Administrator
ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት ጅማ በይፋ ተከፍቷል
አስረኛው ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት ጅማ፣ ባለፈው ሐሙስ ታህሳስ 24 ቀን 2017 ዓ.ም በጅማ ተመርቆ ተከፈተ፡፡ ባለ 4 ኮከቡ ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት ጅማ፤ የተለያዩ ዘመናዊ አገልግሎቶች የተሟሉላቸው 105 የመኝታ ክፍሎች ያሉት ሲሆን፤ የቪአይፒ አገልግሎት የሚሰጡና እያንዳንዳቸው አራት ክፍል ያላቸው ሁለት ቪላዎች፣ 5 የኦዲዮቪዥዋል መሳሪያዎች የተገጠሙላቸው የስብሰባ አዳራሾች አሉት፡፡ ሆቴልና ሪዞርቱ አራት ባህላዊና ዘመናዊ ምግቦችን የሚያቀርቡ ሬስቶራንቶች፣ለመዝናናትም ሆነ ጤንነትን ለመጠበቅ የሚያስችሉ የአዋቂና የህፃናት የመዋኛ ገንዳዎች ያሉት ሲሆን ጂምናዚየም፣ ስፓና ስቲም ባዝ፣ ሳውና ባዝና ሞሮኮ ባዝ ተሟልቶለታል፡፡ በይቻላል መርሁ የሚታወቀው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ የወላይታውን ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት ባስመረቀ በ10ኛ ወሩ የጅማውን ያስመረቀ ሲሆን፤ “ይህም በአንድ ዓመት ከአምስት ወር አንድ ሆቴል ለመገንባት የገባነውን ቃል ማክበራችንን ያሳያል” ብሏል፡፡ በምርቃት ሥነስርዓቱ ላይ የተገኙት የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር ባደረጉት ንግግር፤ “ጥንታዊቷና ታሪካዊቷ ጅማ የበለጠ እንድትፈለግና የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆን ሻለቃ ኃይሌ ትልቅ ስራ ሰርቶልናል፤ እኛም በሕይወት እስካለን የጅማን ሰላም እንጠብቃለን” ሲሉ በሆቴሉ ግንባታ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል።ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ግንባታው መጠናቀቁ የተነገረለት ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት ጅማ፤ 1.7 ቢሊዮን ብር ፈጅቷል ተብሏል፡፡ ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት ጅማ በአሁኑ ወቅት ለ210 ቋሚ ሰራተኞች የሥራ እድል የፈጠረ ሲሆን፤ በሙሉ አቅሙ ስራ ሲጀምር የሰራተኞቹን ቁጥር ወደ 400 እንደሚያሳድግ ማኔጂንግ ዳይሬክተሩ አቶ ጋዲሳ ግርማ ገልጸዋል። ኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች በቅርቡ የሻሸመኔውንና የደብረብርሃን ከተማ መዳረሻውን ለማስመረቅና ሥራ ለማስጀመር ቀን ከሌት እየሰራ መሆኑንም አቶ ጋዲሳ ግርማ ተናግረዋል። ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት ቀጣይ መዳረሻውን ወደ ምስራቅ ኢትዮጵያ በማዞር፣ በድሬደዋና በሐረር አድርጎ፣ በዚያው ወደ ጎረቤት አገር የመሻገር እቅድ እንዳለውም ተጠቁሟል፡፡የሃዋሳው ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት እንዲገነባ መሬት በመፍቀድ ከ24 ዓመት በፊት አስተዋፅኦ ያደረጉት የቀድሞው የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አባተ ኪሾ በምርቃቱ ላይ በክብር እንግድነት ታድመዋል፡፡
የ25 ዓመት ረዥም ጉዞ የተጀመረው በዚህ ነው!!
የ25 ዓመት ረዥም ጉዞ የተጀመረው በዚህ ነው!!
ውድ የአዲስ አድማስ ቤተሰቦች፡- የመጀመሪያው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ታትሞ ለንባብ የበቃው ታህሳስ 29 ቀን 1992 ዓ.ም ነበር - የዛሬ 25 ዓመት በዕለተ ቅዳሜ፡፡ ከዚያን ጊዜ አንስቶ ያለ አንድ ቅዳሜ በስተቀር ጋዜጣው ያልወጣበት ቀን የለም፡፡ እሱም ቢሆን የተከሰተው በ97 ምርጫ ማግስት በተከሰተው ፖለቲካዊ ቀውስ ሳቢያ ነበር፡፡
የዛሬ 20 ዓመት፣ የአዲስ አድማስ ጠንሳሽ፣ መሥራችና ባለቤት አሰፋ ጎሳዬ (አሴ) በድንገተኛ ህመም ህይወቱ ባለፈበት ወቅት እንኳን ጋዜጣው ሳይታተም አልቀረም፡፡ ረቡዕ ከቀብር በኋላ ቢሮ ገብተን የቅዳሜውን ጋዜጣ ስናዘጋጅ ትዝ ይለኛል፡፡ እያነባንም ቢሆን የቅዳሜውን ሳምንታዊ ጋዜጣ በጉጉት ለሚጠብቀን ውድ አንባቢ አድርሰናል፡፡
አሁን ሳስበው ታዲያ ያኔ ትክክለኛ ሥራ ነው የሰራነው፡፡ የአሴ ነፍስ በዚያ ተግባራችን ጮቤ እንደረገጠች አልጠራጠርም፡፡ እርሱ በህይወት ባይኖርም አዲስ አድማስ መታተሟ፣ ህልምና ራዕዩን ማስቀጠያ ብቸኛ መንገድ ነበር፡፡
እነሆ ከዚያም በኋላ ሁለት አሰርት ዓመታትን አስቆጥራ፣ በብዙ ውጣ ውረዶችና ተግዳሮቶች አልፍ እነሆ ለ25ኛ ዓመቷ በቅታለች፡፡ በግሉ ፕሬስ ሩብ ክፍለዘመን ቀላል ጊዜ አይደለም፡፡ ቀላል ዕድሜ አይደለም፡፡ የ25 ዓመት ጉዞ ሀ ብሎ የተጀመረው ግን በዚህ ነው፡፡ ታህሳስ 29 ቀን 1992 ዓ.ም በታተመችው አዲስ አድማሰ ጋዜጣ፡፡
እንኳን አደረሳችሁ፤ አደረሰን!!
