Administrator
Thursday, 23 July 2026 18:22
የቤተ ክርስቲያን ሚዲያዎች ባካችሁ ይዘት ላይ ሥሩ!
የቤተ ክርስቲያን ሚዲያዎች 'ይሻሻላሉ፣ ገና ጅምር ላይ ናቸው፣ ብዬ በተስፈኝነት ጠበቅሁ። እኔን ብሎ ተስፈኛ! እነርሱ ግን እያደር የጳጳሳት_ዲያሪ ሆነው ቁጭ!
"ብፁዕነታቸው መሠረት ጣሉ፣ ጎበኙ፣ ከፈቱ፣ ተጓዙ...።" non sense! የሚዲያ ይዘት እንዲህም ይሞታል እንዴ?! ኃፍረት ወዝንጓጔ ማለት ለእናንተ! እያደር ማዘቅዘቅ! እንደ ተዘዋዋሪ ሰባኪ በየንግሡ ለአበል ሩጫ ብቻ! ያሳዝናል! ሚዲያችን contentwise ክፉኛ፣ ያውም ፀዋግ ሞት እየሞተ ነው።
ኅሡ ርእሰክሙ አኃው።
ቤተ ክህነቱን እንደ መደብ ጀርባው እንደሚቆጥር ደብተራ ባላችሁ ይዘትም ሆነ አቀራረብ ኃዘንም ኃፍረትም ይሰማኛል።
የላዕላይ መዋቅሩ የዕለት ተዕለት ውሎ ዘጋቢ ሆናችሁ እየቀራችሁ ነው። ሁሌ "የሙከራ ስርጭት" ላይ ያላችሁ መስላችሁ መታየት ደስ አይልም። አዘጋገባችሁ ቤተ ክርሰቲያን ማለት "ጳጳሳት/መምሪያዎች ብቻ" ያስመስላል።
ባካችሁ ይዘት ላይ ሥሩ፣ የካህኑና የምዕመኑ እንዲሁም የአጥቢያዎች ድምፅ ለመሆንም ሞክሩ። የይዘት ሳይሆን የአደባባይ ተርእዮ መድረክ እየሆናችሁ ነው።
በአማን ነጸረ
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ህብረተሰብ
Tagged under
Thursday, 23 July 2026 18:19
ጄነራል ታደሰ ወረደ ወዴት ተሰወሩ?
የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ በመቀሌ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው መሰወራቸው ተሰማ። እስከ ማክሰኞ ጠዋት ድረስ መኖሪያ ቤታቸው በከፍተኛ ሁኔታ የሚጠበቅና በጥበቃ ተሽከርካሪዎች የተከበበ የነበረ ቢሆንም፣ ከማክሰኞ ምሽት ጀምሮ ግን አብረዋቸው የነበሩ ጥበቃዎችና ሰራተኞች ከአካባቢው ሙሉ በሙሉ ጠፍተዋል።
ጄነራሉ ከጥቂት ቀናት በፊት ከአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ጋር እንዳይገናኙ በትግራይ ጸጥታ ቢሮ ተከልክለው እንደነበርና ቤተሰቦቻቸውም ስለ ደህንነታቸው ስጋት አድሮባቸው እንደነበር ይታወቃል።
ጄነራል ታደሰ ወረደ በፌደራል መንግሥት ዳግም በተሾሙ በጥቂት ቀናት ውስጥ በሕወሓት ከኃላፊነታቸው መነሳታቸው የሚታወስ ነው። ከኃላፊነታቸው ከመነሳታቸው በፊትም ጊዜያዊ አስተዳደሩን በኃይል ለመገልበጥ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ ክልሉን ወደ አዲስ ጦርነት እንደሚያስገባ አስጠንቅቀው ነበር።
በአሁኑ ወቅት በሕወሓት እና በፌደራል መንግሥት መካከል ያለው የፖለቲካ ውጥረት በጨመረበት ሁኔታ፣ የጄነራሉ ከአካባቢው መሰወር በትግራይ ክልል አዲስ የጸጥታ ስጋት ደቅኗል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ዜና
Tagged under
Thursday, 23 July 2026 18:15
100 እንቁላል በ1 ብር!
