Administrator

Administrator

Saturday, 14 January 2017 16:14

“ESOG… 25ኛ አመት...”

ጥር 25-27 የኢትዮያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር 25ኛ አመት የብር ኢዮቤልዩ፣
ጥር 25-27 የኢትዮያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ESOG ›መታዊ ጉባኤ፣
ጥር 25-27 የአፍሪካ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ፌደሬሽን 2ኛ ጉባኤ ይካሄዳል።
የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ከተቋቋመ 25 አመት ሞላው። ጉባኤው የሚከና ወነው የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ጤና ጥበቃ ሚኒስር፣ የአለም የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ፌደሬሽን እና የአፍሪካ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ፌደሬሽን በተባባሪነት በማ ዘጋጀት ነው። የኢትዮያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ባለፉት 25 አመታት የሰራቸው ስራዎች ምን እንደሚመስሉ ዶ/ር ደረጀ ንጉሴ የማህበሩ ፕሬዝዳንት እንደሚከተለው አብራርተዋል።
በስነተዋልዶ ጤና የሚያገለግሉ ሙያዊ ትንተናዎችን ለማቅረብ በአገር ደረጃ በሚዋቀሩ የተለያዩ ኮሚዎች ውስጥ በመሳተፍ ሁነኛ የሆነ አስተዋጽኦ አድርጎአል።
ባለፉት 25 አመታት ከ20 በላይ የሆኑ እጅግ ተጠቃሽ የሆኑ ፕሮጀክቶችን ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር አከናውኖአል።
ኤችአይቪ ከእናት ወደልጅ እንዳይተላለፍ ለመግታት ደረጃውን የጠበቀ ሕክምና እንዲሰጥ ከማድረግ አኩዋያ ወደ 70የሚሆኑ የህክምና ድርጅቶች ውስጥ የሚገኙ ባለሙያዎችን ማሰልጠንና በተጨማሪም ክትትል በማድረግ የበኩሉን ሚና ተጫውቶአል።
በመካከለኛ ደረጃ የሚገኙ የጤና ባለሙያዎችን በማዋለድ ተግባር ላይ የተሸለ ክህሎት ኖሮአቸው በተለይም በኦፕራሲዮን መውለድ የሚያስፈልጋቸውን እናቶች ከመደገፍ አኩዋያ ቁጥራቸው ወደ 47 ለሚሆኑ የጤና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቶአል። ይህ ስልጠና እስከ 6 ወር የደረሰ ተከታታይ ስልጠና ሲሆን በተለይም እስፔሻሊስት ሐኪሞች በማይገኙበት ቦታ ለወላድ እናቶች ባለሙያው አስፈላጊውን እገዛ ሊያደርግ የሚችልበት ስራ ተሰርቶአል። በዚህም ፕሮጀክት እስከ መቶ ሺህ እናቶች ተጠቃሚ ሆነዋል።
በወሲባዊ ጥቃት እና ትንኮሳ ዙሪያ በተለይም ሴቶች ጥቃቱ ከደረሰባቸው በሁዋላ ተገቢውን ሕክምና እንዲያገኙ እና ክትትል እንዲደረግላቸው የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን በአዲስ አበባና በተለያዩ መስተዳድሮች ዋና ዋና ከተሞች ውስጥ 6 ሞዴል ክሊኒኮችን በመመስረት ደረጃውን የጠበቀ ሕክምናና እንክብካቤ እንዲያገኙ አድርጎአል።
በማደግ ላይ ባሉ ክልሎችና በአርብቶ አደሮች አካባቢ የማህረሰቡን የስነተዋልዶ እውቀ ትና ግንዛቤ ከማሳደግ አኩዋያ የሚሰሩ ስራዎች ያሉ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም ሙያተ ኞች እርህራሔንና ተገቢ የሆነን የህክምና እርዳታ ለተገልጋዩ ለማዳረስ የሚችሉበትን ስልጠና ማህበሩ በመስጠት ላይ ነው።
ማህበሩ ከ20 በላይ የሚሆኑ ሙያነክ መመሪያዎችን በማዘጋጀት ደረጃውን የጠበቀ ግልጋሎት ለማህበረሰቡ እንዲሰጥ ሲያደርግ ቆይቶአል።
 ስለዚህም በአጠቃላይ ላለፉት 25 አመታት ዘርፈ ብዙ የሆኑ በስነተዋልዶ ጤና ዙሪያ የተሰሩ ስራዎችን ማህበሩ አከናውኖአል። ከዚህም በተረፈ በአገር ውስጥ ከሚካሄዱት እንቅስ ቃሴዎች ባሻገር በምስራቅ ፣በመካከለኛውና በደቡብ አፍሪካ ሐገራት በተመሰረተው የማህጸንና ጽንስ ሕክምና ማህበር ፌደሬሽን ተሳትፎ ከማድረግም ባሻገር ማህበሩን የመምራት ኃላፊነትም ለኢትዮጵያ ጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር የተሰጠበት ሁኔታ ታይቶአል። የአፍሪካው የጽንስና ማህጸን ሕክምና ማህበር ፌደሬሽን በሚቋቋምበት ጊዜ የኢትዮጵያ ጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር አባላት ተሳትፎ ከማድረግም ባሻገር አሁንም በስራ አስፈጻሚ ቦርድ ውስጥ ሁለት የማህበሩ አባላት በመስራት ላይ ናቸው። በአለም አቀፍ የጽንስና ማህጸን ሕክምና ፌደ ሬሽን ውስጥም ለመጀመሪያ ጊዜ ከሰሐራ በታች ያሉ ሐገራትን በመወከል በስራ አስፈጻሚነት ውስጥ ካሉ 6 ኦፊሰሮች ውስጥ አንዱ የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር አባል ስለሆነ ይህም ማህበሩ ከአገር ውስጥ እንቅስቃሴው አልፎ በአፍሪካና በአለም አቀፍ ደረጃም ሙያዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ያለ ድርጅት መሆኑን ዶ/ር ደረጀ አብራርተዋል።
 የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር 25ኛውን የብር ኢዮቤልዩ እና አመታዊ ጉባኤውን በሚያከብርበት ጊዜ የአፍሪካው የጽንስና ማህጸን ሕክምና ፌደሬሽንም ስብሰባውን አብሮ ያካሂዳል። የአፍሪካው ፌደሬሽን የመጀመሪያውን ስብሰባ ያደረገው እዚሁ አዲስ አበባ ሲሆን በዚያን ጊዜ በስብሰባው የተሳተፉት ወደ 800 የሚሆኑ እንግዶች ነበሩ። የተሳተፉት ሐገራት ብዛትም ወደ 67 ይደርስ ነበር። ሁለተኛው ስብሰባም በኬንያ የተካሄደ ሲሆን አሁን ደግሞ በኢትዮጵያ ሊካሄድ ታቅዶአል። ዶ/ር ይርጉ ገ/ሕይወት የአፍሪካ ጽንስና ማህጸን ሕክምና ፌደሬሽን የመጀመሪው ፕሬዝዳንት የነበሩ ሲሆን አሁንም በአለም አቀፉ የጽንስና ማህጸን ሕክምና ፌደሬሽን ስራ አስፈጻሚነት የሚሰሩ ናቸው።
 እንደዶ/ር ይርጉ ማብራሪያ በአፍሪካ ውስጥ 54 ሀገራት የሚገኙ ሲሆን በአፍሪካው የጽንስና ማህጸን ሕክምና ፌደሬሽን የተወከሉት ግን 32 ሐገራት ብቻ ናቸው። ይህ የሆነበት ምክንያትም ፌደሬሽኑ አባል የሚያደርገው ግለሰቦችን ሳይሆን በማህበር ደረጃ እውቅና ያላቸውን ሐገራት ብቻ ስለሆነ ነው። አንዳንድ ሐገራት ውስጥ በቂ የጽንስና ማህጸን ሐኪም ባለመኖሩ ወይንም በአንዳንድ ሐገራት ደግሞ ቁጥራቸው አነስተኛ በመሆኑ የተነሳ ማህበር ስላልመሰረቱ በአፍሪካ ፌደሬሽን ላይ መወከል አልቻሉም። ስለዚህም በቀጣዮቹ አመታት በየሀገራቱ በሚኖ ረው የጥንካሬ ደረጃ፣ በሚያፈሩት የሰው ኃይል እና በሚመሰርቱት ማህበር መሰረት የሚወ ከሉት ሐገሮች ቁጥር ይጨምራል የሚል ተስፋ አለን። ኢትዮጵያ ግን ፌደሬሽኑ ከመቋቋሙ በፊትም መስፈርቱን ያሟላች ስለነበረች በፌደሬሽኑ ተሳታፊ ሆናለች። ዶ/ር ርጉ ገ/ሕይወት ይህ ጉባኤ በሚካሄድበት ወቅት ስለሚደረጉት አበይት ክንውኖችም እንደሚከተለው ገልጸዋል።
 በኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህር 25ኛ አመት በአልና አመታዊ ጉባኤ እንዲሁም በአፍሪካው የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ፌደሬሽን ስብሰባ ላይ ብዙ ሳይንሳዊ ጽሁፎች የሚቀርቡ ሲሆን ህብረተሰቡን እስከአሁን ከነበረው በተሻለ መንገድ ማገልገል እንዲያስችሉ የተነደፉ የተለያዩ ስልጠናዎች ይሰጣሉ።
ብሰባው ከመጀመሩ ሁለት ቀናት በፊት የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር አባሎችን በምርምር ስራ ማለትም የምርምር ጽሁፎችን በብቃት እና በጥራት የመጻፍ ክህሎት የሚያገኙበትን ስልጠና በአሜሪካ የጽንስና ማህጸን ኮሌጅ ማህበር ከሚመጡ ባለ ሙያዎች ጋር በመሆን እንሰጣለን። ይህም ምርምራቸውንም በጥራት በአገር ውስ ጥም ይሁን ከአገር ውጭ ለህትመት እንዲያበቁ የሚያስችል እውቀትን የሚያዳብር ነው።
የማህበሩ የስብሰባ መክፈቻ ቀንና ከዚያ አንድ ቀን በፊት በተከታታይ በአልትራሳውንድና የእርግዝና ክትትልን በሚመለከት የላቀ ሕክምና መስጠትን የሚያስችል ስልጠና ማህበሩ ከቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ ጋር በመሆን ይሰጣል።
ከሌሎች ሐገሮች ከሚመጡ ተመሳሳይ ሙያ ካላቸው ባለሙያዎች ጋር በመተባበር ማህበሩ የአንድ ቀን ስልጠና ያካሂዳል። በዚሁ ቀን በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሃቨቋስቈቄ -ቋሰቄቅቨ የሚባለውን የህክምና ዘዴ በሚመለከት በተለይም የማህጸን ችግሮችን ማወቅና መለየት የሚቻልበትን አዲስ ክህሎት ለማህበሩ አባላት የሚሰጥበት ይሆናል።
የጽንስና ማህጸን ድንገተኛ ሕክምናን በተመለከተ ዘመናዊ ወይንም ወቅታዊ የሆኑ እውቀቶች እና ክህሎቶችን በመፈተሽ አሁን ከሚሰራበት በተሻለ ምን ምስራት ይቻላል የሚለውን ማህበሩ ከአሜሪካው የጽንስና ማህጸን ሕክምና ማህበር ጋር በመተባበር ያካሂዳል።
በማህጸን ጫፍ ካንሰርና ከማህጸን ግድግዳ በሚነሳ ካንሰር ላይ ያሉትን ለውጦች ወይንም ወቅታዊ ግኝቶች ከጀርመንና ከአሜሪካ ከሚመጡ ሙያተኞች ጋር በመተባበር ስልጠና ይሰጣል።
በቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ላይ በተለይም በቋሚነትና ለረጅም ጊዜ በሚያገለግሉ የቤተሰብ እቅድ ዘዴዎች ላይ ግማሽ ቀን የሚወስድ ስልጠና ይሰጣል።
 ዶ/ር ይርጉ በስተመጨረሻም ለስብሰባው በተያዙት ቀናት እ.ኤ.አ ፌብረዋሪ 2-4 ወይንም ከጥር 25-27 ድረስ ስልጠናውን የሚያገኙት የማህበሩ አባላትና ከሌሎችም ሐገራት የሚመጡ ተሳታፊዎች በጣም ዘመናዊና የመጨረሻ የሆነውን እውቀትና ክህሎት የሚያገኙበት መድረክ ነው። በዚህም ወቅት ወደ 60 የሚደርሱ ጥናታዊ ጽሁፎች በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ የሚቀርቡ ሲሆን የባለሙያዎችን እውቀት የሚያሰፋ እና ለህብረተሰቡም ጠቃሚ የህክምና አገልግሎትን ለመስጠት የሚያስችል ነው ብለዋል።

