Administrator

Administrator

• በመልካም አስተዳደር---በዲሞክራሲ ግንባታ----በግልጽነት---??
• መንግስትስ እንዲጠናከሩ በምን በኩል ደገፋቸው?
   የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት ኤጀንሲ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት እንዲስፋፉና ተልዕኳቸውን በሕግ መሰረት እንዲወጡ ብሎም አሰራራቸው ግልፅነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት እንዲሆን እየሰራ ይገኛል፡፡ ኤጀንሲው በህገ-መንግስቱ አንቀፅ 31 የተደነገገውን የዜጎች የመደራጀት መብት እውን ለማድረግ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራትን መዝግቦ ፈቃድ በመስጠት ዘርፈ ብዙ የክትትልና ድጋፍ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ማህበራት በሀገራቸው ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታና የልማት ስራዎች ላይ የመሳተፍ እድል አግኝተዋል፡፡ በርካታ ቁጥር ያላቸው የሙያና የብዙኃን ማህበራት ተደራጅተው ፍቃድ በመውሰድ በሀገሪቱ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ። ምንም እንኳ አብዛኞቹ ማህበራት ተመዝግበው መንቀሳቀስ የጀመሩት በቅርብ ዓመታት ቢሆኑም ከተመሰረቱ ግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ እድሜ ያላቸው ማህበራትም አሉ፡፡ ሆኖም እንደ ቁጥራቸው ብዛትና እንደ እድሜያቸው ልክ የሙያ ማህበራት በሀገሪቷ የፖለቲካ ህይወት ውስጥ የራሳቸውን አሻራ አኑረዋል ማለት ግን አይቻልም፡፡ የሙያም ሆኑ የብዙሃን ማህበራት የህዝብን ጥያቄ በተደራጀ መልኩ እያቀረቡ እንዲፈቱ ለማስቻል፣ በመንግስትና በህብረተሰቡ መካከል እንደ ድልድይ ሆነው እያገለገሉ አይደለም። በበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት ኤጀንሲ ተመዝግበው ፍቃድ የወሰዱ በጥቅሉ 333 ገደማ የሚሆኑ የሙያና የብዙኃን ማህበራት ቢኖሩም የረባ ስራ ሰርተዋል ለማለት አያስደፍርም፡፡ ሆኖም በጥቅሉ ሁሉም ማህበራት ለተቋቋሙለት ዓላማ በተገቢው መልኩ አስተዋፅኦ አላበረከቱም ማለታችን አይደለም። ለዓብነት የሚጠቀሱ ስኬታማ ስራ መስራት የቻሉ ማህበራት መኖራቸው አይካድም፡፡ እንደ ኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ያሉ ጥሩ ተሞክሮ ያላቸው በጣት የሚቆጠሩ ማህበራት መኖራቸው ልብ ሊባል ይገባል፡፡  