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ገጼን ሳይ Zerihun Gultie የ1955 ጋዜጣ ለጥፏል። ጋዜጣው ከሚያወሳቸው አንዱ ዜና 785,275 ኪሎ ግራም በቆሎ በ78,267 ብር ለሱማሊያና ለየመን እንደተሸጠ ይገልጻል።
ይህ ሽያጭ እስከ አሰብ የተጓጓዘው በኛ ትራንስፖርት ከሆነ በኩንታል ከብር 30.00 በታች መሆኑ ነው። ያኔ የሀገር ውስጥ ዋጋ በኪሎ ከ0.25 ሳንቲም አይበልጥም ነበር። እንቁላልም በኪሎ ከ1.00 በታች እንደሆነና በ2058 ብር ልዩ ልዩ የተሻለ ዝርያ ያላቸው ከብቶችን ከውጭ አገር ማስገባታችንንና አሜሪካ 225 ግመሎች ማጓጓዣውን ጨምሮ በ5060 ብር መግዛቷን ጋዜጣው ያወሳል።
የብርም ዋጋ ከዶላር በላይ ነበር። ባልሳሳት ያኔ 3USD 1EthD ነበር። ለማንኛውም በቆሎ ለውጭ የተሸጠው በ12 እጥፍ ሲሆ፣ እኔ ሳውቅ በአንድ ብር 100 እንቁላል ስለነበር ብዙ እጥፍ መሆኑ ነው። የምርጥ ከብቶቹንና የግመሎቹን ስሌት ለናንተ ልተወው። በአሁኑ ጊዜ ግን ለውጭ ገበያ የሚቀርበው ከሀገር ቤት ባነሰ ይመስለኛል።
ጋዜጣውን ለለጠፈው ወዳጄ ምስጋና አቀርባለሁ።
Teshome Berhanu Kemal
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ማራኪ አንቀፅ
Tagged under
Thursday, 23 July 2026 18:14
የትራምፕ አስተዳደር በማሊ በሚገኙ አማፂያን ላይ ወታደራዊ ጥቃት ለማድረስ እያሰበ ነው
የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በማሊ ከሚንቀሳቀሰውና ከአልቃኢዳ ጋር ግንኙነት ካለው አማፂ ቡድን ጋር በተያያዘ ወታደራዊ ጥቃት ለማድረስ እያሰበ መሆኑን የአሜሪካ ባለስልጣናት ገልጸዋል።
ይህ ውሳኔ ከጸደቀ ማሊ በትራምፕ ሁለተኛ የፕሬዝዳንትነት ዘመን አሜሪካ ወታደራዊ ጥቃት የፈጸመችባት 8ኛዋ ሀገር ትሆናለች፤ ይህም አሜሪካ ከሽብርተኝነት ጋር በተያያዘ የምታደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ይበልጥ የሚያሰፋው ይሆናል። እስካሁን ድረስ የተላለፈ የመጨረሻ ውሳኔ የሌለ ሲሆን በጉዳዩ ላይ በአስተዳደሩ ውስጥ ውይይቶች አሁንም ቀጥለዋል።
Published in
ከአለም ዙሪያ
Tagged under
Thursday, 23 July 2026 18:11
የቀድሞው የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎበኙ
የቀድሞው የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የቶኒ ብሌየር ኢንስቲትዩት መስራችና ሊቀመንበር ሰር ቶኒ ብሌየር የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን የጎበኙ ሲሆን፣ ከአመራሮች ጋር በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱም ወቅት ሰር ቶኒ ብሌየር አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ረገድ ያለውን ከፍተኛ ሚና አጉልተው በመናገር፣ ተቋማቸው ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በትብብር ለመስራት ሙሉ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የቶኒ ብሌየር ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያን የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ለመደገፍ እያደረገ ላለው አበርክቶ ምስጋና አቅርበዋል። ሁለቱ ተቋማት በቀጣይም በኢትዮጵያ የኤ.አይ (AI) ቴክኖሎጂ ልማትን እና ተግባራዊነትን ለማረጋገጥ በጋራ እና በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ተመላክቷል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ዜና
