Administrator

Administrator

    ከዕለታት አንድ ቀን አንዲት መነኩሲት ጎኅ ሲቀድ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሊሄዱ ይነሳሉ፡፡ አንድ ዛፍ አጠገብ ሲደርሱ ተንበረከኩና ሁለት እጃቸውን በልመና መልክ ዘርግተው፤ ፀለዩ፡-
“አምላኬ ሆይ! መቼም አንተ የነገሩህን የማትረሳ፣ የለመኑህን የማትነሳ፣ ሰማይን ያለ ካስማ ያቆምክ፣ የማይዘሩ የማያጭዱትን ወፎች የእለት ምግባቸውን የምትሰጥ ነህ! አሁን እኔ የምለምንህ እጅግ ትንሽ ነገር ናት፡- አምላኬ ሆይ! አደራህን ዕድሜዬን ጨምርልኝ?” አሉት
ወደ ቤተ ክርስቲያን መንገድ ቀጠሉ፡፡ ወደ ቤት ተመልሰውም፣ ይሄንኑ ሲያብሰለስሉ አመሹ፡፡
በሚቀጥለው ቀን ማለዳ ጎኅ ሲቀድ፤ ተነስተው ወደዚያው ዛፍ ስር ሄደው፤ ምናልባት ፀሎቴን አሳንሼው ይሆናል በሚል፤
“አምላኬ ሆይ! ድንገት ከወትሮው ፀሎቴ አሳንሼብህ ይሆናል፡፡ የከዋክብት ብዛቱን፣ የውቂያኖስ ስፋቱን፣ የሙሴ በትሩን፣ የገብርኤል ተዓምሩን፣ የእመቤታችን አማላጅነቷን የምታውቅ፣ የምትሰጥ፤ የነገሩህን የማትረሳ፣ የለመኑህን የማትነሳ፣ ሰማይን ያለ ካስማ ያቆምክ፣ የማያርሱ የማይዘሩ ወፎችን የእለት ጉሮሮ የምትዘጋ፣ ምንም የማይሳንህ አምላክ ሆይ! ካንተ ልግስና አንፃር እጅግ ትንሽ ነገር ነው የምለምንህ፡- እባክህ ዕድሜዬን ጨምርልኝ?”
ለካ ይህን ፀሎታቸውን ሲያደርሱ፣ ሁሌ ቁጥቋጦ ውስጥ ተደብቆ የሚያዳምጣቸው አንድ ተንኮለኛ የቆሎ ተማሪ ኖሯል፡፡
በሚቀጥለው ማለዳ ጎኅ በቀደደ ሰዓት ያ የቆሎ ተማሪ፣ ቀደም ብሎ ዛፉ ላይ ወጥቶ ይጠብቃቸዋል። እሳቸው እንደልማዳቸው መጥተው ፀሎትና ልመናቸውን አሰሙ፡፡ በመጨረሻም፤ “ዕድሜዬን ጨምርልኝ፣አደራ!” አሉ፡፡
ይሄኔ፤ ያ የቆሎ ተማሪ፤
“አንቺ መነኩሲት! ምን ያህል ዕድሜ ልጨምርልሽ?” አለ ድምፁን ጎላ አድርጎ፡፡ መነኩሲቷ ደነገጡ። ፀሎታቸው ተሰማ! ሲያስቡት ሃያም ትንሽ ነው፡፡ አርባም ትንሽ ነው፡፡ መቶም ትንሽ ዕድሜ ነው። በመጨረሻ እንዲህ ሲሉ መለሱ፤ “አምላኬ ሆይ! አንድ ድሃህን ከነጭራሹስ እዚሁ ብትተወኝ፣ ምን እጎዳሃለሁ?!” አሉ፡፡
*             *           *
የዓለም ኢኮኖሚ ጉዳይ አንጋፋ ባለሙያ የሚባለው አዳም ስሚዝ፤ “የሰው ልጅ ፍላጎት ወሰን የለውም” ያለንን ከላየ ያየነው ተረት በአበሽኛ ሳይገለጥልን አልቀረም - Human wants are unlimited ማለት ይሄው ነው፡፡ ዛሬ መጠለያ ጠየቅን፡፡ ነገ ምግብ እንጠይቃለን፡፡ ከነገ ወዲያ መንቀሳቀሻ መኪና እንፈልጋለን። ከዚያ ወዲያ ሰፋ ያለ ግቢ እንዲኖረን እንጠይቃለን፤ ወዘተረፈ ችግሩ የሚመጣውና የሚስፋፋው መሰረታዊ ፍላቶታችን ከተሟላ በኋላ ነው፡፡ ወለሉ ግን መሰረታዊ ፍላጎት ነው፡፡ ኢኮኖሚያችን ከዚህ ወለል በታች ከሆነስ? “እዚሁ ላይ ነው ችግሩ” እንዳለው ነው ሼክስፒር፡፡ “መሆን ወይስ አለመሆን?” የሚባለው ጥያቄ፣ ማናቸውም ጉዳይ ለውሳኔ አሳሳቢ ደረጃ ሲደርስ የሚመጣ ነው፡፡ ውስጥን መፈተሽ አለመፈተሽ፣ እርምጃ መውሰድ አለመውሰድ? ነው ጉዱ! ምኞት ከአቅም በላይ መሆን እንደሌለበት ማንም ጅል አይስተውም። የፍላጎት አቅማችን እየኮሰሰ፣ ምኞታችንን ሲያጫጨው፤ የተስፋ መቁረጥ ጉድባ ውስጥ እንገባለን፡፡ ዜግነታችን ራሱ ያስጠላናል፡፡ የሀገር ፍቅራችን ይሟሽሻል፡፡ ሁሉን ነገር አሉታዊ እሳቤ ውስጥ እንከተዋለን። መንገድ ተሰራ ስንባል የሚሄዱበት እነሱ እንላለን፡፡ ፎቅ ተሰራ፤ ‹የማን ነውና!› ዘር ከዘር ታጋጨ፤ ‹ማን አመጣውና› ዕውነትም ውሸትም አለው ነገሩ፡፡ ህይወታችን የምንግዴ ህይወት ይሆናል፡፡
ሰብዓዊም ሆነ ቁሳዊ ዕሴት ያለን አይመስለንም፡፡ ይሄ የተስፋ ቆራጭነት ሁኔታ (desperado state) ለሀገርም፣ ለህዝብም አደገኛ ነው! አይበጅም! የኢኮኖሚ ችግር፣ የፖለቲካ ድንግዝግዝነትን (obscurantism) ብሎም ጠርዘኝነትንና ዕንፋዊ ጥላቻን ሲፈጥር፤ ‹የመጣው ይምጣ› አስተሳሰብ ይከሰታል፡፡ ማህበራዊ ቀውስ፣ ሥርዓተ-አልበኝነት፣ ምን ዳኝነት፣ ዘራፌነት፣ እኔ ምንተዳዬነት ወዘተ … ይነግሳሉ፡፡ አጠቃላይ ድቀት ይከተላል፡፡ ማንም ስለ ማንም መጨነቁን ይተዋል፡፡ ከዚህ ይሰውረን!!
ዛሬ በሀገራችን የአሳሳች መረጃዎችና ሰነዶች መብዛት ከአቅም በላይ የደረሰ ይመስላል፡፡ የወንጀለኛ መቅጫ ህጉ አለ፡፡ የተጭበረበሩ ሰነዶች ግን ከመፈጠር አላባሩም፡፡ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ፣ በሀሰት የተፈበረከ (Forged) ፈቃድ… ለምሳሌ የህንፃ ፈቃድ፣ የቀበሌ መታወቂያ፣ የግንባታ ፈቃድ፣ የመንጃ ፈቃድ፣ የንግድ ፈቃድ፣ አልፎ ተርፎም የጋብቻ ሰርተፍኬት ሳይቀር በሙስና አዋላጅነት፣ በሽበሽ ሆነዋል! የቀረው የአመፅ ፈቃድ “በፎርጅድ” ማሰራት ብቻ ነው ተብሏል! እጅ ላይ ያለው ችግር በአግባቡ መፍትሄ ባለማግኘቱ፤ ከድጡ ወደ ማጡ መሄዳችን ግድ ሆኗል፡፡ ብዙ ነገር ካንሰር - አከል በሽታ ሆኖብናል። አሰቃቂው ነገር፤ የጉዳዩ ተወናዮች- አለቃውም ምንዝሩም፣ ህግ አውጪውም፣ አስፈፃሚውም፣ መሆናቸው ነው! እርምጃ ማን ይውሰድ? አሰኝቶናል፡፡ ህገ-መንግሥቱንም፣ ህዝቡንም የረሱ አያሌ ሹማምንት ለመኖራቸው ዛሬ ብዙ አያጠራጥርም! ህገ ወጥነት ጣራውጋ ሲደርስ ማጣፊው ያጥራል! “የንጉሡን ፊት አይተህ ፈገግ በል›› የሚለውን ተረት፤ በየደረጃው እንደመሪ መፈክር የያዙ በርካታ ናቸው። ሁኔታዎች ከቁጥጥር ውጪ የሆኑ ለታ ግን ሁሉን ጥፋት በክልል ከማላከክ አልፈን የራስ ተጠያቂነት አፍጦ ይመጣል፡ ‹‹ባሪያ ላግዝሽ ሲሏት መጇን ትደብቃለች›› የሚለው ተረትም በመንግስትና በባለሙያ መካከል ይታያል፡፡
እያደር ዕውን የሆነና የሚሆን ግጭት፣ ፍጭት፣ ወደ ዘረኝነት አቅጣጫ ለመሄድ እርሾው የሚታይና አብሲቱ የተጣለ የሚመስልበት ሁኔታ፣ ብዙው የፖለቲካ ጨዋታ ሲሟጠጥ እንደሚሆነው ሁሉ ወደ ጡንቻ የሚሄድ፣ የደም መፋሰስ ትርዒት ማየት፣ ስለ ብዙ ሰላም ለምታወራ አገር የሚያምር ቁም ነገር አይደለም፡፡ ያለመረጋጋት አስረጅ ይሆናልና ከወዲሁ መገደብና ሰላማዊ መፍትሔ መሻት አስፈላጊ ነው። ቁጣን በቁጣ መመለስ አባዜው ብዙ ነው! የተኙት ብዙዎች፣ የተናደዱትና የነቁት ጥቂቶች ሲሆን፤ የበሠለ አመራር በስሜታዊነት ይዋጣል፡፡ ቁጣ ቦታ የሚያገኘው ይሄኔ ነው፡፡ መጠንቀቅ ይገባል፡፡ ሆድ ሰፊ መንግሥት an eye for an eye (ዐይን ያወጣ ዐይኑ ይውጣ) ከሚል ጥንታዊ ‹ህግ› የተላቀቀ ሊሆን ይገባዋል፡፡ የሠለጠነ ህግ አለውና፡፡ ህግ እንዳለ ከረሳን ግን የአልዛይመር ምርመራ ማረግ ነው፡፡
አሁንም የውስጥ ምርመራ ያስፈልጋል- የከአንገት በላይ ምርመራው ብቻ በቂ አይሆንምና፡፡ ትንሽ ቁስል ሰፍታ ሰፍታ የአገር ህመም የምትሆን ከሆነ ጠቅላላ ምርመራ የግድ ነው፡፡ ክፍሎቻችን ሁሉ በቅጡ ይመርመሩ!!
የሚጠራቀሙ ጥቃቅን ብሶቶች፤ ልክ ጠብ ጠብ እንደሚሉ የውሃ ጠብታዎች ናቸው፡፡ ሲጠራቀሙና አቅም ሲያገኙ ጎርፍ ይሆናሉ፤ ይላሉ የጥንቱ የጠዋቱ የቻይናው ማዖ ዜዱንግ፤ ትግላቸውን ነብሱን ይማረውና፡፡ ጫማ ልክ አልሆን ሲል እግር የመቁረጥ ፖለቲካም አይሠራም ይላሉ፡፡ ጥቃቅንና አነስተኛ ችግሮች፤ ያለ አራሚ እንደሚያድጉ አረሞች ናቸው፡፡ እያደር ዙሪያ ገባውን ዳዋ እንዲውጠው ያደርጋሉና። ከዚያ ‹‹አይጥ በበላ ዳዋ ተመታ›› ነው ተከታዩ፡፡ ሀገራችን ከዚህ ‹‹ውጣ እምቢ፣ ግባ እምቢ›› አጣብቂኝ የሚያወጣት መላ መምታት አለባት፡፡ ቅርቃር ውስጥ ናት - በሰላምና በሰላም ማጣት ራስ-ምታት መካከል። ቅርቃሩ ጊዜያዊ ነው ወይስ አይደለም? መመርመር ነው!! አሁንም ጠብታዎች ጎርፍ፣ ጎርፎች ዥረቶች፣ ዥረቶች ወንዞች እንዳይሆኑ፤ ቅድመ ማስጠንቀቂያዎችን ማየት ደግ ነው፡፡ ላቲኖች፤ ‹‹ጎርፍም ያለ እርከን፤ ምራቅም ያለ ከንፈር አይቆምም›› ያሉት ልብ ማለት ይጠቅመናል፡፡


• ሁሉም የኢትዮጵያ ብሔር፣ የአንድ አባትና እናት ልጆች ነው
• አዳም የተፈጠረው ጎጃም፤ ኖህ መርከቡን ያሳረፈው አራራት ተራራ ላይ ነው
• ስለ ኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አጥንቼ አለሁ ይላሉ …


ኑሮአቸውን በአሜሪካ ያደረጉት ታዋቂው የሥነፅሁፍ ምሁር ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሣ፤ የፃፉት‹‹የኦሮሞና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ›› የተሰኘ አዲስ አነጋጋሪ የታሪክ መፅሐፍ ዛሬ ለገበያ ይቀርባል፡፡ የኦሮሞና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ ማን እንደሆነ በጥናት ደርሼበታለሁ
የሚሉት ፕሮፌሰሩ፤ እስከ ዛሬ የተለያዩ የታሪክ ምሁራን ከተናገሩት ፍፁም የተለየና አዲስ የጥናት
ውጤት ማግኘታቸውን ይናገራሉ፡፡ የሁለቱ ቋንቋዎች አመጣጥም በጥናቱ ተካቷል ብለዋል፡
፡ በሊንከን ዩኒቨርሲቲ በሂዩማኒቲስ የትምህርት ዘርፍ የሚያስተምሩት ፍቅሬ ቶሎሳ ፤ከዚህ ቀደም
‹‹Heaven to Eden›› እና ‹‹The Hidden and untold History of the Jewish People and
Ethiopians›› የሚሉ መጽሐፍትን በእንግሊዝኛ ቋንቋ ያሳተሙ ሲሆን ሁለቱም በኢንተርኔት
“አማዞን” በተባለ የመፅሃፍ ሽያጭ ድረገፅ ላይ ከተፈላጊ መፃህፍት ተርታ ተሰልፈዋል፡፡ በሙያቸው
ፀሃፌ-ተውኔትና የሥነ ፅሁፍ ምሁር ሲሆኑ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ጥልቅ ጥናትና ምርምሮችን
በማድረግም ይታወቃሉ፡፡ አንጋፋው ምሁር ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም በቅርቡ ለንባብ ባበቁት
“አዳፍኔ” የተሰኘ መፅሃፋቸው ላይ፤“የኦሮሞን ታሪክ ሙሉ አደርጎ ሊፅፍ የሚችለው ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ ብቻ ነው” ሲሉ ለብቃታቸው ምስክርነትና ዕውቅና መስጠታቸው አይዘነጋም፡፡ ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሣ በርካታ ቲያትሮችን ለደረክ ያበቁ ሲሆን ከእነዚህም መካከል “ጓደኛሞቹ”፣ “ፍቅር በአሜሪካ” እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡ በቅርቡም ‹‹ላሟ›› የተሰኘ ባለ ሁለት ገቢር ቲያትር ፅፈው ማጠናቀቃቸውንም ተናግረዋል፡፡ ፕሮፌሠሩ ለአጭር ጊዜ ዕረፍት ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበረ ሲሆን ወደ አሜሪካ ከመመለሳቸው በፊት ከአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ ጋር በታሪክ ጥናቶቻቸው ዙሪያ ቃለ ምልልስ አድርገዋል፡