የቢራ ገበያውን ከተቀላቀለ አንድ አመት ተኩል የሆነው ሀበሻ ቢራ፤ በገና ዋዜማ ከጆርካ ኤቨንት ኦርጋናይዘር ጋር በመተባበር ባዘጋጀው ‹‹ኢትዮጵያዊ›› የተሰኘ የሙዚቃ ኮንሰርት ከተገኘው የትኬት ሽያጭ ትርፍ 50 በመቶውን ሽሮሜዳ አካባቢ ለሚገኘው ‹‹ጌርጌሴኖን” የአዕምሮ ህሙማን ማዕከል ለገሰ፡፡ ባለፈው ማክሰኞ የኮንሰርቱን አጠቃላይ ሁኔታ ለመገምገምና ተባባሪ አካላትን ለማመስገን፣ በራማዳ አዲስ ሆቴል በተዘጋጀ የእራት ግብዥ ላይ ነው ግማሽ ሚሊዮን ብሩ የለገሰው፡፡
የሀበሻ ቢራ ማርኬቲንግ ማናጀር አቶ ጌታነህ አስፋው - ለ“ጌርጌሴኖን” የአዕምሮ ህሙማን ማዕከል መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ መለሰ አየለ ገንዘቡን ካስረከቡ በኋላ ባደረጉት ንግግር፤ የ“ገና በዓል የምስጋና፣ የመረዳዳት፣ የመጠያየቅና ደምቆ የመታያ በዓል በመሆኑ ከተገኘው የትኬት ሽያጭ ትርፍ ላይ 50 በመቶውን፣ (ግማሽ ሚሊዬን ብሩን) ለአዕምሮ ህሙማን መለገሳችን ያስደስተናል፤ ማዕከሉን በቀጣይ ለመደገፍ ድርጅቱ ዝግጁ ነው” ብለዋል፡፡
ድጋፍ በማጣት ማዕከሉን ወደ መዝጋት ታቀርበው እንደነበር የተናገሩት የ“ጌርጌሴኖን” መስራችና ስራ አስኪያጅ አቶ መለሰ አየለ፤ በተደረገላቸው ድጋፍ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው፣ ሀበሻ ቢራና ሰራተኞቹ ማዕከሉን ሲደግፉ የመጀመሪያቸው እንዳልሆነ ጠቁመው በህሙማኑ ስም አመስግነዋል፡፡ ሀሻ ቢራ፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ ኮንሰርቱን ያዘጋጀውን ጆርካ ኤቨንትን ያመሰገነ ሲሆን በቀጣይ አብሮ ለመስራት ፍላጎት እንዳለው ገልጿል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የሙዚቃ ኮንስርቶችን በማዘጋጀት የሚታወቀው ጆርካ ኤቨንት፤ በአንድ ወር ውስጥ በመጀመሪያ አልበሙ ተወዳጅነት ያተረፈውን የሳሚ ዳንን ኮንሰርት እንደሚያዘጋጅ ገልፆ በቅርቡ አጠቃላይ የኮንሰርቱን መረጃዎች ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡ ድርጀቱ በኢትዮጵያ ትልቁን የሙዚቃ ሽልማት ለማዘጋጀት በመሰናዳት ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል፡፡