Tagged under
Wednesday, 22 July 2026 00:00
እስራኤል የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን አወደሰች
በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭራሃም ንጉሴ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚና የኢንዱስትሪ እድገት በጣም አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ አድናቆታቸውን ለግሰዋል።
ይህ የእስራኤል ድጋፍ የመጣው የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢትዮጵያ ግድቡን በብቸኝነት እያንቀሳቀሰች ነው ሲሉ ከከሰሱ በኋላ ሲሆን፣ አምባሳደሩ በተጨማሪም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በእርሻ፣ በጠብታ መስኖና በዓሣ ሀብት ልማት ላይ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በካይሮና በአዲስ አበባ መካከል ያለው የቃላት ልውውጥ እና ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት እየጨመረ መጥቷል። ግብፅና ሱዳን ያለ ህጋዊ ስምምነት ግድቡን መሙላትና ማካሄድ የውሃ ደህንነታችንን ይጎዳል ሲሉ ሲቃወሙ፣ ኢትዮጵያ በበኩሏ የ4 ቢሊዮን ዶላሩ ግድብ በታችኞቹ ሀገራት ላይ ምንም ዓይነት ጎጂ ተጽዕኖ እንደማያደርስና ለሀገሪቱ የኃይል ፍላጎት ወሳኝ መሆኑን አጥብቃ ትገልጻለች።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ዜና
Tagged under
Tuesday, 21 July 2026 13:54
“ሀሰተኛ ሪፖርት ማቅረብ ከሌብነት እኩል ያስጠይቃል!”
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በ2018 በጀት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ላይ እንደገለጹት፣ በተቋማት መካከል ተመሳሳይ መዋቅር፣ በጀትና የሰው ኃይል ተመድቦ ሳለ በአፈጻጸም ሰፊ ልዩነት መታየቱ የሚያስጠይቅ ነው።
በአመራሩ ዘንድ በሚታዩ የሪፖርት ግድፈቶችና የመረጃ አያያዝ ክፍተቶች ላይ ጠንከር ያለ ትችት የሰነዘሩት ከንቲባዋ፣ ትክክለኛ ያልሆነ መረጃ ማቅረብ ከሌብነት ጋር በተመሳሳይ ደረጃ የሚያስጠይቅ እንደሆነ በማስጠንቀቅ ወደፊት የሚቀርቡ ሪፖርቶች በሕዝቡ ሕይወት ላይ ያመጡትን ሁለንተናዊ ለውጥና ጥቅም በግልጽ ማሳየት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በተጨማሪም የኮሪደር ልማትን በማስመልከት የፅዳት ሥራ የእያንዳንዱ ነዋሪ የዕለት ተዕለት ባህል ሊሆን እንደሚገባና ነዋሪው ደጃፉን በባለቤትነት ማጽዳት እንዳለበት አስገንዝበዋል። የኑሮ ውድነትን ለመከላከል፣ የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግና በቤት ልማት ያረጁ የከተማ ክፍሎችን የማደስ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የተናገሩት ከንቲባዋ፤ ለመሠረተ ልማቶች ከፍተኛ በጀት መመደቡን ገልጸው፣ ለተመዘገቡት ስኬቶች የሕዝብና የልማት አጋሮች ተሳትፎ ከፍተኛ እንደነበር በመጠቆም፣ በቀጣይም ይህ ትስስር ይበልጥ እንዲጠናከር ጥሪ አቅርበዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ዜና
Tagged under
Monday, 20 July 2026 00:00
"ጌቶ ኪድስ" ከሻኪራ እና ከበርና ቦይ ጋር የዓለም ዋንጫን መድረክ አደመቁ