በእንግሊዝኛ ቋንቋ ያሳተሟቸው “Heaven to Eden” እና “The Hidden and untold History of the Jewish People and Ethiopians›› የሚሉት መፃህፍት በአለማቀፍ ደረጃ ሰፊ ተቀባይነት ያገኙበት ሚስጥር ምንድነው? በምን ርዕሰ ጉዳይ ላይ ነው የሚያተኩሩት?
የመፅሐፍቱ ይዘት ነው ወሳኙ፡፡ ተቀባይነት ያገኙት በቋንቋ አጠቃቀም ለአንባቢያን ምቹ ስለሆኑ ይመስለኛል፡፡
በአይሁዶች ታሪክ ላይ የሚያተኩረው መፅሐፍ፤በጉዳዩ ላይ ከተጻፉ ሌሎች መጻህፍትና በተለምዶ ስለ አይሁዶች ከሚታወቀው ምን የተለየ ነገር ይዟል?
ብዙ ጊዜ ስለ አይሁዳውያን ሲወራ፣ቀዳማዊ ሚኒልክ የዛሬ 3ሺህ ዓመት፣ 40ሺህ አይሁዳውያንን ይዞ መጣ የሚለውን ነው የምናውቀው፡፡ ከመጡት መካከል 12ሺህ ያህሉ ንፁህ እስራኤላውያን ናቸው። 28ሺህ ያህሉ እነሱን በሥራ ያገለግሉ የነበሩ ኢያቡሳውያን የሚባሉ ነገዶች ናቸው፡፡ ቀዳማዊ ሚኒልክ ለ12 ሺህዎቹ ልዩ ቦታ ሰጥቷቸው፣ በሀገሪቷ ላይ ካህናት አድርጎ ታቦት እያስቀረፀ፣ ኢትዮጵያ ላይ በዚህ መልክ ሾሟቸው ነበር፡፡ ኢያቡሳውያን ደግሞ ንጉሱን በእጅ ስራና በውትድርና ያገለግሉት ነበር፡፡ ይሄ እንግዲህ አይሁዳውያን ወደ ኢትዮጵያ ያደረጉት ሁለተኛው ፍልሰት ነው፡፡
የመጀመሪያውና ብዙም የማይነገረው የአይሁዳውያን ፍልሰት፣ የእስራኤላውያኑ መሪ ሙሴ በህይወት እያለ አባ ብሄር የሚባል ልኡል ነበር። የሙሴ አማች ነው፡፡ አባ ብሄር የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ሊሆን ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣ፣አይሁዳውያን ተከትለውት መጥተው ነበር፡፡ ምክንያቱም አባ ብሄር ያገባት ልጅ የሙሴ እህት ነበረች፡፡ ሙሴ በወቅቱ ለአባ ብሄር ፅላት ቀርፆ እንዲሁም ቀይ ባህርን የከፈለባትን በትር ሰጥቶት፣ወደ ሳባ ከተማ መጥቶ ነግሷል፡፡ በወቅቱ ብዙ አይሁዳውያንም ተከትለውት መጥተው ነበር፡፡
ሶስተኛው ፍልሰት የምንለው፣የኢራቁ ናቡከደነፆር አሸንፏቸው በሚያሳድዳቸው ጊዜ፤ “ኢትዮጵያ ውስጥ አይሁዳውያን ወገኖች አሉን” ብለው ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል፡፡ አይሁዳውያን በነዚህ መንገዶች ነው ወደ ኢትዮጵያ የመጡት፡፡
 ትክክለኛዎቹ አይሁዳውያን በኢትዮጵያ ያሉት ናቸው የሚሉ ወገኖች አሉ…?
የሃይማኖታቸውን ስርአት፣ መፅሃፍትና ህግጋት ከመጠበቃቸው አንፃር ከሌላ ህዝብ ጋር ስላልተደባለቁ ትክክለኛው ያለው እነሱ ጋ ነው፡፡ ሌሎቹ ወደ አውሮፓ፣ እስያ፣ አሜሪካ የተሰደዱት እነዚህን ነገሮች በተለያዩ ጫናዎች የተነሳ ሙሉ ለሙሉ ጠብቀው አላቆዩትም፡፡ ወደዚህ የመጡት ግን በግድ ባህላችሁን ሃይማኖታችሁን ለውጡ ተብለው በኢትዮጵያውያን አልተረበሹም፤ነፃነት ነበራቸው፡፡ መሬትና ሁሉ ነገር የተመቻቸላቸው ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ነበር፡፡ ሌላ አገር ላይ ቦታ እንዳይኖራቸው ተደርገው በየጊዜው ይሰደዱ ነበር፡፡ እንደውም በሩሲያ ውስጥ በድንገት አይሁዳውያንን የመግደል ድርጊት ይፈፀም ነበር። ሩሲያውያኑ ተሰባስበው፤“ዛሬ አይሁዳውያንን ገድለን እንምጣ” እያሉ ይዘምቱባቸው ነበር፡፡ ወደ መንደራቸው ሄደው አውድመዋቸው ይመለሳሉ፡፡ ማንም ስለማይበቀልላቸው ደማቸው ደመ ከልብ ሆኖ ነበር የሚቀረው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ግን ከተሰጣቸው ክብር የተነሳ በትንንሽ ንጉስነት ጭምር ይሾሙ ነበር፡፡ በርካቶቹም ካህናትና ሊቀ-ካህናት ተደርገው ለአይሁድ እምነት ተሹመል፡፡ ቀጥሎ ደግሞ የሰለሞን ዘር ነን በሚሉት ውስጥም ገብተው፣ ስርወ መንግስት እስከ መመስረት የደረሱ ነበሩ፡፡ በዓለም ላይ አይሁዳውያን ደልቷቸው የኖሩት ኢትዮጵያ ላይ ብቻ ነው፡፡ በጠቅላላው በኢትዮጵያ ሀገራት ማለትም፡- በግብፅ፣ የመን፣ ኑቢያ---ኢትዮጵያ ባስተዳደረቻቸው አካባቢዎች በሙሉ በክብር ተይዘው ነው የኖሩት፡፡ ትልቁ ማስረጃ ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ፣ እናቱ ማርያምና ቅዱስ ዮሴፍ በስደቱ ዘመኑ እኛ ጋ ብቻ ነው ጥገኝነት ያገኙት። በወቅቱ ግብፅ ለሁለት ተከፍሎ ነበር፡፡ አንዱ ክፍል በሮማውያን ቁጥጥር ስር ነበር፡፡ ሁለተኛው የኢትዮጵያ ክፍል ነው፡፡ ኢየሱስ ከመወለዱ ከ880 ዓመት በፊት አማራዎች፤ አማሩላ ደልታ ወደሚባል ቦታ ሄደው፣ አክሱማይት የተባለውን ህፃን ልጅ ዙፋን በመጠበቅ ያገለግሉ ነበር፡፡ በኋላ በ800 ዓመታት ውስጥ አማሩላ ደልታ የሚባል መንደር መስርተው ነበር፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ጋርና ከቅዱስ ዮሴፍ ጋር ሲሸሹ፣ እዚያ ነው ማረፊያ ያገኙት፡፡ ይሄ መፅሃፍ ቅዱስ ውስጥ የለም፤እኛ ግን ከተለያዩ መዛግብት እናገኘዋለን፡፡ በወቅቱ የአካባቢው ንጉስ አማናቱ ተትናይ ይባላሉ፡፡ ከጎጃም ከጣና አካባቢ ነው ወደዚያ የሄደው፡፡ ሌላው አይሁዳውያኑ መፅሐፍ ቅዱሳቸው ሲጠፋባቸው ከኛ ነው የወሰዱት፡፡ አፄ ደንቀዝ የተባለው ንጉሰ ነገስት ነው ከግዕዝ ወደ እብራይስጥ አስተርጉሞ የሰጣቸው፡፡
ትክክለኛውን የአይሁድ ባህልና እምነት በመጠበቅ በኢትዮጵያ ያሉት አይሁዳውያን ብቸኞቹ ናቸው ማለት ይቻላል?
አዎ! ኦሪትን ይዘዋል፡፡ ግን በደማቸው ከኛ ተደባልቀዋል፡፡ በዚህ ምክንያት ነው ሃበሻ የተባሉት። ሃበሻ ማለት የተደባለቀ ነው፡፡ “አበሳ” ያለበት ወይም እንከን ያለበት ማለት ነው፤ ሃበሻ ማለት፡፡ በቀዳማዊ ሚኒልክ ጊዜ የመጡት ከኛ ጋር ተደባልቀው 560 ዓመት ከቆዩ በኋላ በባቢሎን ስደት ጊዜ ሶስተኛዎቹ ሲመጡ፣ነባሮችን ሲያዩአቸው በመልካቸው አይሁዳውያንን አልመስል አሏቸው። ስለዚህ፤“እናንተማ ክልስ ናችሁ፤አበሳ አለባችሁ” ብለው ይሰድቧቸዋል፡፡  ነባሮቹ አይሁዶች ደግሞ፤ “እናንተ ፈላሾች፤እኛ ሀገር አለን” እያሉ ይሰድቧቸው ነበር፡፡ በዚህም “አበሻ” እና “ፈላሻ” የሚለው መጠሪያቸው ሆነ፡፡ “ሀበሻ” የሚለው ቃል እኛን አይወክለንም የምለው ለዚህ ነው፤ሀበሻ አይሁዳውያኑን ነው የሚወክለው፡፡ እኛ የኢትዮጰያ ልጆች ነን፤ ኢትዮጵያውያን ነን፡፡
“በሃበሻነቴ እኮራለሁ” ስንል የከረምነውስ-----ቀለጠ ማለት ነው?
አዎ! እኔ ኢትዮጵያዊ እንጂ ሀበሻ አይደለሁም። ሀበሻ የሚለው ቃል የስድብ ቃል ነው፡፡ እኛን አይወክለንም፡፡ አይሁዳዊ ካልሆነ በስተቀር አንድ ሰው ራሱን “ሀበሻ ነኝ” ብሎ ሊጠራ አይገባውም። ስድብ አያኮራም፡፡ ብዙ ሰው ስለማያውቅ ነው በሀበሻነቴ እኮራለሁ የሚለው፡፡ በአረብኛም ብናየው “የተደባለቀ”፤ “ንፁህ ያልሆነ” ማለት ነው። ይሄ መልካም ቃል አይደለም፡፡ ግን ሀበሻ የሚለው “አበሳ” ከሚለው እንጂ ከአረብኛ የመጣ አይደለም። ሁለቱ አይሁዳውያን መሃል ያለ የመሰዳደቢያ ቃል ነው እንጂ እኛ ኢትዮጵያውያንን አይመለከተንም፡፡
‹‹ኢትዮጵያ›› የሚለውስ ከየት የመጣ ነው?
ኢትዮጵያ የሚለው ‹‹ኢትዮጵ›› ከተባለው ሰው የመጣ ነው፡፡ ኢትዮጵ ማን ነው ካልን፣ በመፅሐፍ ቅዱስ ላይ የተጠቀሰው መልከፀዴቅ የሚባል የሳሌም ንጉሰ ነገስትና ሊቀካህን ነበር፡፡ ይህ ሰው ሃገር ያስተዳድራልም፤ሃይማኖትም ይመራል፡፡ እሱም የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነበር፡፡ ይሄ እንዴት ይሆናል ከተባለ፣ኢየሱስ በምፅአት ቀን ሲመጣ፣ የንጉስ ንጉስ፣ የካህን  ካህን ሆኖ ነው፤መልከፀዴቅም የዚህ ምሳሌ ነው፡፡ ኢትዮጵያን ከዚሁ ጋር ምን ያገናኛታል ሊባል ይችላል፡፡ በጣም የሚያኮራ ግንኙነት አለው፡፡ የመልከፀድቅ ልጅ ኢትኤል ይባል ነበር፡፡ እግዚአብሔር ኢትኤልን ካለህበት የሳሌም ምድር ለቀህ ጣና ላይ ስፈር አለው፡፡ ‹‹ከዚያም ያንተ የልጅ ልጆች፣ እኔ ከ2000 አመታት በኋላ በምወለድበት ጊዜ በኢትዮጵያ  ግዛት ላይ ስለ መወለዴ ኮከብ አሳይሃለሁ” ይለዋል (እንደኔ ምርምር፤ይሄ ኮከብ የተባለው መልአኩ ገብርኤል ነው) በዚህ ሁኔታ ኢትኤል አሁን ወዳለችው ኢትዮጵያ ሲደርስ እግዚአብሔር፤‹‹ኢትዮጵ›› ተብለህ ተጠራ አለው፡፡ ‹‹ኢት›› - ስጦታ ማለት ነው፡፡ ‹‹ዮጵ” - ማለት ደግሞ ቢጫ ወርቅ ነው፡፡ ስለዚህ “ቢጫ ወርቅ ስጦታ” ተባለ፡፡ በኋላ ሃገሪቷን ኢትዮጵያ አሠኛት፡፡
በመፅሐፍ ቅዱስ በተደጋጋሚ ኢትዮጵያ ተብሎ የሚጠቀሰው ስም የትኛዋን ኢትዮጵያ ነው የሚወክለው?
እሱ አሁን ያለችውን ኢትዮጵያን ነው የሚወክለው፡፡ ግን ኢትዮጵያ የሚለው መጠሪያ እስከ 13ኛው ክ/ዘመን ድረስ ለመላዋ አፍሪካ መጠሪያ ሆኖ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ በኋላም የመጣው አፍሪካ የሚለው ስም ከዚሁ ከኢትዮጵያ የተገኘ ነው፡፡ ከአፋሮች ነው አፍሪካ መጠሪያዋን ያገኘችው፡፡ በመፅሃፈ እዝራ ምዕራፍ ስድስት ላይ፤‹‹አፍሪካንሳውያን›› ይላል፡፡ ይሄ አፋሮችን ነው የሚወክለው፡፡ በመርከብ ስራ በቀይ ባህር ላይ የተራቀቁ ሰዎች ነበሩ፡፡ የዛሬ 3ሺህ አመት ንጉስ ሰለሞን ቤተመቅደሱን ሲሰራ፤ልዩ እንጨት፣ እጣን፣ ወርቅ (ኦፊር የተባለ ታዋቂ ወርቅ- በነሱ የተሰየመ) ጭምር ይነግዱና ለንጉሡ ያቀርቡ ስለነበር፣ስማቸው የገነነ ሆኖ አፍሪካንሳውያን የተባሉት፡፡ በሳይንሱም አፋር የሰው ዘር መገኛ እያልን ነው፡፡ ኢስያውያንም ስያሜያቸውን ያገኙት ከሣባ ቀድሞ ከነገሰው ‹‹ኢስአኤል›› ከተባለው ንጉስ ነው፡፡ ምድሪቱን ያስተዳድር ስለነበር ኢስያ ተባለች፡፡ ‹‹አፄ” የሚለውም ከዚህ የመጣ ነው፡፡
ኢትዮጵያ የሚለው ከግሪክ ቃል የመጣ ነው የሚለውስ ---?
ኢትዮጵያ የሚለው ከግሪክ ቃል  የመጣ ነው የሚለው ውሸት ነው፡፡ ይሄን አጣርቻለሁ፡፡ በነሱ መዝገበ ቃላት ውስጥ ይሄ ቃል የለም፡፡ ‹‹ፊቱ የተቃጠለ›› የሚለው ቃል በግሪክ ቋንቋ ኢትዮጵያ የሚለውን ሳይሆን ሌላ ትርጉም ነው የሚኖረው፡፡ ግሪኮቹ ከኛው ሰምተው ነው መልሠው ኢትዮጵያ ያሉን፡፡ እኛ ከነሱ በፊት ነበርን እንጂ እነሱ ከኛ በፊት አልነበሩም፤ ስማችንን ሊያወጡልን አይችሉም፡፡
በምርምርዎ አዳምና ሄዋን የተፈጠሩበት ቦታ የት ሆኖ አገኙት?
ኢትዮጵያ ውስጥ ነው፡፡ ጎጃም፤ ዳሞትና ጣና አካባቢ ያለ ቦታ ነው፡፡
 ለዚህ ድምዳሜ ማስረጃዎ ምንድን ነው?
አንደኛ ኤደንን ከሚያጠጡ አራት ወንዞች ውስጥ አባይ የምንለው ነው ኤፌሶን የሚባለው። በኦፌር ወርቅ ዙሪያ የሚዞር መሆኑ ተፅፏል፡፡ በኔ ድምዳሜ፣የኤፌሶን ወንዝ የአሁኑ ዋቢ ሸበሌ ነው። ጤግሮስና ኤፈራጥስ ደግሞ ጊዮን ራሱ ጥንት ሜዲትራኒያን ባህር ይገባ ነበር፡፡ ድሮ ሜድትራኒያን “ኪቲ” ይባል ነበር፡፡ ጥንት ጊዮን ወንዝ ሜድትራኒያን ሲደርስ ተራራ ስለነበር ተጋጭቶ ይመለስ ነበር፡፡ ከዚያ ነው መሬት ተነቃንቆ፣ቦታው ተቆራርጦ አሁን ወዳለበት ኢራቅ የሄደው እንጂ አካባቢው እዚሁ ነበር፡፡
አዳም የት ተፈጠረ ለሚለው በመፅሃፈ ሄኖክ ላይ “ኤልዳ” በሚባል ቦታ ተፈጠረ ይላል፡፡ ኤልዳ ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ያለው፡፡ ምክንያቱም አስሌዳውያን ወይም ኤልዳውያን የሚባሉ አሁንም ድረስ ጎጃም ውስጥ አሉ፡፡ ሄኖክ በመፅሃፉ ኤልዳ ነው የተፈጠረው ይላል፡፡ ከዚያ ወስዶ ነው እግዚአብሄር በ40 ቀኑ ወደ ኤደን ገነት የከተተው ይላል፡፡ ሄዋንን ደግሞ ከአዳም ጎን አውጥቷት ነው በ80 ቀኗ ወደ ኤደን ገነት የከተታት፡፡ ከዚህ ተነስቶ ነው ወንድ በ40፣ ሴት በ80 ቀን ክርስትና የሚነሱት። ይሄ አይነቱ ስርአት በዓለም ላይ የትም የለም፤እና ይሄ በሄኖክ መፅሃፍ የተፃፈውና አሁን ያለው እውነታ ይገኛል፡፡
ሌላው ኮሬብ የሚባል ዋሻ ውስጥ አዳም ተቀበረ ይላል፡፡ በእርግጥ በሲናይ በረሃ አካባቢ ኮሬብ የሚባል ቦታ አለ፤ ግን በተመሳሳይ ይህ ቦታ ኢትዮጵያ ውስጥም አለ፡፡ ሌላው ኖህ መርከቡን ያሳረፈው አራራት ተራራ ላይ ነው ይላል፡፡ አራራት ተራራን ለመፈለግ ወደ ቦታው ሄጄ ነበር፤ በታንኳ ጣናን አቋርጬ፡፡ አራራት ተራራ የሚባለውን ሳገኘውና አቀማመጡን ሳጠናው፣ ለመርከብ ማሳረፊያነት በአናቱ ላይ ምቹ ሜዳ አለው፡፡ ኖህ ወይን ጠጅ ጠጥቶ ሰክሮ ነበር ይላል፤መፅሃፍ ቅዱስ፡፡ በእርግጥም ቦታው የወይን ጠጅ ፍሬ ለማብቀል ተስማሚ ነው፡፡ አሁንም አትክልቶችና ጌሾ ይበቅልበታል፡፡ ከዚሁ ማስረጃ ሳልወጣ፣አዲስ አመትን አበቦች አብበው አከበረ፤የእንጨት መስዋዕትም አደረገ ይላል፡፡ ይሄ እንግዲህ ዛሬ በመላ ኢትዮጵያ ያለው የአዲስ ዓመት መቀበያ ስርአት፣ ከየት መጣነትን ሊያስረዳ ይችላል። በኋላ ወደ ክርስትናው የመስቀል በዓል ደመራነት ተለወጠ እንጂ በፊት ደመራ የሚነደው በአዲስ ዓመት መጀመሪያ ላይ ነው፡፡ ለዚህ ማስረጃው አሁንም ድረስ ክርስቲያን ያልሆኑ የሀገራችን ሰዎች የደመራ ስርአት አላቸው። ይሄ የአባታቸው የኖህ ትዝታ (ማስታወሻ) ነው ሲወረስ ሲዋረስ የመጣው፡፡ በዚህና በኖህ ጉዳይ ሰፊ ጥናት እያደረግሁ ነው፤ወደፊት ይፋ ይሆናል፡፡ አንድ እዚህ ላይ ልጠቅሰው የምፈልገው፣ሌላ አራራት የሚባል ተራራ አርመን ውስጥ አለ፡፡ ተራራው ግን በረዶ ያለበት፣ ገደላገደል፣ እንኳን መርከብ ሊያሳርፍ ለሰው ልጅ የማይመችና የማያብብ ቦታ ነው፤ ስለዚህ ያ ሊሆን አይችልም፡፡
በሰንደቅ አላማው ላይም የተለየ መከራከሪያ ያቀርባሉ፡፡ ለኢትዮጵያ የተሰጠ ስጦታ ነው ሲሉ ምን ማለትዎ ነው?
 ሰንደቅ አላማው ለኖህ ከተሰጠው ምልክት የመጣ ነው፡፡ አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ የጎሉበት ቀለማት ሰማይ ላይ ታይተዋል፡፡ እነዚያ ቀለማት ናቸው ዛሬ ያሉት፡፡ ከንግስት ሳባ በፊት የነገሰው አፄ ኢሲአኤል ነው ሰንደቅ አላማ እንዲውለበለብ ያደረገው፡፡ ሰንደቅ አላማ የሚለው የመጣው የኢስአኤል መንግስት “ሰንደቅ አለማ” ከሚለው ነው፡፡ ከዚያ የመጣ ነው። እሱ በወቅቱ የመረጠው፡- አረንጓዴ ቢጫ፣ቀይና ሰማያዊ ቀለማት ነበር፡፡ ለሰንደቅ አላማው ያልተገዛና ያላውለበለበ ይቀጣል ብሎ ለመጀመሪያ ጊዜ አስገዳጅ ህግ ያወጣውም እሱ ነበር፡፡ በሰንደቋ አናት ላይ ኮከብ ነበር የሚቀመጠው፡፡ ኢየሱስ ሲወለድ የሚጠቁመውን ኮከብ ለማስታወስ ይጠቀም ነበር፡፡ በዓለም ላይ ሰንደቅ አላማን የፈለሰፈ የመጀመሪያው ሰውም ሊሆን ይችላል፡፡
የኢትዮጵ የልጅ ልጅ የሆነው ኢስአኤል ከፈለሰፈው ሰንደቅ አላማ ነው፣ዛሬ ያሉት የሰንደቅ አላማ ቀለማት የመጡት፡፡ ስለዚህ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሰንደቅ አላማው ላይ ከዚህ ተነስቶ አንድ አይነት አቋም ቢይዝ መልካም ነው፡፡ ኢስአኤል ለኦሮሞውም፣ ለአማራውም፣ ለትግሬውም፣ለአፋሩም ለሌላውም ብሄረሰብ ሁሉ አባት ነው፡፡ ከአባቶቻችን የወረደ ሰንደቅ አላማ እንጂ ከባዕድ የመጣ አይደለም፡፡
ሰውየው እጅግ ጠቢብ ነበር፤ልእለ ሰብዕ (superman) ነበር፡፡ 150 አንበሳ መግደሉን ለማስታወስ ጭምር አፄ ኢስአኤል የሰብዕ እና የአውሬዎች ንጉሰ ነገስት ብሎ ነበር ራሱን የሚጠራው፡፡ ሰውየው እጅግ ጠቢብ ከመሆኑ የተነሳ የጀነቲክ ኢንጅነሪንግን የፈለሰፈውም እሱ ነው፡፡ እንስሳን ከእንስሳ፣ ዘርን ከዘር እየቀላቀለ የፈለሰፈ የመጀመሪያው የጀነቲክ ኢንጅነር ነበር። በቅሎን የፈጠረውም እሱ ነው፡፡ አህያንና ፈረስን አዳቅሎ፡፡ ይህ ሰው የሁሉም ኢትዮጵያውን አባት ነው፡፡ የኢትዮጵ ልጅ ነው፡፡ የኢትዮጵ 10 ወንዶች ልጆች ናቸው፤ አሁን የምናያቸውን የኢትዮጵያውያን ጎሳዎች ሁሉ የፈጠሩት፡፡    
ሰሞኑን ለአንባቢያን የሚቀርብ መፅሃፍ እንዳዘጋጁም ሰምቼአለሁ፡፡ የመፅሐፉን ይዘት በአጭሩ ሊነግሩኝ ይችላሉ?
መፅሐፉ፤“የኦሮሞና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ” የሚል ነው፡፡ አሁን ያሉት ኢትዮጵያውያን በሞላ የኢትዮጵ ልጆች መሆናቸውን ከላይ አስረድቻለሁ፡፡
አሁን እንደምናው በሁላችንም ላይ የማንነት ቀውስ አለ፡፡ የማንነት ቀውሱ የመጣውም እኛ ማን እንደሆንን በትክክል ባለማወቃችን ነው፡፡ ስለዚህ ይህ መፅሐፍ እኛ ማን እንደሆንን፣በርካታ ታሪካዊ ማስረጃዎችና ሰነዶችን አስደግፎ፣ግልጥልጥ አድርጎ  ያስረዳናል፡፡ ይህ የማንነት ቀውሳችን ከተስተካከለና ራሳችንን ካወቅን፣ በመካከላችን ግጭቶች ሊኖሩ አይችሉም፡፡ መፅሐፉ፤ፍቅር፣ ሰላምና ህብር ሊፈጥር ይችላል የሚል እምነት አለኝ፡፡ እኛ የትልቅ ሰው ዘር ነን የሚለውን በማስረጃ የሚያሳየን ነው፡፡ የሰው ዘር ምንጭ ናሙናዎች መሆናችን ይተነትናል፡፡ ማንነታችንን በትክክል ተረድተን፣ አንድ ላይ ለመጓዝ ያስችለናል ብዬ አስባለሁ - ይህ ብዙ የተደከመበት የምርምር ውጤት፡፡
የኦሮሞና የአማራ የዘር ሀረግ አንድ ነው የሚለውን ነው መፅሃፉ የሚያስረዳው?
አማራና ኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ሁሉም በኢትዮጵያ ግዛት ያለው ብሄር፣ ጎሳ ከ10ሩ የኢትዮጵ ልጆች ነው የመጣው፡፡ ዝቅ ሲል ደግሞ የኢትዮጵ የልጅ ልጅ የሆነ፣ ጎጃም ላይ አዳምና ሄዋን ተፈጥረዋል ብዬ ባልኩት አካባቢ አንድ ጠቢብ ሰው ነበር፡፡ “ደሴት” ወይም “ደሸት” ይባላል፡፡ እሱ ነው የኦሮሞና የአማራ አባት፡፡ የዛሬ 3600 ዓመት 4 ወንዶች ልጆች ወለደ፡- መንዲ፣ መደባይ፣ ማጂ፣ ጅማ የሚባሉ፡፡ እነዚህ 4ቱም አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ የሀገር መጠሪያ ሆነዋል። ማጂ ደግሞ ማራ እና ጀማን ይወልዳል። ዛሬ አማራ የምንለው ማራ ነው፡፡ “ማራ” ማለት “እውነተኛ ብርሃን” ማለት ነው፡፡ አማራ ያሉት አጋዚያን ወይም የግዕዝ ቋንቋ ተናጋሪዎች ናቸው፡፡ ማጂ ማራን ወለደ ካልን፤ ጀማ እና ማራ ወንድማማቾ ናቸው፡፡ ሁለቱ ወንድማማቾች በአካባቢው ካሉት ጋፋቶች ጋር መዋጋት ሰልችቷቸው፣ ሃገር ለቀው ወደ ሸዋ ሲመጡ አንድ ወንዝ ያገኛሉ፡፡ ወንዙን ጀማ አሉት። አሁን የጀማ ወይም የ“ዠማ” ወንዝ ማለት ነው። ከአካባቢው እየራቁ ሲሄዱ የጥንት አባቶቻቸውን ቋንቋ “ሱባ”ን ትተዉ አማርኛን መፈልሰፍ ጀመሩ፡፡ መደባይ፣ ጅማና መንዲ ደግሞ ግማሾቹ ጎጃም ላይ ቀሩ፤ ግማሾቹ ወለጋ ሄዱ፤ሌሎቹም እየራቁ በምስራቅ አፍሪካ ተሰራጩ፡፡ ኦሮሚኛ ቋንቋ የሚባለውንም ፈጠሩ፡፡ በዚህ ሁኔታ ነው ዛሬ ያሉት ኦሮሞና አማራ የመጡት፡፡ ዘረ ደሸት ይባላሉ፡፡ የደሸት ልጆች ናቸው። የዘር ሀረጋቸው አንድ ነው፡፡ ቋንቋቸው የተለያየ የሆነው በሂደት ነው፡፡
ኦሮሞው የኩሽቲክ፣ አማራው የሰሜቲክ ዘር ናቸው፤ የመጡትም ከውጭ ነው የሚለው ለዘመናት የዘለቀ ታሪክስ …?
እሱ ፈፅሞ ውሸት ነው፡፡ ሁለቱም ከውጭ አልመጡም፡፡ እንዳስረዳሁት እዚሁ የበቀሉ ናቸው። የአማራም የኦሮሞም አባት ደሸትም ሆነ ታላቁ አባት ኢትዮጵ ኩሽ ነው፡፡ መልከፀዴቅም ኩሽ ነው። ኦሮሞና አማራ ሁለቱም ኩሽ ናቸው፡፡ አማራ ሴም አይደለም፤ ኩሽ ነው፡፡
እስከ ዛሬ ሲነገር የነበረው ውሸት ነው። ምናልባት የአማርኛ ቋንቋ ከሌሎች ጋር ሲደበላለቅ ሴሜቲክ ቤተሰብ ውስጥ ተገኝቶ ሊሆን ይችላል። ሁሉም ኢትዮጵያውያን የኩሽ ዘሮች ናቸው። በዚሁ መፅሐፌ ላይ ስለ ቋንቋም አስረድቻለሁ፡፡ በእብራይስጥም ሆነ በአረቢክ የሌሉ እንደ ጨ፣ቀ፣ፀ ያሉ ድምጾች በአማርኛና በኦሮሚኛ ቋንቋ ውስጥ አሉ። ይሄን በዝርዝር በመፅሐፉ አስቀምጫለሁ፡፡
ኦሮሞና አማራ አንድ ነው የሚለው አመለካከት በተለይ በኦሮሞ ምሁራን ዘንድ እምብዛም ተቀባይነት ያገኘ አይመስልም፡፡ በግድ ኦሮሞን አማራ ለማድረግ ነው በሚል ወቀሳ የሚሰነዝሩ አሉ …
እንዲህ የሚሉት ሁሉም ከኢትዮጵ ዘር የመጣው የደሸት ልጆች መሆናቸውን ባለማወቃቸው ነው። ይሄ መረጃ ስለሌላቸው ራሳቸውን እንደ ባዕድ አግልለው ስለሚያዩ ነው እንጂ አሁን ይሄ እኔ ያቀረብኩትን ማስረጃ በቅን ልቦና አገናዝበው ለመረዳት ከሞከሩ፣ የትልቁ ሰው የኢትዮጵ፣ የጠቢቡና የሊቀካህናቱ የደሸት ልጅ እንደሆኑ በሚያውቁ ጊዜ፣ እነሱ እንደተሳሳቱ ተገንዝበው ወደ ማንነታቸው ላይ አተኩረው ይኮሩበታል ብዬ አስባለሁ፡፡ የመጣነው ከትልቅ ዘር ነው፡፡ ኦሮሞውም አማራውም የመጣው ከዚህ ትልቅ ሰው ነው፡፡ በዚህ ሁላችንም ልንኮራ ይገባናል፡፡
የአሁኗ እና የቀድሞዋ ኢትዮጵያ ልዩነታቸውና አንድነታቸው ምንድን ነው?
በግዛት ከሄድን ጥንት መላው አፍሪካ ኢትዮጵያ ነው የሚባለው፡፡ ከየመን አልፎ ሁሉ ይሄዳል፡፡ ግብፅ ውስጥ ፈርኦኖች የሚባሉት ኢትዮጵያውያን ነበሩ፡፡ ኢትዮጵያውያን ከአባይ ላይ ከመርከብ ወርደው ሜዳ አግኝተው የሰፈሩበት ቦታ ነው፤ ግብፅ፡፡ የአፍሪካ ሁሉ ነገር ከኛ አይወጣም፡፡
የኢትዮጵያ ታሪክ የ3ሺህ ዘመን ነው ይባላል፡፡ እርሶ የደረሱበት የጥናት ውጤት ምን ይላል?-
አዎ፤ በተለምዶ 3ሺህ አመት ይባላል እንጂ ከ7ሺ በላይ ነው፤ የኢትዮጵያ ታሪክ፡፡ ኖህ ኢትዮጵያ ላይ ነግሷል፤ ከዚያ ጀምሮ 7ሺህ አመት ነው፡፡
እስካሁን በነገሩን ታሪክ ውስጥ መፅሐፍ ቅዱስ ብቻ ነው በማስረጃነት የሚጠቅሱት፡፡ መፅሐፍ ቅዱስን ብቻ የታሪክ ምንጭ ማድረግ ይቻላል?
መፅሐፍ ቅዱስ ብቻ አይደለም፡፡ 42 ሰነዶችን አሁን በሚወጣው መፅሐፌ ላይ በግልፅ አስቀምጫለሁ። እነዚህ ሰነዶች በተለያዩ ሰዎች በጥንት ጊዜ የተፃፉ ናቸው፡፡ ኑቢያ ውስጥ ጀበል ኑባ በተባለ ቦታ ተቀብረው የቀሩ፣በጥንት ፍርስራሽ የኢትዮጵያ ቤተ-ክርስቲያን (ከእስልምና በፊት የነበረ) ድንጋይ ሳጥን ውስጥ ተቀብረው የነበሩ የብራና ሰነዶች አግኝቻለሁ፡፡  በዚያ ላይም የተመሰረተ ነው። ከመፅሐፍ ቅዱስ ውጪ 42 ተጨማሪ የታሪክ ሰነዶችን ተጠቅሜያለሁ፤ይሄን መፅሐፍ ሳዘጋጅ፡፡
ቀጣይዋ ኢትዮጵያ ምን መምሰል አለባት ይላሉ?
አሁን ማንነታችንን አውቀን፣ የማንነት ቀውሳችንን ፈትተን፣ሁላችንም የኢትዮጵያ ዘር፣ የአንድ አባትና እናት ልጆች-----መሆናችንን ተገንዝበን፤ በፍቅር፣ በሰላም፣ በመከባበር፣ በእኩልነት መኖር አለብን ብዬ አስባለሁ፡፡ ሁላችንንም ኢትዮጵ ያገናኘናል፡፡    

