Administrator

Administrator

ከዕለታት አንድ ቀን፣ አንድ በዓል ቀን፣ ባልና ሚስት አንድ እንግዳ ይመጣባቸዋል፡፡ የከበደ እንግዳ! ዶሮ ወጥ ተሰርቷል፡፡ በግ ታርዷል፡፡ ቤቱ በዓል በዓል ይሸታል፡፡ ስኒ ረከቦቱ ላይ ተደርድሯል፡፡ እጣኑ ቦለል ቦለል ይላል፡፡
እንግዳውና ቤተሰቡ ግብዣውን ለመብላት አኮብኩበዋል፡፡
ራቱ ተጀመረ፡፡ በመካከል “እ!እ!እ!” የሚል የትንሽ ልጅ የለቅሶ ድምፅ ይሰማል፡፡
እንግዳው፣
“ምንድን ነው ይሄ የሚሰማው ድምፅ?” ሲል ጠየቀ፡፡
አባት፤
“አይ፣ የእኛ ልጅ ነው ተወው” አለ፡፡
እንግዳውም፤
“እንዴት እተወዋለሁ? በዓመት በዓል እንዴት ከቤተሰቡ ይለያል? የት ነው ያለው አሳዩኝ” ብሎ ድርቅ አለ፡፡
እንግዳው፤
“እንዲያውም አልበላም” አለ፡፡
“ና ላሳይህ” ብሎ ወደ ጓዳ ወሰደው፡፡
ልጁ፤ ቆጡ ላይ ታስሯል፡፡
እንግዳው በጣም አዘነ፡፡
“ምን አድርጎ ነው እንዲህ ዓይነት ቅጣት የፈፀማችሁበት?”
አባት፤
“ምንም አላደረገም፣ ግን ከልምድ እንደምናውቀው፣ ከእንግዳ ጋር ገበታ ከቀረበ እጁ ባለጌ ነው!
ከእንግዳ ፊት ብድግ ያደርጋል፡፡ ብትቆጣውም አይሰማም” አለ፡፡
እንግዳው፣
“ኧረ በጣም ነውር ነው፡፡ ግዴለም፤ ይምጣ፣ ይምጣ፡፡ እናስተምረዋለን፤ ሥነ ስርዓት፡፡” አለና አግባባቸው፡፡
ልጁ ተፈቀደለትና ከእስር ተፈታ፡፡ ከቆጡ ወረደና ገበታ ቀረበ፡፡
የዶሮ ብልት በፈርጅ በፈርጁ ይቀርብ ጀመር፡፡
ልጁ ዕውነትም አደገኛ ኖሯል፡፡
እንግዳው ፊት የቀረበውን ሁለት የዶሮ እግር በተከታታይ እያነሳ ነጨ! ከዚያ የአባቱን የፈረሰኛ ብልት አነሳ! ይሄኔ ግራ የተጋባችው እናት በቁጣ፤
“ይሄን እንዲች ብለህ እንዳትነካ፤ ነግሬሃለሁ!” ብላ ለእንግዳው ሌላ ብልት ስታቀርብ፤ ልጁ ይሄ ሊመልሰው ነው? እጁን ሰደደ፡፡ ይሄኔ እንግዳው የልጁን እጅ ቀብ አድርጎ፣ ፈጥኖ አጠንክሮ ያዘና፤ ወደ ባለቤቶቹ ዞሮ፤ “እንግዲህ፣ ሸብ አድርጉልኝ ይሄን ልጅ!” አለ፡፡ ልጁም ከሶስት የዶሮ ብልት በኋላ፣ ሸብ ተደርጎ፣ ተመልሶ ቆጡ ላይ ሰፈረ!
*          *        *
ልማድ የልጅነት አባዜ አለው፤ አድጎ ተመንድጎም ራሳችን ላይ ፎቅ ሊሰራብን ይችላል። መላቀቅ ያለብን ብዙ ልማድ አለ! ይሄ ከባህላችን፣ ከማህበራዊ ኑሯችን፣ ከፖለቲካችንና ጋር በቅርብ የተሳሰረ ነው፡፡ ስነ ልቦናዊ ግንኙነቱም ከዚሁ የሚመነጭ ነው፡፡ ይሄን ወደ አገር ጉዳይ መንዝሮ ማየት ጉዳዩን በሚገባ መሰረት ያበጅለታል፡፡ እየተዘወተሩና እየተለመዱ የሚመጡ የአገራችን ጉዳዮች ውለው አድረው፣ ጎልበተው መታየታቸው አይቀሬ ነው፡፡ ትናንሽ ዕቅዶች ወደ ትላልቅ ፈቅዶች የሚያድጉት ትናንሾቹ በአግባቡ ሲፈፀሙ ነው፡፡ ለዚያ የጊዜ ስሌት፣ የዝርዝር አያያዝና የቁጥጥርና ግምገማ ሥርዓት በአግባቡ ማዘጋጀት ተገቢ ነው፡፡ ይህን ፈፃሚውና አስፈፃሚው አካል፣ የራሱ አቅልና ብስለት ያለው ሊሆን ይገባል፡፡ እዚህ ላይ ነው እንግዲህ የራስ አመለካከት ከአገር አመለካከት ጋር ይራራቅና ጣጣ የሚያመጣው፡፡ እያንዳንዱን ሰው ቀርፆ፣ ሰው ለማድረግ አዳጋች ነው፡፡ ይህን የሚሠሩ ተቋማት እጅግ ጥቂት ናቸው፡፡ ለዚህ ብሩህ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የሲቪል ማህበራት ቁጥርም፣ አቅምም በጣም ውስን ነው፡፡ ይህ የሆነው ፋይዳቸውን ከልቡ ያመነበት ወገን ባለመኖሩ ነው፡፡ ጊዜም ባይኖር ጊዜ ወስዶ፣ ለጥያቄው መልስ መስጠት ያስፈልጋል፡፡ አማካዩ መንገድ ይሄው ነው፡፡ ከገዢው ፓርቲና ከተቃዋሚው ድርድር ባሻገር የህዝብን አስተሳሰብ የሚያሰባስብ፣ ወደ ተግባር እንዲያመራም የሚያግዝ ኃይል ያስፈልጋል፡፡
‹‹ከእናንተ ሌላ እኛም አለንኮ›› የሚል የህብረተሰብን ክፍል ማን ይታደገው ማለት አለብን፡፡ በጥቁርና በነጭ መካከል ያለውን ግራጫ መስመር፣ ስፋቱን ስለማንገነዘብ ጠቀሜታውም የዚያኑ ያህል ይሳሳብናል፡፡ ‹‹መካር የሌለው ንጉሥ፣ ለአንድ ዓመት አይነግሥ›› የሚለው አባባል፣ አበው ያለ ነገር አላሉትም፡፡ ለአመራሩ፣ ለገዢው ክፍል፣አማካሪ ያስፈልገዋል፡፡ በእርግጥ አማካሪ ሲባል በዕውቀት የረቀቀ፤ በልምድ የበለፀገና  ጊዜ ያስተማረው ሊሆን ይገባል! መንግሥት ሲቸኩል የሚያለዝበውም፣ ሲጠጥር የሚያልመው፤ ግትር ሲል የሚያላላው፣ አይዞህ ባይም፣ ገሳጭም፣ ነው የሚያሻው፡፡ የጥንት የጠዋቱ ገጣሚ ገሞራው፤ እንዳለው፡- ‹‹…ነገሩ አልሆን ብሎ፣ ሁኔታው ሲጠጥር
 ጠጣሩ እንዲላላ፣ የላላውን ወጥር…›› የሚሉ በሳሎች ያስፈልጋሉ፡፡ በመደራደር ብዙ መንገድ መሄድ ይቻላል፡፡ ነገር ግን አንድ ዕውነት መረሳት የለበትም፡፡ ማናቸውም ወገን ብቻውን በቂ አይደለም፡፡ ገና ሶስተኛም ወገን ተጨምሮ አይበቃም ብሎ ማሰብ ብልህነት ነው። ጉዳዩን መሠረታዊ የሚያደርገው የሀገራችን ችግር ስፋት ነው፡፡ የፍትሕ መጓደል፣ የዲሞክራሲ አለመብሰል፣ የሀብት አለመደላደል፣ የተቋማት ሥርዓት አለመሻሻል፣ መልካም አስተዳደር አለመታደል፣ ያልተመለሱት ጥያቄዎች መልስ አጥተው መንሳፈፍ፣ ወዘተ ምኑ ቅጡ! ለዚህ ነው አገር ሙሉ ድርጅት ቢፈጠር እንኳ የአገር ቋት አይሞላም የምንለው!
እነዚህ ሁሉ በቅጡ ቢሰባሰቡና ኢኮኖሚውን ካቀረቀረበት ቢያቀኑት ድንገት ፎቀቅ እንል እንደሁ እንጂ ነገረ-ሥራችን እንኳ ከድጡ ወደ ማጡ እየሆነብን መቸገራችን የዕለት የሠርክ ሀቅ ነው፡፡ ስለዚህ ተራው ዜጋ ‹‹የምበላው ሳጣ፣ ልጄ ጥርስ አወጣ›› ቢል አይፈረድበትም! ኑሮው ከሥረ-መሠረቱ እናሻሽልለት! በዓል በመጣ ቁጥር የሚሰቀቀው አያሌ ነው! የእኛን መጥገብ ብቻ አንይ!! ይህንን ተደራዳሪዎቹ ወገኖች፣ እነሆ ወቅቱ መጥቷልና በምን መቀነቻ አጥብቀን እንያዘው ብለው ማሰብ ይገባቸዋል፡፡ ፀፀታችንን ሳይሆን ነገርአችንን እናስብ! የመሪዎችን ጉባኤ ስናስብም የአገራችንን መረጋጋት እንፈይድ!! 