Saturday, 14 January 2017 16:12

የቴክኖሎጂ ጥግ

ግብርና ዛሬ የተለየ መልክ ይዟል-
ገበሬዎቻችን አቅጣጫ ማመላከቻ ቴክኖሎጂ
(GPS) እየተጠ ቀሙ ነው፡፡ የመስኖ
ሥራህን በኢንተርኔት መቆጣጠር መከታተል
ትችላለህ፡፡
ዴቢ ስታብናው
· ኢንተርኔት፤ ደ ለራሲያንናለተደራሲያኖቻቸው
አዳዲስ የተለያዩ ዕድሎችንና ነፃነትን
ፈጥሮላቸዋል፡፡
ፍሬድሪክ ፎርሲዝ
· ኢንተርኔት የዓለማችን ትልቁ ቤተ መፃህፍት
ነው፡፡ መፃህፍቱ በሙሉ ያሉት ግን ወለሉ
ላይ ነው፡፡
ጆን አሌን ፓውሎስ
· በአሁኑ ዘመን እንግሊዝኛ የማይናገርና
ኢንተርኔት መጠቀም የማይችል እንደ ኋላ
ቀር ነው የሚቆጠረው፡፡
ልኡል አል-ዋሊድ፤ ሳኡዲ አረቢያ
· አይፓድ ሰዎች ከሙዚቃ ጋር ያላቸውን
አግባብ ሙሉ በሙሉ ለውጦታል፡፡
ካርል ላገርፊልድ
· ስማርት ቴክኖሎጂ እያደደበን ነው፡፡
ዳኒ ሜኪክ
· ቴክኖሎጂ ህይወትህን ማሻሻል እንጂ
ህይወትህ መሆን የለበትም፡፡
ቢሊ ኮክስ
· ቴክኖሎጂ የሰዎችን መሰረታዊ ፍላጎት ወይም
ተፈጥሮ አይለውጥም፡፡
ፕሪያ ኦርዲስ
· የዛሬ ዘመን ሳይንስ፣ የነገ ቴክኖሎጂ ነው፡፡
ኢድዋርድ ቴለር
· ቴክኖሎጂ ህብረተሰብን ይቀርፃል፤እናም
ህብረተሰብ ቴክኖሎጂን ይቀርፃል፡፡
ሮበርት ዊንተሮፕ ዋይት
· በዓለም ላይ ያሉ ቴክኖሎጂዎች በሙሉ ፈፅሞ
በጎ አስተሳሰብን አይተኩም፡፡
ሃርቬይ ማክኬይ

ለምዝገባ 500 ዶላር? የተሸላሚዎች ዝርዝር ውስጥ አልተካተቱም?


ባለፈው ህዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም በአሜሪካ ካሊፎርኒያ፣ትልቁ የአፍሪካ የፊልም ሽልማት “ናፍካ” ሥነ-ስርዓት ተካሂዷል፡፡ በየዓመቱ የሚካሄደው ይኼው የሽልማት ሥነስርዓት፣ ለመጀመሪያ ጊዜ በወኪሉ “ቆንጆ ፕሮሞሽን”በኩል ኢትዮጵያውያን አርቲስቶች እንዲወዳደሩ በሰጠውእድል ተዋንያን፣ ዳይሬክተሮች፣ የሜካፕ አርቲስቶች፣ሲኒማቶግራፈሮችና አንድ የበጎ አድራጎት መስራች በድምሩ
9 ሰዎች በእጩነት ወደ አሜሪካ ተጉዘው ነበር፡፡በተለይም ዝነኞቹ ተዋንያን ግሩም ኤርሚያስና ሩታመንግስተ አብ፤“ምርጥ የህዝብ ምርጫ ተዋንያን” በሚለውዘርፍ አሸናፊ መሆናቸው ተገልፆ፣በአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ተዘግቦ ነበር፡፡ የሽልማቱ ቦታ ላይ ሲደርሱ ግን
ብዙ ችግር እንደገጠማቸው፣ የናፍካው የኢትዮጵያ ተወካይ ሀሰተኛ እንደሆነና በሽልማት ቦታው ላይ ግራ ተጋብተው
እንደነበር፣ ሲወራ ሰንብቷል፡፡ከሽልማት ሥነ ስርዓቱ መካሄድ በኋላ አንድ ወር ከ10 ቀን ያህል በአሜሪካ ቆይቶ የተመለሰው አርቲስት ግሩም
ኤርሚያስ፤ በሽልማቱ ዙሪያ ያለውን እውነታ እንዲገልጽ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛዋ ናፍቆት ዮሴፍ እንደሚከተለው አነጋግራዋለች፡