  በደርግ ስርዓት የኢህአፓ ታጋይ ሆነው ለእስርና ለእንግልት ስለተዳረጉ ወጣቶች የሚተርከው ‹‹ከኒያ ልጆች ጋር›› የተሰኘ መፅሐፍ ሰሞኑን ገበያ ላይ ዋለ፡፡ ከአባላቱ አንዱ በነበረው ትንሳኤ የተባለ የኢህአፓ ታጋይ ጋር በተደረገ ቃለ ምልልስ፣ በፋሲካ መለሰ የተዘጋጀው መጽሐፉ፤ባለታሪኩ በእስርና በስደት ባሳለፈው ህይወት ላይ ተመስርቶ ስለ ሌሎች ተመሳሳይ ህይወት ያሳለፉ ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች የሚተርክ ሲሆን ወጣቶቹ ምን አይነት ገድል እንደፈፀሙ፤እንዴት እንደታሰሩና እንዴት እንደተፈቱ በስፋት ይተነትናል ተብሏል፡፡ በ17 ምዕራፎች  የተከፋፈለው መፅሐፉ፤ በፋርኢስት ማተሚያ ቤት ታትሞ በክብሩ መፅሐፍ መደብር እየተከፋፈለ ሲሆን በ90 ብር ከ99 ሳንቲም ለአገር ውስጥና በ20 ዶላር በውጭ አገራት ለገበያ መቅረቡ ታውቋል፡፡