Sunday, 29 January 2017 00:00

የዘላለም ጥግ

(ዝነኞች በመሞቻቸው ሰዓት)
‹‹መጋረጃውን አውርዱት- ቧልቱ አብቅቷል››
ፍራንሶይስ ራቤላይስ (ፈረንሳዊ ፈላስፋና ኮሚክ)
“ዕድሜህን ሙሉ ሳትፀልይ በመጨረሻ ሰዓት መፀለይ ዋጋ የለውም!››
ኢታሎ ስቬቮ (አይሁዳዊ ደራሲ)
‹‹መኖር እፈልጋለሁ፤ ምክንያቱም ልሰራቸው የምፈልጋቸው ጥቂት ነገሮች አሉ››
አኔዩሪን ቤቫን
 (በመጨረሻ የህመሙ ሰዓት የተናገረው)                      
‹‹እግዚአብሄር ይቅር ይለኛል፡፡ ምክንያቱም ሥራው ነው››
ሔይንሪክ ሄይን
‹‹የደስታ ዘመኔ አክትሟል››
 (ጄምስ ዲን
የመኪና አደጋ ሊደርስበት ሲል የተናገረው)
‹‹ስንት ሰዓት ነው? ተዉት፡፡ አስፈላጊ አይደለም..››
ጃኖስ አራኒ  (ሃንጋሪያዊ ገጣሚ)
‹‹እንደ ፈላስፋ ኖሬአለሁ፤እናም እንደ ክርስትያን እሞታለሁ››
ኒያኮም ካሳኖቫ (ጣልያናዊ ጀብደኛና ደራሲ)
“ወደ ትውልድ ስፍራዬ ውሰዱኝ። የተወለድኩት ደቡብ ነው፡፡ መሞትና መቀበር የምሻውም ደቡብ ነው”
ቡከር ቲ. ዋሺንግተን
“ደህና ሁኚ … ከተገናኘን …”
ማርክ ትዌይን (ለሴት ልጁ ለክላራ የተናገረው)
(አሜሪካዊ ደራሲ)
“በመንግስተ ሰማያት ስዕል እንደሚኖር፣ በሙሉ ልቤ ተስፋ አደርጋለሁ”
ዣን-ባፕቲስቴ- ካሚሌ ኮሮት (ፈረንሳዊ ሰዓሊ)
“ቡና ስጡኝ፤ ልፅፍ ነው”
ኦላቮ ቢላክ (ብራዚላዊ ገጣሚ)
“ሚላን፡ ለመሞት እንዴት ያለ ውብ ሥፍራ ነው”
ጆን ካራዲን (አሜሪካዊ የፊልም ተዋናይ)
“ከእናንተ ውስጥ ለሰይጣን መልዕክት ያለው ካለ፣ ለእኔ ይስጠኝ፤ አሁን ላገኘው መሄዴ ነው”
ላቪና ፊሸር (በነፍስ ማጥፋት በስቅላት የተቀጣች)
“እዚህ ህመም ይሰማኛል”
ቻርልስ ደ ጎል (የፈረንሳይ መሪ)

ፍንዳታው ያስከተለው ክስተት ለጨው አምራቾች ስጋት፣ ለቱሪስቶች መስህብ ሆኗል
ከቀድሞው የበለጠ አዲስ የቀለጠ አለት ሃይቅ ተፈጥሯል