ወቅታዊው የጸጥታ መደፍረስና የኑሮ ውድነት ፈተና እንደሆኑበት ዝግባ የሕጻናትና አረጋውያን መርጃ የበጎ አድራጎት ድርጅት አስታወቀ
ከተመሰረተ 16 ዓመታትን ያስቆጠረው ዝግባ የሕጻናትና አረጋውያን መርጃ የበጎ አድራጎት ድርጅት፤ በአማራ ክልል የተፈጠረው የጸጥታ መደፍረስና የኑሮ ውድነት ፈተና እንደሆኑበት አስታውቋል። ድርጅቱ የምስረታ ክብረ በዓሉን ለማክበር በዝግጅት ላይ መሆኑንም ገልጿል።
ባለፈው ሐሙስ ታህሳስ 24 ቀን 2017 ዓ.ም. በጌትፋም ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የድርጅቱ ሃላፊዎችና የበጎ ፈቃድ አምባሳደሮች የተገኙ ሲሆን፣ ስለድርጅቱ ዝርዝር ማብራሪያ አቅርበዋል። በማብራሪያቸውም ላይ ድርጅቱ ዋና መቀመጫውን በባሕር ዳር ከተማ በማድረግ ከ2 ሺሕ 650 በላይ ወላጆቻቸውን በሞት ላጡና ለከፋ ችግር የተጋለጡ ሕፃናትና ጧሪ አልባ የሆኑ አረጋውያን በመደገፍ፣ እንዲሁም ችግረኛ ሴቶችን በገቢ ማስገኛ ስራ በማሰማራት ኑሯቸውን እንዲያደላድሉ ማስቻሉን የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ስለሺ ጌታቸው አመልክተዋል።
በ27 በጎ ፈቃደኛ ግለሰቦች የተቋቋመው ይህ የበጎ አድራጎት ድርጀት፣ የራሱ ተሽከረካሪዎች እንደሌሉት፤ የቦታ ጥበት እንዳለበት፤ የከርሰ ምድር ውሃ ችግር ስለመኖሩ በዚሁ መግለጫ ተነግሯል። ከዚህም ባለፈ በአማራ ክልል የተፈጠረውን የጸጥታ መደፍረስና የኑሮ ውድነቱን ተከትሎ፣ የተፈጠረው የፍጆታ ዕቃዎች አቅርቦት ዕጥረት "እየፈተነኝ ነው" ሲል ድርጅቱ አስረድቷል።
"ለአካል ጉዳተኞች እና ዕድሜያቸው ለገፋ ሰዎች የሚያገልግል ዊልቸር ዕጥረት ተፈጥሮብኛል" ያለው ድርጅቱ፣ በጎ ፈቃደኛ የሆኑ ግለሰቦች፤ በተለይም ከዚህ ቀደም ድጋፍ ለማድረግ ቃል የገቡ ባለሃብቶች ቃላቸውን ተግባር ላይ እንዲያውሉ ጠይቋል። የድርጅቱ የገቢ ምንጭ በአብዛኛው ከአባሎች በሚገኝ መዋጮ፣ በድርጅቱ ስር ካለው ትምሕርት ቤት እና በባሕር ዳር ከተማ ከከፈተው የፍራፍሬ ጭማቂ መሸጫ ቤት የሚመነጭ በመሆኑ፣ በስሩ ለሚገኙ 50 ቋሚ ሰራተኞች ደመወዝ ከመክፈል እና በማዕከሉ ላሉ ድጋፍ የሚሹ ወገኖች ድጋፍ ከማድረግ በዘለለ መጠነ ሰፊ ስራዎችን እንዳይሰራ ተግዳሮት እንደሆኑበት ጠቁሟል።
ዝግባ የሕጻናትና አረጋውያን መርጃ የበጎ አድራጎት ድርጅት 16ኛ ዓመት የምስረታ ክብረ በዓሉን ለማክበር መዘጋጀቱን በመጠቆም፣ ገቢ ከማሰባሰብ በተጨማሪ የመገናኛ ብዙሃን ትኩረታቸውን ለድርጅቱ እንዲያውሉ ዕንቅስቃሴ እንደሚያደርግ አብራርቷል።
ዓለምፍሬ ፒንክሃውስ ካንሰር ፋውንዴሽን የድጋፍ ጥሪ አቀረበ
ዓለምፍሬ ፒንክሃውስ ካንሰር ፋውንዴሽን ለመላ ኢትዮጵያውያን የድጋፍ ጥሪ አቅርቧል። ፋውንዴሽኑ በተደጋጋሚ የመሬት ጥያቄ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጥያቄ ቢያቀርብም፣ ምላሽ እንዳላገኘ አመልክቷል።
ባለፈው ዓርብ ታሕሳስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም. በግዮን ሆቴል ሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ፋውንዴሽኑ በዶክተር ፍሬሕይወት ደርሶ ከአስራ ሶስት ዓመታት በፊት በአሜሪካ አትላንታ እንደተመሰረተ በማውሳት፣ በካንሰር ሕመም ላይ ቅድመ መከላከል የግንዛቤ መስጠት ስራ ሲሰራ መቆየቱ ተብራርቷል። በአዲስ አበባ እና ጎንደር ከተሞች ከ8 ሺሕ በላይ የካንሰር ታማሚዎችን የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ እያደረገ የሚገኝ ድርጅት መሆኑም ተገልጿል።
የድርጅቱ የቦርድ አባል ወይዘሮ ጸዳለ ጽጌ እንዳስታወቁት፣ ፋውንዴሽኑ በዓመት ሁለት ጊዜ በካንሰር ሕመም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ኮንፈረንስ ያዘጋጃል። አክለውም፣ በሁለተኛው ኮንፈረንስ አማካይነት በሕመሙ የተጠቁ ወገኖች እርስ በርሳቸው የውይይት መድረክ እንደሚያካሂዱ አስረድተዋል።
"የካንሰር ታማሚዎች ጤና የእርስዎም፣ የእኔም፣ የሁላችንም ጉዳይ ነው" የሚለው ፋውንዴሽኑ፣ መላ ኢትዮጵያውያን የድጋፍ እጃቸውን እንዲዘረጉ ጠይቋል። አሁን ላይ እየሰራቸው ካሉ ስራዎች በተጨማሪ፣ በቀጣይ ሌሎች በርካታ ዕንቅስቃሴዎችን ለማድረግ የተለያዩ ዕቅዶችን እንደነደፈ ተነግሯል።
ባቡል ኸይር በ1.2 ቢ.ብር የአረጋውያን መጠለያ ሁለገብ ማዕከል ሊያስገነባ ነው
• ለግንባታው እውን መሆን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ድጋፍ
እንዲያደርግ ተጠይቋል
ባቡል ኸይር የበጎ አድራጎት ድርጅት፣ በቤተል አለም ባንክ የምገባና የአረጋዊያን መጠለያ ሁለገብ ማዕከል ፕሮጀክት ዋና መሥሪያ ቤትን በ1.2 ቢ.ብር ለማስገንባት እንቅስቃሴ መጀመሩን ያስታወቀ ሲሆን፤ ለግንባታ ሥራው አቅም ይሆን ዘንድ ከ11 ሚሊዮን በር በላይ ወጪ በማድረግ የከርሰ ምድር የንጹህ ውሃ መጠጥ ማውጣቱንና በ5 ሚሊዮን ብር ወጪ የመብራት ዝርጋታ ማከናወኑን ገለጸ፡፡
በ5ሺ ካሬ ሜትር ላይ መሰረቱ የተጣለውን የባቡል ኸይር የምገባና የአረጋዊያን መጠለያ ሁለገብ ማዕከል ለመገንባት የሁሉም ኢትዮጵያውያን ድጋፍና እገዛ ያስፈልጋል ተብሏል፡፡
በሌላ በኩል፣ የበጎ አድራጎት ድርጅቱ የፊታችን ጥር 4 ቀን 20፞17 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ «አምስት ዓመታትን በሰብአዊነት» በሚል መሪ ቃል የተመሰረተበትን አምስተኛ ዓመት የሚያከብር ሲሆን በዕለቱም በአለም ባንክ አካባቢ መሠረቱ የተጣለለት ይኸው የባቡል ኸይር የምገባና የአረጋዊያን መጠለያ ማዕከል ይጎበኛል ተብሏል፡፡
በዛሬው ዕለት ታህሳስ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ጠዋት ረፋድ ላይ የባቡል ኸይር በጎ አድራጎት ድርጅት መሥራች ወይዘሮ ሀናን መሀመድና ወጣቱ ባለሃብት ምህረተአብ ሙሉጌታ እንዲሁም ኡስታዝ አብዱር አማሊ ሱልጣን በክብረ በዓሉ ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደተብራራው፤ የበጎ አድራገት ድርጅቱ አምስተኛ ዓመት በዚሁ ማዕከል ከባቡል ኸይር ቤተሰብና አረጋዊያን ጋር አብሮ በማሳለፍና በጉብኝት ይከበራል፡፡