አብዛኞቹ የሙያና ብዙኃን ማህበራት የሚፈለገውን ውጤት እንዳያመጡ እንቅፋት የሆነባቸው ሀገሪቱ በዘርፉ የምትከተለው ህግ መሆኑን በአፅንኦት ይገልፃሉ፡፡ ለምሳሌ የ10/90 ህግ፣ ማህበራት የገንዘብ ድጋፍ ከውጭ ሀገር እንዳያገኙ በማድረጉ ለመዳከማቸው ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳደረገ ይናገራሉ። ሆኖም ህገ-መንግስቱ በደነገገው መሰረት፣ በማህበር የመደራጀት መብት የተሰጠው ለዜጎች ብቻ ነው፡፡ በአዋጅ 621/2001 መሠረት፣ የኢትዮጵያ ማህበራት ፍቃድ ወስደው ለመስራት ሁሉም አባላት ኢትዮጵያዊ መሆን ይኖርባቸዋል እንዲሁም የገቢ ምንጫቸው ከሀገር ውስጥ መሆን እንዳለበት ተደንግጓል፡፡ በመሆኑም በህግ ከተፈቀደው ውጪ ከውጭ የገንዘብ ምንጭ መጠቀም አይቻልም፡፡ የሙያና ብዙሃን ማህበራት የአባላትን መብትና ጥቅም ለማስጠበቅ የሚሰሩ በመሆናቸው፣ እንደ በጎ አድራጎት ድርጅቶች ሰፊ የሀብት መጠን ላያስፈልጋቸው ይችላል፡፡ 90 ከመቶ የሚሆነውን ሀብት ከሀገር ውስጥ በማመንጨት እንዲሁም 10 ከመቶ የማይበልጠውን ከውጭ ሀገር በማምጣት ከሰሩ የተቋቋሙለትን አላማ ከዳር ማድረስ ይችላሉ፡፡ ማህበራት የአባላትን መብትና ጥቅም ለማስከበር የውጭ እርዳታ ሳያስፈልግ በሀገር ውስጥ ሀብት መስራት ይችላሉ፡፡ በመሆኑም በሀገራችን እየተንቀሳቀሱ ያሉ ማህበራት የ10/90 ህግ ውጤታማ ላለመሆናቸው ምክንያት ሊሆን አይችልም፡፡ ይህ ህግ ሲወጣ ማህበራት ሀብት የማግኘት አቅማቸው እንዳይዳከም ብዙ ታሳቢ የተደረጉ ጉዳዮች አሉ፡፡ ለዓብነት ያህል ማህበራት ከተቋቋሙለት ዓላማ ጋር ግንኙነት ባላቸው ብሎም ዓላማቸውን ለማስፈፀም ብቻ የሚውል የተለያዩ ገቢ ማስገኛ ስራዎች ላይ እንዲሰማሩ አማራጮች ተቀምጠዋል፡፡ የንግድ ህግ ጠብቀው ተጨማሪ ገቢ ማስገኛ ስራዎች ላይ መሰማራት ይችላሉ፡፡ የተለያዩ መንገዶችን ተጠቅመው ህዝባዊ መዋጮ በማካሄድ ከሀገር ውስጥ ሀብት ማመንጨት ይችላሉ። እነዚህ ሁሉ አማራጮችን ተጠቅመው ከጥገኝነትና ከተመፅዋችነት አመለካከት ተላቀው፣ ራሳቸውን ችለው መንቀሳቀስ ስለሚችሉ የ10/90 ህግ አላሰራንም ማለት ምክንያት ማብዛትና ከህግ አንፃርም ተገቢነት የሌለው በመሆኑ፣ ማህበራት ቆም ብለው ማጤን ይኖርባቸዋል፡፡ ህልውናቸው የሚወሰነው እራሳቸውን ለማጠናከር በሚሰሩት ስራ ነው፡፡
ይህ ሲባል የብዙሃንና የሙያ ማህበራት ምንም ተግዳሮቶች የሉባቸውም ማለት አይደለም፡፡ አብዛኞቹ ስራ መስሪያ ቢሮ የላቸውም፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ለስራቸው ግብዓት የሚሆኑ ቁሳቁሶችን የማግኘት ችግር አለባቸው፡፡ በየዘርፉ ያሉ የመንግስት ተቋማት ለሙያና ብዙሃን ማህበራት ድጋፍ ሊያደርጉላቸው ይገባል፡፡ የሙያ ማህበራትም ለአባላት ስልጠና እና የትምህርት እድልን ከማመቻቸት ባለፈ ያላቸውን እውቀትና ክህሎት ተጠቅመው ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን በማካሄድ፣ ለፖሊሲና ስትራቴጂዎች ግብዓት የሚሆኑ የመፍትሄ ሀሳቦችን በማቅረብ እንዲሁም መንግስትን በማማከር ለሀገሪቷ አቅም መፍጠር አለባቸው፡፡ ይህንን ኃላፊነት በመወጣት ረገድ ማህበራት የጎላ አስተዋፅኦ አድርገዋል ማለት አይቻልም፡፡ በቀጣይ በመስኩ የሚፈለገው ውጤት እንዲመጣ፣ የሙያ ማህበራት በየዘርፋቸው ከሚገኙ የመንግስት ተቋማት ጋር የጠበቀ ቁርኝት ፈጥረው፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን እጅና ጓንት ሆነው መፍታት አለባቸው፡፡ የሙያ ማህበራት ውጤታማ የሚሆኑት ያላቸውን እምቅ እውቀትና ክህሎት ሳይሰስቱ ለሀገራቸው ማበርከት ሲችሉ ነው፡፡ በሌላ በኩል መንግስት፣ እነዚህ በጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት እንዲጠናከሩ የማህበራዊ ተጠያቂነት ፈንድ (Social Accountability fund) ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ይኖርበታል፡፡   
