Administrator

Administrator

የቦስተን ፓርትነርስ መስራችና የኩሪፍቱ ሪዞርትስ እና ስፓ ባለቤት ኢትዮጵያዊው ባለሀብት ታዲዮስ በለጠ፣ በኬንያ የቱሪዝም ዘርፍ ትልቅ ኢንቨስትመንት ለማድረግ መዘጋጀታቸውን አስታወቁ።
ባለሀብቱ በኬንያዋ የወደብ ከተማ ሞምባሳ ከሀገሪቱ ባለሀብቶች ጋር በመተባበር ግዙፍ የውሃ ፓርክ (Water Park) ለማቋቋም ማቀዳቸውን ይፋ ያደረጉ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና ትልቁ የውሃ ፓርክ እንደሚሆን በኬንያ መገናኛ ብዙኃን የወጡ ዘገባዎች አመልክተዋል።
ይህ ትልቅ የኢንቨስትመንት ብስራት ይፋ የሆነው፣ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በናይሮቢ ያዘጋጀውን የኢትዮጵያን የቱሪዝም መስህቦች የማስተዋወቅ መድረክ ተከትሎ ነው። ሚኒስቴሩ በዚሁ መድረክ ላይ ለኬንያውያን ባለሀብቶች፣ ለአስጎብኝ ድርጅቶች፣ ጋዜጠኞች እና የሶሻል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ማብራሪያ የሰጠ ሲሆን፣ በቀጣይም የኬንያ አስጎብኝዎችንና የሜዲያ አካላትን ወደ ኢትዮጵያ በመጋበዝ የሀገሪቱን የቱሪዝም ሀብቶች ለማስጎብኘት ማቀዱን አስታውቋል።
[ዋዜማ]-
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አማካሪና የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ፣ የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ከኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በሚስጢር መገናኘታቸውን በመግለጽ ከባድ ክስ ሰንዝረዋል። ጌታቸው ረዳ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፣ ደብረጽዮን ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጋር የተገናኙት የጦር መሣሪያ ድጋፍ ለመጠየቅ እንደነበር ገልጸዋል።
እንደ ጌታቸው ገለጻ፣ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ለሕወሓት ሊቀመንበር በሰጡት ምላሽ በኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥት ላይ ድጋሚ ጦርነት ከከፈታችሁ በኋላ አስፈላጊውን ድጋፍ እናደርግላችኋለን ማለታቸውን ተናግረዋል። ሆኖም ግን ይህ ምስጢራዊ ስብሰባ መቼ እና የት ቦታ እንደተካሄደ ጌታቸው ረዳ በጽሑፋቸው ላይ የጠቀሱት ነገር የለም።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይን አስመልክተው ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት፤ በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በቦረና ወረዳ በሚገኘው ግዮን አባይ ገዳመ አስቄጥስ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. በተፈጸመ አሰቃቂ ጥቃት የመናንያን መነኮሳይያት ሕይወት በግፍ መጥፋቱን፣ በርካቶች መቁሰላቸውን እና የገዳሙ ንዋየ ቅዱሳት መውደማቸውን በከፍተኛ ሐዘን ገልጸዋል። ከዚህም በተጨማሪ በሐድያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የአምልኮ ሥፍራ በኃይል መፍረሱና በምእመናን ላይ ጥቃት መድረሱ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው እና የተወገዘ ተግባር መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