• ጃንሆይ አምላክ መባላቸውን በመቃወም፣ጃማይካ ውስጥ የቤተ-ክርስቲያን ማሰሪያ ገንዘብ ሰጥተዋል
• በሻሸመኔ መጀመሪያ መሬት የተሰጣቸው ጥቁር አሜሪካውያን እንጂ ራስ ተፈሪያን አይደሉም
• መስፍን አበበ “በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጊታር ተጫዋች ነኝ” ማለቱ ውሸት ነው

የፎቶግራፍ ባለሙያው ንጉሴ ተሾመ ደጀኔ የተወለዱት በአዲስ አበባ ልደታ አካባቢ ነው፡፡ በልጅነታቸው ከቤተሰቦቻቸው ጋር በኤርትራ ደቀመሀሪ ለተወሰኑ ዓመታት ተቀምጠው ወደ አዲስ አበባ የተመለሱ ሲሆን ለአንድ ዓመት በሊሴ ገ/ማርያም ት/ቤት ተምረው እንደገና ከቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ ሻሸመኔ በማቅናት፣ በአፄ ናኦድ ት/ቤት እስከ 8ኛ ክፍል መማራቸውን ይናገራሉ፡፡ ላለፉት 50 ዓመታት በፎቶግራፍ ባለሙያነት የሰሩት አቶ ንጉሴ፤ ፎቶግራፍ የተጻፈ ታሪክን ተጨባጭና ተዓማኒ ያደርገዋል ይላሉ፡፡ በተለይ እውነቱን የማውቀው ታሪክ ተጣሞና ተዛብቶ ሲቀርብ በጣም እናደዳለሁ የሚሉት ባለሙያው፤ በፎቶግራፎች ማስረጃነት የተዛቡ ታሪኮች እንዲታረሙ ተደጋጋሚ ጥረት ማድረጋቸውን ይናገራሉ፡፡ “ራስ ተፈሪና የራስ ተፈሪያን ማንነት” በሚል ርዕስ የጻፉት መጽሃፍም የህትመት ብርሃን እየተጠባበቀ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ ለመሆኑ ወደ ፎቶግራፍ ባለሙያነት እንዴት ገቡ? ፎቶግራፍና ታሪክን እንዴት አስተሳሰሩት? እስካሁን ምን ያህል የተዛቡ ታሪኮችን በፎቶግራፎች ማስረጃነት ለማረም ሞከሩ? ሥራና ኑሮአቸውስ ምን ይመስላል? የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ለስራ አዳማ በሄደችበት ወቅት፣ የፎቶግራፍ ባለሙያውን አቶ ንጉሴ ተሾመን አግኝታ በሙያቸው ዙሪያ አነጋግራቸዋለች፡፡ እንዲህ ተጠናቅሯል፡-