የድርጅቱ አጋርና ደጋፊ እንዲሁም የበዓሉ አስተባባሪ ኮሚቴ አባል ወጣቱ ባለጸጋ ምህረትአብ ሙሉጌታ ባደረገው ንግግር፤ “ባቡልኸይር ራሱን በራሱ ለመርዳት መንግስት በሰጠው መሬት ላይ ትልቅ ህንጻ ለመገንባት የጀመረው አካሄድ ይበል የሚያሠኝና የእኛን ድጋፍ የሚሻ በመሆኑ ደጋግ ኢትዮጵያውያን በቻላችሁት አቅም በማገዝ አሻራችሁን ልታሥቀምጡ ይገባል።” ብሏል፡፡
በተጨማሪም ለ5ኛ አመት ክብረ በአሉም ሁላችንም ተገኝተን የቻልነውን እናግዝ ሲል ጥሪ አስተላልፏል።
126 ሰዎችን በመመገብ የበጎ አድራጎት ሥራውን ሀ ብሎ የጀመረው ባቡል ኸይር፤ ዛሬ ላይ ከ5 ሺህ በላይ ችግረኛ ወገኖችን በቀን ሁለት ጊዜ ምሳና እራት እየመገበ የሚገኝ ሲሆን፤ የጤና መድህናቸውንም ማረጋገጥ ችሏል ተብሏል፡፡
በርካታ ቁጥር ያላቸውን ወጣቶችና ሴቶችን በተለያዩ ሙያዎች (ልብስ ስፌት፣ የኮምፒዩተር ስልጠና፣ የጫማ ስራ) እያሰለጠነና የስራ እድሎችን ጭምር እያመቻቸ እንደሚገኝም ለማወቅ ተችሏል፡፡
ዛሬ ላይ ባቡል ኸይር በአበበ ቢቂላ የመመገቢያ ማዕከልና የሙያ ስልጠና ማሳያ ስፍራ፣ በአቃቂ ቃሊቲ የስልጠና ማዕከልና የህፃናት ማቋያ ያለው ሲሆን፤ በኦሎንኮሚ ለወጣቶች የስራ እድልን እየፈጠረ የሚገኝ የብሎኬት ፕሮጀክት ግንባታ እያከናወነ ይገኛል።
“ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ የጣለብንን ዕግድ እንደሚያነሳ ተስፋ አደርጋለሁ”
ከአንድ ሳምንት በፊት በሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን የታገደው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አቶ ያሬድ ሃይለማርያም፤ “ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የጣለብንን ዕግድ እንደሚያነሳ ተስፋ አደርጋለሁ” ሲሉ ለአዲስ አድማስ ተናገሩ፡፡ የሚመሩት ማዕከል ከሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በዕግዱ ዙሪያ እየተመካከረ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ከታገደ አንድ ሳምንቱ መሆኑን የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ አዲስ አበባ የሚገኘው የማዕከሉ ዋና ጽሕፈት ቤት ስራ አቁሞ መዘጋቱን ገልጸዋል። የማዕከሉ የባንክ ሂሳብ መታገዱንም አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ሕጋዊ መንገድን ተከትሎ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን ያስረዱት አቶ ያሬድ፤ ድርጅቱ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ ባሳለፋቸው አራት ዓመታት ከመንግስት ጫና ደርሶበት እንደማያውቅ አስታውቀዋል። ይሁንና በሌሎች የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ተቋማት ላይ የሚደርሱ ጫናዎችን አስመልክቶ መግለጫዎችን ሲያወጣ መቆየቱን አልሸሸጉም፡፡
በማያያዝም፣ ማዕከሉ ትኩረቱን በጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ላይ በማድረግ፣ ከተለያዩ ወገኖች የሚደርስባቸውን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እንደሚያጋልጥ ዋና ዳይሬክተሩ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል።
ታህሳስ 16 ቀን 2017 ዓ.ም. የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ለማዕከሉ ደብዳቤ ከመጻፉ አስቀድሞ ምንም ዓይነት የማስጠንቀቂያም ሆነ የምርመራ ሂደት እንዳልተከናወነ አቶ ያሬድ አስረድተዋል። ይህንን አስመልክቶም ማዕከሉ ለባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ደብዳቤ እንደጻፈና በዕግዱ ዙሪያ ከመስሪያ ቤቱ ጋር እየመከረ መሆኑን ጠቁመው፤ “ባለስልጣኑ የጣለብንን ዕግድ እንደሚያነሳ ተስፋ አደርጋለሁ” ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል፣ በሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ዓዋጅ መሰረት በ2013 ዓ.ም. የተመሰረተ ተቋም ነው።
መባዕ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ. የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤውን ያካሒዳል
በቅርቡ ወደ ፋይናንስ ሴክተሩ የተቀላቀለው መባዕ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ.፣ አንደኛ መደበኛ እና አንደኛ አስቸኳይ የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤውን፣ ነገ ቅዳሜ፣ ታኅሣሥ 26 ቀን 2017 ዓ.ም. ከጠዋቱ በ2:00 በራስ ዓምባ ሆቴል ያካሒዳል፡፡
ከ850 በላይ በሚኾኑ ባለአክሲዮኖች የተቋቋመውና ከአምስት ወራት በፊት ሥራ የጀመረው ተቋሙ፣ የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤውን ለማካሔድ ዝግጅቱን አጠናቋል።
ጠቅላላ ጉባኤው፣ በተቋሙ የዳይሬክተሮች ቦርድ በሚቀርበው ሪፖርት፣ የተቋሙን ካፒታል ማሳደግ፣ በውጪ ኦዲተር ሪፖርት እና መሰል አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል፡፡
በጠቅላላ ጉባኤው ላይ፥ ባለአክሲዮኖች፣ የዳይሬክተሮች ቦርድ፣ የተቋሙ አመራር እና ሠራተኞች እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የሰነዶች ማረጋገጫ ተወካዮች እንደሚገኙ ይጠበቃል፡፡
የአዲስ አፍሪካ ዓለማቀፍ ኤግዚቢሽንና ኮንቬንሽን ማዕከል - በዓለማቀፍ ውድድር ውስጥ
የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራሮች፣ ሰራተኞችና ሠልጣኝ የበጎ ፈቃድ ዲፕሎማቶች በአዲስ አበባ ከተማ የተገነቡና አሁን በመገንባት ላይ የሚገኙ የአዲስ አፍሪካ አለም አቀፍ ኤግዚቢሽንና ኮንቬንሽን ማዕከል፣ የአድዋ ድል ሙዚየምንና የኮረደር ልማት ስራዎችን ሰሞኑን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ጉብኝት ብቻም አይደለም፡፡ “በአዲስ አበባ ከተማ የተሰሩ ግዙፍ ስራዎች” በሚል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ እናትዓለም መለሰ ተሰጥቷቸዋል፡፡