ቅዱስነታቸው ራሳቸውን ለመከላከል ምንም ዓይነት ቁሳዊ ዝግጅት በሌላቸው ንጹሐን መናንያን ላይ እጅን ማንሣት በእግዚአብሔር ዘንድ የተከለከለና በታሪክ ፊት የሚያሳፍር መሆኑን ጠቁመው፣ ጥቃቱን የፈጸሙ አካላት ለፍትሕ እንዲቀርቡ እና የገዳማትና አድባራት ደኅንነት እንዲጠበቅ ለሚመለከታቸው አካላት ጥሪ አስተላልፈዋል። ሕዝበ ክርስቲያንና መላው ኢትዮጵያውያን የጥቃት ሰለባ ከሆኑት ወገኖች ጋር በመንፈሳዊም ሆነ በሰብአዊ ድጋፍ አብረው እንዲቆሙም አባታዊ አደራቸውን አስተላልፈዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በንግድ ፖሊሲው ላይ ባደረገው አዲስ ክለሳ ከዋና ዋና የንግድ አጋሮቹ በሚገቡ ምርቶች ላይ አዲስ የገቢ ንግድ ታሪፍ መጣሉን ይፋ አድርጓል።

በዚህ አዲስ ውሳኔ መሠረት 12.5 በመቶ የታሪፍ ጭማሪ ከተጣለባቸው ሀገራት መካከል አልጄሪያ፣ አንጎላ፣ ግብፅ፣ ሊቢያ፣ ሞሮኮ፣ ናይጄሪያ እና ደቡብ አፍሪካ የተካተቱ ሲሆን፣ እርምጃው አሜሪካ የዓለም አቀፍ ንግድ ማዕቀፏን ዳግም ለመቅረጽ የምታደርገው ጥረት አካል እንደሆነ ተገልጿል።

ይህ አዲስ አሰራር በተለይም የነዳጅ፣ የጨርቃጨርቅ እና የምግብ ምርቶችን ወደ አሜሪካ በሚልኩት በእነዚህ የአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ጫና ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል። ውሳኔው የአሜሪካን የአገር ውስጥ አምራቾች ለመጠበቅ እና የንግድ ሚዛን እጥረትን ለመቀነስ ያለመ ነው ቢባልም፣ በዓለም አቀፍ የንግድ ትስስር እና ኤክስፖርት ላይ አዲስ ፈተና ደቅኗል።

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

በአንድ ሳምንት አምስት ቴአትሮችን እየሰራ ስላለው ብርቱው ተዋናይ ትእዛዙ ታዬ ጥቂት መረጃ አድርሼ ነበር። እሱን ተንተርሶ ተጨማሪ ሀሳብ አርቲስት መርዕድ ተስፋዬ አከለበት። እንዲህ ሲል፦
***
በጣም የሚገርመኝ የትዕዛዙ ልዩ ችሎታ ደግሞ የሌሎች ተዋንያንን ገፀ ባህሪ በአጭር ጊዜ አጥንቶ ተክቶ በመስራት ብዙ ቴአትሮችን ከመዘጋት ታድጓል!!!.....ቁጠሩ እንግዲህ....
ለምሳሌ ለመጥቀስ ያህል:-
1."ህንደኬ" ላይ....ተዋናይ ደረጄ ደመቀን ተክቶ
ሰርቷል፡፡
2."ሶስተኛው ችሎት" ላይ....ተዋናይ ፈለቀ የማር ውሀ አበበ እና ተዋናይ ሱራፌል ተካ የሚሰሩትን ገፀ ባህሪ ተክቶ ሰርቷል፡፡
3."አሉ" ቴአትር ላይ ተዋናይ ሳሙኤል ተስፋዬን
ተክቶ ሰርቷል፡፡
4."መንታ መንገድ" ላይ ተዋናይ ተስፋዬ ገ/ሐናን
ተክቶ ሰርቷል፡፡
5.አሁን በቅርቡ ደግሞ "12ቱ እንግዶች" ላይ ተዋናይ ዳንኤል አሸናፊን ተክቶ ሰርቷል!!!......ይሔኔ እኮ ያልጠቀስኩትም ይኖራል!!!.......ለማንኛውም ትዜ ከትወናውም ውጪ ቴአትርን በብዙ ነገር እየደገፈ ያለ ጎበዝ እና ልበ ቅን ባለሙያ ነው!!!