በኣፋር ክልል የሚገኘው የኤርታሌ የቀለጠ አለት ሃይቅ ባልተለመደ መልኩ በከፍተኛ ሁኔታ በመንተክተክና ሃይለኛ ፍንዳታ አስከትሎ፣ ከቀድሞው የበለጠ አዲስ የቀለጠ አለት ሃይቅ በመፍጠር በሁሉም አቅጣጫ በፍጥነት መፍሰስ መጀመሩን “ቮልካኖ ዲስከቨሪ” ድረገጽ ከትናንት በስቲያ ዘግቧል፡፡
ኤርታሌ ከዚህ በፊትም እየተንተከተከ መጠኑን በመጨመር፣ ለሁለትና ለሶስት ቀናት ከፍና ዝቅ ይል እንደበር፤ አልፎ አልፎም ከጉድጓዱ ወጥቶ በመፍሰስ፣ ተመልሶ ወደነባሩ ሁኔታው ይመለስ እንደነበር  ያስታወሰው ዘገባው፣ ከሰሞኑ ግን ያልተለመደ ከፍተኛ ፍንዳታና ፍሰት መፍጠሩን ገልጧል፡፡
“በኦሪጅንስ ኢትዮጵያ ቱር ኤንድ ትራቭል” የቱር የኦፕሬሽን ማናጀር የሆኑት የስነ-ምድር ባለሙያው አቶ እንቁ ሙሉጌታ በተለይ ለአዲስ አድማስ ትናንት እንደገለጹት፣ ከጥቅምት መጨረሻ አንስቶ ለተራዘመ ጊዜ ከነባሩ ጉድጓድ እስከ አስር ሜትር ከፍታ በመውጣትና በመውረድ፣ አልፎ አልፎም ከጉድጓዱ አልፎ ሲፈስ የቆየው ኤርታሌ፣ ጥር 8 ቀን 2009 ዓ.ም ግን ባልተለመደ ሁኔታ ተፈጥሮውን ቀይሮ፣ ከፍተኛ ፍንዳታ በመፍጠር ብዛት ያለው የቀለጠ አለት በሁሉም አቅጣጫ መፍሰስ ጀምሯል፡፡
ይህ አዲስ ክስተት ከቀለጠ አለቱ የፍሰት ፍጥነት፣ መጠንና ከአለቱ የመረጨት ወሰን አንጻር እጅግ ያልተመለደና ከፍተኛ እንደሆነ የገለጹት አቶ እንቁ፣ ኤርታሌ እስከ 20 ሜትር ከፍታ እየዘለለ በመረጨት፣ በሰከንድ 50 ሜትር ኪዩብ የቀለጠ አለት እያወጣ በሁሉም አቅጣጫ በሰዓት 55 ኪሎ ሜትር ፍጥነት መፍሰሱንና 3 ሜትር ውፍረት ያለው ይህ የአለት እሳት ወንዝ በአራት ቀናት ቆይታው ጉድጓዱ እስከ 700 ሜትር ርቆ መጓዙን ተናግረዋል፡፡
ክስተቱ ለአራት ቀናት ያህል በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ በኋላ፣ ጥር 14 ቀን 2009 ዓ.ም ወደ ደቡብ አቅጣጫ “አቶሚክ ኤክስፕሎሲቭ” የተባለ ሃይለኛ ፍንዳታ መፍጠሩን የጠቆሙት አቶ እንቁ፣ ይሄን ተከትሎም በኤርታሌ የነበሩት ሁለት የቀለጠ አለት ሃይቆች በመካከላቸው ሰፊ ስንጥቅ በማስከተል ሌላ አዲስ የቀለጠ አለት ሃይቅ ጉድጓድ መፍጠራቸውን አስረድተዋል፡፡
አዲስ የተፈጠረው ጉድጓድ ከነባሮቹ በስፋቱ የበለየና ብዛት ያለው የቀለጠ አለት የያዘ መሆኑን የጠቆሙት ባለሙያው፤ ከአዲሱ ጉድጓድ እየገነፈለ በየአቅጣጫው ለቀናት ሲፈስ የቆየው የቀለጠ አለት ከትናንት በስቲያ መብረድ መጀመሩንም ገልጸዋል፡፡
ነዋሪዎች መሰል ተፈጥሯዊ ክስተቶች ከሚታዩባቸው አካባቢዎች ሰዎች በ150 ኪ.ሜትር ያህል መራቅ እንዳለባቸው ይመከራል ያሉት ባለሙያው፣ የአፍዴራ የጨው ማምረቻ ከኤርታሌ በ50 ኪሎ ሜትር ያህል ርቆ የሚገኝ መሆኑን አስታውሰው፣ ተመሳሳይ ሁለት እና ሶስት ክስተቶች ቢከሰቱ በጨው አምራቾች ላይ ጉዳት ሊያስከትል እንደሚችል ገልጸዋል፡፡ ከኤርታሌ በሌላ አቅጣጫ እስከ 50 ኪ.ሜትሮች ርቀው በሚገኙ ትንንሽ የአፋር መንደሮች የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችም፣ የአደጋ ስጋት ክልል ውስጥ በመሆናቸው ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባልም ብለዋል፡፡
ይህ ክስተት ለጨው አምራቾችና ለአካባቢው ነዋሪዎች ደህንነት ስጋት ቢሆንም፣ ለቱሪዝሙ ግን አዲስ ተጨማሪ መስህብ መፍጠሩ ተነግሯል፡፡  በርካታ አለማቀፍ የቱሪዝምና የተፈጥሮ ክስተቶችና አደጋዎች ላይ የሚሰሩ ድረ-ገጾችና ተቋማት ያልተመለደውን የሰሞኑ የኤርታሌ ክስተት በስፋት መዘገባቸውን ተከትሎ፣ ወደ አካባቢው የሚያቀኑና ለመጎብኘት ያቀዱ ቱሪስቶች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱንም መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
ከአገሪቱ የቱሪስት መዳረሻዎች አንዱ የሆነውና በአብዛኛው ከመስከረም እስከ መጋቢት ባሉት ወራት በቱሪስቶች የሚጎበኘው  ኤርታሌ፣ በእነዚህ ወራት በቀን በአማካይ እስከ 40 በሚደርሱ ቱሪስቶች እንደሚጎበኝ ይገመታል፡፡