የስልጠናው ዓላማ በተለይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የበጎፈቃድ ዲፕሎማቶች በመዲናዋ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ለውጭው ዓለም በማስተዋወቅ የሃገርን ገጽታ በመገንባት ረገድ የበኩላቸውን እንዲወጡ ለማስቻል ነው፡፡ ከእነዚህ ግዙፍ ፕሮጀክቶች አንዱ ደግሞ የመጀመሪያ የሥራው ምዕራፍ በመገባደድ ላይ የሚገኘው የአዲስ አፍሪካ ዓለማቀፍ ኮንቬንሽንና ኤግዚቢሽን ማዕከል ነው፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አበቤ ስለማዕከሉ ሲናገሩ፤ አዲስ አበባ የዓለም ዓቀፍ ኤግዚቢሽኖችና ጉባኤዎች መነሃሪያነቷን የምናረጋግጥበት፣ የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከልነቷን በኩራት የምንመሰክርበት ይሆናል ነው ያሉት፡፡
የዛሬ ጽሁፋችን የአዲስ አፍሪካ ዓለማቀፍ ኤግዚቢሽንና ኮንቬንሽን ማዕከል ላይ የሚያተኩር ቢሆንም፣ በቀጥታ ወደዚያ ከመሻገራችን በፊት ግን ዓለማቀፍ ተሞክሮዎችን በጥቂቱ ለማስቃኘት ወደድን - ለግንዛቤ ያህል፡፡ ከአሜሪካው ቦስተን ኮንቬንሽንና ኤግዚቢሽን ማዕከል እንጀምር፡፡
ማዕከሉ፤ በዓመት 1.6 ሚሊዮን እንግዶችንና ተሳታፊዎችን ባስተናገደበት ዓመት፣ ለሆቴል ቢዝነሶች ብቻ የ900 ሚሊዮን ዶላር ገበያ እንዳስገኘላቸው ተመዝግቦለታል። በዓመት ከ500 በላይ ዝግጅቶችን እንደሚያስተናግድ የሚነገርለት ማዕከሉ፤ እስካሁን ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ከ2.5 ቢሊዮን ዶላር በላይ አስተዋጽኦ እንዳበረከተ በ2022 የታተመው ሪፖርት ይገልጻል።
ሌላኛው ከዓመት በፊት የተመረቀው “አቢጃን የኤግዚቢሽን ማዕከል”፣ በምዕራብ አፍሪካ ብቻ ሳይሆን ከሰሀራ በታች ትልቁ የኤግዚቢሽን ማዕከል ነው ይባልለታል። ማዕከሉ በ130 ሚሊዮን ዶላር የተገነባ ሲሆን፤ 7 ሺ ካሬ ሜትር የኤግዚቢሽን አዳራሽ አለው። የጣራው ከፍታ 15 ሜትር ነው። ማዕከሉ 5 ሺ ተሰብሳቢዎችን የሚያስተናግድ የጉባኤ አዳራሽ እንዲሁም የአስተዳደር ሕንጻዎችን ያካትታል። መድረኩና ወንበሮቹ ተገጣጣሚና ተጣጣፊ ስለሆኑ፣ አዳራሹ ኤግዚቢሽን ለማሳየትም ያገለግላል። 800 የመኪና ማቆሚያ ቦታዎችም ተዘጋጅተውለታል። በውስጡ የእንግዳ ማረፊያ ወይም ሆቴል ባይኖረውም፣ የባሕር ዳርቻ መዝናኛ አጠገብ የተገነባ በመሆኑ ጠቅሞታል። ለአካባቢው ነዋሪዎች ጥሩ ገበያ ያመጣላቸዋል። ለአገሪቱ ለአይቮሪኮስት የቱሪዝም ገቢ እያስገኘላት ይገኛል።
በአገራችን አዲስ አበባ እየተገነባ የሚገኘው ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽንና ኮንቬንሽን ማዕከል፣ ከቱሪዝም ገቢ በተጨማሪም፣ በርካታ ጥቅሞችን ያበረክታል። በዙሪያው የቢዝነስና የስራ ዕድሎችን የሚያስፋፋ፣ የእድገትና የብልጽግና ግንኙነቶችን የሚፈጥር የኢኮኖሚ መነሃሪያ (Hub) በመሆን ያገለግላል። ባሕላዊ፣ ጥበባዊና ማኅበራዊ ፋይዳዎችን የሚያበራክትም ነው - አገልግሎቶቹ በዓይነታቸው ብዙ ናቸው።
ይህም ብቻ አይደለም። የኢንዱስትሪዎች፣ የቴክኖሎጂዎች፣ የምርቶችና የአገልግሎቶች ዓለማቀፍ ኤግዚቢሽን ሲዘጋጅ፣ የዕውቀት ሽግግርን ያቀላጥፋል። የኢንቨስትመንትና የቢዝነስ አማራጮችን ይከፍታል። የንግድና የገበያ ግንኙነቶችን ለመፍጠር፣ ውል ለመፈራረም፣ ሽያጭና ግዢ ለመጀመር መልካም አጋጣሚዎችን ይፈጥራል። ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችንና ዝግጅቶችን የሚያስተናግድ አገር፣ በዓለማቀፍ የዲፕሎማሲና ኢኮኖሚ መድረክ ተሰሚነቱ ይጨምራል። የኢኮኖሚ ድርሻው እያደገ ይሄዳል።
አዲስ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽንና ኮንቬንሽን ማዕከል 5ሺ እና 2ሺ ተሳታፊዎችን የሚያስተናግዱ ትልልቅ አዳራሾች ፣ ለኤግዚቢሽኖች እንዲሁም ለጉባኤዎች በስምንት ንዑስ አዳራሽ በርካታ ስብሰባዎችን በአንድ ጊዜ ማስተናገድ የሚያስችል ነው። በአዲስ አበባ ትልቁ ባለ 5 ኮኮብ ሆቴልም ተገንብቷል፤ 980 የእንግዳ ማረፊያዎችን መያዝ የሚችል እንዲሁም ከመስቀል አደባባይ በመቀጠል የሚጠቀስ ትልቅ አደባባይ፣ እንዲሁም ሁለት “የአምፊ ቲያትር” ስፍራዎችም እየተገነቡና እየተዘጋጁ ነው።
በዓለም የኤግዚቢሽንና የኮንፈረንስ ቱሪዝም ካርታ ላይ የኢትዮጵያ ስምና ድርሻ ጎልቶ እንዲታይ የሚያደርግ ሰፊ ፕሮጀክት ነው። ከተጓዳኝ ግንባታዎች ጋር 15 ሄክታር ይሸፍናል። በዓለም ደረጃ የመወዳደርና ተመራጭነትን የማግኘት ብቃት እንዲኖረው ታስቦ የተገነባ መሆኑ ይነገርለታል፡፡
መዲናችን አዲስ አበባ ዓለም ዓቀፍ ኤግዚቢሽኖችን፣ ጉባኤዎችንና ስብሰባዎችን በአንድ ማዕከል የማስተናገድ አቅም አልነበራትም ፣ ይህን የአገራችንን ጉድለት የሚያሟላ ማዕከል ተገንብቶ ወደ ፍጻሜው እየደረሰ ያለው ፕሮጀክት፤ ለከተማችንና ለአገራችን ተጨማሪ የስበት ማዕከል እንደሚሆን ይታመናል፡፡
ከተማችን በጣም እያደገች እየተለወጠች ነው። ተወዳዳሪነቷ እየጨመረ ነው። ግን በኮሪደር ልማት ብቻ እንዳልሆነ የአዲስ አበባ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ይናገራሉ። በእርግጥ የኮሪደር ልማቱም ሰፊ ነው። መሀል ከተማውን በስፋት ያካለለ፣ ከ130 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ርዝመትን የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ከተማዋን ከዳር ዳር እያዳረሰ ነው ማለት ይቻላል። ነገር ግን ከመሀል ከተማ ወደ ዳር ወጣ ስትሉም ብዙ አዳዲስ ግንባታዎችን ታያላችሁ። ጸዳ ያሉ መኖሪያ ቤቶች በብዛት እየተሰሩ ነው። ለኮሪደር ልማት የተነሱ ነዋሪዎች ምትክ መኖሪያ ቤት እንዲሁም የቤት መሥሪያ ምትክ ቦታ እየተሰጣቸው ነው። ነዋሪዎች በነጻ የሚገለገሉባቸው የመዝናኛና የመናፈሻ ስፍራዎች በአረንጓዴ መስክና በፏፏቴ ተውበው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።