ለናፍካ ሽልማት ወደ አሜሪካ ያደረጋችሁት ጉዞ ምን ይመስል ነበር?
እንግዲህ ለሽልማት ወደ ካሊፎርኒያ የሄድነው ሐሙስ ዕለት ማታ ነው፡፡ ለ21 ሰዓት በረራ አድርገናል፡፡ አርብ ጠዋት ደረስን፤ ቅዳሜ ሽልማቱ ነበር፡፡ አመሻሽ ላይ ነው ሽልማቱ የተካሄደው፡፡ እኛ ካረፍንበት ራቅ ያለ ቦታ ላይ ነው፡፡ በትራፊክ መጨናነቅና በራሳችንም ምክንያት ወደ አዳራሹ ዘግየት ብለን ብንደርስም፣ ሽልማታችንን ግን ተቀብለናል፡፡
ከዚህ ስለ ሽልማቱ ብዙ ተወርቶ ብትሄዱም፣ እዚያ ከደረሳችሁ በኋላ ችግር እንደገጠማችሁና የእናንተ ስም በተሸላሚዎች ዝርዝር ውስጥ እንዳልተካተተ፣ በተለያዩ የአገር ውስጥ ሚዲያዎች ተወርቷል፡፡ ወሬው ከየት የመጣ ነው?
በዚህ መልኩ የተፈጠረ ችግር የለም፡፡ መድረክ አካባቢ ትንሽ ማስተባበር የጎደላቸው ነገሮች ነበሩ። ለምሳሌ ተሸላሚዎች ስማቸው መድረክ ላይ ተጠርቶ ሽልማቱ ሳይቀርብ፣ ከመድረክ ጀርባ የወሰዱ አሉ፡፡ በሌላ በኩል፤ መድረክ መሪዎቹ “ከ1-5 የወጡ ፊልሞች እነዚህ ናቸው፤ አንደኛ የወጣው ደግሞ ይሄ ነው” ማለት ሲገባቸው፣ ቀድሞ ስክሪን ላይ ይለቀቅ ነበር፡፡ ይሄ አጓጊነቱን ይቀንሰዋል። እና የሽልማት ሂደቱ ላይ በአዘጋጆቹ ችግር ትንሽ የተዘበራረቁ ነገሮች ነበሩ እንጂ እኔና ሩታ ላይ ብቻ ተለይቶ የደረሰ ነገር አልነበረም፡፡ ከዝግጅቱ በኋላ እንዲህ የተዘበራረቀበትን ምክንያት ለማወቅ ሙከራ ስናደርግ፣ ከዚህ በፊት የተካሄዱትን አምስት የናፍካ ሽልማቶች ራሱ ሸላሚው ድርጅት ያዘጋጃቸው ሲሆኑ ጥሩ ሂደት እንደነበራቸው ሰምተናል፡፡ የዘንድሮው ለሌላ ኤጀንት በመሰጠቱ፣ ኤጀንቱ እንደ ጀማሪነቱ ትንሽ ክፍተት እንደተፈጠረበት ነው የተገለፀልን፡፡
ሁለታችሁ ሽልማቱን እንዳላገኛችሁ----በተለይም ሩታ ታጨች በተባለችበት ዘርፍ አንዲት ናይጀሪያዊት ሽልማቱን ይዛ ፎቶ መነሳቷ---እየተወራ ያለው ከምን መነሻ ነው?
እኔ ይሄ ነገር በምን መነሻ እንደተወራ፣ ወሬውን ማን እንዳዛመተውም አላውቅም፡፡ እኛ የሄድነው መዘጋጀቱ እውን በሆነ የሽልማት ስነ-ስርዓት ላይ ለመገኘት ነው፡፡ ሽልማታችንን አግኝተን ተመልሰናል። ይሄ “በሬ ወለደ” አይነት ወሬ በጣም ገርሞኛል፡፡ ሙያችንን እናሳድጋለን ብለን በምንጥርበት ጊዜ፣ እንዲህ አይነት ወፍ ዘራሽ ወሬዎች መናፈሳቸው እጅግ አሳፋሪ ነው፡፡
በናፍካ የኢትዮጵያ ተወካይ ነው የተባለውና የ“ቆንጆ ፕሮሞሽን” ስራ አስኪያጅ አቶ ማይክ በናፍካ እንዳልተወከለ፣ በአሜሪካ የታክሲ ሹፌር እንደሆነና ከኪነ-ጥበብ ጋር ግንኙነት እንደሌለውም ተወርቷል፡፡ ለምዝገባ እያንዳንዳችሁ 500 ዶላር ከፍላችኋል የተባለውስ--- ሰምተኸዋል?
የመጀመሪያው ነገር የናፍካ ተወካይ የታክሲ ሹፌር ከሆነም ነውር አይደለም፡፡ ሹፍርናም የተከበረ ሙያ ነው፡፡ ዋናው ነገር ይህንን እድል ለአገራችን ማምጣቱና የያዘው ራዕይ ትልቅ መሆኑ ነው፡፡ አንድ ሰው ታክሲ እየነዳ ወይም ሌላ ስራ እየሰራ፣ ጎን ለጎን ሌላ ተጨማሪ ስራ ቢሰራ ችግሩ ምንድን ነው፡፡ አየሽ ወሬው ሰውንና የሰውን ሙያ ከመናቅ ይጀምራል፤ ይሄ በጣም ያሳፍራል፡፡ እንደኔ እንደኔ ማይክ ሁሉቃ ወደ ኢትዮጵያ ይዞት የመጣው እድል፣ ለአርቲስቱና ለአገር ይጠቅማል አይጠቅምም የሚለው ነው መታየት ያለበት እንጂ ሌላው ነገር አይደለም፡፡ እንዲህ አይነት ጥሩ ዕድሎች ሲመጡ፣ ለማበላሸትና የሚሰራን ሰው ሞራል ለመንካት የሚደረግ ሩጫ ያሳዝናል፡፡ ዌብ ሳይቱን ናፍካ ብሎ ገብቶ ማየት ይቻላል፤ ሁሉም ነገር በግልፅ ይገኛል፡፡
ሩታን በተመለከተ ስሟ በስነ ስርዓቱ ተጠርቶ፣ መድረክ ላይ ወጥታ ንግግር አድርጋ፣ ሽልማቷን ተቀብላለች፡፡ እኔም እንደዛው፤ ሽልማቴ በቤቴ ይገኛል፡፡ በመጀመሪያ ሚዲያዎች ይህን ወሬ ተቀብለው  ዜና ሲሰሩ፣  እኛን የጉዳዩን ባለቤቶች ለምን አልጠየቁንም? ልክ አሁን አንቺ እንደምትጠይቂን፣ ለምን አልተጠየቅንም፡፡ እኛ በቦታው የነበርነውን የጉዳዩን ባለቤቶች መጠየቅ ነበረባቸው፡፡ ከሆነ አካል ወሬ ሰሙ፤ ዋና ባለቤቶቹን ሳይጠይቁ፣ የአንድ ወገን ሃሰተኛ ወሬ ይዘው ወጡ። ይሄ ነው ሁላችንንም ወደ ኋላ እየጎተተን ያለው፡፡ ቀደም ብዬ እንደነገርኩሽ በዝግጅቱ በኩል አንዳንድ ክፍተቶች ነበሩ፤ ለምሳሌ ሰው ስሙ እየተጠራ መድረክ ላይ ሲወጣ፣ ገና አዋርዱ ወደ መድረክ አልመጣም፡፡ ብዙ ተሸላሚ ማለት ይቻላል … ሽልማቱን ከመድረክ ጀርባ ነው የወሰደው፡፡ ይሄ የእኔም ሆነ የሩታ ወይም የሌሎች ተሸላሚዎች ችግር ሳይሆን የአዘጋጁ ነው፡፡ እዚያም የሽልማት ቦታ ላይ የተፈጠረው አንዳንድ ክፍተት እንደዚህ ነው የሆነው፤ አዘጋጆቹ ናቸው ሊጠየቁ የሚገባው፡፡