***
ባለሙያ በቅንነት እንዲህ ማድነቅ ሲችል ደስ ይላል። እናመሰግናለን መርዕድ።
ውድነህ ክፍሌ-
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከ«ሰዎች ለሰዎች» ድርጅት ጋር በመተባበር በሀገራችን በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታ በይፋ አስጀምሯል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለጹት፣ የዚህ ኮሌጅ ግንባታ ሲጠናቀቅ ወጣቶችን በማኑፋክቸሪንግ፣ በአውቶሞቲቭ፣ በኤሌክትሪክና ኤሌክትሮኒክስ፣ በኮሚዩኒኬሽንስ፣ በቴክስታይል እና በሲኤንሲ ቴክኖሎጂዎች ላይ ዘመናዊና ተግባር ተኮር ስልጠናዎችን የሚሰጥ ይሆናል። ፕሮጀክቱ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ወጣቶችን ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት፣ ከንድፈ-ሃሳብ ደግሞ ወደ ተግባር የሚያሸጋግር አዲስ የክህሎት ድልድይ እንደሚሆንም ተመልክቷል።
ሀገርን ማልማትና ከድህነት መላቀቅ በንድፈ-ሃሳብ ብቻ ስለማይቻል ሃሳብ የሚያፈልቁ አዕምሮዎችንና የሚሰሩ እጆችን ያጣመረ ክህሎት መር የሰው ሀይል አስፈላጊ መሆኑን ከንቲባዋ ጠቁመዋል።
ከሐምሌ 22 እስከ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በዲፕሎማሲ መዲናዋ አዲስ አበባ «አዲስ ዓለም አፍሪካ የጋራ መፃኢ እድልን በመቅረጽ ረገድ» በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው ታሪካዊ ጉባኤ ላይ ከ700 በላይ የመንግሥት መሪዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የቢዝነስ ባለሀብቶች፣ የፈጠራ ባለሙያዎችና የሲቪል ማህበራት ተወካዮች ይሳተፋሉ።
ይህ ታላቅ መድረክ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ አህጉሪቱ በዓለም አቀፍ ንግድ፣ ዘላቂ ልማትና ሕዝባዊ ዲፕሎማሲ ላይ ያላትን እየጎለበተ የመጣ ማዕከላዊ ሚና የሚያንፀባርቅ ነው። ጉባኤው በስፖርትና በባህል አማካኝነት ሰዎችን እንደሚያቀራርበው የዓለም ዋንጫ ሁሉ፣ የተለያዩ ዓለም አቀፍ አካላትን በማሰባሰብ ለኢኮኖሚያዊ፣ ቴክኖሎጂያዊና ማህበራዊ ጥያቄዎች የጋራ መፍትሔ ለመፈለግ ያለመ ነው።
የጉባኤው ዋና ማዕከል ከሆኑት ዝግጅቶች አንዱ «አንድነት» (Unity) የተሰኘው ዓለም አቀፍ ዘመናዊ የኪነ-ጥበብ ኤግዚቢሽን ሲሆን፣ ከ16 የአፍሪካ ሀገራትና ከዳያስፖራው የተውጣጡ ታዋቂ አርቲስቶችን ያሰባስባል። በተጨማሪም «የዛምቤዚ ወንዝ፡ ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና መንፈስ» በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሳይንሳዊ ጥናት የሚቀርብ ሲሆን፣ ጥናቱ ወንዙ በስድስት የአፍሪካ ሀገራት እድገት ላይ ያለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ በስፋት እንደሚመረምር ተገልጿል።
የጠቅላላው ምክር ቤት ሊቀመንበር አማካሪ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እንደገለጹት፣ ጥበብ ልክ እንደ ስፖርት ሁሉ የሰው ልጅ የጋራ ቋንቋ እና የሕዝብ ዲፕሎማሲ መሣሪያ በመሆኑ ሰዎችን በማቀራረብ ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
የሰርቭ ግሎባል ምክትል የሀገር ውስጥ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ነጋሽ በበኩላቸው፣ ጉባኤው በንግድ ድርድር ላይ ሳይሆን የእውነተኛ አንድነትን በማሳየት ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች የሚሰራ አዲስ ዓለም ለመገንባት መንገድ ይጠርጋል። ይህ በአዲስ አበባ የሚካሄደው የአፍሪካ ጉባኤ ዓመቱን ሙሉ የሚቀጥል ዓለም አቀፍ የትብብር መድረክ አካል ሲሆን፣ ቀጣዩ ዓለም አቀፍ መድረክ በመስከረም ወር በሩሲያ ሞስኮ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ አረጋግጠዋል።