ከደረጃ ዝቅ የተደረጉ፤ ከሥራና ደመወዝ የታገዱና የተሰናበቱ ይገኙበታል
የዋና ሥራ አስኪያጁ አካሔድ የፓትርያርኩን መመሪያ የጣሰ ነው፤ ተብሏል
    ከሚገባቸው በላይ የሰው ኃይል ክምችት በመያዝ እየተጨናነቁ በሚገኙት የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት፣ የሚካሔደው የሓላፊዎችና የሠራተኞች ዝውውር እንዲሁም ከሥራ የማገድና የማሰናበት ርምጃ በአስቸኳይ እንዲጣራ፣ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አዘዙ፡፡
ፓትርያርኩ ትእዛዙን የሰጡት፣ በመ/ር ጎይትኦም ያይኑ ዋና ሥራ አስኪያጅነት የሚመራው የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት፣ ከሕግና ሥነ ሥርዓት ውጭ የአስተዳደር በደል አድርሶብናል፤ የሚሉ የሃያ አመልካቾችን አቤቱታ፣ በአካልና በጽሑፍ ከተቀበሉ በኋላ በልዩ ጽ/ቤታቸው በኩል በጻፉት ደብዳቤ ነው፡፡
ከአስተዳዳሪነት ጀምሮ ባሉት የጽ/ቤት ሓላፊነቶች የሚሠሩት አቤቱታ አቅራቢዎቹ፦ ደመወዝ፣ አበልና የሥራ ደረጃን በሚቀንስ እንዲሁም፣ የተዛወሩበትን የሥራ መደብ፣ ደመወዝና አበል በማይጠቅስ ውሳኔ ተገቢ ያልሆነ ዝውውር ተፈጽሞብናል፤ ባልተጣራና ባልተወሰነ የሥራ ግድፈት ከሥራና ደመወዝ እንድንታገድና እንድንሰናበት በማድረግ በደል ደርሶብናል፤ በሚል ማመልከታቸውንና ፍትሐዊ ውሳኔ እንዲሰጣቸው መጠየቃቸውን ልዩ ጽ/ቤቱ በደብዳቤው ገልጿል፡፡
ሠራተኞቹ፣ ከአንዱ አጥቢያ ወደ ሌላው እንዲዛወሩ፤ ከሥራና ደመወዝ እንዲሰናበቱ የተደረገበት ማስረጃ ተገቢነት፣ ካቀረቡት አቤቱታና ከቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግጋት አንፃር እየተገናዘበ በሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ እንዲመረመር ፓትርያርኩ አዘዋል፤ አፈጻጸሙም፣ ሕጋዊውን አሠራር ያልተከተለ ኾኖ ሲገኝ፣ የሀገረ ስብከቱ አስተዳደር በምልዓተ ጉባኤ አስተካክሎና አርሞ አፋጣኝ ውሳኔ በመስጠት፣ ውጤቱ በአስቸኳይ እንዲገለጽላቸው በመመሪያቸው ማሳሰባቸውንም ልዩ ጽ/ቤቱ አስታውቋል፡፡
አቤቱታው፣ ባለፈው ኅዳር ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ቀርቦ የታየና ሀገረ ስብከቱ በሕጉ መሠረት አስቸኳይ አስተዳደራዊ ውሳኔ እንዲሰጥ አስቀድሞ የታዘዘበት ከመሆኑም በላይ፤ ለሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ ለሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንና ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴርም ደርሶ በሚመለከተው አካል መፍትሔ እንዲያገኝ ሲጠየቅ መቆየቱ ተወስቷል፡፡
አቤት ባዮቹ፣ በተለይ ለሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በጻፉት ደብዳቤ፣ የሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ፥ ከሕገ ወጥ ዝውውር በተጨማሪ፣ የሙስና ተግባራትን እንደሚፈጽሙና ያለምንም ጥፋት ከባድ ማስጠንቀቂያ የጻፉባቸውም ይህን በመቃወማቸውና የመብት ጥያቄ በማንሣታቸው እንደኾነ በቅሬታቸው ጠቅሰዋል፡፡
በሌላ በኩል፣ አቤቱታውን የሚያጣራ ስምንት አባላት ያሉት ቡድን ባለፈው ማክሰኞ በዋና ሥራ አስኪያጁ ተቋቁሞ ጉዳዩን የሚመለከት ሰነድ በማስቀረብ ሲያጠና መቆየቱን የጠቀሱ የሀገረ ስብከቱ ምንጮች፤ የማጣራቱ ውጤትም፣ ከትላንት በስቲያ በተካሔደውና ዋና ሥራ አስኪያጁን ጨምሮ 11 የዋና ክፍል ሓላፊዎች በተገኙበት የአስተዳደር ጉባኤ ታይቶ ውሳኔ ማግኘቱን ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡
ምንጮቹ እንደተናገሩት፣ ከኻያዎቹ አቅራቢዎች መካከል፣ ሦስት የአድባራት ጸሐፊዎች፣ በዝውውሩ የተቀነሰባቸው ደመወዝ ካለ ባሉበት እንዲስተካከል፤ ታቦት ታቅፈው ሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ድረስ ይዘው በመምጣት ከፍተኛ ድፍረትና የቀኖና ጥሰት ፈጽመዋል በሚል ከሥራና ደመወዝ በተሰናበቱ አንድ አለቃና ሦስት ሠራተኞች ላይ የተወሰደው የማሰናበት ውሳኔ ባለበት እንዲጸና፤ የተቀሩት 13 ሠራተኞችም፣ ይቅርታ እየጠየቁ በተገኘው ቦታ እንዲመደቡ መወሰኑን አስታውቀዋል፡፡
በበርካታ የሰነድ ማስረጃዎች የተደገፈውን አቤቱታ ማጣራት የሚገባው፣ 14 አባላት ያሉት የሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ እንጂ፣ ዋና ሥራ አስኪያጁ በራሳቸው መርጠው ያቋቋሙት ቡድን አለመኾኑን የሚጠቅሱ ወገኖች በበኩላቸው፤ አካሔዱ፣ የፓትርያርኩን መመሪያ እንደሚፃረር፤ በጥቅማጥቅምና በአቅም ማነስ የተሠሩ የጽ/ቤቱን ስሕተቶች ለመሸፋፈን የተደረገ ሙከራ በመሆኑ እንደሚቃወሙት ገልጸዋል፡፡  
በሕገ ቤተ ክርስቲያን በሰፈረው የልዩ ሀገረ ስብከት ድንጋጌ መሠረት፣ በፓትርያርኩ የበላይ ሓላፊነት የሚመራው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት፤ በእገሌ ሥራና በጀት እየተባሉ መዋቅርን፣ ዕውቀትን፣ ልምድንና በጀትን ማዕከል ባላደረጉ የዝውውር፣ ቅጥርና ሽግሽግ አሠራሮች ጋራ ተያይዘው በሚነሡ ውዝግቦች እየታወከ እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡ ራሱን ችሎ ሊቀ ጳጳስ እንዲመደብለትና ሓላፊነትና ተጠያቂነት ያለበት ጠንካራ መዋቅርና አደረጃጀት እንዲዘረጋለት የተላለፉ ውሳኔዎች አፈጻጸምም መጓተቱን ምንጮች ጨምረው ገልጸዋል፡፡