ተወካዩን በተመለከተ የናፍካ አርማና ማህተም ባለው ደብዳቤ፤ ‹‹On behalf of Nafca›› ተብሎ ስሙ ተጠቅሶ፣ ውክልና የተሰጠበትን ደብዳቤ አይቼ ነው ወደ ጉዳዩ የገባሁት፡፡ እኔ ህፃን ልጅ አይደለሁም፤ በምንም መልኩ ልታለል አልችልም። ወይም ደግሞ ዋንጫ የመሸለም ሱስ የለብኝም። እንዴት የኢትዮጵያን ህዝብ አታልላለሁ፤ ሰው ድምፅ ሰጥቶናል፤ እንዲህ አይነት ወሬ ማውራት የደገፈንን ሰው መናቅ ነው፡፡ እያንዳንዱ ነገር በዶክመንት የተደገፈ፣ በተፈለገው ጊዜ ሊታይ የሚችል ነገር ነው የተካሄደው፡፡ እንደተባለው በአየር ላይ የተናፈሰ ወሬ፣ ወይም በክፍያ የተከናወነ አይደለም። ናፍካም ትልቅ የአፍሪካ የፊልም ሽልማት ነው፤ ለ6ኛ ጊዜ የተካሄደ። እኔም ሩታም ይዘን የመጣነው ኩራታችንን፣ የሚገባንን ሽልማት ነው፤ ይሄ ደረቴን ነፍቼ በኩራት የምናገረው ነው። አንድ ጥቁር አሜሪካዊ የሆነውን ልንገርሽ፡፡ ለሽልማት ስሙ ተጠራ፤ነገር ግን ሽልማቱ የለም፤ ለምን ብሎ ሲጠይቅ፤ ”የአንተን ሽልማት ኢ-ሜይል እናደርግልሃለን” አሉት፡፡ የእኔን ሽልማት ይዞ ነው ፎቶ የተነሳው፤ ይሄ የናፍካ ስህተት ነው። በእንዲህ አይነት ስነ-ስርዓቶች ላይ ትልልቅ ስህተቶች ይፈጠራሉ፡፡ ለምሳሌ በዓለም የቁንጅና ውድድር ላይ አንደኛ ለወጣችው ሽልማቱ መሰጠት ሲገባው፣ ሁለተኛ ለወጣችው ተሰጥቷል፡፡ ይሄ ያጋጥማል፤ ስህተት እየተሰራ ይቀጥል ለማለት ግን አይደለም፡፡
የሽልማቱ ሥነ ስርዓት ከተካሄደ በኋላ፣ ከ1ወር በላይ ቆይታችሁ ነው ወደ አገራችሁ የተመለሳችሁት። እግረ መንገዳችሁን ያከናወናችሁት ነገር ነበር?
ከሄድንበት ፕሮግራም መጠናቀቅ በኋላም እዚያው ሎስ አንጀለስ ስለነበርን መጀመሪያ ያደረግነው ‹‹ዩኒቨርሳል ስቱዲዮ›› የተሰኘውን ትልቅ የፊልም ኩባንያ መጎብኘት ነው፡፡ በጣም አስደናቂ ስቱዲዮ ነው፡፡ አሜሪካ በጣም ከተደነቅኩባቸውና ከተገረምኩባቸው ነገሮች አንዱና ዋነኛው “ዩኒቨርሳል ስቱዲዮ” ነው፡፡ ይህ ስቱዲዮ አንድ የፊልም ባለሙያ ማየት የሚገባው ወሳኝ ቦታ ነው፡፡ ብዙ ልምዶችን ቀስመናል፡፡ ከዚህ በኋላ ያደረግነው በበጎ አድራጎት ዘርፍ የመሰረት በጎ አድራጎት ድርጅት መስራችና ዳይሬክተር እጩ ነበረች፡፡ በእርግጥ በዚህ ዘርፍ አንዲት ጣሊያናዊት ካቶሊክ በጎ አድራጊ ሴት ናቸው የተሸለሙት፡፡ እናም የተለያዩ ግዛቶች እየተዘዋወርን፣መሰረት ለምትረዳቸው ህፃናትና እናቶች፣ የገቢ ማሰባሰቢያ ስራዎችን ሰርተናል፡፡
በሌላ በኩል፤ብዙዎቻችን የየራሳችን ህልም አለን፡፡ ወደ ህልማችን ለመጠጋት ብዙ ጥረናል። ከተለያዩ የአፍሪካ ፊልም ሰሪዎች ጋር በብዙ ስራዎች ዙሪያ ተነጋግረናል፡፡ በተለይ አንድ የጋና ትልቅ የፊልም ባለሙያ፣ ሆሜስ ማክቪል ይባላል። “One Night in Vegas” እና “Paparazi” በተሰኙ ፊልሞቹ ይታወቃል፡፡ ከዚህ ባለሙያ ጋር በጣም ተወያይተናል፡፡ በቀጣይ ስለምንሰራውም እየተነጋገርን እንገኛለን፡፡ ዲሲም ሄደን አቶ ታምራት የተባሉ፣ ላለፉት 42 ዓመታት በዲሲ የኖሩ ሰውን አነጋግረናል፡፡ ብቻ ብዙ ነገሮችን ከውነናል፡፡ መቼም ዋናው ህልማችን የናፍካን ሽልማት ወስዶ ለመመለስ ብቻ አይደለም፡፡ ወደ ህልማችን የሚያስጠጋንን ነገር እግረ መንገዳችንን ፈፅመን መጥተናል፡፡
በቆይታህ ካገኘኸው ልምድ የፊልሙን ኢንዱስትሪ ለማሳደግ ምን አስበሀል?
እኔ እንግዲህ ሁሌም ተማሪ ነኝ ብዬ ነው የማስበው፡፡ እኔ እንደ ችግር የማየው፣ ራሳችንን ለሌላው ዓለም አላሳየንም፤ ኤክስፖዠር ያስፈልገናል። እነዚህን ነገሮች ለማድረግ በግሌ እጥራለሁ፡፡ ነገር ግን እድሎች ሲመጡ እንዲህ አይነት ያልተፈጠረ ነገር እያወሩ ሙያውን ከማቀጨጭ፣ በቅን ልቦና ማሰብ፣ መቻቻልና መተራረም የተሻለ ነው፡፡ እድሎችን ባበላሸን ቁጥር፣ ሙያችንን ወደ ዓለም ገበያ ለማቅረብ እንቸገራለን፡፡ በተረፈ አገራችን ላይ ጥሩ ተሰጥኦ ያላቸው ተዋንያን፣ ደራሲያን፣ ዳይሬክተሮች አሉ፡፡ ከመላው ዓለም ጋር መፎካከር የሚችሉ ባለሙያዎች አሉን፡፡ ሌላው የሚጎድለን እርስ በእርስ በሙያችን መደጋገፍና አብሮ የመስራት ነገር ነው፡፡ የናይጄሪያና የጋና ፊልም ሰሪዎች፣ የዓለምን ገበያ የተቀላቀሉት አብሮ የመስራት ባህል ስላላቸው ነው፡፡   