በዓለም ዙሪያ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተመልካቾች የ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ የዕረፍት ሰዓት ትርኢት በተከታተሉበት ወቅት፣ የኡጋንዳውያኑ "ጌቶ ኪድስ" የዳንስ ቡድን ታሪክ ሰርተዋል።
እነዚህ ወጣት የዳንስ ከዋክብት ከዓለም አቀፏ የፖፕ ንግሥት ሻኪራ እና ከታዋቂው የአፍሮቢትስ ኮከብ በርና ቦይ ጋር በመሆን በዓለም እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የቴሌቪዥን ተመልካች በተከታተለው መድረክ ላይ የሚያስደምምና መንፈስን የሚያነቃቃ የዳንስ ትርኢታቸውን አቅርበዋል።
Published in
ስፖርት አድማስ
Tagged under
Tuesday, 21 July 2026 13:49
ዋልያን የመታደግ ዘመቻ፦ ከዓለም አቀፍ ስጋት ወደ አዲስ ተስፋ
በኢትዮጵያ ስሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ ብቻ የሚገኘውና የዩኔስኮ የዓለም ቅርስ መለያ የሆነው ብርቅዬው ዋልያ፣ በቅርብ ዓመታት በነበረው ግጭትና የሕግ መላላት ምክንያት ቁጥሩ ከ638 ወደ 306 ዝቅ ብሏል። በዚህም ሳቢያ አካባቢው ለሕገ-ወጥ አደን በመጋለጡ፣ ዓለም አቀፍ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ኅብረት (IUCN) ዋልያን «ከፍተኛ የመጥፋት አደጋ የተደቀነበት» ሲል በአደጋ መዝገቡ ውስጥ አካትቶታል። ሆኖም ይህ ምዝገባ ለእንስሳው ዓለም አቀፍ ትኩረት፣ ምርምርና የገንዘብ ድጋፍ ለማሰባሰብ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር በመሆኑ እንደ መልካም አጋጣሚ ተወስዷል።
ችግሩን ዘላቂ በሆነ መንገድ ለመፍታት የኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለሥልጣንና የፓርኩ ጽሕፈት ቤት የ10 ዓመት ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ሥራ ገብተዋል። በዚሁ መሠረት «የዋልያ አምባሳደሮች» የተሰኙ 12 ባለሙያዎችን በማሰማራት፣ ከኅብረተሰቡ ጋር በመተባበር ሌት ተቀን ቅኝት በማድረግ ሕገ-ወጥ አደንን ሙሉ በሙሉ ማስቆም ተችሏል። ቀደም ሲልም በ1983 ዓ.ም በተደረገ ጥበቃ እንስሳቱን ከአደጋ ቀጠና ማውጣት የተቻለ ሲሆን፣ አሁንም በአንዳንድ አካባቢዎች እስከ 15 የሚደርሱ አዳዲስ ግልገሎች መታየታቸው የዋልያ ቁጥር በፍጥነት እንደሚያገግም ትልቅ ተስፋ ፈጥሯል።
AMECO-
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ህብረተሰብ
Tagged under
Tuesday, 21 July 2026 13:48
ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ ከለንደኑ ኮንሰርት መልስ መታመሙን ገለጸ!
በኢትዮጵያ የሙዚቃ አድናቂዎች ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈው ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ በለንደን ያቀረበውን ስኬታማ ኮንሰርት አጠናቆ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በኋላ የጤና መታወክ እንዳጋጠመው በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጹ ገለጸ።
ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ባልደረባ ጋር የተነሳውን ፎቶግራፍ በማያያዝ «ታምሜ ገባሁ :: ስለሁሉ ግን እግዚአብሔር ይመስገን !!» ሲል ያሰፈረው መልዕክት በበርካታ አድናቂዎቹ ዘንድ ስጋትን የፈጠረ ሲሆን፣ ህመሙ ምን እንደሆነ በዝርዝር ባይታወቅም በርካታ ወዳጆቹ አብሮነታቸውን እየገለጹለት ይገኛሉ።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
Tagged under