ቤተሰቦችዎ ከቦታ ቦታ የሚዘዋወሩት በምን ምክንያት ነበር?
በወቅቱ አባቴ ሹፌር ስለነበሩ የተለያየ ቦታ ይጓዛሉ፡፡ በዚህ ምክንያት ቤተሰባችን ተረጋግቶ አይቀመጥም ነበር፡፡ በኋላ ላይ አባቴ ማዕከላቸውን ሻሸመኔ አደረጉና፣ እኛም ከ1949 ዓ.ም ጀምሮ እዚያ መኖር ጀመርን፡፡ አፄ ናኦድ ት/ቤት እስከ 8ኛ ክፍል ተማርኩኝ፤ አባቴም ዲላ ወላይታ እየሄዱ በሹፍርና ይሰሩ ነበር፡፡ በቃ እዚያው አደግሁኝ፡፡ ስለ ሻሸመኔ ብዙ ነገር አውቃለሁ፤ ብዙ የፎቶግራፍ ማስረጃዎችም አሉኝ፡፡
እንዴት ወደ ፎቶግራፍ አንሺነት ሙያ ሊገቡ ቻሉ? ለመጀመሪያ ጊዜ ፎቶግራፍ ያነሱትና ካሜራ የጨበጡት መቼ ነበር?
በ1963 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቴን እንዳጠናቀቅኩ በ27 ብር “ሉቢቴልቱ” የተባለች የራሺያ ካሜራ ከነማኑዋሏ ገዝቼ፣ ከዚያን ጊዜ አንስቶ ከተማ እየዞርኩ ታሪክ ማስቀረት ጀመርኩ። ፍላጎቱ ያደረብኝ በአሰብ መንገድ አንድ ተኮላ የሚባል ኢንጂነር መንገድ እያሰራ ፎቶ ያነሳና ስዕል ይሰራል፤ ስዕሉን ከፎቶው ላይ ነበር አስመስሎ በትልቁ የሚስለው፡፡ እሱ በወቅቱ ያቀረበውን የስዕል ኤግዚቢሽን በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አየሁኝ፡፡ በካሜራ ካነሳሁ በኋላ ነው የምስለው ብሎ ሲናገርም ሰማሁ፤ ለምን እኔስ በካሜራ እያነሳሁ አልስልም በሚል ካሜራውን ገዛሁ፤ከዚያ በኋላ ማንሳቱን ቀጠልኩኝ ማለት ነው፡፡
እስከ ዛሬ ከ200 ሺህ በላይ ፎቶዎችን አንስተዋል ይባላል፡፡ እውነት ነው?
አይበልጥም ብለሽ ነው፡፡ ምክንያቱም ዲጂታል ካሜራ ከመጣ ያነሳሁት እንኳን ብዙ ስለሆነ ያለኝ የፎቶ ብዛት ወደ 300 ሺህ ሳይጠጋ አይቀርም፡፡ የካሴት ከቨር የሆኑ ወደ 300 አልበም ፎቶዎች አሉኝ። የቀድሞው ቱሪዝም ኮሚሽን የሚያሳትመውን ፖስተርና ፖስት ካርድ ሰብስቤ ከ400 በላይ አለኝ፡፡ እነሱ ጋ አንድም የለም፤ሸጠው ሸጠው ጨርሰውታል፤የተሳሳተ ነገር ሲያወጡ እየፃፍኩ አርማቸዋለሁ፡፡  
በሻሸመኔ መጀመሪያ መሬት የተሰጠው ለራስ ተፈሪያን አይደለም፤የሚለውን ማስረጃ ከየት ነው ያገኙት?
 ቀደም ብዬ እንደነገርኩሽ እኛ ሻሸመኔ በቋሚነት መኖር የጀመርነው በ1949 ዓ.ም ነው፡፡ በ1942 ግን በጃንሆይ በጎ ፈቃድ መሬት የተሰጠው ለሶስት አፍሮ አሜሪካዊያን ነው፡፡ እነሱም፡- ግላድስተን ሮቢንሰን፣ ጀምስ ፓይፐር እና ባለቤታቸው ወ/ሮ ፓይፐር ብቻ ነበሩ፡፡
እነዚህ አፍሪካ አሜሪካዊያን እንዴት ከጃንሆይ መሬቱ ሊሰጣቸው ቻለ?
በጣም ጥሩ፡፡ ፋሽስት ጣሊያን ለሁለተኛ ጊዜ አገራችንን በ1928 ዓ.ም በወረረ ጊዜ ጃንሆይ ለአምስት አመታት ለንደን ነበሩ፡፡ ያኔ ጥቁር አሜሪካውያን ኒውዮርክ ሀርለም ላይ ኢትዮጵያን ለማገዝና ለመዋጋት 17 ሺህ ያህል ሆነው ተመዝግበው ነበር፡፡ ነገር ግን ፈረንሳይ፣ ጣሊያንና እንግሊዝ ዙሪያውን ከበው ስለነበር መግባት አይቻልም ነበር፡፡ ስለዚህ ሶስት ተደማጭነት ያላቸው አፍሮ አሜሪካዊያን ተመርጠውና ተወክለው ጃንሆይ የሚኖሩበት ለንደን ድረስ ሄደው አነጋገሯቸው፡፡ የጥቁር አሜሪካዊያኑንም ኢትዮጵያን የማገዝ ፍላጎት አስረዷቸው፡፡ ከህዝቡ ማለትም ከአሜሪካውያኑ የተውጣጣውን አራት ሚሊዮን ብርም ሰጧቸው፤ ምክንያቱም ኒውዮርክ ላይ “የምኒሊክ ክበብ” የሚል አቋቁመው የእርዳታ ገንዘብ ያሰባስቡ ነበር፤ ጥቁር አሜሪካውያኑ፡፡ በኋላ ጃንሆይ “ወደ ኢትዮጵያ መግባት አትችሉም፤ዙሪያውን በቅኝ ገዢዎች የተከበበ ነው፤ ለስንቅና ትጥቅም አይመቻችሁም፤ እዛው ሆናችሁ ታገሉልን” አሏቸው “እንግዲያውስ አንድ አስተባባሪ ስጡን; ብለው ጠየቁ፡፡ ከዚያ ዶክተር መላኩ አማኑኤል በያን የተባለውን የአጎታቸውን ልጅ፣ ጃንሆይ በአስተባባሪነት ሰጧቸው፡፡ ዶ/ር መላኩ በአሜሪካ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ዶ/ር ነው፡፡ ዶ/ር መላኩም አሜሪካ ሄዶ “Ethiopian World Federation” የተባለ ማህበር እ.ኤ.አ በ1937 አቋቋመ፡፡ ከዚያም እርዳታውን እያስተባበረ ለአርበኞች ትጥቅና ስንቅ፣ መድሀኒት፣ ለጃንሆይ መኖሪያ ሁሉን ማሟላት ጀመረ፡፡
 ጦርነቱ ካበቃ በኋላ ጃንሆይ ወደ አገራቸው እንደተመለሱ ለጥቁር አሜሪካዊያኑ ደብዳቤ ፃፉ፡፡ በጣሊያን ወረራ ጊዜ ላደረጉት ውለታ ለማመስገን፣ ሻሸመኔ ላይ መጥተው እንዲኖሩ የሚጋብዝ ደብዳቤ ነው፡፡ በዚህ ግብዣ መሰረት ሚስተር ጀምስ ፓይፐር፣ ባለቤታቸው ወ/ሮ ፓይፐርና ግላድስተን ሮቢንሰን በ1942 ዓ.ም ወደ ኢትዮጰያ መጥተው ሻሸመኔ መኖር ጀመሩ፡፡ የሚገርምሽ ወ/ሮ ፓይፐር ለንደን ውስጥ ለጃንሆይ ምግብ ያበስሉላቸው ነበር፡፡ እንዲያውም በወቅቱ የሻሸመኔ አካባቢ ባላባትና ሹም ፊታውራሪ ጁላ ሾቤ ይባሉ ነበር፡፡ ከዚያም ጃንሆይ ለፊታውራሪው፤“እነዚህ ባለውለታችን ስለሆኑ አምስት ጋሻ መሬት ፈልገህ ለአውራ ጎዳናው ቅርብ የሆነ ቦታ ስጣቸው” ብለው አዘዙ፡፡ ፊታውራሪውም፤ “ጃንሆይ፤ የመንግስት መሬት አውራ ጎዳናው ላይ የለም፤ መሬት ያለው ከከተማው ርቆ ወደ ኮፈሌ ገጠሩ ውስጥ ነው፤እዚያ ደግሞ አውሬዎች በብዛት ስላሉ ለመኖር አስቸጋሪ ነው፡፡ ስለዚህ ወደ ወላይታ ይሂዱና እዚያ ይኑሩ” የሚል ምላሽ ሰጡ፡፡ ጃንሆይ ደግሞ “አይ አንዴ አዝዤሀለሁ፤ከየትኛውም ሰው ላይ ቀምተህ ስጣቸውና ቤተ-መንግስት መጥተህ ሪፖርት አድርግ” የሚል ቀጭን ትዕዛዝ አስተላለፉ፡፡ በዚህ መሰረት ፊታውራሪ ጁላ፤ ከቄስ ገመኔ ላይ ሶስት ጋሻ መሬት፣ ከዋቻሞው ባላባት ላይ ሁለት ጋሻ ቀምተው አውራ ጎዳናው ላይ ያለ መሬት ሰጧቸው፡፡ ከዚያ ጀምስ ፓይፐርና ባለቤታቸው ወይዘሮ ፓይፐር እንዲሁም ግላድስተን ሮቢንሰን ከ1942 ጀምሮ መኖር ጀመሩ፡፡ ባልና ሚስቱ የአይሁድ እምነት ተከታይ ሲሆኑ ግላድስተን ሮቢንሰን የኦርቶዶክስ እምነትን ተቀብሎ ተጠምቆ በኋላ ስሙ ፍቅረ ስላሴ ይባል ነበር፡፡ ስምህ ማን ነው ሲባል እንኳን የባርነት ስሜ ግላድስተን ሮቢንሰን፣ የነፃነት ስሜ ፍቅረ ሥላሴ እያለ ይመልስ ነበር፡፡ በቅርብ ከአራት አመት በፊት ነው ፍቅረ ስላሴ የሞተው፤ እንቀራረብ ነበር፡፡
ታዲያ ጃማይካዊያን መቼ ነው ወደ ሻሸመኔ የመጡት?
ጃማይካዊያኑ በ1962 ዓ.ም ማለትም አፍሮ አሜሪካኑ ከመጡ ከ20 ዓመታት በኋላ ነው ስምንት ሆነው ወደ ሻሸመኔ የመጡት፡፡ አፍሮ አሜሪካኑ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ጃማይካዊያን በወቅቱ በእንግሊዝ ቅኝ አገዛዝ ስር ስለነበሩ ሻይቅጠልና ትምባሆ እያስተከሏቸው ነበር፡፡ ያን  ጊዜ ለራሳቸውም ነፃነት ስላልነበራቸው ኢትዮጵያን እንደ አሜሪካዊያን ሊያግዙ አልቻሉም ነበር፡፡ ከ20 ዓመታት በኋላ በ1962 ዓ.ም ስምንት ጃማይካዊያን መጡ፤በወቅቱ የግቢ ሚኒስትር በነበሩት ፀሐፌ ትዕዛዝ ተፈራወርቅ ኪዳነወልድ፣ ከቤተ መንግስት፤ “በሉ እንግዲህ ከእናንተ ጋር ይኑሩ” ብለው ወደ ሻሸመኔ ላኳቸው፡፡ አፍሮ አሜሪካኖቹ ተቃወሙ፡፡
ምን ብለው ተቃወሙ?
“እኛ አፍሮ አሜሪካዊያን ነን፤እነሱ ጃማይካዊያን ናቸው፤ በምንም አንገናኝም እንዴት አብረን እንኖራለን፤ይሄ መሬት የተሰጠው በኢትዮጵያ ወርልድ ፌደሬሽን ስም ለእኛ ነው” የሚል ነበር ተቃውሞው፡፡ ከዚያም የላኳቸው ፀሀፌ ትዕዛዝ፤“መልካችሁ አንድ አይነት ነው የአገራችሁ ርቀትም እንደዚያው፤በዚያ ላይ ለኢትዮጵያም ያላችሁ ፍቅር አንድ አይነት ነው ስለዚህ አብራችሁ ኑሩ” ሲባል “አብረን አንኖርም” ብለው አሻፈረኝ ሲሉ፣ የጃንሆይ ልጅ ልዕልት ተናኘወርቅ ጣልቃ ገብተው፤ “ለወደፊቱ እኔ ወንዶገነት ወዳለኝ መሬት እወስዳቸዋለሁ፤ አሁን አምስት አምስት ሄክታር ይሰጣቸውና ይቀመጡ; ተብሎ የዝዋይ አውራጃ ገዢ በተገኙበት (ፊታውራሪ ጁላ በወቅቱ ሞተው ስለነበር) ልጃቸው ነጌሶ ጁላ እየለካ፣ አምስት አምስት ሄክታር ሰጥቷቸው መኖር ጀመሩ፡፡ ይህ ሲደረግ የተፈረመው ደብዳቤ በእጄ ላይ ስላለ ማስረጃ ነው፡፡ ይህንን እውነታ ለምን እንደሚቆለምሙት አይገባኝም፡፡
ጃንሆይ ጃማይካን ለመጎብኘት በሄዱ ቀን ሲዘንብ ያደረ ዝናብ ቆመ እንጂ እሳቸው እዚያ ሲደርሱ ዝናብ አልዘነበም ብለው እንደሚከራከሩም ሰምቻለሁ-----
አዎ እከራከራለሁ፡፡ ለምን መሰለሽ----ጃንሆይ በጃማይካዎቹ አምላክ የተባሉት በ1923 ገና ዘውድ እንደጫኑ ነው፡፡ ጃማይካን የጎበኙት እ.ኤ.አ በ1958 ሊወርዱ ሲሉ ነው፡፡ ጉብኝቱም በጃማይካ መንግስት ግብዣ የተደረገ ነው፡፡ የዝናቡን ጉዳይ በተመለከተ ጃንሆይ እዚያ ከመድረሳቸው ከአንድ ቀን በፊት ሲዘንብ አደረና፣ ከገጠር ከአገሪቱ ጥግ ሁሉ ኪንግስተን ከተማ አምላኩን ለመቀበል የመጣውን የጃማይካ ህዝብ ሲቀጠቅጥ አድሮ፣ በነጋታው ጃንሆይ እዚያ ሲደርሱ ዝናብ አልነበረም፡፡ ፊልሙ እኔ ጋር ይገኛል፤ላሳይሽ እችላለሁ፤በዕለቱ በአቀባበሉ ላይ ጃንጥላም አልተያዘም፡፡
ጃንሆይን አምላክ ብሎ የተቀበለውም ያልተቀበለውም የጃማይካ ህዝብ እሳቸውን ለማየት ኪንግስተን ከተማ ወጥቶ ዝናብ እየቀጠቀጠው ስለነበር ጃንሆይ ከአውሮፕላን ሳይወርዱ አየር ላይ ለሶስት ሰዓት ያህል ቆይተዋል የሚባለውስ----?
ትክክለኛውን ስሚኝ፡፡ አየር ላይ አልቆዩም፤እንደውም ከአውሮፕላን ሲወርዱ ህዝቡ አጥሩን ሰብሮ ክቡር ዘበኛውን ጥሶ፣ አውሮፕላኑ ስር ይፍለከለክ ነበር፤ ይሄ ነው የሆነው፡፡
ታዲያ የታሪክ መፋለሱ የመጣው ከታሪክ ፀሐፊዎች ነው ወይስ በጃንሆይ ወገን የተወራ ነው?
እንደውም ጃንሆይ ስለ ራሳቸው አጋንነው የሚያወሩት ነገር የለም፡፡ አንድ ጊዜ ማርከስ ጋርቬይ እንግሊዝ ሊጎበኛቸው ሄዶ እንኳን አልተቀበሉትም፡፡
ማርከስ ጋርቬይ በ1890ዎቹ መጨረሻ “ከኢትዮጵያ አምላክ ይወጣል ወደ አፍሪካ ተመለሱ” እያለ የነበረና አሜሪካ የሚኖር ጃማይካዊ አይደለም እንዴ?
አዎ፤ እሱ ጃንሆይን አምላክ ነው ብሎ የሚናገር፣ በጃማይካዊያን ዘንድ እንደ ትንቢት ተናጋሪ የሚቆጠር ስለነበር፣ እኔ አምላክ ሳልሆን አምላክ እያለ ያወራል ብለው አልተቀበሉትም ነበር። በኋላ ጃንሆይ “ህዝባቸውን ለጣሊያን ትተው ወደ እንግሊዝ ሄደዋል” እያለ ሲከሰሳቸው ዶ/ር መላኩ አማኑኤል በያን ያልኩሽ የጃንሆይ የአጎት ልጅ፣ ክሱን በመቃወም መልስ ይሰጠው ነበር። ስለዚህ ጃንሆይ አምላክ መባላቸውን አጥብቀው ከመቃወማቸው የተነሳ ጃማይካ ውስጥ የቤተ ክርስቲያን ማሰሪያ የሚሆን ገንዘብ ሰጥተዋል፤ ትልልቅ የሀይማኖት መሪዎቻቸውን ሰብስበው፡፡ አባ ላዕከ ማሪያም የተባሉ የኦርቶዶክስ ቄስ በአጥማቂነት መድበው፣ “እኛ የምንከተለውን የኦርቶዶክስ ሀይማኖት ተከተሉ፤ እኛ አምላክ አይደለንም” ነው ያሉት ጃንሆይ። ጃማይካዎች “እናውቃለን ይሄ የትህትና ንግግር ነው፤ ኢየሱስ ክርስቶስም እኔ ክርስቶስ መሆኔን ለማንም እንዳትናገሩ ብሏል በመፅሀፍ ቅዱስ፤ ስለዚህ እኛ እርሶ አምላክ እንደሆኑ እናምናለን” አሉ፡፡ ኦርቶዶክስን የተቀበሉ ተጠመቁ፤ ያልተቀበሉ እርሳቸውን አምላክ ናቸው ብለው ቀጠሉ፤ ይሄው ነው፡፡ ወሬው ግን ከየት ተነስቶ የት እንደሚደርስ ተመልከቺ፡፡ ለምሳሌ የሻሸመኔ ልጆች ማህበር አለን፡፡ ከመሃላችን ትልልቅ የመንግስት ኃላፊዎችም አሉ፤የአካባቢው ተወላጆች የሆኑ----ስንሰበሰብና ራስ ተፈሪያን መጀመሪያ መሬት እንዳልተሰጣቸው፣ ለጥቁር አሜሪካውያኑ የተሰጠ የምስጋና መሬት እንደሆነ በፊት ለፊታቸው ስንናገር፣ ትንፍሽ አይሉም፤ እውነታውን ያውቁታላ፡፡
እርስዎ እንግዲህ የፎግራፍ ባለሙያ እንጂ የታሪክ ተመራማሪ አይደሉም፡፡ ይህን ሁሉ ታሪክ ያወቁት አካባቢው ላይ ስለኖሩ ብቻ ነው ወይስ ታሪክ የመሰነድ ፍላጎትም አለዎት?
በነገራችን ላይ ፎቶግራፍ ስታነሺም ታሪክ ነው የምታሰባስቢው፡፡ አንዳንድ ታሪኮች ተፅፈው በፎቶግራፍ ሲደገፉ ታሪክን የበለጠ ተጨባጭና ተዓማኒ ያደርጉታል፡፡ በዚያ ላይ ፎቶግራፍ ስታነሺ ገብቶሽ አንድን ነገር መሰረት አድርገሽ ስለምታነሺ፣በመረጃነት በአዕምሮሽም በወረቀትም ይቀመጣል፡፡ ታዲያ ታሪክ ሲዛባ ስትመለከቺ፣ ለምን የሚለውን ጥያቄ ታነሺና ፎቶዎቹን በማስረጃነት ታቀርቢያለሽ፡፡ ለምሳሌ በቅርቡ የጊታር ተጫዋቹ መስፍን አበበ በሰይፉ በኢቢኤስ ላይ ቀርቦ፣ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጊታር ተጫዋች ነኝ ብሎ ተናግሯል፡፡ ነገር ግን ውሸት ነው፤አሁን በእርግጥ በህይወት የለም እንጂ ፊት ለፊት እንነጋገር ነበር፡፡ የሆነ ሆኖ እኔ ዘንድ በርካታ መረጃ አለ፡፡ መስፍን አበበ አምስተኛ ጊታር ተጫዋች ነው፡፡ ለዚህም “የጊታር አጀማመር በኢትዮጵያ” በሚል 60 ገፅ ፅሁፍ ፅፌ፣ 120 ያህል ፎቶግራፎች አስገብቼበት ተቀምጧል፡፡ በቅርቡ ይፋ ይሆናል፡፡
የመጀመሪያዎቹን ማለትም ከመስፍን አበበ በፊት ጊታር ተጫውተዋል የሚሏቸውን በቅደም ተከተል ሊነግሩኝ ይችላሉ?
አንደኛ የክቡር ዘበኛው ተዘራ ሃይለሚካኤል በ1952 ዓ.ም ተጫውቷል፣ ሁለተኛው የጅማው ግርማ ምንተስኖት በ1962 ጊታር ይጫወት ነበር፤ በኢቲቪ ሁሉ ይታይ ነበር፡፡ ሶስተኛው በ1968 የዘፈነው ፀጋዬ መርጊያ ነው፣ ሙሉጌታ ረታ አለሙ በ1970 በጊታር ዘፍኗል፡፡ መስፍን አበበ ከአራቱ በኋላ በ1972 ነው የመጣው፡፡ ይሄ መስተካከል አለበት፤ በሚል በመረጃ አስደግፌ በቅርቡ እለቀዋለሁ ብያለሁ፡፡
ሌላው የአርሲዋ ሴት ጉደቱ ካዎ ጉዳይ ነው። ይህቺ የአርሲ ሴት የቀድሞው ቱሪዝም ኮሚሽን ፎቶዋን በፖስት ካርድነት ይጠቀመው የነበረች ሴት ናት፡፡ ስለዚህች ሴት እኔ በ1981 ዓ.ም በዛሬይቱ ኢትዮጵያ ጋዜጣ ላይ፣ “አባቴን አፈላልጉኝ” በሚል ርዕስ ከአስር በላይ መጣጥፍ ፅፌ ነበር፡፡
 ምክንያቱም ፎቶውን ያነሳሁት እኔ ነኝ በሚሉ ሰዎች መሀል ጭቅጭቅ ተነስቶ ነበር፡፡ የሆነ ሆኖ በ2000 ዓ.ም የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር የነበሩት መሀመድ ድሪር፣ የግብርና ሚኒስትር የነበሩት ሰው፣ የኦሮሚያ ባህል ቢሮ ኃላፊው እሷም አሀራ ተቀምጣ፣ ትልቅ ዝግጅት ተዘጋጅቶ አዳማ ላይ 105 ካ.ሜ ቦታ ተሸልማለች፡፡ የሀራምቤ ኮሌጅ ባለቤት ለ10 ዓመት በየወሩ 300 ብር እንድትወስድ ቃል ሲገባ በቦታው ተገኝቼ ፎቶ አንስቻለሁ፤ ስትወስድም አውቃለሁ፡፡ ቦታውን 45 ሺህ ብር መሸጧንም አውቃለሁ፤ነገር ግን በ2006 ዓ.ም በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ምንም እንዳልተደረገላት ክዳለች፡፡
ጋዜጠኛውን ስለ ራሷ የተፃፉ 10 የጋዜጣ ኮፒና 15 ፎቶግራፎች ሰጥተነው፣ 15 ቀን ስጡኝ አስተካክላለሁ ብሎ ሁለት ወር ተጠበቀ፤ አልመለሰም፡፡ ከዚያ እውነታውን በፌስቡክ “የኢቲቪ ጋዜጠኛ የቀደዳ አርበኛ” በሚል ለቀቅኩት፡፡ ይሄው እዚህ አዳራሽ ውስጥ ለጥፌዋለሁ፤ አንብቢው፡፡ እውነተኛ ማስረጃ ስላለኝ አንድም ሰው አልተቃወመም፡፡ ለምን ታሪክ ይዛባል። አቶ ሀብተስላሴ ታፈሰስ መዋሸት ነበረባቸው?
አቶ ሀብተስላሴ-----?
 አቶ ሀብተስላሴ ታፈሰ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት ናቸው፡፡ እኔ በግሌ ለቱሪዝም መበልፀግ በሰሩት ትልቅ ስራ ክብር አለኝ፤ ነገር ግን በዚች ሴት ፖስት ካርድ ላይ አሻጥር ሰርተዋል። ፎቶውን ያነሳት አንቶኒዮ ቪራኖ የተባለው ጣሊያናዊ ነው፡፡ ክሪያዚዝ ዜርፎዝ የተባለ ፎቶ ቤት የነበረው አርመን፣ አሁን ፒያሳ ክሪያዚዝ ኬክ ቤት አጠገብ የነበረ ፎቶ ቤት ባለቤት “ከለር ማተም ጀምሬያለሁና ስጠኝ ጥሩ አድርጌ ላትምልህ” ይልና ከአንቶኒዮ ይቀበላል፡፡ ኮሚሽነሩ የክሪያዚዝ ጓደኛ ስለነበሩ፣እሳቸው ጋ ወስዶ በራሱ ስም አሳተማት፡፡
 አንቶኒዮና ክሪያዚዝ አቶ ሀብተስላሴ ጋ ሄደው ይካሰሳሉ፡፡ ለክሪያዚዝ አግዘው ፍርድ ሳይሰጡ ፎቶዋን እንደያዙ ደርግ መጣና እስር ቤት ከተታቸው፡፡ ከዚያ ራሱ ደርግ ፈታና መልሶ የቱሪዝም ኮሚሽን ኮሚሽነር አደረጋቸው፡፡ ፊልሟን አገኟትና በራሳቸው ስም፤ “Girl On the Baro River Gambella” ብለው አወጥዋት፡፡ ይሄንን ታሪክ ከራሷ ከጉዳቱ ካዎ መስማት ትችያለሽ፤ አርሲ ነገሌ በህይወት ያለች ሴት ናት፤ ታገኚያታለሽ፡፡ ላገናኝሽ እችላለሁ፡፡
ይህን ሁሉ ውሸት ለማጋለጥ ነው በ1981 በዛሬይቱ ኢትዮጵያ ላይ “አባቴን አፈላልጉኝ” በሚል ርዕስ በተከታታይ 10 መጣጥፍ ያወጣሁት፡፡ ያኔ ቱሪዝም ኮሚሽን “ስህተቱን እናርማለን” በሚል የፃፈልኝ ደብዳቤ በእጄ ላይ አለ፡፡
 የኢቲቪው ጋዜጠኛ ይህን ሁሉ ማስረጃ ካሰባሰበ በኋላ ነው ያልሆነ ታሪክ ያወጣው፡፡ በጣም ያሳዝናል፡፡ በተለይ እውነታውን እያወቅሁት ተጣሞና ተዛብቶ ሲቀርብ በጣም እናደዳለሁ፡፡
ሌላው ሰው ጋ የማይገኝና እኔ ብቻ አለኝ የሚሉት ፎቶ አለዎት?
እኔ ከሌላው የምለየው በአንድ ወቅት በምንም ሁኔታ ያነሳሁትን ፎቶ አልጥልም፤ ምክኒያቱም ፎቶ ቅርስ ነው፣ማስረጃ መፅሀፍ ነው፡፡ ሌላው ያነሳና ይጥለዋል፡፡ እኔ  በማንኛውም ጉዳይ ላይ መረጃ ስፈልግ አቀርባለሁ፤ልክ አሁን ለተዛቡ ታሪኮች መረጃ እንደማቀርበው ማለት ነው፡፡ ለፎቶግራፎች ክብር ሰጥቼ በማስቀመጤ ነው ከሌላው የምለየው፡፡ ስለዚህ አንቺ ፎቶ አንስተሸ ከጣልሽ እኔ ጋ አለ፤አንቺ ጋ የለም ማለት ነው፡፡
የፎቶግራፍ ኤግዚቢሽን አቅርበው ያውቃሉ?
በጣም ብዙ ጊዜ በተለያየ ቦታ አቅርቤያለሁ። በጣሊያን ካልቸር፣ በአሊያንስ ኢትዮ-ፍራንሴዝ፣ በፑሽኪን አዳራሽ ---- በበርካታ ቦታዎች አቅርቤያለሁ፡፡
በራስ ተፈሪያን ላይ የጻፉት መጽሀፍ በምን ደረጃ ላይ ነው?
ተፅፎ ካለቀ ቆይቷል፡፡ ታሪኩን በትክክል እንዲቀመጥ ለማድረግ ነው እንጂ ብር የለኝም። አሁን ግን የኔ የፎቶ ተማሪ የነበረ፣ እንደገና እኔን ኤዲቲንግ ያስተማረኝ በኃይሉ ግርማ የተባለ ልጅ፣እንደሚያሳትምልኝ ቃል ገብቷል፤እግዚአብሔር ይርዳው እንግዲህ፡፡
እስኪ ስለ ራስዎ ይንገሩኝ---በምን ሁኔታ ነው የሚኖሩት?
አሁን በቋሚነት የምኖረው አዳማ ነው፡፡ 45 ዓመት እዚህ የኖርንበትን ቤት፣ “ለእናታችሁ ነው ያከራየነው አናቅህም” ተብዬ ሰባት ዓመት ተከራክሬ አሸንፌ፣እዚሁ ቤት ውስጥ ብቻዬን እኖራለሁ። በትዳር በኩል የመጀመሪያዋ ባለቤቴ ከመላዕክና ከሰው የተፈጠረች ነበረች፤ በጣም ትረዳኝ ነበር ፈጣሪ ወሰዳት፤ አላመሰገንኩትም መሰለኝ፡፡
ሁለተኛዋ ባለቤቴ፣ ጥሩ ጥሩ ልጆች ሰጥታኛለች፤ሶ ስት ልጆች ከሰጠችኝ በኋላ እራሴ እንደመጣሁ እራሴ እሄዳለሁ አለች፤ ሸኘሁ መቼስ ምን አደርጋለሁ፡፡ አሁን ብቻዬን ነው የምኖረው፡፡
ልጆችዎ የት ነው ያሉት?
ልጆቹን ወስዳቸዋለች፡፡ ከአባት እናት ይበልጣል በሚል ሀዋሳ ይዛቸው ትኖራለች፡፡ ከሟች ሚስቴ የወለድኳት የመጀመሪያ ልጄ ትዝታ ንጉሴ፣ ራሷን ችላ እየሰራች ነው፡፡ እኔም ራሴን ችዬ እየኖርኩ ነው።