Saturday, 14 January 2017 16:04

የቴክኖሎጂ ጥግ

የፍቅር ጥግ
· ማፍቀር እንጂ በፍቅር መውደቅ የለብንም፤
ምክንያቱም የሚወድቅ ነገር ሁሉ ይሰበራል፡፡
ቴይለር ስዊፍት
· አንድ ላይ መሆን የቱንም ያህል ፈታኝ ቢሆን
ግዴለኝም፤ ከመለያየት የሚብስ ነገር የለም፡፡
ጆሴፊን አንጄሊኒ
· ራሳችሁን ለመሆን ለማይፈቅድላችሁ
ግንኙነት እጅ አትስጡ፡፡
ኦፕራ ዊንፍሬይ
· ከራሱ ጋር በፍቅር የሚወድቅ፣ ማንም
ተፎካካሪ የለውም
ቤንጃሚን ፍራንክሊን
· እናንተ እብደት ትሉታላችሁ፤ እኔ ግን ፍቅር
እለዋለሁ፡፡
ዶን ቢያስ
· ፍቅር አብሮን የተፈጠረ ሲሆን ፍርሃት እዚህ
የተማርነው ነው፡፡
ማርያኔ ዊሊያምሰን
· ፍቅር ባለቤትነትን አይጠይቅም፤ ነፃነትን
ያጎናፅፋል እንጂ፡፡
ራቢንድራናዝ ታጎ
· ፍቅር፤ ፍቅርን የሚያመነጭ ኃይል ነው፡፡
ኤሪክ ፎርም
· ሰዎችን ልትወዳቸው እንጂ ልታድናቸው
አትችልም፡፡
አናይስ ኒን
· ሁለት ነፍሶች ግን አንድ ሃሳብ፤ ሁለት ልቦች
ግን እንደ አንድ የሚመቱ፡፡
ፍሬድሪክ ሃልም
· የማይቻለውን የሚቻል የሚያደርገው ፍቅር
ነው፡፡
የህንዶች አባባል
· ፍቅር፤ በትዳር የሚድን ጊዜያዊ እብደት
ነው።
አምብሮሴ ቢርስ

አለማችን በሲጋራ ሳቢያ በአመት 1 ትሪሊዮን ዶላር ታጣለች
- በ2030 በየአመቱ የሚሞቱ አጫሾች ቁጥር 8 ሚሊዮን ይደርሳል

የሩስያ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እ.ኤ.አ ከ2015 በኋላ ለተወለዱ ሁሉም የአገሪቱ ዜጎች ሲጋራ እንዳይሸጥ የሚከለክል እጅግ ጥብቅ
ህግ በማውጣት ተግባራዊ ለማድረግ ማቀዱን የእንግሊዙ ዘ ታይምስ ዘገበ፡፡ ቀጣዩን የሩስያ ትውልድን ከሲጋራ ነጻ እንደሚያደርግ ቢታሰብም የአፈጻጸሙ ጉዳይ አጠያያቂ ነው የተባለው የሚኒስቴሩ ዕቅድ፣ እንደታሰበው ተግባራዊ የሚደረግ ከሆነ፣ ሩስያ ከአለማችን አገራት እጅግ ጥብቅ የጸረ-ትምባሆ ህግ ያወጣች የመጀመሪያ አገር ትሆናለች ያለው ዘገባው፤ አገሪቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በትምባሆ ዙሪያ ጉልህ እርምጃዎችን መውሰድ መጀመሯን ጠቁሟል፡፡ ዕቅዱ ጤናማ ዜጋ ለመፍጠር ቢያስችልም፣ በሌላ በኩል ግን ከጥራት በታች የሆነ የትምባሆ ምርት በጥቁር ገበያ ህገወጥ መንገድ እየተሸጠ የዜጎችን ጤና የከፋ አደጋ ላይ እንዲጥል ምክንያት ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት መፍጠሩን እንዲሁም ለሁሉም ዜጎች ሲጋራ አትሽጡ የሚለው ህግ በተጠቃሚዎችና በትምባሆ አምራች ኩባንያዎች ዘንድ ቁጣን ሊቀሰቅስ እንደሚችል መነገሩንም ዘገባው
አመልክቷል፡፡ የሩስያ መንግስት ባለፉት አመታት የሲጋራ አጫሾችን ቁጥር ለመቀነስ በሚል በወሰዳቸው የተለያዩ እርምጃዎች ከፍተኛ ውጤት
ማስመዝገቡን ያስታወሰው ዘገባው፣ ባለፈው የፈረንጆች አመት 2016 ብቻ የአገሪቱ አጫሾች ቁጥር በ10 በመቶ መቀነሱንም አክሎ ገልጧል፡፡
በተያያዘ ዜናም፣ የአለማችን ኢኮኖሚ በሲጋራ ሳቢያ በየአመቱ 1 ትሪሊዮን ዶላር ገደማ ኪሳራ እንደሚገጥመውና በሲጋራ ማጨስ
ሳቢያ በየአመቱ ለህልፈተ ህይወት የሚዳረጉ ሰዎች ቁጥር በመጪዎቹ 13 አመታት፣ 8 ሚሊዮን ያህል ይደርሳል ተብሎ እንደሚገመት
የአለም የጤና ድርጅት ሰሞኑን ባወጣው መረጃ ማስታወቁን ዘገባው አስረድቷል፡፡ ድርጅቱ ባለፈው ማክሰኞ ያወጣውን የጥናት ውጤት
ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው፣ እስካሁን ባለው መረጃ በአለማቀፍ ደረጃ በሲጋራ ሳቢያ 6 ሚሊዮን ያህል ሰዎች በየአመቱ የሚሞቱ
ሲሆን፣ ይህ ቁጥር እስከ 2030 ድረስ 8 ሚሊዮን ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በሲጋራ ለህልፈተ ህይወት ከሚዳረጉት
ሰዎች መካከል ከ80 በመቶ በላይ የሚሆኑት በመካከለኛና በዝቅተኛ ገቢ አገራት የሚገኙ እንደሆኑም ዘገባው ጠቁሟል፡፡