የቀድሞው የሊቨርፑል እና ባየርን ሙኒክ ኮከብ እግር ኳስ ተጫዋች ሳዲዮ ማኔ፣ ከስፖርት ህይወቱ ያገኘውን በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር በትውልድ መንደሩ ማህበራዊ እድገት ላይ በማዋል ላይ ይገኛል። ማኔ በተለይም በጤና፣ በትምህርት እና በማህበረሰብ ልማት ዘርፎች ላይ ትኩረት በማድረግ የአካባቢውን ህዝብ ህይወት የሚቀይሩ በርካታ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን እውን አድርጓል።
በህጻንነቱ የነበረበትን የጤና አገልግሎት እጥረት መሰረት በማድረግ፣ በማህበረሰቡ የህክምና አገልግሎቶች ተደራሽ እንዲሆኑ ዘመናዊ ሆስፒታል አስገንብቷል። ከዚህ በተጨማሪም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመገንባት፣ ለተማሪዎች ላፕቶፖችን በማቅረብ፣ በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡት ማበረታቻ በመስጠት እና ወጣት ተማሪዎችን በመደገፍ በትምህርት ዘርፍ ትልቅ አሻራ አሳርፏል።
የማኔ በጎ አድራጎት በትውልድ ስፍራው ባምባሊ እንደ ማዶ ጋዝ ማደያ፣ የፖስታ ቤት፣ የ4ጂ ኢንተርኔት አገልግሎት እና ታዳጊ ተጫዋቾችን የሚያበቁ የእግር ኳስ ቁሳቁሶችን በማቅረብ መሰረታዊ ልማቶች እንዲሟሉ አስችሏል። ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት ለአካባቢው ቤተሰቦች የወርሃዊ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ የዕለት ተዕለት ኑሯቸውን እንዲወጡ ያግዛቸዋል። ለማኔ ስኬት ማለት የግል ውጤታማነት ብቻ ሳይሆን እሱን ለፈጠረው ማህበረሰብ ምላሽ መስጠት ነው።
Great Africa-
ኢራን በባሕረ ሰላጤው በሚገኙ የሲአይኤ ተቋማት ላይ በድሮን በፈጸመችው ጥቃት ላይ ሩሲያ የመረጃ ወይም የቴክኖሎጂ ድጋፍ አድርጋለች በሚል ምርመራ ሊደረግበት እንደሚገባ የአሜሪካ የደኅንነት ባልደረቦች ገለጹ። እንደ ሪያድ እና ምስራቃዊ ኢራቅ ባሉ ስፍራዎች በተፈጸሙት በእነዚህ ጥቃቶች ላይ የሩሲያ ቀጥተኛ ተሳትፎ ስለመኖሩ ገና ሙሉ ድምዳሜ ላይ ያልተደረሰ ቢሆንም፣ የጥቃቶቹ ዒላማቸውን የጠበቁ እና እጅግ ውጤታማ መሆን የደኅንነት ተቋማቱን ከፍተኛ ጥርጣሬ ውስጥ ጥሏቸዋል።
ሮይተርስ እንደዘገበው፣ የአሜሪካ ባለሥልጣናት ሩሲያ ለኢራን የምታደርገውን ሰፊ የቴክኒክ ድጋፍ የሚያውቁ ሲሆን፣ ይህም ለጥርጣሬው በቂ ምክንያት ሆኗል። በመጋቢት ወር ከተፈጸሙት ጥቃቶች በተጨማሪ ሌሎች የሲአይኤ ተቋማትም ጥቃት እንደደረሰባቸው ምንጮች የጠቆሙ ሲሆን፣ የሩሲያ የመረጃ አገልግሎት ወይም የተሻሻለ የድሮን ቴክኖሎጂ አቅርቦት ለዚህ ድርጊት ሽፋን ሰጥቶ እንደሆነ ለማረጋገጥ ምርመራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መገለጹን ቢቢሲ ዘግቧል።
በኢራን ይደገፋሉ የሚባሉት የየመኑ ሁቲዎች በባብ ኤል መንደብ ወሽመጥ ሁለት የሳዑዲ አረቢያ የነዳጅ መርከቦችን መትተዋል። ሁቲዎች ይህንን አስፈላጊ የባህር መስመር እንደሚዘጉና ወደ ሳዑዲ የሚሄዱ መርከቦችን እንደሚመቱ ያስጠነቀቁት፣ ባለፈው ሳምንት የሳዑዲ ጦር በሰንዓ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ድብደባ ካደረገ በኋላ ነው።
በሌላ በኩል ሳዑዲ አረቢያ፣ አሜሪካና ወዳጆቻቸው፡ «የሁቲዎች እርምጃ ከእነሱ ጋር ውጥረት ውስጥ ለምትገኘው ኢራን ድጋፍ ለመስጠት የተደረገ ሴራ ነው» ሲሉ ይከሷቸዋል። የጥቃቱ ዜና እንደተሰማ የዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ በአንዴ በ6 በመቶ በመጨመር አንድ በርሚል ነዳጅ 100 ዶላር ገብቷል።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ጦር በሁቲዎችና በኢራን ላይ የሚያደርገውን የአየር ድብደባ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ዝተዋል።
Page 5 of 818