በመሀል ከተማ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ግንባታ ከአኩሪ ታሪካችን ጋር የተያያዘ ጥሩ ነገር ፈጥረናል። የትልቅ ታሪክ መዘክር ከመሆኑም በተጨማሪ፣ በግንባታው ጥራትና ውበት፣ በጠቅላላ ይዘቱና በተሟላ አገልግሎቱ ምን ያህል ተመራጭነትን እንዳገኘ በተግባር አይተናል። የኮንፈረንስ ቱሪዝም ስበት ለመሆን ችሏል። ከመሀል ከተማ ወደ ዳር ወጣ ብለን ደግሞ ሌላ ግዙፍ ማዕከል እየጨመርንበት ነው። አዲስ አበባ የዓለም ዓቀፍ ኤግዚቢሽኖችና ጉባኤዎች መነሃሪያነቷን የምናረጋግጥበት፣ የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከልነቷን በኩራት የምንመሰክርበት ይሆናል።
ኢትዮጵያ በአመቺ ጸጋዎች የታደለች አገር እንደሆነች የገለጹት የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፤ በርካታ ታሪካዊ ቅርሶችና ሀብቶች፣ የተፈጥሮ ጸጋዎችና ውበቶች አሏት። የአፍሪካ አንድነት መሥራችና የአፍሪካ ሕብረት ዋና መቀመጫ ናት። ቢያንስ ቢያንስ በዓመት አንዴ የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ ይካሄዳል። አገራችን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መሥራችም ናት። የተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የሚገኘው በአዲስ አበባ ነው። ከዚህም ጋር ተያይዞ በርካታ የተመድ ተቋማት በአዲስ አበባ ከትመዋል። ይሄ ሌሎች አገራት የማያገኙት ዕድል ነው። የዓለም የዲፕሎማሲ ማዕከላት ተብለው የሚጠቀሱ የዓለማችን አገራት በጣት የሚቆጠሩ ናቸው። ኢትዮጵያ ከእነዚህ መካከል አንዷ ናት።
በታሪካዊ ሀብቶችና በተፈጥሮ ጸጋዎች የታደለች ቢሆንም ግን፣ በዓለም አቀፍ ቱሪዝምና ኢኮኖሚ ውስጥ ተገቢውን ጥቅምና ድርሻ እያገኘች አይደለችም። በተመድና በአፍሪካ ሕብረት ስር የተካተቱ ብዙ ተቋማት በከተማችን አሉ። ዓለም ዓቀፍ ኤግዚቢሽኖችንና ጉባኤዎችን ማካሄድ ይፈልጋሉ። እዚሁ አገራችን ውስጥ ቢሆንላቸው ይመርጣሉ - ብዙዎቹ። ነገር ግን፣ ተስማሚ ማዕከላትና አማራጮች ፍለጋ ወደ ሌሎች አገራት ያማትራሉ።
ትልልቅ ዓለም ዓቀፍ ኤግዚቢሽኖችን በብቃት ለማስተናገድ የምንችልበት፣ ዓለም ዓቀፍ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት የሚሰጥና ዘመናዊ መሠረተ ልማቶች የተሟሉለት ማዕከል በብቃት ሳናሰናዳ ስለቆየን በየዓመቱ ብዙ ዕድሎችን ያስቀርብናል። የአገራችንን ኢኮኖሚ ሊያሳድጉ የሚችሉ የሥራና የገበያ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ዕድሎች ዓይናችን እያየ ያመልጡን ነበር። አሁን ግን በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ጥራቱን የጠበቀና የተሟላ አገልግሎት የሚሰጥ ማዕከል ተገንብቷል ፤ብለዋል የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ - አዲስ ዓለም ዓቀፍ ኤግዚቢሽንና ጉባኤ ማዕከል።
የማዕከሉ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሲሳይ ገመቹ እንደሚሉት፣ የግንባታውን ጥራትና ውበት በርካታ ባለሙያዎች አይተው መስክረውለታል። ትልቁን አዳራሽ ሁለገብ አዳራሽ ይሉታል - ለስብሰባም ለኤግዚቢሽን ማሰናጃም ይሆናል። 5 ሺ ተሳታፊዎችን ማስተናገድ ይችላል። ዲዛይኑ የሕንጻውን ንድፍ በግላጭ የሚያሳይ “ስቲል ስትራክቸር” እንደሆነ ጠቅሰው፣ በባለ ሙያዎችም ሆነ በተመልካቾች ዐይን ሲታይ ያምራል ብለዋል። ለእያንዳንዱ የስብሰባ ወይም የኤግዚቢሽን ይዘት በሚስማማ መንገድ አዳራሹን ለማስጌጥ እንዲያመች ታስቦበት የተሠራ እንደሆነም ገልጸዋል።
በርካታ ሺ ሰዎችን በአንዴ የሚያስተናግድ ሰፊ አዳራሽ ቢሆንም፣ አየር እንደልብ ስለሚያንሸራሽር፣ የጣሪያው ከፍታም 28 ሜትር ስለሆነ የሙቀት መቆጣጠሪያ አያስፈልገውም። በተፈጥሯዊ ብርሃን አዳራሹን የሚያጥለቀልቁ ረዣዥምና ሰፋፊ መስኮቶች አሉት። የፊልም ምስሎችን ለማየት ወይም የኤሌክትሪክ መብራት መጠቀም ካስፈለገም፣ መስኮቶቹን ሙሉ ለሙሉ መጋረድ ይቻላል።
ሁለት የምግብ አቅርቦት ማስተናበሪያ ስፍራ፣ እንዲሁም የእረፍት ሰዓት የሻይ የቡና መስተናገጃ ሰፊ ቦታ አለው። ከአዳራሹ ሥር በታችኛው ፎቅ ወደ ተዘጋጁት በርካታ የመጸዳጃ ቤቶች የሚያደርስ መተላለፊያ የሚገኘውም በዚሁ አቅጣጫ ነው። በአዳራሹ ሌላኛው ጎን የክብር እንግዶች መቆያ ቦታና ተጨማሪ የመጸዳጃ አገልግሎት ስፍራዎች ተሰርተውለታል።
የኤግዚቢሽን አዳራሽ - በ5 ሺ ካሬ ሜትር ስፋት
ከሁለገብ አዳራሽ ቀጥሎ ከላይ የምናገኘው ትልቅ አዳራሽ ዋና አገልግሎቱ ለኤግዚቢሽን ነው። መካከለኛ አዳራሽ ነው ይሉታል - ዋና ስራ አስፈጻሚው ሲሳይ ገመቹ። አንድ ሺ ሰዎችን ያስተናግዳል። ዘና ያለ መንፈስ እንዲኖረው፣ አየር በደንብ እንዲንሸራሸር፣ የተፈጥሮ ብርሃን በሰፊው እንዲያስገባ ታስቦበት የተሰራው አዳራሽ፣ ጣሪያው 28 ሜትር ቁመት አለው።
ከአንድ አቅጣጫ በኩል፣ ከአዳራሹ አጠገብ የመጋዘን ክፍሎች አሉት። በሌላኛው አቅጣጫ ደግሞ ቢሮዎችን ይዟል። በአጠቃላይ ከኤግዚቢሽን ዝግጅት ጋር የተዛመዱ አገልግሎቶችን ሁሉ እንዲያሟላ ተድርጎ ነው የተሠራው።
ሰፊ የትዕይንት አዳራሽ - በተገጣጣሚ ግድግዳም ሲከፋፍሉት ደግሞ ሰባት ንዑስ አዳራሾች፡፡ አራተኛ ፎቅ ላይ የምናገኘው ሰፊ አዳራሽ፣ 2 ሺ ሰዎችን ማስተናገድ ይችላል። ለትልቅ ጉባኤ ሊያገለግል ይችላል። ስዕሎችን ለማሳየት ወይም ሌላ ለእይታ የሚቀርቡ ድግሶችን ለማዘጋጀትም የአዳራሹ ቅርጽ ይመቻል። ተመልካቾች በአንዱ ጫፍ ገብተው፣ በእይታ ድግሶችን ተስተናግደው ዓይናቸውን ረክቶ በሌላኛው ጥግ ይወጣሉ። ካስፈለገ ደግሞ ረዥሙ አዳራሽ ውስጥ ተገጣጣሚ ግድግዳዎች ተዘርግተው፣ ለንዑስ ስብሰባዎች የሚያገለግሉ 7 መካከለኛና አነስተኛ አዳራሾች ይወጣዋል። ግድግዳዎቹ ተጣጣፊ ተገጣጣሚ ቢሆኑም፣ ከመደበኛ ግድግዳ አይተናነሱም። ድምጽ አያሳልፉም፤ ሲታዩም ያምራሉ ብለዋል - የማዕከሉ ዋና ስራ አስፈጻሚ።
አዳራሹ አራተኛ ፎቅ ላይ ቢሆንም፣ ከበቂ በላይ መተላለፊያዎች አሉት። በየአቅጣጫው በተሠሩ በርካታ ሰፋፊ ደረጃዎች አማካኝነት መግባትና መውጣት ይቻላል። ከደረጃዎች ጎን “ስካሌተሮች” አሉ። ከእነዚህ በተጨማሪም አሳንሰሮች (ሊፍቶችን) መጠቀም ይቻላል።