   ሌሊቱ እንደ ልማዱ አሸልቦ ማለዳው ለረፋዱ ቦታውን ሲለቅ ዝናቡም በካፊያ ይተካ ጀመር፡፡ ቀስ በቀስም ሰማዩ እየጠራ ብሩህ ቀን ከፊት ለመዘርጋቱ ተስፋ ይሰጥ ጀመር፡፡
 ሰኔ 23 ቀን 2ዐዐ8 ዓ.ም፣ ቢሾፍቱ ከተማ፡፡ የጨለለቃን ሀይቅ የሚጎራበተውና ሁሌም ፀዓዳ የማይለየው ባለግርማ ሞገሱ ጄክዶ ኦፖርቹኒቲ ፎር ቼንጅ የሥልጠና ማዕከል ግቢ ድባቡ ከወትሮው ለየት ብሏል፡፡ አለፍ አለፍ ብለው በተተከሉ ነጫጭ ድንኳኖች፣ በፌዴራልና በክልል ባንዲራዎችና በማስታወቂያ ባነሮች አሸብርቆ ለሁለተኛ ጊዜ የማህበረሰብ ምሥርት ተቋማትን የመልካም ተሞክሮ ዓመታዊ በዓል ለማክበር ዝግጅቱን ሁሉ አጠናቅቋል፡፡
የዕለቱ ዝናብ ያልበገራቸው የማህበረሰብ ምስርት ተቋማት አመራሮችም በየድንኳኖቻቸው ደጃፍ ላይ ቆመው ለወራት ሲለፉበት የነበረውን ድግሳቸውን ለማቋደስ ጉብኝዎቻቸውን በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡
በኢየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት (ኢ/ህ/ማ/ል/ድ) አዘጋጅነት “የማህበረሰብ ምሥርት ተቋማት አጋርነት ለዘላቂ ልማት” በሚል መሪ ቃል የሚከበረው ይህ በዓል ከተለያዩ የአገሪቷ ክልሎች የተወጣጡ 60 የሚደርሱ የኢ/ህ/ማ/ል/ድ አጋር የማህበረሰብ ምሥርት ተቋማትን ያሳተፈ ነው፡፡ ለችግር ለተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ሁለገብ ድጋፍ በመስጠት የተሻለ ኑሮ እንዲኖሩ በማስቻል ሥራ ላይ ከተጠመደ 30 ዓመታትን ያስቆጠረው ኢ/ህ/ማ/ል/ድ  በአሁኑ ሰዓት በአማራ፣ በኦሮሚያና በደ/ብ/ብ/ህ ክልሎችና በአዲስ አበባና በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች ውስጥ በተለያዩ የማህበረሰብ ልማት እንቅስቃሴዎች ላይ ጠንካራ ተሳትፎ እያደረገ ነው፡፡ በተለይ ላለፉት 15 ዓመታት የማህበረሰብ አቀፍ ተቋማት ጋር በጋራ በመሥራትና አቅማቸውን በተለያየ መልኩ በመገንባት ሕብረተሰቡ የራሱን ችግር በራሱ እንዲፈታ በማስቻል በኩል ጠንካራ ልምድ አካብቷል፡፡ የዚሁ ጥረቱ አካል የሆነው የቢሾፍቱው መርሀ-ግብርም ያለፉትን ስኬቶች ከመዘከር በሻገር የወደፊት አቅጣጫዎች የሚመላከቱበት፤ ማህበራቱም ጠቃሚ ተሞክሮዎችን የሚጋሩበትና የእርስ በርስ ትስስርም የሚፈጥሩበት መድረክ ነው፡፡
የተለያዩ ከተሞች የመንግስት ጽ/ቤቶች፣ የማህበረሰብ ምሥርት ተቋማት፣ የለጋሽ ድርጅቶች እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተወካዮች፣ ጋዜጠኞች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ሁሉ ቀስ በቀስ ወደማዕከሉ እየደረሱ ጊቢውም ሞላ ማለት ጀመረ፡፡ የዕለቱ ዋነኛ ባለጉዳዮች የማህበረሰብ ምሥርት ተቋማት ተወካዮችም እስከመጨረሻው ሰዓት ድረስ ተፍ ተፍ ማለታቸውን አላቋረጡም፡፡  
ልክ ከጠዋቱ 3፡3ዐ ሰዓት ሲሆን የዕለቱ የክብር እንግዳ የቢሾፍቱ ከተማ ከንቲባ ተወካይ፣ ወ/ሮ ዘውድነሽ አሰፋ የበዓሉን በይፋ መከፈት አበሰሩ፡፡ እናም የሁሉም ትኩረት የመጀመሪያው መርሀ-ግብር ወደሆነው ወደ ተቋማቱ የልማት አስተዋፅኦ ዐውደ-ርዕይ ሆነ፡፡ ይሄን ጊዜ በማህበረሰባቸው ለማህበረሰባቸው የተቋቋሙትና በሰዎች ሞት ጊዜ ከመረዳዳት ባሻገር በድህነት ግብዓተ መሬት ላይ ለመረባረብ የቆረጡት ዕድሮች ያካበቷቸውን ልምዶች በፎቶግራፍና በሠነድ አስደግፈው በተራ በተራ በርቱዕ አንደበት ለታዳሚው ማካፈል ጀመሩ፡፡ ሁሉም ጆሮውን ሰጥቷል፤ ባየውና በሰማው መደሰቱንና አድናቆቱን ይገልጻል፤ ተጨማሪ ማብራሪያ የፈለገ ይጠይቃል፤ ሌላው ዐውዱን በፎቶ ግራፍና በተንቀሳቃሽ ምሥል ለማስቀረት ይጣጣራል ወዘተ. ብቻ ከአንድ ነጭ ድንኳን ወደ ሌላ ነጭ ድንኳን ሲታለፍ ሌላ ቁም ነገር፣ ሌላ ስኬት፣ ሌላ መደመም!
ክብርት ወ/ሮ ዘውድነሽ አሰፋ ዐውደ ርዕዩን አስመልክተው ሲናገሩ “መርሀ-ግብሩ ህብረተሰቡን ማዕከል ያደረገ ሰፊ ሕዝባዊ መሠረት ያለው የልማት ሥራ በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች እንዲሰራጭ ልዩ ዕድል ይፈጥራል” ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡ የማህበራቱ ተወካዮችም ይህንኑ መስክረዋል፡፡ “ተረጂዎችን በተናጠል ከመደገፍ ይልቅ ዘላቂነት ባለው መልኩ ራሳቸውን ችለው እንዲንቀሳቀሱ በቡድን በማደራጀት የገቢ ምንጫቸውን እንዲያዳብሩ ለማስቻል በሌሎች ማህበራት የሚደረገውን ጥረት ተምረን በሥራ ላይ ለማዋል አስበናል” በማለት የጋይንት ንፋስ መውጫ ከተማ የዕድሮች ህብረትን ወክለው የተገኙት አቶ መቆያ ፈንቴ የክብርት ወ/ሮ ዘውድነሽን ሀሳብ ያጠናክራሉ፡፡
በዐውደ ርዕይው የተደመሙትና ከማህበራቱ በርካታ ተሞክሮ የተቋደሱት የበዓሉ ታዳሚዎች በባህላዊ ጭፈራ እየተዝናኑ አጠር ያለ የሻይ እረፍት ካደረጉ በኋላ ወደተንጣለለው የማዕከሉ አዳራሽ በመከተት ወደተከታዩ መርሀ-ግብር ተሸጋገሩ፡፡
ከጥቂት ክንውን በኋላም ሁሉንም ያስጨበጨበ የምሥራች ከማህበራቱ ዘንድ ተሰማ፡፡ ባለፈው አንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ብቻ
ለ5,974 ለችግር የተጋለጡ ህፃናት የተቀናጀ ድጋፍ በመስጠት፣
ለ4,670 ለችግር የተጋለጡ ህፃናት አሳዳጊዎች፣ ቤተሰቦች እና ሴቶች የኑሮ ማሻሻያ ድጋፍ በመስጠት፣
ለ956 ለችግር የተጋለጡ ወጣቶች የሥልጠናና የሥራ ፈጠራ ዕድል በማመቻቸት፣ እንዲሁም
1,750 ለሚሆኑ የማህበረሰብ አባላት በዘላቂ የማህበረሰብ ልማት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ በመስጠት የዜጎች ህይወት እንዲለወጥ ትልቅ ሚና ተጫውተናል፤  ወደፊትም የበለጠ አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የኢ/ህ/ማ/ል/ድ አጋር የሆኑ 46 የማህበረሰብ ምሥርት ተቋማት በተወካያቸው አማካይነት ለቤቱ አሳወቁ፡፡
ተከታዩ ዝግጅት የፓናል ውይይት ነበር፡፡ በውይይቱ የማህበረሰብ ምሥርት ተቋማት ለዘላቂ ልማት ያላቸውን አስተዋፅኦ ዙሪያ የተካሄደ የዳሰሳ ጥናት ግኝት ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል፡፡ እንደጥናቱ ከሆነ  ተቋማቱ በዘላቂ ልማት ውስጥ ያላቸው ሚና እንደማያጠያይቅ እና ለዚህም ያበቃቸው አደረጃጀታቸውና አሠራራቸው ሕዝባዊ መሠረት ያለው መሆኑ፤ አመራራቸው በበጎ ፈቃደኞች መሸፈኑ እና ከመንግሥትና ከሕግ አስፈፃሚ አካላት ጋር ያላቸው ትብብርና ትሥሥር ተጠቃሽ ናቸው፡፡
እንዲያም ሆኖ የጥናቱ ሌላ ገፅታ የማህበረሰብ ምሥርት ተቋማት ግሥጋሤ ከተግዳሮቶች የፀዳ አለመሆኑን አሳይቷል፡፡ በበጎ ፈቃደኝነት የሚያገለግሉ ተተኪዎችን የማፍራት ሥራ ከፍተኛ ጥረት መጠየቁ እና የግል ባለሀብቶችን በማስተባበር ሀብት የማሰባሰቡ ሥራ በስፋት አለመሠራቱ በዚህ ረገድ ከተነሱት ዋና ዋና ነጥቦች መካከል ናቸው፡፡  ከዚህ ባሻገር ከተለያዩ አካላት ጋር ያለውአጋርነት፣ አዎንታዊ የሆነ አስተሳሰብ ለውጥ ማስፈን እና ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር መቀናጀት በማህበረሰብ ምሥርት ተቋማት አማካይነት ዘላቂ ልማትን ለማምጣት የሚያስችሉ ጠቃሚ መሣሪያዎች እንደሆኑ በውይይቱ ተመላክተዋል፡፡
በውይይቱ ከተሠነዘሩና ማህበራቱን በእጅጉ ካበረታቱ ሀሳቦች መካከል ተጠቃሽ የሚሆነው የተከበሩ አቶ ታጠቅ አምሳሉ፣ የደብረ ብርሃን ከተማ ከንቲባ ቃል ነው፡፡ “ዘላቂ ልማት በመንግሥት ብቻ አይመጣም” በማለት የጀመሩት ክቡር ከንቲባው “የማህበረሰብ ምሥርት ተቋማት የመንግሥት የልማት አቅሞች እንደመሆናቸው መጠን መንግሥት ተቋማቱን በቅርበት ማወቅና ማገዝ ያስፈልጋል” ብለዋል፡፡ አክለውም “ማህበራቱን ከማወቅ በዘለለ የሚጎላቸውን ለይቶ አውቆ ያንን ክፍተት በመሙላት በኩል ከህበረተሰቡና ከመንግሥት ብዙ ይጠበቃል” ብለዋል፡፡ በመንግሥት የልማት ዕቅዶች ውስጥ የማህበረሰብ ምሥርት ተቋማትን ፍላጎትና ያልተነካ አቅም ማካተትና መጠቀም አስፈላጊ እንደሆነ ከንቲባው ሳይጠቁሙ አላለፉም፡፡በዓሉ ከመጠናቀቁ በፊት የተከናወነው ሌላ ቁም ነገር 60 ለሚሆኑ የነቃ የልማት ተሳትፎ ላደረጉና 7 የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የማህበረሰብ ምሥርት ተቋማት እውቅናና የማበረታቻ ሽልማት መስጠት ነው፡፡ በመጨረሻም አዘጋጆቹም ሆኑ ተጋባዦች ሁሉም ባዩትና በሰሙት ረክተው፣ የገበዩትንም እውቀት ለነገአቸው ሰንቀው በታላቅ ቁርጠኝነት ተሰነባበቱ፡፡ ማን ነበር “ነገ ዛሬ ጠንክረው ለሠሩት ነው” ያለው?