የፊሊፒንሱ ፕሬዚዳንት ሮድሪጎ ዱቴሬ፤ ከአደንዛዥ ዕጽ ህገወጥ ንግድ ጋር ንክኪ ያላቸው የአገሪቱ ከንቲባዎችና ባለስልጣናት ከህገወጥ ተግባራቸው እንዲታቀቡ አልያ ግን ያለአንዳች ማመንታት በግድያ እንደሚያስወግዷቸው ባለፈው ሰኞ ማስጠንቀቃቸውን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል፡፡ ፕሬዚዳንቱ በአደንዛዥ ዕጾች ንግድ ውስጥ ተሳትፈዋል የተባሉ 10 ሺህ የሚደርሱ የአገሪቱ ከንቲባዎች፣ አገረ ገዢዎች፣ የፖሊስ መኮንኖችና ሌሎች የመንግስት ባለስልጣናትን ስሞች የያዘ ዝርዝር ሰነድ ማሰናዳታቸውንና እርምጃ ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡ በዚህ ዝርዝር ውስጥ ስማቸው የተጠቀሰ ከንቲባዎች፣ ዛሬ ነገ ሳይሉ በአፋጣኝ ስራቸውን በገዛ ፈቃዳቸው እንዲለቁና ከህገወጥ ስራቸው እንዲታቀቡ ያሳሰቡት ፕሬዚዳንቱ፤ ይህን በማያደርጉት ላይ ፈጣን የግድያ እርምጃ እንደሚወስዱ ዝተዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ከዚህ ቀደምም በከንቲባነት ሲሰሩ፣ከአደንዛዥ ዕጾች ህገወጥ ንግድ ጋር ንክኪ አላቸው ያሏቸውን የመንግስት ባለስልጣናት መግደላቸውን ማመናቸው የተዘገበ ሲሆን፣ ፕሬዚዳንቱ ከጉዳዩ ጋር ንክኪ አላቸው ባሏቸው ዜጎች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ማዘዛቸውን ተከትሎ፣ በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ከ5 ሺህ 900 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ሲኤንኤን በቅርቡ ባወጣው ዘገባ አስረድቷል፡፡

ድንገት በእሳት በሚጋየው ጋላክሲ ኖት 7 ምርቱ ሳቢያ በታሪኩ የከፋ በተባለው ቀውስ እየተናጠ አመቱን የሸኘው ግዙፉ ሳምሰንግ ኤሌክትሮኒክስ፤ በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖም በመጨረሻው የሩብ አመት ትርፉ ካለፈው አመት በ50 በመቶ እድገት ማሳየቱን አስታውቋል፡፡ ኩባንያው ባለፈው ሳምንት ይፋ ባደረገው መረጃ፣ የ2016 የመጨረሻው ሩብ አመት ትርፉ ባለፈው አመት ተመሳሳይ ጊዜ ካስመዘገበው ትርፍ የ50 በመቶ ያህል ጭማሪ በማሳየት፣ 7.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን እንዳስታወቀ አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡ ሳምሰንግ በአመቱ ያስመዘገበው ገቢ ካለፈው አመት የ10 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱንና ይህም ባለፉት ሶስት አመታት ካገኘው ገቢ ከፍተኛው መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፤ ትርፋማነቱ ማደጉን ይፋ ማድረጉን ተከትሎም የአክሲዮን ድርሻው በ1.9 በመቶ ማደጉን አስታውቋል፡፡ ኩባንያው ከገባበት ቀውስ ለመውጣት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ያመለከተው ዘገባው፤ የተለያዩ ምርቶቹን በስፋት ወደ ገበያ ለማቅረብ በማቀድ በአስር ቢሊዮኖች ዶላር መድቦ፣ የማስፋፊያ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም ገልጧል፡፡

የኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዮሪ ሙሴቬኒ፣ የአገሪቱ ልዩ የጦር ሃይል ሃላፊ ሆኖ ሲሰራ የቆየውን የመጀመሪያ ልጃቸውን ሜጀር ጄኔራል ሙሆዚ
ኬነሩግባን የፕሬዚዳንቱ ልዩ አማካሪ አድርገው መሾማቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ፕሬዚዳንት ሙሴቬኒ ደህንነታቸውን ለማስጠበቅ የተቋቋመውን ልዩ ሃይል ሲመራ የቆየውን የበኸር ልጃቸውን የ42 አመቱን ጄኔራል ሙሆዚ ኬነሩግባን በአማካሪነት መሾማቸው በአገሪቱ ቀጣይ ፖለቲካ ላይ ትልቅ ትርጉም እንዳለው የጠቆመው ዘገባው፤ ስልጣናቸውን ለማራዘም የያዙት እቅድ አካል ነው መባሉን ገልጧል፡፡
ባለፈው ማክሰኞ በአገሪቱ የጦር ሃይል መኮንኖች ሹም ሽር ያደረጉት ሙሴቬኒ፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ የስልጣን ዕድገት ያገኘውን ልጃቸውን በወሳኙ የአማካሪነት ቦታ ላይ መሾማቸው፣ ልጅዬው የሆነ ጊዜ ላይ የአባቱን ስልጣን ተረክቦ የአገሪቱ መሪ መሆኑ አይቀርም የሚለውን የቆየ ጥርጣሬ አባብሶታል ተብሏል፡፡የፕሬዚዳንቱ ልጅ ሜጀር ጄኔራል ሙሆዚ ኬነሩግባ፣ በጦር ሃይሉ ውስጥ ያለው ስልጣን
በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍ እያለ መምጣቱን የጠቆመው ዘገባው፤ ባለፈው አመት ከብርጋዴር ጄኔራልነት ወደ ሜጀር ጄኔራልነት ማደጉንም አስታውሷል፡፡ እ.ኤ.አ በ1986 ለመጀመሪያ ጊዜ ስልጣን ላይ የወጡትና ለአምስት ተከታታይ የስልጣን ዘመናት አገሪቱን በመምራት ላይ የሚገኙት የ72 አመቱ ሙሴቬኒ፤ ስልጣን ከእጃቸው እንዳይወጣ በማሰብ ዘመዶቻቸውን በወሳኝ ቦታዎች ላይ እንደሚሾሙ
የጠቆመው ዘገባው፣ ወንድማቸው ሳሊም ሳልህ የፕሬዚዳንቱ አማካሪ፣ ሚስታቸው ጃኔት ሙሴቬኒ ደግሞ የትምህርት ሚኒስትር ሆነው በመስራት ላይ እንደሚገኙ ገልጧል፡፡