የአዳራሾቹን አገልግሎት በትክክል ለማከናወንና ለመቆጣጠር የሚያገለግሉ የቴክኒክና የቴክኖሎጂ ክፍሎችን ጨምሮ፣ የጥበቃና የክትትል ስራውም በሚገባ እንደታሰበበት ስራ አስፈጻሚው ያስረዳሉ። የጥበቃ ስራዎችን በምሳሌነት አንስተው ሲናገሩ፣ ዋናዎቹ ቁልፍ ነገሮች የባለሙያ ስልጠናና ቴክኖሎጂ ናቸው ይላሉ። ኤግዚቢሽኖችና ጉባኤዎች በተቃና ሁኔታ እንዲካሄዱ ነው - የጥበቃ አስፈላጊነት። አዘጋጆች፣ ተሳታፊዎችና ተመልካቾች የተሟላ ምቹ አገልግሎት እንዲያገኙም ነው - የጥበቃ አላማው።
ለዚህም የጥበቃ ካሜራዎችና መከታተያ ቴክኖሎጂዎችን አሟልተናል ይላሉ - አቶ ሲሳይ። የጥበቃ ባለሙያዎች የተሰብሳቢዎችን ትኩረት በማይረብሽ ሁኔታ ስራቸውን እንዲያከናውኑም በቂ ስልጠና ይኖራቸዋል።
ከኤግዚቢሽንና ከጉባኤ አዳራሾች በተጨማሪ፣ ማዕከሉ ሌሎች በርካታ ግንባታዎችንንና አገልግሎቶችን ያካትታል። ባለ 5 ኮከብ ሆቴል - 980 የእንግዶች ማረፊያ ያለው። ከአዳራሾቹ አጠገብ የተገነባው ሆቴል፣ ስራው አልቋል ማለት ይቻላል። ተቀብቶ አጊጦ አምሯል። በሆቴል አገልግሎት በከተማችን በትልቅነቱ ቀዳሚነትን የያዘ ሆቴል እንደሚሆን የተናገሩት ከንቲባ አዳነች አበቤ፤ 980 የእንግዳ ማረፊያዎችን መያዝ ይችላል ብለዋል። የአገልግሎቱ ጥራት ከስካይ ላይት ጋር በእኩል ደረጃ የሚቀመጥ ነው ብለዋል። ነገር ግን የአዳራሾችና የሆቴል ግንባታ ጉዳይ ብቻ አይደለም።
ሰፊ የስበት መናኸሪያ
እዚህ አካባቢ ምንም ሆቴል አልነበረም ይላሉ - ከንቲባ አዳነች። አሁን ሦስት ሆቴሎች ተሰርተዋል። አራተኛው ከማዶ በኩል አለ። ተደማምረው 1400 የእንግዳ ማረፊያ አገልግሎት የማቅረብ አቅም አላቸው። ምርጥ ምርጥ አፓርትመንቶች በአካባቢው ተሰርተዋል። ለሕዝብ አገልግሎት ክፍት የሚሆኑ አረንጓዴ ስፍራዎችና ተቋማትም እየተዘጋጁ ነው። ፊት ለፊት ለሚ ፓርክ አለ። ሰፊ ነው። ከመስቀል አደባባይ በመቀጠል የሚጠቀስ የከተማችን ትልቅ አደባባይ ነው። ከኤግዚቢሽንና ከጉባኤ ማዕከሉ ጋር ተያይዞ ነው ስራው የሚከናወነው።
ይህም ብቻ አይደለም። የአዳራሾችና የሆቴል ግንባታዎችን ጨምሮ፣ በተጓዳኝ የሚካሄዱ የፓርክና የተለያዩ አገልግሎቶች ግንባታዎች ብዙ ናቸው። ከአዳራሾቹ አጠገብ በሁለት አቅጣጫ፣ ሰፋፊ አምፊቴአትሮች እየተገነቡና እየተዘጋጁ ነው።
ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖምና ባልደረቦቻቸው ከአየር ጥቃት ተረፉ
ከዚህ ሥር በአጭሩ ስለ አሁናዊ ሁኔታችን የተሰማኝን አወጋለሁ…
…ከምንኖረው ይልቅ የምንሰማው የሚያሳስበን ሕዝቦች ሆነናል፤ ከላመው፣ ከጣመው፣ ካጣጣምነው፣ ከቀመስነው በላይ የተነገረንን አስቀድመን እናስሰልፋለን፤ በአመክኒዮ የትምህርት ዘርፍ ‹‹The problem of proof›› ይሉት ጉዳይ አለ፤ ትክክል መሆንን የማረጋገጥ ክፍተት እንበለው መሰለኝ፤ መድረሻችን፣ ወይም ድምዳሜያችን መነሻን መሠረት ያደረገ መሆን እንዳለበት የሚተነትን ሲሆን፣ ድምዳሜ ላይ ለመድረስ ሁነኛ፣ ወይም ትክክለኛ መነሻ ሊኖረን እንደሚገባ ያትታል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ሐይማኖቶች (በርካቶቹ) ከመጡ/ከተዋወቁ ረጅም ጊዜን አስቆጥረዋል፤ ሕዝቡም በተለያዩ ሐይማኖቶች ሥር ተቻችሎ ረጅም ዓመታትን ኖሯል፤ ብሔርም ቢሆን የቆየ ጉዳይ ነው፤ ነገር ግን አልፎ፣ አልፎ በተወሰኑ ግለሰቦች ዘንድ በሐይማኖትና በብሔር ጎራ ከፍሎ መናቸፍ አለ፤ ሐይማኖት የሚያጣላን፣ ብሔር የሚያናክሰን ከሆነ፣ ‹እስከዛሬ ለምን ሳያናክስ ቆየ?› ብሎ መጠየቅ የሕዝቡ ጉዳይ ነው፤ እስከዛሬ በሠላም የኖርን ሰዎች ደርሰን የምንጣላ ከሆነ፣ ሐይማኖት ወይም ብሔር ሳይሆኑ ጥፋተኞቹ እኛው ነን።
ይኼን ሁሉ ዘመን ኖረን፣ ኖረን አሁን ላይ የምንናቸፍበት ምንም ምክንያት ሊኖር አይገባም በማለት መለስ ብሎ የኖርነውን ዘመን ማሰብ መልካም ነው፤ ስህተቶቹ ሕዝቦች ነን፤ በሶስዮሎጂ መስክ ደግሞ ‹‹Noble Lies›› የሚባል ነገር አለ፤ ዋሽቶ ማስታረቅ ዓይነት ጉዳይ ነው፤ ዋሽቼ ላስታርቃችሁ አይደለም፤ ሕጸጻችሁን አምናችሁ መነቃቅራችሁ እንድትጥሉት ለመናገር ያህል ነው። ከመስማት መኖር፣ ከመቅዳት ማጣጣም ይቀድማሉና ኑሯችሁን እመኑ።
ኑሯችንን ስለማናምን ጠንካራ ሐይማኖተኛ፣ ጠንካራ ዜጋ፣ ተቆርቋሪ ትውልድ ከማፍራት አፈግፍገናል፤ ስለ ሀገሩ የሚጮኽ እንጂ ስለ ሀገሩ የሚተጋ ማግኘት ዘበት እየሆነ መጥቷል፤ ሰሚዎች፣ ጢያራ ጋላቢዎች፣ አጉል ተስፈኞች፣ ተነጂዎች ስለሆንን እውንና ሕልማችን ተባርዘዋል፤ ጠንካራ ሕዝብና መንግሥት እንዳይኖረን ከሚያደርጉ ጉዳዮች መካከል አንዱ ይኼው አመላችን ነው።
ሕዝብን የሚቀርጸው ሕዝብ ነው፤ መንግሥትንም ቢሆን በአብዛኛው የሚቀርጸው ሕዝብ ነው፤ ሕዝቡ መንግሥትን ሥራህን ሥራ ሊለው ይገባል፤ መንግሥትን ሊመከርና ሊዘክር ይጠበቃል፤ መንግሥትን መደገፍ አንድ ነገር ነው፤ ለሀገር ዋስትና ሀገርን የሚያስቀድም መንግሥት ሊደገፍ ይገባል፤ ነገር ግን በእኛ ዘመን መንግሥትን ማበረታታት፣ መደገፍ፣ ከጎኑ መሆን… ሳይሆን እየተደረገ ያለው የመንግሥት አክቲቪስት የመሆን ዳርዳርታ ነው።
ቢቻል መንግሥትን ደግፎ፣ መንግሥትን አበርትቶ ለሕዝብ ነው አክቲቪስት መሆን የሚገባው፤ የሕዝባዊ ግዴታን መወጣት፣ መብትና ግዴታን አውቆ በሕግና ሥርዐት መተዳደር፣ ልማትን በንቃት መተግበር… መንግሥትን ከመደገፍ የሚመደቡ እና የዜግነት ግዴታ ተብለው ከሚታሰቡ ጉዳዮች መካከል ዋንኞቹ ናቸው፤ ነገር ግን ለመንግሥት ማጎብደድ፣ ለሕዝቡ ጠብ የማይል ሥራን እየሠራ ሕዝቡን የሚያንገሸግሸውን መንግሥት ሙጥኝ ማለት የአመክኒዮ ክፍተት ነው።
አሁን፣ አሁን ላይ አብዛኛው ሕዝብ በአንቂ ንግግሮች፣ በተራ ተስፋ ሰጪ ወሬዎች፣ ሐሳዊ በሆኑ አብቂ አባባሎች ታጅሎ ኑሮውን በመግፋት ላይ እንዳለ መገመት ከባድ አይደለም፤ በሚሰማው የተቀነባበረ አንቂ ንግግር ነገውን ይጠባበቃል፤ አንገሽጋሽ ኑሮው የሚነግረውን ከማመን ባለፈ የመንግሥትንና የሚዲያዎችን ተረታ፣ ተረት እየቀረደደ ይባትላል።
ማነው መባተል ዕጣ-ፈንታችሁ ነው ያለን? ማነው ጢያራ ስትጋልቡ፣ ነፋስ ስትከተሉ ከርማችሁ ኑ ያለን? በውል መንገዋለልና መንከራተት ምንድር ነው? መንግሥትም ቢሆን የተያያዘው ጉዳይ የማንቃት ሥነ-ዘዴውን ነው፤ ‹‹motivational speech›› መሳይ ነገሮች፣ ነገር ግን ከሥሌት ይልቅ ሥሜት የበዛባቸው ሥራዎችና ድርጊቶች አጥለቅልቀውናል…