የዛምቢያ መንግስት በህገወጥ መንገድ ወደ ግዛቴ ገብተዋል በሚል አስሯቸው የነበሩና በቅርቡ ይቅርታ ያደረገላቸውን 147 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከትናንት በስቲያ ወደ አገራቸው መመለሱን አስታውቋል፡፡
እነዚሁ 145 ወንድ እና 2 ሴት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በአለማቀፉ የስደተኞች ድርጅት ድጋፍ ባለፈው ሃሙስ ተሲያት ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ማድረጉን፣ የአገሪቱ የስደተኞች ጉዳይ ቢሮ ማስታወቁን ዥንዋ ትናንት ዘግቧል፡፡

   በኩዌት አሠሪዋን ገድላለች፤ የተባለችውን ኢትዮጵያዊት የቤት ሠራተኛ ጨምሮ 7 ሰዎች በስቅላት መቀጣታቸው፣ ከአለማቀፉ ማህበረሰብ ውግዘትን እያስተናገደ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መንግስት በጉዳዩ ላይ እስካሁን ዝርዝር ማብራሪያ ባይሰጥም፣ በኩዌት የሚገኘው ኤምባሲ የሐዘን መግለጫ በድረ ገፁ አሰራጭቷል፡፡
ስሟ በውል ያልተገለፀው ኢትዮጵያዊቷ ወጣት፣ ከ6 ዓመት በፊት አሠሪዋን ገድላለች፤ በሚል የተፈረደባት የሞት ፍርድ፣ ረቡዕ ጥር 17 ቀን 2009 ዓ.ም፣ በሀገሪቱ ማዕከላዊ እስር ቤት በስቅላት ተፈፃሚ ሆኗል፡፡
በኩዌት የኢትዮጵያ ኤምባሲ በበኩሉ፣ በድረ ገፁ ባሰራጨው የሐዘን መግለጫው፣ አሠሪዋን በመግደል ወንጀል ጥፋተኛ ነች፣ በማለት የኩዌት የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በሞት እንድትቀጣ ያስተላለፈውን ብያኔ ተከትሎ ለከፍተኛ ፍ/ቤት ይግባኝ ቀርቦ የነበረ መሆኑን በመጥቀስ፣ ይግባኙ ተቀባይነት በማጣቱ የተላለፈው የሞት ፍርድ እንዲፀና በመወሰኑ ተፈፃሚ መሆኑን አብራርቷል፡፡ ይሁንና የሞት ፍርዱ ረቡዕ ዕለት ከመፈፀሙ በፊት ኤምባሲው ከዋናው እስር ቤት ኃላፊ ጋር በመነጋገር፣ የሀገሩ አሰራር በሚፈቅደው መሰረት፤ ፍርደኛዋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታይ በመሆኗ የኑዛዜና የንስሐ ሥርአት እንዲፈፀምላት ማድረጉን ኤምባሲው አስታውቋል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዝርዝር ማብራሪያ ለማግኘት በተደጋጋሚ ጥረት ብናደርግም፣ ቃል አቃባዩ አቶ ተወልደ ሙሉጌታ፣ ስብሰባ ላይ እንደሆኑ በአጭር የሞባይል መልዕክት በማሳወቃቸው ያደረግነው ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡  የሃገሪቱን ልኡል ሼክ ፋይሠል አብዱላህ አልሳባህ ጨምሮ አንዲት የሃገሬው ዜጋ፣ 2 ግብፃውያን፣ 1 ባንግላዴሽና አንድ ፊሊፕኖ ሰው በመግደል፣ አስገድዶ በመድፈርና ሰው በመደብደብ ወንጀል ተከሰው ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው የተወሰነባቸው የሞት ፍርድ በስቅላት ተፈፃሚ ሆኖባቸዋል፡፡
የሃገሪቱ ልኡል በሞት እንዲቀጣ የተወሰነበት፣ የአጎቱን ልጅ በመግደልና ህገ ወጥ መሳሪያ ይዞ በመገኘት በሞት ሲቀጣ፤ ቀሪዎቹ ሰው በመግደልና አስገድዶ በመድፈር ወንጀል ነው፣ በስቅላት እንዲቀጡ የተበየነባቸው፡፡
የሞት ፍርዱን መፈፀም ተከትሎ፣ አምንስቲ ኢንተርናሽናል፣ ሂውማን ራይትስዎች እና ሌሎች የሠብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ድርጊቱን አውግዘዋል፡፡
የፈሊፒንስ መንግስት በበኩሉ ዜጋውን ከቅጣቱ ለማዳን ሰፊ ጥረት ማድረጉን፣ ነገር ግን እንዳልተሳካላት አስታውቋል፡፡ በተያያዘ ዜና፣ ሁለት ዜጎቻቸውን በቅጣቱ ያጡት ባንግላዴሻውያን፣ ከትላንት በስቲያ የሟቾችን ፎቶ ግራፍ በመያዝ ለተቃውሞ አደባባይ ወጥተው እንደነበር ተዘግቧል፡፡