የሆሊውድ አክተሩ - ፊደል ካስትሮ
የኩባው ኮሙኒስት መሪ ፊደል ካስትሮና የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ሮናልድ ሬጋን አንድ የሚያመሳስላቸው ነገር አለ ከተባለ፣ የፊልም ባለሙያ የነበሩ መሆናቸው ነው፡፡ ሁለቱም በሆሊውድ ፊልሞች ላይ ተውነዋል - የየአገሮቻቸው መሪ ከመሆናቸው በፊት፡፡ በርግጥ የሬጋንን መሪ ተዋናይነት፣ የአዘቦት ቀን ተመልካች ያልሆኑ የድሮ ፊልም አድናቂዎች ሳይቀሩ አሳምረው ያውቁታል። የካስትሮ ግን የተረሳ የሆሊውድ ታሪክ ሆኗል፡፡ ለምን? ፊደል ካስትሮ እ.ኤ.አ በ1946 በተሰሩ ሁለት ፊልሞች ውስጥ ነው የተሳተፉት፡፡ አንደኛው “Holiday in Mexico” የሚል ሲሆን ሁለተኛው “Easy To Wed” ይሰኛል፡፡ ካስትሮ በሁለቱም ፊልሞች ላይ በአጃቢነት ነበር የተሳተፉት፡፡ በአንደኛው ፊልም ላይ አንድ መስመር ንግግር የነበራቸው ቢሆንም ከተቀረፁ በኋላ ዳይሬክተሩ ቆርጦ ካስትሮ ብግን ብለው ነበር አሉ፡፡ “አሜሪካ የምወዳት አገር ነበረች … አሁን ግን” … ብለው በንዴት ወደ አገራቸው ተመልሰዋል፡፡  
የመፅሃፍ ቀበኛው ፕሬዚዳንት
የአሜሪካ 26ኛው ፕሬዚዳንት ቴዎዶር ሩዝቬልት፤ በመፅሃፍ አንባቢነታቸው ዝነኛ ነበሩ፡፡ መፅሐፍ “የሰጠ ይድከም” የሚባልላቸው ዓይነት ሰው ናቸው፡፡ በህይወት ዘመናቸው በ10ሺዎች የሚቆጠሩ መፃህፍት እንዳነበቡ የሚነገርላቸው ሩዝቬልት፤ በአማካይ በቀን አንድ መፅሀፍ ያነቡ ነበር ተብሏል፡፡ በል በል ያላቸው ዕለት ደግሞ ከቁርስ በፊት አንድ መፅሀፍ፣ እስከ እራት ደግሞ ሁለት መፅሀፍት እምሽክ ያደርጉ ነበር፡፡ በፕሬዚዳትነት ዘመናቸውም ከንባብ ያላቀቃቸው አልተገኘም፡፡ የሥራ ጉዞ በባቡር ሲያደርጉ እንኳን ረዥም ሰዓት በንባብ ተመስጠው ነበር የሚያሳልፉት፡፡
የአገር መሪ ምን ዓይነት መፃህፍትን ማንበብ እንዳለበት ተጠይቀው ሲመልሱ፡- ሥነ ግጥምና ረዥም ልብ ወለዶችን እንዲሁም አጭር ልብ ወለዶችን ጠቅሰዋል። እኒህ ብቻ ግን አይደሉም፡፡ የሂብሩ ነቢያትንና የግሪክ ፀሐፌ ተውኔቶችን የማያደንቅ ከሆነ በራሱ ማዘን አለበት ብለዋል፡፡ በታሪክና በመንግስት እንዲሁም በሳይንስና በፍልስፍና ዙሪያ የተፃፉ መፃህፍትንም ማንበብ እንዳለበት ይመክራሉ - አንብበው የማይጠግቡት ሩዝቤልት፡፡
ተዋናይቷ ሂትለርን ለመግደል ትመኝ ነበር
ትውልደ - ስዊድን አሜሪካዊቷ የፊልም ተዋናይት ግሬታ ጋርቦ፤ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ካበቃ ከአስርት ዓመታት በኋላ፣ ለቅርብ ጓደኞቿ አንድ ምስጢርና ምኞቷን አካፍላቸው ነበር፡፡ እንዲህ ስትል፤ “ሚ/ር ሂትለር በጣም ነበር የሚፈልገኝ፡፡ ሁልጊዜ ይፅፍልኛል፤ ወደ ጀርመን እንድመጣም ይጋብዘኝ ነበር፡፡ ጦርነቱ በወቅቱ ባይጀመር ኖሮ፣ እሄድለትና ከቦርሳዬ ውስጥ ሽጉጤን አውጥቼ እደፋው ነበር፤ ምክንያቱም እኔ ብቻ ነኝ ሳልፈተሽ ልገባ የምችል ብቸኛ ሰው፡፡”
በነገራችን ላይ በአሜሪካ በ1920ዎቹና 30ዎቹ ዓመታት ዝነኛ ተዋናይት የነበረችው ግሬታ ጋርቦ፤ በምርጥ ተዋናይትነት ሦስት ጊዜ ለኦስካር ታጭታ ነበር፡፡  
ለ20 ሚ. ዶላር ጀርባውን የሰጠ ኮሜዲያን
እንግሊዛዊው ኮሜዲያን ራስል ብራንድ፣ ከድምፃዊት ሚስቱ ካቲ ፔሪ ጋር የመሰረተውን ትዳር ከ14 ወራት በኋላ እ.ኤ.አ በ2012 በፍቺ ሲደመድም፣ ከ44 ሚ. ዶላር ሀብቷ ላይ ግማሹን የመውሰድ ህጋዊ መብት ነበረው - 20 ሚ. ዶላር ገደማ፡፡ ራስል ግን ከሚስቱ ገንዘብ ላይ ድምቡሎ መውሰድ እንደማይፈልግና በተቻለ መጠን መለያየታቸው ሰላም የሰፈነበት ይሆን ዘንድ እንደሚሻ መናገሩን TMZ.com በወቅቱ ዘግቦታል፡፡ በሴት አውልነቱ በእጅጉ የሚታወቀው ራስል፤ ፍቺው ከመጠናቀቁ በፊት እንኳን ከአንድ ከሁለት ሴቶች ጋር ግንኙነት ጀምሮ ነበር ተብሏል፡፡  የፖላንድ ተወላጇ ፈረንሳዊት ሳይንቲስት ሜሪ ኩሪ፤ የዘመኗ ዝነኛ የፊዚክስና ኬሚስትሪ ተመራማሪ ነበረች፡፡ ከባለቤቷ ከፒሬ ጋር እ.ኤ.አ በ1903 ዓ.ም በፊዚክስ የኖቤል ሽልማት ያሸነፈችው ኩሪ፤ በ1911 ዓ.ም ሁለተኛውን የኖቤል ሽልማት በኬሚስትሪ ተሸልማለች። ኩሪ ራዲየም የተሰኘውን የኬሚካል ንጥረ ነገር ያገኘች ዝነኛ ሳይንቲስት ናት፡፡ ሆኖም ከወንዶች የሙያ አቻዎቿ ተቃውሞና ተፅዕኖ ይደርስባት እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ከዚሁ ሁሉ ስኬትና ሽልማት በኋላ ስመ ጥር የሆነው የፈረንሳይ አካዳሚ አባል እንድትሆን አልተፈቀደላትም ነበር፡፡ በሌላ ምክንያት አልነበረም -  ሴት በመሆኗ ብቻ!