

በጀምስ ሬድፊልድ “The Celestine Prophecy” በሚል ርዕስ ተፅፎ በደራሲና ተርጓሚ አፈወርቅ በቀለ “የመጨረሻው መጀመሪያ” ተብሎ የተተረጐመው መጽሐፍ የዛሬ ሳምንት ቅዳሜ በ11 ሰዓት በዋቢሸበሌ ሆቴል አዳራሽ ይመረቃል፡፡ መጽሐፉ ለደራሲው አምስተኛ የትርጉም ሥራው ሲሆን በምረቃው ሥነስርዓት ላይ የሥነጽሑፍ ባለሙያዎችና ጥበብ አፍቃሪያን እንደሚታደሙ ታውቋል፡፡

    በዓመቱ እስካሁን ያሳለፍነው መልካም ነበር፡፡ በስራ ነው ያሳለፍነው፡፡ ከአመት ወደ አመት የስራ አፈፃፀማችን እየተሻሻለ ነው፡፡ ሠራተኞቻችን ጤናቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ፣ እንዲማሩ ማድረጋችን፣ ተማሪዎችን ማስመረቃችን እንደቀጠለ ነው፡፡ በሌላ በኩል በየቦታው የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን የመፍታት ብቃታችን ከእለት ወደ እለት እየተሻሻለ ነው፡፡ ችግሮችን በጋራ በመፍታት ረገድ ጥሩ ክንውን ነበረን፡፡
በቀጣይ አመት ደግሞ የጀመርናቸው የ8 ሚሊዮን ብር የማስፋፊያ ስራዎችን አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡ ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚውሉ ምርቶች ላይ ትኩረት ለማድረግ እንፈልጋለን፡፡ ወደ ውጭ መላክ ብቻ አይደለም ትልቅ የሚያደርገን ብለን ስለምናምን፣ ሀገር ውስጥ ያለውን ተጠቃሚ ፍላጐት ማሟላት መቻል አለብን፡፡ የሀገር ውስጥ ተጠቃሚው እያደገ ነው፡፡ ይሄን ፍላጐት ለማሟላት በአዲሱ አመት ጠንክረን እንሠራለን፡፡