Sunday, 29 January 2017 00:00

የፖለቲካ ጥግ

· በእርግጥ ነፃ ፕሬስ ጥሩ ወይም መጥፎ ሊሆን
ይችላል፡፡ ግን ያለጥርጥር ነፃነት በሌለበት
ፕሬሱ መጥፎ ከመሆን በቀር ሌላ ምንም
ሊሆን አይችልም፡፡
አልበርት ካሙ
· በዲሞክራሲያዊ መንግስት ጠንካራ የፍትህ
ሥርዓት ሊኖርህ ይገባል፡፡ የመናገር ነፃነት
ያስፈልጋሃል፡፡ የጥበብ ነጻነትም እንዲሁ፡፡ ነፃ
ፕሬስም የግድ ነው፡፡
ቲዚፒ ሊቭኒ
· ነፃ ፕሬስ የዲሞክራሲ የማዕዘን ድንጋይ ነው፤
ይሄ ምንም አያጠያይቅም፡፡
ሁግ ግራንት
· ነፃ ፕሬስ የተከበረ ፕሬስ ሊሆን ይገባል፡፡
ቶም ስቶፓርድ
· ነፃ ፕሬስን በእጅጉ እደግፋለሁ፤ ነገር ግን
አስተማሪና መረጃ ሰጪ ሊሆን ይገባል፡፡ በዚህ
ረገድ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ፕሬሱ ወድቋል ብዬ
አምናለሁ፡፡
ሳሙኤል ዳሽ
· ፕሬሱ ዋነኛ የርዕዮተ ዓለም መሳሪያችን ነው፡፡
ኒኪታ ክሩስቼቭ
· የአሜሪካ ህዝብ ፕሬዚዳንቱን በፕሬስ በኩል
ብቻ ሳይሆን በቀጥታ የማየትና አስተያየቱን
የመስማት መብት አለው፡፡
ሪቻርጅ ኤ ም. ኒ ክሰን
· ራስን በማጥፋትና በሰማዕትነት መካከል
ያለው ብቸኛ ልዩነት የፕሬስ ሽፋን ነው፡፡
ቹክ ፓላህኒዩክ
· ብሪቴን በጣም ትንሽ አገር ሆና፣ በጣም ብዙ
ፕሬስ ያላት አገር ናት፡፡
ዴቪድ ሆክኔይ
· ሁሉም ፕሬዚዳንት ፕሬሱን አይወደውም፡፡
ሔለን ቶማስ
· እውነቱን ለመናገር ፕሬሱን አላነብም፡፡ ምን
እያሉ እንደሆነ አላውቅም፡፡
ሴሬና ዊሊያምስ
· የፕሬስ ነጻነት የተረጋገጠው የፕሬስ ባለቤት
ለሆኑቱ ብቻ ነው፡፡
ኤ.ጄ.ላይብሊንግ  

Wednesday, 25 January 2017 07:44

የፍቅር ጥግ

- የመጀመሪያ ፍቅርን የሚያህል ነገር የለም፡፡
   ኒኮላስ ስፓርክስ
- ፍቅር ቃል የመግባት ጉዳይ አይደለም፤ የማመን ጉዳይ እንጂ፡፡
   አናሚካ ሚሽራ
- የመጀመሪያ ፍቅሬ፡፡ እሱ የመጀመሪያ ተወዳጅ ስህተቴ ነበር፡፡
  ሎውረን ብላክሌይ
- የመጀመሪያ ፍቅር ሁልጊዜ ልዩ ቦታ ይይዛል፡፡
   ሊ ኮኒትዝ
- የመጀመሪያ ፍቅር አደገኛ የሚሆነው የመጨረሻም ጭምር ሲሆን ብቻ ነው፡፡
   ብራኒስላቭ ኑሲክ
- የሴት ልጅ ደስታ የሚጀምረው በመጀመሪያ ፍቅሯ ነው፡፡ ከዚያም ያከትማል፡፡
   ጆርጅ በርናርድ ሾው
- እኛ፤ ይገባናል ብለን የምናስበውን ፍቅር እንቀበላለን፡፡
    ስቲፈን ቸቦስኪ
- አፍቃሪ ልብ ሁልጊዜ ወጣት ነው፡፡
    የግሪኮች አባባል
- ቤተሰብ ከየት ይጀምራል? ጥንስሱ የሚጀምረው ኮቦሌው ከኮረዳዋ ጋር በፍቅር ሲወድቅ ነው፡፡ እስካሁን ሌላ የላቀ አማራጭ አልተገኘም፡፡
    ሰር ዊንስተን ቸርችል
- የ40 ዓመት ጎልማሳ ከ20 ዓመት ኮረዳ ጋር በፍቅር ሲወድቅ፤ እየፈለገ ያለው የእሷን ወጣትነት ሳይሆን የራሱን ነው፡፡
    ሊኖሬ ኮፊ
- ፍቅር እንደ አበባ ነው፤ አንዴ ከቀጠፍከው በኋላ ቀስ እያለ ይጠወልጋል፡፡
    ያልታወቀ ጸሃፊ