   ተቀማጭነቱ በእስራኤል የሆነው ሹራት ሃዲን የተባለ የመብቶች ተሟጋች ቡድን በቅርቡ በፍልስጤም ከተከሰቱ የሽብር ጥቃቶች ጋር በተያያዘ በታዋቂው የማህበራዊ ድረገጽ ፌስቡክ ላይ የአንድ ቢሊዮን ዶላር ካሳ የሚጠይቅ ክስ መመስረቱን አሶሼትድ ፕሬስ ዘገበ፡፡
በሽብር ጥቃቶች የተገደሉ አሜሪካውያን ግለሰቦችን ቤተሰቦች በመወከል ክሱን የመሰረተው ቡድኑ፣ የማህበራዊ ድረገጹ የአሜሪካን የጸረ ሽብር አዋጅ በመጣስ ለሽብርተኞች የጥፋት መልዕክቶችን ማሰራጫ መንገድ ሆኖ አገልግሏል በሚል ፌስቡክን ለደረሰው ጥፋት ተጠያቂ ማድረጉን ዘገባው ገልጧል፡፡
የመብት ተሟጋች ቡድኑ ሃማስን የመሳሰሉ ቡድኖች አዳዲስ አባላትን እንዲመለምሉ፣ ጽንፈኛ አመለካከቶቻቸውን እንዲያራምዱና ለሽብር ለሚያሰማሯቸው ታጣቂዎች መመሪያ እንዲያስተላልፉ ምቹ ዕድል ፈጥሯል በሚል ባለፈው ሰኞ በኒውዮርክ በሚገኝ ፍርድ ቤት በፌስቡክ ላይ ክሱን እንደመሰረተ ተነግሯል፡፡
ቡድኑ በመሰረተው ክስ ላይ የተጠቀሱት የሽብር ጥቃት ሰለቦች የሆኑ አምስት ቤተሰቦች ሁሉም አሜሪካውያን እንደሆኑ የጠቆመው ዘገባው፣ ከእነዚህም መካከል ባለፈው መጋቢት ወር ላይ እስራኤልን ሲጎበኝ በፍልስጤማውያን ጥቃት የተገደለው ቴለር ፎርስ የተባለው የ28 አመት አሜሪካዊ ቤተሰቦች እንደሚገኙበት አክሎ ገልጧል።

     አለማቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በዘር ማጥፋት ወንጀል የከሰስኳቸውንና የእስር ትዕዛዝ ያወጣሁባቸውን የሱዳኑ ፕሬዚዳንት አልበሽርን በቁጥጥር ስር አላዋሉም በሚል በጅቡቲና በኡጋንዳ መንግስታት ላይ ወቀሳ ማሰማቱን አሶሼትድ ፕሬስ ዘገበ፡፡
ፕሬዚዳንት አልበሽር ባለፈው ግንቦት ወር ወደ ሁለቱ አገራት አምርተው እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ ፍርድ ቤቱም የአገራቱ መንግስታት ይህን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ፕሬዚዳንቱን በቁጥጥር ስር አላዋሉም ሲል ባለፈው ማክሰኞ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት መውቀሱን ገልጧል፡፡
ፍርድ ቤቱ የጦር ወንጀልና ኢ-ሰብዓዊ የወንጀል ተግባራትን መፈጸም የሚሉ ሁለት ክሶችን በ2009 አልበሽር ላይ መመስረቱንና ከአንድ አመት በኋላም የዘር ማጥፋት የሚል ተጨማሪ ክስ መመስረቱን ያስታወሰው ዘገባው፣ ፍርድ ቤቱ በፕሬዚዳንቱ ላይ የእስር ትዕዛዝ ቢያስተላልፍም አንድም አገር ተፈጻሚ እንዳላደረገው ጠቁሟል፡፡ ፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንት አልበሽርን ለማሰር ፈቃደኞች አልሆኑም በሚል ተመሳሳይ ወቀሳዎችን ሲያሰማ መቆየቱን ያስታወሰው ዘገባው፤ ባለፈው ሰኔ ወር ላይም የፍርድ ቤቱ ዋና አቃቤ ህግ አልበሽርን አናስርም ባሉ አገራት ላይ እርምጃ አልወሰደም በሚል በተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ላይ ትችት መሰንዘራቸውንም አክሎ ገልጧል፡፡


ቴለር ስዊፍት በ12 ወራት 170 ሚ. ዶላር በማግኘት ትመራለች
    ታዋቂው ፎርብስ መጽሄት በ2016 ከፍተኛ ገቢ ያገኙ የዓለማችን 100 ዝነኞችን ዝርዝር በሳምንቱ መጀመሪያ ይፋ ያደረገ ሲሆን አለማቀፍ ዝናን ያተረፈቺው ድምጻዊቷ ቴለር ስዊፍት ባለፉት 12 ወራት 170 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት በዝርዝሩ የመጀመሪያውን ደረጃ ይዛለች፡፡
ድምጻዊቷ በአመቱ ያከናወነቺው 1989 የተባለ አለማቀፍ የሙዚቃ ጉዞ ከፍተኛ ገቢን እንዳስገኘላት የጠቆመው ፎርብስ፤በማስታወቂያና በሌሎች መንገዶች ያገኘቺው ገቢ ተደምሮ በአመቱ ከፍተኛ ገቢ ያገኘች ቁጥር አንድ የዓለማችን ዝነኛ እንዳደረጋት ገልጧል፡፡ዋን ዳይሬክሽን የተባለው የሙዚቃ ቡድን በ110 ሚሊዮን ዶላር ሁለተኛ ደረጃን ሲይዝ፣ ታዋቂው ደራሲ ጄምስ ፓተርሰን በ93 ሚሊዮን ዶላር ሶስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን የገለጸው ፎርብስ፤ ዶክተር ፊል ማክግሮው በ88 ሚሊዮን ዶላር፣ ፖርቹጋላዊው የእግር ኳስ ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ88 ሚሊዮን ዶላር የአራተኛና የአምስተኛ ደረጃ መያዛቸውን አስታውቋል፡፡
በዘንድሮው የፎርብስ ዝርዝር ውስጥ ድምጻውያን፣ የፊልም ተዋንያን፣ ኮሜዲያን፣ አትሌቶች፣ የእግር ኳስ ተጫዋቾችና በሌሎች ዘርፎች ታዋቂ የሆኑ የአለማችን ዝነኞች የተካተቱ ሲሆን እነዚህ 100 ዝነኞች ከሰኔ ወር 2015 እስከ ሰኔ ወር 2016 ባለው ጊዜ ውስጥ በድምሩ 5.1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘታቸው ተነግሯል፡፡
በፈረንጆች አመት 2015 በዝርዝሩ ውስጥ ተካተው የነበሩ 34 የዓለማችን ታዋቂ ግለሰቦች፣ በዘንድሮው ዝርዝር ውስጥ ለመካተት በለስ እንዳልቀናቸው የጠቆመው ፎርብስ፤ ከእነዚህም መካከል ታዋቂዎቹ ድምጻውያን ሌዲ ጋጋ እና ጀስቲን ቲምበርሌክ እንደሚገኙበት አስታውቋል፡፡
እስከ 20ኛ ባለው ደረጃ ከተቀመጡት የአለማችን ታዋቂ ድምጻውያን መካከል በ80 ሚሊዮን ዶላር 9ኛ ስፍራን ያያዘቺው አዴል፣ በ76.5 ሚሊዮን ዶላር 12 ደረጃን የያዘቺው ማዶና እና በ75 ሚሊዮን ዶላር 13ኛ ደረጃን የያዘቺው ማዶና ይገኙበታል፡፡

    ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ሰው በጠና ታመመና አልጋ ላይ ዋለ፡፡ በየጊዜው እየሄደ ዶክተሮች ያነጋግራል፡፡
1ኛው ሐኪም - “አይዞህ ቀላል ነው፡፡ ለክፉ አይሰጥህም” አለው፡፡
ህመምተኛው - “ዕውን ሐኪም በዚህ ተፅናንቼ ልቀመጥ?”
1ኛው ሐኪም - “እርግጡን ነው የነገርኩህ”
ህመምተኛው - “እንዳፍዎ ያድርግልኝ!”
ግን አያርፍም ህመምተኛው - ወደ ሁለተኛው ዶክተር ይሄዳል፡፡  
ሁለተኛው ሐኪም - “ምንም ችግር የለብህም፤ አሁን የያዘህ በሽታ በረዥም ጊዜ የሚድን ስለሆነ ብቻ ነው አልጋ መያዝ ያስፈለገህ”
ህመምተኛው - “ቃልዎትን አምኜ ዝም ብዬ ልተኛ ሐኪም?”
ሁለተኛው ሀኪም - “እቺን ታክል አትጠራጠር!”
ህመምተኛው - “እንዳፍዎ ያድርግልኝ!”
ወደ ሶስተኛው ሀኪም በሚቀጥለው ቀን ይሄዳል፡፡
ሶስተኛው ሐኪም - ከሁሉም የተለየ ነገር ነው የነገረው፡፡
“ወዳጄ የያዘህ በሽታ ፈፅሞ ጊዜ የሚሰጥ አይደለም፡፡ እንዲያውም ሀያ አራት ሰዓት ለመቆየት መቻልህን እጠራጠራለሁ፡፡ ስለዚህ ምንም አላደርግልህም”
ህመምተኛው አመስግኖ ሄደ፡፡
ሁኔታው ሶስተኛው ሐኪም እንዳለው ሳይሆን ቀረ፡፡ ሰውየው ከቀን ቀን እየተሻለው መጣና በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ካልጋው ተላቆ ቆሞ መሄድ ቻለ፡፡ በእርግጥ ግን ህመሙ ብዙ ስጋውን ስለበላው በአፅሙ የሚሄድ ይመስላል፡፡
አንድ ቀን መንገድ ላይ ሶስተኛውን ሐኪም አገኘው፡፡ ሐኪሙ በጭራሽ ያየውን ማመን አልቻለምና፤
“የወዲያኛውን ዓለም አይተህ ተመልሰህ መጥተህ መሆን አለበት፡፡ ለዚህ ጥርጥር የለኝም፡፡ ከዚህ ቀደም ተለይተውን ወደ ሰማይ ቤት የሄዱት ወዳጆቻችን እንዴት ናቸው ባክህ?”
ህመምተኛውም - “እጅግ በጣም ተመችቷቸው፣ ደልቷቸው ነው የሚኖሩት፡፡ ዘለዓለማዊውን ውሃ ጠጥተውና የዓለም ችግር ሁሉ ረስተው፤ በጣም ተመችቷቸው ይኖራሉ፡፡ በነገራችን ላይ እኔ ከዛ ለቅቄ እየመጣሁ ሳለሁ ምድር ላይ ባሉ ዶክተሮች ላይ ፍርድ ለመስጠት እየተዘጋጁ ነበር፡፡ ያስቀመጡት ምክንያት ህመምተኛ ሰዎች በተፈጥሮአዊ መንገድ እንዳይሞቱ ጥበብ እየተጠቀሙ በህይወት እንዲቆዩ በማድረጋቸው ነው፡፡ አንተንም ከሌሎቹ ጋር እንደሚቀጡህ ሲያስቡ ነበር፡፡ እኔ ግን እሱን ተዉት፤ ምክንያቱም እሱ አባይ ጠንቋይ እንጂ ዶክተር አይደለም አልኳቸው!”
*              *           *
ውሸተኛ ዐባይ ጠንቋዮች እየበዙ፣ ዕውነተኛ ዶክተሮች እየሳሱ ከመጡ አገራችን አደጋ ላይ ናት! ዐባይ መምህራን እየበዙ ዕውነተኛ መምህራን ከተመናመኑ የትምህርት ነገር አዲዮስ! የሚባል ይሆናል! ዐባይ ጠበቆችና ዐባይ ዳኞች ከተበራከቱና ዕውነተኛ ዳኞችና ሀቀኛ ጠበቆች ከጠፉ “O! Justice thy has flown to beasts!!” (ፍትሕ ሆይ! ወደ አራዊት በረርሽን!) እንዳለው ሼክስፒር ይሆናል፡፡ ግልፅነትና ተጠያቂነት ለአፍ አመል ብቻ እየተስፋፉ በተግባር ግን ሁሉ ድብቅ፣ ሁሉ የአዋቂ አጥፊ እየሆነ የሚገኝ ከሆነ፤ የለበጣ ዲሞክራሲ እንጂ ሌላ የለም፤ ሃሳዊ መብት እንጂ ለዕድገት የቆመ ሀቀኛ ሥርዓት አይኖርም፡፡ የካብነው እየተናደ፣ አደግን ያልነው ቁልቁል እየሔደ፤ በየቀኑ በችግር ማጥ ውስጥ መላሸቃችን አሳዛኝ ነው! የግል ት/ቤቶች ዕውቅናና ፈቃድ አስቂኝ  ደረጃ ላይ ደርሷል! የት/ቤቶች ተቋማት ዕድሳት ዘወትር በማስጠንቀቂያና በማስፈራሪያ የሚታለፍ የመስፈራሪቾ (Scare-crow) ሂደት ሆኗል፡፡ ሥርአተ- ትምህርት አደረጃጀቱን ማጥራት እንዳቃተው ከረመ! የግብዓት አቅርቦትና አገልግሎት እንከን አልባ ለመሆን አልታደለም! የዝውውር ፖሊሲ እንደተሽመደመደ ነው፡፡ የመረጃ አያያዝ የተቆጣጣሪ ያለህ! እያሰኘ ነው፡፡ በት/ቤት ተቋማት ውስጥ ‹‹በአጋዥ መፃሕፍት› ሰበብ ያለንግድ ፈቃድ የችብቸባ ሥርዓት መፈጠር ዘግናኝ ዕውነት ነው፡፡ የወላጆች አቤቱታ የምድረ ባዳ ጩኸት ሆኗል (Crying in the Wilderness)፡፡ የዚህ ሁሉ ውጤት የሆነው የፈተና ብቃት አለ ወይ? ብለን ገና መልስ ሳናገኝ፤ የፈተና ስርቆሽ አደጋ አናታችን ላይ ያንዥብባል? ያውም ኢንተርኔት እስከማዘጋት የደረሰ የሌብነት መንግሥታዊ ሥጋት … ይህ ሁሉ ሲታይ እንዴት ሚሥጥራችን በሀገር ደረጃ ይጠበቃል? ብለን ዕምነት እንጣል፡፡ ዕምነት ማጣት ያለመረጋጋት እናት መሆኑን እንርሳ!
ችግሮችን የመፍታት መንገዳችን ወይ መንገድ አደለም፤ ወይ ወልጋዳ መንገድ ነው፡፡ ይህ ማለት ችግርን ለመፍታት ሌላ ችግር መንገድ ነው፡፡ ይህ ማለት ችግርን ለመፍታት ሌላ ችግር መቀፍቀፍ ነው፡፡ ችግር በችግር አይፈታም፡፡ ዘላቂ መፍትሔ በማይሆን መልኩ ጥገናዊ ማስታመሚያዎች ብንደረድር ቁስላችን ማመርቀዙ አይቀሬ ነው፡፡ ውስጣችን መፈተሽ አለበት፡፡ አንዱ ባንዱ ላይ በማላከክ ሳይሆን ዕውነተኛውን በሽታ ፈልቅቆ በማውጣት ነው ህክምናችን የተሳካ የሚሆነው፡፡ አለበለዚያ፤ አንደኛው ሀኪም ቀላል ነው፤ ሁለተኛው ሀኪም በረዥም ጊዜ የሚድን በሽታ ነው፤ ሦስተኛ ሀኪም- ሀያ አራት ሰዓት አትቆይም! አይነት መፍትሔ ይዘን እንደ አፍዎ ያርግልኝ እያልን በጥንቆላ የምንተዳደር ሊመስለን አይገባም፡፡ በሽታችን የሚወሳሰበው ጊዜ ወስደን በጥሞና ስለማንከታተለው ነው፡፡ የበሽታችንን መንስዔ ከስር መሰረቱ ለማወቅ፣ አካሚውም ታካሚውም ግልፅነት ስለሌለን ነው፡፡ በሽታውን የደበቀ መድሀኒት አይገኝለትም የሚለው ዕውነት እንዳለ ሆኖ፤ መድህን አያገኝም የሚለው ታክሎብናል፡፡ የመጨረሻው አሳሳቢ ነገር ደግሞ ትክክለኛውን መረጃ አለማግኘት ነው፡፡ ይህ እክል አንድም ከመረጃ ሰጪ ንፉግነት የሚመነጭ ነው፡፡ አንድም የመረጃ ሥርዓቱ ብቃት ማጣትና ይሆነኝ ተብሎ እንዲጥመለመል ማድረጉ ነው፡፡ አሊያም ጨርሶ ለመረጃ ፋይዳ ጥረት አለመስጠት ነው! ከሁሉም ይሠውረን፡፡ እጅግ አስከፊው ገፅታችን ግን፤ ‹‹ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ›› እንዲሆን ካደረግን ነው፡፡ ሆን ብለን መረጃ ካጣመምን ማለትም መረጃ ተቀባይ ትክክለኛውን መረጃ ሳይሆን የተሳሳተውን ወስዶ ሌሎችን እንሳስት አድርገን፤ እኛም መልሰን እሱን ከሳሽ ከሆንን የመርገምት ሁሉ መርገምት ይሆንብናል! እንዲህ ያለውን ሂደት መዋጋት የግድ ነው፡፡ መረጃ፤ መረጃ የሚሆነው ለሚመለከተው ጉዳይ በአግባቡ ሲውል ነው፡፡ አለበለዚያ፤ ‹‹ከአንበሳና ከዝሆን ማን ያሸንፋል?›› ቢለው፤ ‹‹ከሁሉም ከሁሉም አሳ ሙልጭልጭ ነው!›› የሚለውን ተረት ስናደምቅ መኖራችን ነው!