…ይኼ የአንቂ ነገር ጉዳይ ሊታሰብበት ይገባል፤ መንግሥት የሀገር ማልማትና የነገን መንገድ ጥርጊያ ድርጊቱን ቸል ብሎ አንቂ ሆኖ አርፏል፤ አንቂዎች በነቂው ላይ ምቹ ሥሜትን፣ ተነሳሽነትን መፍጠር እንጂ ማጃጃል ሥራቸው አይደለም። ነቂ በአጉል ብጽዕና ታጅሎ ዛሬን ሳይኖር ነገን መጠባበቅ የለበትም። የተያያዝነው ጉዳይ ሐይማኖት አይደለምና መሬት ባለ ነገር እንጅ በተሰፈረ የአንቂ ንግግር ብቻ መወሰን ያለበት አይመስለኝም።
በበኩሌ፣ መሬት ባልረገጠ መናኛ ተስፋ አላምንም፤ በተነገረኝ ሳይሆን በኖርኩበት ልክ ነገሮችን ልመዝን እገደዳለሁ፤ እውነት የስብከት ውጤት ብቻ አይደለም፤ እውነት የሚነገረን መሸንገያ ሳይሆን፣ የምንኖረው ኑሮ ነው፤ በዚህ ዘመን ጥጋብ ረሃባችንን፣ ጥማት ቁርጥማታችንን፣ መውደቅ መነሳታችንን…መንግሥት ነው የሚነግረን፤ የምንኖረው እኛ፤ የሚነግረን ሌላ ከሆነ መጣረስ ተከትሏል ማለት ነው፤ መድኀኒት መግዣ ተወዶብኝ የምንገላታውን እኔ ነኝ የማውቀው እንጂ አድገሃል ስለተባልኩ አዎ የምልበት ምንም ምክንያት የለም፤ ኑሮዬን፣ መንገፍገፌን እኔው አውቀዋለሁና ለእኔው ተውልኝ…
ጉዳዩ የእኛው ክፍተት እንደሆነም ጭምር አድርገን መውሰድ ብልሃት ነው፤ ሕዝብ ተብለን እስከተጠራን እምነትና ተስፋችንን በመልክ፣ በመልኩ ማድረግ አለብን፤ መረጃዎችን ማጥራት፤ ምንጮችን መገምገም ግዴታ ነው፤ ለነገሩ ከመኖር በላይ ምን እውነት አለ? የኖርነውን ለመገምገም ምን አደከመን? መገምገም የቤት ሥራችን ይሁን፤ የማይገመግም ማኅበረሰብ የማሰላሰል ክፍተት እንዳለበት ይገመታል፤ ነገሮችን በቁም በውርዳቸው መሰልቀጥ መዘዙ ብዙ ነውና፣ ቆም ብሎ ማጤን ተገቢ ነው።
ከዚህ ሥር በአጭሩ ስለ አሁናዊ ሁኔታችን የተሰማኝን አወጋለሁ…
…ከምንኖረው ይልቅ የምንሰማው የሚያሳስበን ሕዝቦች ሆነናል፤ ከላመው፣ ከጣመው፣ ካጣጣምነው፣ ከቀመስነው በላይ የተነገረንን አስቀድመን እናስሰልፋለን፤ በአመክኒዮ የትምህርት ዘርፍ ‹‹The problem of proof›› ይሉት ጉዳይ አለ፤ ትክክል መሆንን የማረጋገጥ ክፍተት እንበለው መሰለኝ፤ መድረሻችን፣ ወይም ድምዳሜያችን መነሻን መሠረት ያደረገ መሆን እንዳለበት የሚተነትን ሲሆን፣ ድምዳሜ ላይ ለመድረስ ሁነኛ፣ ወይም ትክክለኛ መነሻ ሊኖረን እንደሚገባ ያትታል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ሐይማኖቶች (በርካቶቹ) ከመጡ/ከተዋወቁ ረጅም ጊዜን አስቆጥረዋል፤ ሕዝቡም በተለያዩ ሐይማኖቶች ሥር ተቻችሎ ረጅም ዓመታትን ኖሯል፤ ብሔርም ቢሆን የቆየ ጉዳይ ነው፤ ነገር ግን አልፎ፣ አልፎ በተወሰኑ ግለሰቦች ዘንድ በሐይማኖትና በብሔር ጎራ ከፍሎ መናቸፍ አለ፤ ሐይማኖት የሚያጣላን፣ ብሔር የሚያናክሰን ከሆነ፣ ‹እስከዛሬ ለምን ሳያናክስ ቆየ?› ብሎ መጠየቅ የሕዝቡ ጉዳይ ነው፤ እስከዛሬ በሠላም የኖርን ሰዎች ደርሰን የምንጣላ ከሆነ፣ ሐይማኖት ወይም ብሔር ሳይሆኑ ጥፋተኞቹ እኛው ነን።
ይኼን ሁሉ ዘመን ኖረን፣ ኖረን አሁን ላይ የምንናቸፍበት ምንም ምክንያት ሊኖር አይገባም በማለት መለስ ብሎ የኖርነውን ዘመን ማሰብ መልካም ነው፤ ስህተቶቹ ሕዝቦች ነን፤ በሶስዮሎጂ መስክ ደግሞ ‹‹Noble Lies›› የሚባል ነገር አለ፤ ዋሽቶ ማስታረቅ ዓይነት ጉዳይ ነው፤ ዋሽቼ ላስታርቃችሁ አይደለም፤ ሕጸጻችሁን አምናችሁ መነቃቅራችሁ እንድትጥሉት ለመናገር ያህል ነው። ከመስማት መኖር፣ ከመቅዳት ማጣጣም ይቀድማሉና ኑሯችሁን እመኑ።
ኑሯችንን ስለማናምን ጠንካራ ሐይማኖተኛ፣ ጠንካራ ዜጋ፣ ተቆርቋሪ ትውልድ ከማፍራት አፈግፍገናል፤ ስለ ሀገሩ የሚጮኽ እንጂ ስለ ሀገሩ የሚተጋ ማግኘት ዘበት እየሆነ መጥቷል፤ ሰሚዎች፣ ጢያራ ጋላቢዎች፣ አጉል ተስፈኞች፣ ተነጂዎች ስለሆንን እውንና ሕልማችን ተባርዘዋል፤ ጠንካራ ሕዝብና መንግሥት እንዳይኖረን ከሚያደርጉ ጉዳዮች መካከል አንዱ ይኼው አመላችን ነው።
ሕዝብን የሚቀርጸው ሕዝብ ነው፤ መንግሥትንም ቢሆን በአብዛኛው የሚቀርጸው ሕዝብ ነው፤ ሕዝቡ መንግሥትን ሥራህን ሥራ ሊለው ይገባል፤ መንግሥትን ሊመከርና ሊዘክር ይጠበቃል፤ መንግሥትን መደገፍ አንድ ነገር ነው፤ ለሀገር ዋስትና ሀገርን የሚያስቀድም መንግሥት ሊደገፍ ይገባል፤ ነገር ግን በእኛ ዘመን መንግሥትን ማበረታታት፣ መደገፍ፣ ከጎኑ መሆን… ሳይሆን እየተደረገ ያለው የመንግሥት አክቲቪስት የመሆን ዳርዳርታ ነው።
ቢቻል መንግሥትን ደግፎ፣ መንግሥትን አበርትቶ ለሕዝብ ነው አክቲቪስት መሆን የሚገባው፤ የሕዝባዊ ግዴታን መወጣት፣ መብትና ግዴታን አውቆ በሕግና ሥርዐት መተዳደር፣ ልማትን በንቃት መተግበር… መንግሥትን ከመደገፍ የሚመደቡ እና የዜግነት ግዴታ ተብለው ከሚታሰቡ ጉዳዮች መካከል ዋንኞቹ ናቸው፤ ነገር ግን ለመንግሥት ማጎብደድ፣ ለሕዝቡ ጠብ የማይል ሥራን እየሠራ ሕዝቡን የሚያንገሸግሸውን መንግሥት ሙጥኝ ማለት የአመክኒዮ ክፍተት ነው።
አሁን፣ አሁን ላይ አብዛኛው ሕዝብ በአንቂ ንግግሮች፣ በተራ ተስፋ ሰጪ ወሬዎች፣ ሐሳዊ በሆኑ አብቂ አባባሎች ታጅሎ ኑሮውን በመግፋት ላይ እንዳለ መገመት ከባድ አይደለም፤ በሚሰማው የተቀነባበረ አንቂ ንግግር ነገውን ይጠባበቃል፤ አንገሽጋሽ ኑሮው የሚነግረውን ከማመን ባለፈ የመንግሥትንና የሚዲያዎችን ተረታ፣ ተረት እየቀረደደ ይባትላል።
ማነው መባተል ዕጣ-ፈንታችሁ ነው ያለን? ማነው ጢያራ ስትጋልቡ፣ ነፋስ ስትከተሉ ከርማችሁ ኑ ያለን? በውል መንገዋለልና መንከራተት ምንድር ነው? መንግሥትም ቢሆን የተያያዘው ጉዳይ የማንቃት ሥነ-ዘዴውን ነው፤ ‹‹motivational speech›› መሳይ ነገሮች፣ ነገር ግን ከሥሌት ይልቅ ሥሜት የበዛባቸው ሥራዎችና ድርጊቶች አጥለቅልቀውናል…
…ይኼ የአንቂ ነገር ጉዳይ ሊታሰብበት ይገባል፤ መንግሥት የሀገር ማልማትና የነገን መንገድ ጥርጊያ ድርጊቱን ቸል ብሎ አንቂ ሆኖ አርፏል፤ አንቂዎች በነቂው ላይ ምቹ ሥሜትን፣ ተነሳሽነትን መፍጠር እንጂ ማጃጃል ሥራቸው አይደለም። ነቂ በአጉል ብጽዕና ታጅሎ ዛሬን ሳይኖር ነገን መጠባበቅ የለበትም። የተያያዝነው ጉዳይ ሐይማኖት አይደለምና መሬት ባለ ነገር እንጅ በተሰፈረ የአንቂ ንግግር ብቻ መወሰን ያለበት አይመስለኝም።
በበኩሌ፣ መሬት ባልረገጠ መናኛ ተስፋ አላምንም፤ በተነገረኝ ሳይሆን በኖርኩበት ልክ ነገሮችን ልመዝን እገደዳለሁ፤ እውነት የስብከት ውጤት ብቻ አይደለም፤ እውነት የሚነገረን መሸንገያ ሳይሆን፣ የምንኖረው ኑሮ ነው፤ በዚህ ዘመን ጥጋብ ረሃባችንን፣ ጥማት ቁርጥማታችንን፣ መውደቅ መነሳታችንን…መንግሥት ነው የሚነግረን፤ የምንኖረው እኛ፤ የሚነግረን ሌላ ከሆነ መጣረስ ተከትሏል ማለት ነው፤ መድኀኒት መግዣ ተወዶብኝ የምንገላታውን እኔ ነኝ የማውቀው እንጂ አድገሃል ስለተባልኩ አዎ የምልበት ምንም ምክንያት የለም፤ ኑሮዬን፣ መንገፍገፌን እኔው አውቀዋለሁና ለእኔው ተውልኝ…