Wednesday, 25 January 2017 07:33

ማራኪ አንቀፅ

   ሊብራዎች ብልግና አይወዱም፡፡ ሰው ያፈቅራሉ፡፡ ብዙ ህዝብ ወደተሰበሰበበት መሄድ ግን አይፈቅዱም፡፡ እንደ ሰላም ምልክቷ ጨዋ እርግብ፣ የተጣላ ማስታረቅ ይወዳሉ፤ ክርክር ይሆናቸዋል፡፡ ጥሩ ባህሪ ያላቸው ናቸው እና አስደሳቾች ናቸው፡፡ አንዳንዴ ግን ለንቦጫቸውን የሚጥሉ አኩራፊዎችና ትዕዛዝ የማይቀበሉ ለጋሚዎች ይሆናሉ፡፡ በአንድ በኩል እጅግ በጣም ብልሆች ሲሆኑ በሌላ ጎናቸው ደግሞ እጅግ በጣም ገራገርና የዋሆች እንዲሁም ድልሎች ናቸው፡፡ አነብናቢዎች ቢሆኑም ጥ ሩ አ ድማጮችም ይሆናሉ፡፡ ግራ ተጋቡ እንዴ? ራሳቸውም በራሳቸው እስከሚገረሙ ድረስ ሊብራዎች ጠባያቸው ይዋዥቃል፡፡ ብዙ ሰው ሊብራዎች “ፍቅር ናቸው፤ ውበት ናቸው፣ ጣፋጭ ናቸው፣ ብርሃን ናቸው” ይላል፤ ጥሩ ነው። ግን በወርቅ የፍትህ ሚዛን እንደሚመሰሉም ማስታወስ ይጠቅማል፡፡ ሚዛኑ በቀላሉ ይዋዥቃል። ተስተካክሎ እንደቆመ ረግቶ ላይገኝ ይችላል፡፡ የሚዛን ሁሉ ተግባሩ ተስተካክሎ መቆም ነው፡፡ ተስተካክሎ ለመቆም ምን ይሆናል? ይዋዥቃል፡፡ አንዴ በዚህ፣ አንዴ በዚያ ተስተካክሎ እስከሚቆም ይዋዥቃል፡፡ ስለዚህ ሊብራን “ፍቅር፣ ውበት፣ ጣፋጭና ብርሃን” ሆኖ የሚያገኙት እድሜ ልክዎን ሳይሆን ለግማሹ ጊዜዎ ነው፡፡ በግማሹ አናዳጅ፣ ቁንጥንጥና ግራ የተጋባ ሆኖ ሊያገኙት ይችላሉ፡፡ የሊብራ ስሜት እንደሚዛን መዋዠቅ ጠባዩ ነው፡፡ ፍቅር ሰጠት ሲያደርጉት ግን ወዲውኑ ይስተካከላል፡፡ አካላዊ መልካቸውም እንደ ጠባያቸው ይስባል፡፡ ዲምፕል አላቸው፡፡ከዚያ
ይጀምሩ እና ቶሎ በግልጽ ወደማይታየው ውበታቸው ይግቡ፡፡ ዲምፕሉ በጉንጫቸው ላይ ካልታየ በእግራቸው ላይ መገኘቱ አይቀርም፡፡ ዲምፕል ሊብራ ባልሆኑ ሰዎች ላይም የሚገኘው የቬኑስ ተፅዕኖ ካረፈባቸው ነው፡፡ ዲምፕሉን ካገኙ በኋላ ፊታቸውን በአጠቃላይ
ይመልከቱ፣ አስደሳች ውበት ይታይዎታል፡፡ ሲቆጡ እንኳ ገራምነት ይነበብባቸዋል፡፡ ድምጻቸው ጣፋጭና ኮለል፣ እንደሞል ደወል ጥርት ያለ ነው፡፡ ሊብራዎች “ጠላሁህ!፣ ጥርስህን ላረግፍልህ ነው!” ብለው በጥሩ የድምጽ ቃና በግልጽ የሚናገሩ፣ በዓለም ላይ ልዩ የሆኑ ሰዎች ናቸው፡፡ ከንፈሮቻቸው ውቦችና ጉንጮቻቸውም እንደ ቸኮሌት የሚያጓጉ ናቸው፡፡ ሴቶቹም ወንዶቹም ቆንጆዎች ናቸው፡፡ ኮከባቸው ቬኑስ የውበት ተምሳሌት ናት፡፡ ሊብራ ሴቶች ሱሪ መልበስ ይወዳሉ፡፡ ወንዳ ወንድ ናቸው ማለቴ አይደለም፡፡ የተለየ ለዛ ያላቸው ልስልስና ወላንሳ ሴቶች ናቸው፡፡ ደም ግባታቸው ይማርካል፤ ፈገግታቸው ያቀልጣል፤ ሙሉ በሙሉ ካረፈብዎ ወከክ፣ ትርክክ ነው የሚሉት፡፡ ፀጉራቸው ከርል ነው፤ የታውረስ ተጽእኖ ካላረፈባቸው በስተቀር ወፍራሞች አይደሉም፡፡ ሌላው የሚስብዎ ነገር ደስ የሚል ሳቃቸው ነው፡፡ አንዴ ከሰሙት
አይረሳዎትም፡፡ አሁን ባለ ዲምፕልና ማራኪ ሆኖ መወለድ፣ ፍትሀዊና ተፈቃሪ መሆን፣ አስደሳችና በቀላሉም ተደሳች ሆኖ የመፈጠር ፀጋ መሆኑን ሳይረዱ አልቀሩም፡፡ ጨዋነት እና ብልህነት፣ ግርማ ሞገስ እና ሌሎችን የሚገነዘብ /አንደርስታንድ የሚያደርግ/ ኅሊናም የፈጣሪ ስጦታዎች መሆናቸውን ተገንዝበዋል፡፡ ሊብራ የወርቅ ሚዛኑ ሲስተካከልለት እነዚህን ሁሉ ይጣበሳል፡፡ ይህም ሰማያዊ መልዓከ ምድር ላይ የማግኘት ያህል የሚያስደስት ነገር ነው። ችግሩ ሚዛኑ ሲዋዥቅ ነው፤ ቢሆንም ፍቅር ሰጠት ሲያደርጉ ፈጥኖ ይስተካከልለታል፡፡
 
    (ከተርጓሚ አብርሃም ጎዝጉዜ “የፀሐይ ምልክቶች” የተሰኘ የአስትሮሎጂ መፅሃፍ ላይ የተቀነጨበ፡፡ ተርጓሚው የፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳን
   “The True Origin of Oromo and Amhara” የተሰኘ አነጋጋሪ መፅሐፍ “እውነተኛው የኦሮሞና
   የአማራ የዘር ምንጭ” በሚል የተረጎሙ ናቸው፡፡

     የ3000 ዘመን ታሪክ ባለቤት ከሆነችው ኢትዮጵያ አንድ ፍልስፍና ይመዘዛል፡፡ ይኸውም በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ብቅ ያለው የኢትዮጵያ የፍልስፍና አባት ለማለት የምንደፍርለት ዘርዐ ያዕቆብ ነው፡፡ በዓለም ላይ የተከሰቱ ርዕዮተ ዓለሞችን ሁሉ የፍልስፍና ውጥንና ውጤት መሆናቸው እሙን ነው፡፡ የዘርዐ ያዕቆብ ምናብ ብቻ ሳይሆን ዘመን ተሻጋሪ የሆኑ ጥብቅ ሀሳቦች የተነሱበት እውነት፤ ሐተታ ዘርዐ ያዕቆብ የረቀቁ የበለጸጉና የጠለቁ ትንታኔዎችን በመስጠት ነፍሳችንን ይክሰዋል፡፡ ለፍልስፍና አእማድ የሆነው ዘርዐ ያዕቆብ፤ “ማንነትን በበጎ ነገር ማጠር” በማለት የሚያቀነቅነው አስተሳሰብ ውስጥ የሚበቅሉ የእውነት ምንጮችን እናገኝበታለን፡፡ በዚህም ወደ ታላቁ የጥበብ ምንጭ እንመጥቃለን፤ ውለታውን ለማስታወስ፣ ኢትዮጵያዊነቱን ለመመስከር ዝክረ ዘርዐ ያዕቆብ ተዘጋጅቷል፡፡