“መንግስት እንደፈለገ ያድርገን ብለን ቁጭ ብለናል”

   በነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ስሙ ‹ማንጎ› የተባለው አካባቢ፣በቤት ፍርስራሾች ተሞልቷል፡፡ ቦታው በጦርነት ወይም በተፈጥሮ አደጋ የወደመ ነው የሚመስለው፡፡  የወዳደቁ የቤት ፍራሽ እንጨቶች፣የተጨረማመቱ የቤት ክዳን ቆርቆሮዎች ለዓይን ይታክታሉ፡፡ በፍርስራሾቹ ጥጋጥጎች ላይ በተጨረማመተቱ ቆርቆሮዎችና በፕላስቲክ የተሰሩ ዳሶች በብዛት ይታያሉ፡፡ በቤቶቹ ፍርስራሾች ላይ ተፈናቃዮች ተጠልለው ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህም መካከል አረብ ሀገር ሰርታ ባጠራቀመችው ገንዘብ ከአርሶ አደር ላይ ቦታ ገዝታ ባለ 3 ክፍል ቤት በመሥራት፣ ላለፉት 10 ዓመታት በቦታው ላይ መኖሯን የምትናገረው ወጣት ትገኝበታለች፡፡  
  ባለትዳርና የአንድ ልጅ እናት ስትሆን፤ ቤቷ ከፈረሰ በኋላ ከእነቤተሰቦቿ እዚያው ፍርስራሹ ላይ በፕላስቲክና በቀዳዳ ቆርቆሮ ከለላ ሰርታ መጠለሏን ገልጻልናለች፡፡   
በህይወቴ እንዲህ ያለ ምስቅልቅሎሽ አጋጥሞኝ ቀኑ ይጨልምብኛል፣ መግቢያ አጣለሁ ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር የምትለው ወጣቷ፤መሄጃ አጥቼ ከእነልጄ ጭቃ ላይ እየተንከባለልኩ ነው የማድረው ብላለች-ግራ በመጋባት ስሜት ተውጣ፡፡ በዳስዋ ውስጥ ለአፍታ በነበረን ቆይታ ጥቂት ጥያቄዎችን አቅርበንላት መልስ ሰጥታናለች፡-
 ይሄ ሁሉ ቤት በስንት ቀን ነው የፈረሰው?
በአንድ ቀን ነው ያፈረሱት፡፡
አስቀድሞ ይፈርሳል ተብሎ ተነግሯችሁ ነበር?
እኛ አካባቢ ይፈርሳል የሚል ወሬ ፈፅሞ አልሰማሁም፡፡ የሰማሁት ኤራኤልና፣ ጨሬ ቀርሳ ነው፡፡ ግን ሳናስበው ያንን አጋጣሚ ተጠቅመው የኛንም አፈረሱብን፤መግቢያ አሳጡን፡፡
ቤታችሁ ከፈረሰ በኋላ ያነጋገራችሁ የመንግስት አካል አለ?
ማንም ያነጋገረን አካል የለም፡፡ እናንተ ናችሁ ለመጀመሪያ ጊዜ መጥታችሁ የጠየቃችሁን፤ሌላ ዞር ብሎ ያየን የለም፡፡ ሀገር እንደሌለን ሜዳ ላይ ስንወድቅ የጠየቀን ማንም የለም፡፡
እናንተስ ---- ለመንግስት አቤቱታ ለማቅረብ አልሞከራችሁም?
እኛማ ማጣፊያው አጥሮናል’ኮ! የት ብለን ማንን እንጠይቅ፡፡ በቃ የሆነውን እንሁን ብለን እዚችው የቤቷ ፍራሽ ላይ ቀርተናል፡፡ ለራሴም ቤት ሰርቼ፣ አንድ ሁለት ክፍል ሰርቪስ ቤቶች ከጎን ቀጥዬ እያከራየሁ ገቢ አገኝ የነበረው ቀርቶ፣ዛሬ ይኸውና ለራሴም መጠለያ የሌለኝ ሆኛለሁ፡፡ ሀብት ንብረቴ ሁሉ ወድሟል፡፡
አሁን በምንድን ነው የምትተዳደሪው?
ቤቱ ከፈረሰ በኋላ ምንም ገንዘብ የማገኝበት ነገር የለም፤ሰው እየረዳኝ ነው የምኖረው፡፡
የሚከራይ ቤት ለማግኘት አልሞከራችሁም?
እኔ እዚህ ምንም ዘመድ የሌለኝ ሰው ነኝ፡፡ ማን ጋ ልጠጋ? ቤት ተከራይቼ እንዳልኖር ትንሹ የቤት ኪራይ 1500 ብር ነው፤ ከየት አመጣለሁ? ምንም ገቢ የማገኝበት ነገር የለኝምኮ! አቅሜ አይፈቅድም፡፡ በቃ ባዶዬን ቀርቻለሁ፡፡
መንግስት ምን እንዲያደርግ ነው የምትፈልጉት?
 ቦታውን እፈልገዋለሁ ብሎ እንዲህ ካደረገን በኋላ ምንም ማድረግ አንችልም፡፡ እኛም የዚህች ሀገር ዜጎች ነንና ያስብልን፡፡ ለዚህች ሀገር ልማት እናዋጣ የነበርን ዜጎች ነን፡፡ መንግስትን ምን በደልነው? ልጆቻችንስ በልጅነት አይምሮአቸው ለምን ይጎዱ፡፡
 ልጆቼ እየተሳቀቁ የሚበሉት አጥተው እየተቸገርን ነው፡፡ ወንድሜ እስቲ ንገረኝ ---- የገቢ ምንጭ ከወደመ በኋላ ይህችን ልጅ ምን ላብላት? … ዘንድሮ በኔ የመጣ ቁጣ እንዲህ ነው ተብሎ አይነገርም፡፡
“ከጅብ ጋር እየተፋጠጥን ነው የምናድረው”
አንዱ በአንዱ ላይ የተደረማመሱትን ቤቶች እየተመለከትን፣ከአንደኛው የቤት ፍራሽ ጥግ ላይ ወደተቀለሰች ዳስ አመራን፡፡ በዳሱ ውስጥና በራፉ ላይ አራት ሰዎች ቁጭ ብለው ቡና እየጠጡ ነበር፡፡ ጎራ ብለን ማነጋገር ጀመርን፡፡
ቤታችሁ ከፈረሰ በኋላ በእንዲህ ያለ ሁኔታ እዚህ ለመኖር ለምን መረጣችሁ? ቤት ተከራይታችሁ አትኖሩም?
(ከመካከላቸው አንደኛው በፍጥነት ምላሽ መስጠት ጀመረ …)
እየውላችሁ ወንድሞቼ---እኛ የቀን ሰራተኞች ነን፤ ከተማ ገብተን በ4ሺ እና 5ሺህ ብር ቤት ለመከራየት ይቅርና ለእለት ጉርሳችንም ስንቸገር የኖርን ነን፡፡ በምን አቅማችን ነው ቤት የምንከራየው?
በፊት በምን ነበር የምትተዳደሩት?
አንድና ሁለት ክፍል ቤት ከመኖሪያ ቤታችን ጎን ቀጥለን እየሰራን፣እያከራየንም ገቢ እናገኛለን፡፡ አብዛኞቻችን የቀን ሰራተኞች ነን፡፡ እኔ የምሰራው ድንጋይ ፈላጭነት ነው፡፡ ኮብልስቶንም እንሰራለን … በዚህ ነው የምንተዳደረው፡፡
ቦታውን ከአርሶ አደር ላይ ስትገዙ ህገወጥ መሆኑን አታውቁም ነበር?
በወቅቱማ ማንም አልተቃወመንም፡፡ አንድም ቀን ህገ-ወጥ ናችሁ ተብለን አናውቅም፡፡ ቤት ስንሰራ ደንቦች ይመጣሉ፤ግን አፍርሱ አይሉንም ነበር፡፡ አሁን እንኳ ሊፈርስብን ሰሞን መንገድ ለመስራት ባዋጣነው ገንዘብ፣የፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦ ተገዝቶ ሊቀበር በዝግጅት ላይ ነበር፡፡ ገንዘብ አዋጡ ተብለን እያዋጣን መብራት፣ መንገድ፣ ውሃ አስገብተናል፡፡
ውሃ በየግቢያችን እንዲገባ የተላከ ከወረዳው በማህተም የተደገፈ ወረቀት አይተናል፡፡ ለልማት 9 ሚሊዮን ብር ያስፈልጋል ተብለን ስናዋጣ ነበር፡፡
 ይሄን ሁሉ ስናለማ ዝም ብለውን፣ ዛሬ አንገታችንን ቀና አደረግን ስንል፣እንዲህ መልሶ ቅስማችንን የሚሰብረን መንግስት ምን አድርገነው ነው? ምን በድለነው ነው? ለአንድ ቀን እንኳ ማስጠንቀቂያ ቢሰጠን ምን አለበት?
ከመፍረሱ በፊት እቃችሁን አውጥታችሁ ነበር?
ድንገት እኮ ነው ማፍረስ የጀመሩት፡፡ የቻልነውን አትርፈናል፡፡ ብፌ፣ ሶፋ ግን እንዳለ ወድሞብናል፡፡
ለምን እቃችሁን ለማውጣት አልቻላችሁም?
ማን ያውጣው!? ወንዶቹን እየለቀሙ ነው ያሰሩት፤ግማሹ ሸሽቶ ከአካባቢው ራቀ፡፡ ሴቶች ብቻ ነበሩ የቀሩት፡፡ በዚያ ላይ 8 ማሽን ነበር ቤቱን ሲያፈርስ የነበረው፡፡ አካባቢው በአቧራ ታጥኖ … ሁኔታው ሁሉ አስፈሪ ነበር፡፡ እንዲህ እንደሚወራው ቀላል እደለም፡፡
አሁን እንዴት ነው የምትኖሩት?
ይኸው እንደምታዩት ጭቃ ላይ ፍራሽ አንጥፈን ነው የምንተኛው፡፡ አሁን የምንጠጣውን … ቡና ዘመድ ነው ያመጣልን፡፡ ልጆቻችን ተበታትነዋል፡፡
 ሁላችንም ዘመድ ከምናስቸግር ብለን በየቦታው በትነናቸው ነው እኛ እዚሁ የቀረነው፡፡ ት/ቤት ሄደው እስኪመጡ የማናምናቸው ሰዎች ዛሬ ምን ይሁኑ አናውቅም፡፡
ያነጋገራችሁ የመንግስት አካል የለም?
ማንም ዞር ብሎ ያየን የለም … ወገን እንደሌለን ሜዳ ላይ ቀርተናል፡፡
(አባወራዎቹ ቦታውን አንዱን ካሬ ሜትር በ100 ብር ሂሳብ እንደገዙት ይናገራሉ፡፡)
ለወደፊት ተስፋ የምታደርጉት ምንድን ነው?
ምን ተስፋ አለን?! ምንም ተስፋ የለንም፤መሄጃ የለንም፡፡ እንደሚባለው ትርፍ ቤት ቢኖረን እዚህ ቦታ ውሃና ጭቃ ላይ አንተኛም ነበር፡፡ መንግስት እንደፈለገ ያድርገን ብለን ቁጭ ብለናል፡፡