ጉዳዩ የእኛው ክፍተት እንደሆነም ጭምር አድርገን መውሰድ ብልሃት ነው፤ ሕዝብ ተብለን እስከተጠራን እምነትና ተስፋችንን በመልክ፣ በመልኩ ማድረግ አለብን፤ መረጃዎችን ማጥራት፤ ምንጮችን መገምገም ግዴታ ነው፤ ለነገሩ ከመኖር በላይ ምን እውነት አለ? የኖርነውን ለመገምገም ምን አደከመን? መገምገም የቤት ሥራችን ይሁን፤ የማይገመግም ማኅበረሰብ የማሰላሰል ክፍተት እንዳለበት ይገመታል፤ ነገሮችን በቁም በውርዳቸው መሰልቀጥ መዘዙ ብዙ ነውና፣ ቆም ብሎ ማጤን ተገቢ ነው።
ብላ ያለው ተጋግሮ ይጠብቀዋል ተሸከም ያለው ታስሮ ይጠብቀዋል
ከዕለታት አንድ ቀን የገና ዕለት፤ ቤተሰብ ለእራት እየተዘጋጀ ሳለ አንድ የዘመድ ጥቁር እንግዳ ከተፍ ይላል።
“እንዴት ናችሁ?” ይላል ከደጃፍ።
“ደህና፤ እንደምን ሰነበትክ?” ይላሉ አባወራ።
“እኔ ደህና ነኝ። ዛሬ ጥቁር እንግዳ ሆንኩባችሁ”
“ኧረ ምንም አላስቸገርከንም። ዛሬ ገና እኮ ነው። መልካም ቀን መጥተሃል። ጥቂት ሰላምታ እንደተለዋወጡ፣
“እራት ተዘጋጅቷል። ና እንመገብ” ይሉትና እሺ ብሎ ይቀመጣል።
መሶቡ ቀረበ።
ዶሮው በጎድጓዳ ሳህን ከማዕድ ቤት መጣ። ዙሪያውን ከበቡ፤ ቤተሰብ። መሶቡ ተከፈተና መብላት ተጀመረ።
ቤተሰቡ ውስጥ እጅግ አስቸጋሪ፣ እጅግ ሞገደኛ ልጅ አለ። አመለኛ ነው።
ገና መብላት እንደተጀመረ እንግዳው ፊት አንድ ዕንቁላል ሲቀመጥ፣ ያ ልጅ አፈፍ አድርጎ ዋጠው።
አባት፤ “ኧ፤ አንተ ባለጌ! ከፊትህ ብላ!” አለው።
ልጁ አልተበገረም።
እንግዳው፤ “ግዴለም ተወው። ልጅ አይደለም እንዴ?” አለ።
ባለቤትየዋ ለእንግዳው አንድ የዶሮ ብልት አወጣችለት።
በጥቂት ሰከንዶች ልጅ፣ ያቺን ብልት ያለምንተፍረት ላፍ አደረገው።
አባት፤ የልጁን ክንድ ይዞ በንዴት ጠበጠበው።
እንግዳው፤ “በፍፁም አይገባም። ነውር ነው። ገበታ ላይ ልጅ አይመታም። በጊዜ መምከር ነው እንጂ መደብደብ ተገቢ አይደለም።”
የመጨረሻ ብልት ለሁሉም ወጣ። ያ ልጅ የራሱ እያለለት፣ የእንግዳውን አፈፍ አደረገ። አባት ገና ወዳፉ ሳይከተው እጁን በፍጥነት ይዞ ክፉኛ ደበደበውና ወደ እንግዳው ዞሮ፤ “ይቅርታ ወዳጄ፤ ይሄ ልጄ እጅግ ባለጌ ነው።”
እንግዳው በይሉኝታ፤ “ኧረ ይህን ያህል አላጠፋም። የእኛ ልጅ’ኮ ዶሮውን ከነድስቱ ነው ይዞት የሚሄደው!” አለ።
ይሄኔ አባወራው፤ “አይ፤ ለእሱስ ልጃችንን ደህና አርገን ቀጥተነዋል!” አሉ።
* * *
ከመሰረቱ ያልተቀጣ ከመነሻው ሥነ-ምግባር ያልያዘ ሰው፤ ውሎ አድሮ የማይመለስበት አደጋ ላይ ይወድቃል። “የተማርኩ አይደለሁም ወይ? እኔ አድነዋለሁ” ማለት በፍፃሜው አይሆንም! የኋላ ኋላ ችግር እየሆነ ዋጋ ያስከፍለናል!
አቶ ታደሰ ገብረ ኪዳን የተባሉ የሀገራችን ደራሲ በአንድ መጽሐፋቸው፤ ሚስተር ሮበርት ማክናማራ በዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ስለ አፍሪካውያን ችግር አውስተዋል። ኢትዮጵያውያንን አንድ ላይ ተሰባስበን ቢያገኙን ኖሮ፣ “በአገራችሁ ለምንድነው ረሀብ፣ ድንቁርና መታረዝና በሽታ የነገሱት? ለምንድነው ወደፊት መራመድ ያልቻላችሁት?” ብሎ መጠየቁ አይቀሬ ነበር። እኛ ደግሞ ኢትዮጵያን ለማስቀደም የምናደርገው ጥረት የሚመክነው ከቶ ለምንድን ነው? “ከጥረት ማነስ? ጥረታችንን የሚያስተባብር በመጥፋቱ? ወይስ ራሳችን ለራሳችን ፍቱን መርዝ ስለሆንን?” ብለን መጠየቅ ይገባናል።
ይህን ጥያቄ ለመመለስ ያለጥርጣሬ፣ ልብ በልብ መገናኘት ያስፈልገናል። የእኔ ማደግ የሌላው ማነስ ነው የሚለውን አስተሳሰብ አሽቀንጥረን መጣል አለብን። ሁሉን ውንጀላ መንግሥት ላይ ማነጣጠር አይገባንም። ከግለሰብ፣ እስከ ማህበረሰባት፣ ከማህበረሰብና ተቋማት እስከ መንግሥት የየራሳችንን ሙዳ መውሰድ አለብን። ሌላው ጉዳይ አለመናበብ ነው።
አለመናበብ ትልቅ አደጋ ነው። ህግ አውጪው፣ ህግ ተርጓሚውና ህግ አስፈፃሚው አካል ሲጣጣሙ ካየን የበለጠ አደጋ አለ። አለመግባባት ጠፋ ወይም ተዛባ ማለት የአገር ህልውና ሥርዓት ተዛባ ማለት ነው። የህዝብን ጥርጣሬ የሚፈበርኩ ውሳኔዎች አለመረጋጋትን ሲፈጥሩ ወደ አደጋ ያመራሉ። በሀገራችን አደጋ እንዳይፈጠር ከማድረግ ይልቅ ከመጣ በኋላ የመዝመት ባህል አለ። ለአገሪቱ ደህንነት አስጊ አካሄድ ነው።
እንደ ናይጄሪያ የሥልጣን ሹመኞች መቃብርን ገንዘብ ማስቀመጫ ማድረግ ደረጃ መድረስ፣ የአፍሪካን የሙስና ደረጃ ጣራ እያመላከተን ባለንበት ሰዓት፣ እኛስ ወዴት እያመራን ነው? ብለን መጠየቅ ይገባናል። ሐብት የማጋበስ ልማድ አንዴ ከጀመረ ማደጉን አያቆምም። በርናንድ ሾው፤ There is no little pregnancy እንዳለው ነው። (የእርግዝና ትንሽ የለውም እንደ ማለት)።
ያለጥናት የእግረኛ መንገድ ይሠራል፤ የእግረኛ መንገድ ይፈርሳል። ተሰርቶ ሊጠናቀቅ የደረሰ ግዙፍ ህንፃ ከፕላን ውጭ ነው ተብሎ ይፈርሳል። መመሪያ ይወጣል፤ ፉርሽ ባትሉኝ ይባላል። ሁሉንም መሸከሚያ ትከሻ ያለው ህዝብ ይታገሣል። ዛሬ የቀረን ከመነሻው “የማፍረስ መጠባበቂያ ህግ መደንገግ ነው!” ማንም ተጠያቂ፣ ማንም ኃላፊ የለም ለጥፋቱ።
“ድክመቶቻችንን ለማስወገድ መተራረም አስፈላጊ ነው። ነገር ግን ሒስን ስለምንጠላ ሒስ ደርዳሪን እንደ ጦር እንፈራለን። ወቀሳን በፀጋ መቀበል አናውቅበትም። ሰውን ላለማስቀየም እየተባለ ችግሮችን ሸፋፍነን ማለፍ ይቀናናል። … ማስተዳደር ማለት ረግጦ ወይም አዋርዶ መግዛት ይመስለናል። በመሆኑም የበቀል ልጆችን መፈልፈል ብሔራዊ መለያችን ሆኗል። ለችግሮቻችን መፍትሔ ሳናገኝላቸው እየቀረን፣ በችግር ላይ ችግር እየተደራረብን፣ በልማት ወደፊት መግፋት አቅቶናል። በኋላ ቀርነታችን እያንዳንዳችን ጥፋተኞች መሆናችንን አምነን መቀበል አልቻልንም። አንዳችን በሌላችን ማሳበብና እራሳችንን ነፃ ለማውጣት መቀበጣጠር እንጂ ለውድቀታችን ኃላፊነትን መውሰድ አልተማርንም” ይሉናል በዚያው መጽሐፍ። ያ መጽሐፍ ይህን ያስመዘገበን በ1999 ዓ.ም ነው። ዛሬስ? የተጠቀሱት ችግሮች በመቶ ተባዝተው ይገኛሉ። ብዙ የተዛቡ ሕግጋት ለአንድ ተረት ምቹ ሆነው እናያለን። ያንን ልብ ካላልን፣ የባሰ ችግር ውስጥ እንገባለን። ይህ ወቅታዊ ተረት፤”ብላ ያለው ተጋግሮ ይጠብቀዋል፤ ተሸከም ያለው ታሥሮ ይጠብቀዋል!” የሚለው ነው።