ውልደትና እድገት
ዘርዐ ያዕቆብ የክርስትና ስሙ ሲሆን የዓለም ስሙ ወርቄ እንደሆነ በአለቃ ያሬድ ፈንታ “ሐተታ ዘርዐ ያዕቆብ ወልደ ሕይወት” መግቢያ ላይ ተጠቅሷል፡፡ እንደ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ዘርዐ ያዕቆብ በገጠር ስለመወለዱ ታሪኩን የሚዳስሱ የተለያዩ ጽሑፎች ያስረዳሉ፡፡ ከገበሬ ቤተሰብ መገኘቱን በገዛ አንደበቱ የሚናገረው ዘርዐ ያዕቆብ፤ በ1592 ዓ.ም ወደዚህ አለም መጥቷል፡፡ ይሄ ዘመን ደግሞ የአፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመነ መንግስት መሆኑ ነው፡፡
እንደ ቅዱስ ያሬድ፣ እንደ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ለትምህርት የሰነፈ ባይሆንም የድምጹ ሻካራነትና የተማሪ ቤት ወዳጆቹ ስላቅ፣ ሰዋሰውና ቅኔ ለመማር ፊቱን እንዲያዞር ያስገደደው ሲሆን እግዚአብሔርም ጥበቡን እንደገለፀለትም ደስተኛ እንደሆነ መፅሀፈ ፍልስፍና ላይ ተጠቅሷል፡፡ ለንባብና ለማወቅ ያደረገውን ጥረት ሳንቆጥር፣ ዘርዐ ያዕቆብ 14 ዓመት ከሦስት ወር ለትምህርት በመጠቀም የትምህርትን ህልውና ለማሳየት ጥረት አድርጓል፡፡ ያውም በዚያ ዘመን!!

ትዳርና ልጅ
አፈንጋጩ ዘርዐ ያዕቆብ ከፍልስፍና ልጆች የሚቃረነው የትዳር ጓደኛ ምርጫው ጋብቻውን አክባሪነቱ ከመረዳት እንጀምርና ከእርሱ እውቀትና ምጥቀት የማትስተካከለዋን የሀብቱ ቤተሰብ ለማግባት ሲጠይቅ፣ ሲደራደር እሺኝታ ሲያገኝ፣ ሚስቱን ለማስደሰት ሲጥር እንመለከታለን፡፡ በእርሱ አንደበት፤ “ይህ መንገድ ወደ አበሳ ይስባልና ሴት የሌለችው ወንድ ብቻውን ይኖር ዘንድ እንደማይገባው አወቅኩ” ሰዎች ተፈጥሮአቸውን ክደው ሊኖሩ አይገባቸው እያለ ይሞግታል፡፡ ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም ከሚለው መለኮታዊ ሃሳብ ጋር ስምሙ የሚያደርገው፣ እምነቱን በዘመን ተሻጋሪ ስብከቱ ሲያስጠነቅቅ፡- የባልና ሚስት ድንበርና ክልሉ ፍቅር መሆን እንዳለበትም አጽእኖት ይሰጣል፡፡
መልከ ጥፉ እንደሆነች የሚመሰክርላት ሂሩት፤ ምግባሯን ልባምነቷን መመዘኛ ማድረጉ፣ ጠንካራ የሆነ የፍቅር እምነት እንዳለው ለማሳየት ምስክር ይሆናል፡፡ ከአራት ዓመት በኋላ ልጁ ሀብተ እግዚአብሔርን መውለዱ፣ ዘርዐ ያዕቆብ የቤተሰብ ምጣኔን የያኔ ጀምሮታል ለማለት ያስደፍራል። ከፅሁፍ ስራ ባገኘው ሀብት ቤት ከሰራና የቤት እንስሳ ከገዛ በኋላ መውለዱ ለዚህ ማሳያ ነው፡፡ ወደ ምንኩስናው የሸፈተውን የልጁን ልብ መልሶ፣ የሦሶት ልጆች አያት መሆን መቻሉ ለህጋዊነት የላቀ ዋጋ እንደሚሰጥና እምነቱ እንደሆነ ያረጋግጥልናል።

ፍልስፋና
ዘርዐ ዕቆብ ወደ ፍልስፍና የገባባት ምክንያት ምንም ይሁን ምን ተለምዶአዊ አኗኗሮችን በመገርሰስ፤ ባልዘመነ ዘመን፣ ዘመናዊ ጥያቄዎችን በማንሳት ምላሽ ይሰጣል፡፡የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ የተመለከታቸው “ሐተታ ዘርዐ ያዕቆብ” ሆነ “መጽሐፈ ፍልስፋና” ሥለ ፈላስፋው ያለንን ግንዛቤ ከማሳደግና እውቀት ከማዳበር በዘለለ ተቃርኖ የላቸውም፡፡ የዘርዐ ዕቆብ የምርምር ፍልስፋና፤ ወሰን ያልተበጀለትና ሁሉን አቀፍ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል፡፡ በሁለቱም መጽሐፎች ላይ ፈላስፋው በጥልቀት የተመለከታቸውን የእግዚአብሔር ህላዌነት፣ሥነ ምግባር፣ እውነት፣ በዓለም ላይ ስላሉ ሐይማኖቶች እሰጣ ገባ፣ ፍትህ፣ ስለ መለኮታዊውና ሰዋዊ ህግ፣ ማህበራዊ ኑሮና ዘመናዊነት በተመሳሳይ መልኩ ያቀርባል፡፡ አለቃ ያሬድ ፈንታ ለየት ባለ መልኩ የፈላስፋውን የስነ ፍጥረት ሐተታ፣ ከንባብና ትምህርት ስለሚገኝ ጥቅምና ስለተለያዩ ሕይወታዊ ምክሮች በስፋት ሲዳስስ፤ በአንጻሩ “መጽሐፈ ፍልስፋና” በኢትዮጵያዊነቱ ላይ ስለተነሱ ጥቄዎች ምላሽ ይሰጣል፡፡ የዘርዐ ዕቆብ የፍልስፋና ጥልቀት፤ በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ያለው አጥር ክፋት መሆኑን በማስረዳት ይኮንናል፡፡ ፈላስፋው የእግዚአብሔርን መኖር ቢያረጋግጥም የሁሉንም ሐይማኖት ግን ከመንቀፍ ቦዝኖ አያውቅም። ስለዚህ ሐይማኖት ምንድነው ብለን ለመፈተን ጥልቅ ምርምር ይጠይቀናል፡፡ ሰዎች “ሁሌም በራሴ ልክ ነኝ” ከሚል ትምክህት መውጣት አለባቸው የሚለው በምርምሩ የደረሰበት ጥግ ሲሆን ለእናም የሚበጅ መላ ነው፡፡ የፖስት ሞደርኒዝም አቀንቃኝ የሆነው የመካከለኛው ዘመኑ ዘርዐ ያዕቆብ፤ በ68 ዓመቱ ለዚህ ትውልድ የሚረቡ ሁነኛ ሀሳቦችን በተማሪው ግፊት አንደጻፋቸው ይናገራል፡፡