የሙያና ብዙሃን ማህበራት በራሳቸው የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ተምሳሌት መሆን መቻል አለባቸው፡፡ የአባላትን መብትና ጥቅም በማስከበር፣ በጠቅላላ ጉባኤ መሪዎችን መምረጥ፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ነቅሶ በማውጣት እንዲፈቱ ማድረግ፣ ያልተመለሱ መብቶችን ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲመለሱ አባላትን በማለማመድ እንደ ሀገር በሚደረገው የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ መነሻና ትምህርት ቤት መሆን አለባቸው፡፡ የአንዳንድ ማህበራት የስራ ኃላፊዎች የጊዜ ሰሌዳቸውን ጠብቀው ጠቅላላ ጉባኤ በመጥራት የስራ አፈፃፀማቸውን አያቀርቡም፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ለበርካታ አመታት ስልጣናቸውን ለሌሎች አባላት ሳይለቁ የሚቆዩበት ሁኔታ አግባብነት የለውም፡፡ የመተዳደሪያ ደንባቸው ላይ በተቀመጠው መሰረት በየሁለት ዓመቱ የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባዎችን በማካሄድ፣ ስልጣናቸውን አዲስ ለሚመረጡ ሌሎች አባላት አሳልፈው መስጠት አለባቸው፡፡ የማህበራት አመራር አባላቱን በአገራዊ ጉዳዮች ላይ እያወያዩ፣ ዜጎች የጠራ አመለካከት ይዘው ለልማት እንዲነሳሱ የበኩላቸውን ሚና መጫወት አለባቸው፡፡ የሙያና ብዙሃን ማህበራት የሀገሪቷ አይን፣ ጆሮና አፍ መሆን አለባቸው፡፡ ማህበራቱ ሰፊ ቁጥር ያላቸው አባላትን ከመያዛቸው አንጻር ወሳኝ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚኖራቸው የጠራ ግንዛቤ፣ ብሄራዊ መግባባትን ለመፍጠር ትልቅ አስተዋፅኦ ማበርከት ይችላል፡፡
የሙያና ብዙኃን ማህበራት ውስጣዊ አሰራርም ግልፅነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት መሆን አለበት፡፡ ይህ ሲሆን ነው  መልካም አስተዳደርና ዲሞክራሲያዊ አሰራር ሊጎለብት የሚችለው፡፡ ማህበራት በሀገሪቷ የፖለቲካዊ ህይወት ውስጥ የነቃ ተሳትፎ ማድረግ ሲችሉ የዜጎችን ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች በማስከበር ረገድ ጉልህ ሚና ሊጫወቱ ይችላሉ፡፡ አቅም ሲፈጥሩ በሀገሪቱ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ውስጥ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ማበርከት ይችላሉ፡፡ በዚህ ረገድ የሙያም ሆኑ ብዙኃን ማህበራት በጉልህ የሚታይ ነገር አልሰሩም፡፡
አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ የብዙኃን ማህበራት ገዢው ፓርቲ ያቋቋማቸውና ለሱ በመወገን የፖለቲካ ስራ እንደሚሰሩ አድርገው የሚቆጥሩ አካላት አሉ። ነገር ግን የሙያና ብዙኃን ማህበራት ከየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ነፃ ሆነው በገለልተኝነት ለዜጎች እኩል የሚሰሩ ናቸው፡፡ ህጉም ይህንኑ ነው የሚደነግገው፡፡ በሌላ መልኩ የሙያና ብዙኃን ማህበራት በመንግስት መዋቅር ውስጥ ያሉ ክፍተቶችን ነቅሰው በማውጣት እንዲፈቱ ጫና እየፈጠሩ አይደለም፡፡ በእርግጥ ማህበራት ይህንን እንዲያደርጉ መንግስት ምቹ ሁኔታ ፈጥሮላቸዋል ወይ የሚለው ጥያቄ በአግባቡ መፈተሽ አለበት፡፡ ሌላው ቀርቶ የአባላትን መብትና ጥቅም ማስጠበቅ የሚችሉበት ደረጃ ላይ አልደረሱም። ምንም እንኳን ሁሉንም ማህበራት የሚገልፅ ባይሆንም ማህበራት የሙያ ብቃት ባላቸው ግለሰቦች እየተመሩ አይደለም፡፡ ከዚህ በተጨማሪም አንዳንድ ማህበራት ስልጣን ለመያዝ በሚያደርጉት ሽኩቻ በመጠመዳቸው፣ ትርጉም ባለው መልኩ ሀገራዊ ራዕይ አንግበው ሙያውን ለማሳደግ እየሰሩ አይደለም። ይህም በዘርፉ የሚፈለገው ውጤት እንዳይመጣ አሉታዊ ተጽዕኖ አድርጓል፡፡  
የሙያም ሆኑ ብዙኃን ማህበራት በስነ-ምግባር የታነፁና በእውቀት የበለፀጉ፣ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን በማፍራት ረገድ ትኩረት ሰጥተው መስራት አለባቸው፡፡ የአባላትን አቅም በመገንባት ዙሪያ ብዙም የተሰራ ስራ የለም፡፡ ማህበራት በተጨባጭ አባላትን ማፍራትና አቅም መገንባት መቻል አለባቸው፡፡ ማህበራት ሲጠናከሩ የአባላትን መብትና ጥቅም ማስከበር ይችላሉ፡፡ የፋይናንስ አቅማቸው እንዲጠናከር የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችና ለጋሾች ድጋፍ እንዲያደርጉላቸው ጥረት ማድረግ አለባቸው። ከዚሁ ጎን ለጎን ማህበራት እንቅስቃሴያቸው በበጎ ፍቃደኞች እንዲደገፍ ለማስቻል፣ የበጎ ፍቃደኝነት ባህል እንዲዳብር ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል። በሀገሪቱ የሚገኙ የህትመትና የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያዎች ትኩረት ሰጥተው የሙያና ብዙኃን ማህበራትን የስራ እንቅስቃሴ እንዲሁም ያሉባቸው ተግዳሮቶች ላይ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ በሰፊው መስራት አለባቸው፡፡ ሚዲያዎች በዘርፉ ያሉ ድክመቶችን ለመፍታት የሚያስችል ጥልቅ እይታና አቅጣጫ አመላካች የመፍትሄ ሀሳቦችን መስጠት መቻል አለባቸው፡፡
የሙያ ስነ-ምግባርና ብቃትን ከማሳደግ አንፃር የሙያ ማህበራት ብዙ ርቀት መጓዝ ቢኖርባቸውም ስንዝር እንኳን መራመድ አልቻሉም፡፡ ተዝቆ የማያልቅ ትልቅ አቅም ቢኖራቸውም፣ ከስብሰባ የዘለለ ትርጉም ያለው ስራ ለመስራት ለማከናወን  የቁርጠኝነት ማነስ እንዳለባቸው ይጠቀሳል፡፡ ይሄን ድክመታቸውን ማሻሻል አለባቸው፡፡ ነገር ግን ለማህበራት ተገቢውን እገዛ ሳያደርጉ በድፍኑ መውቀስም ተገቢ አይሆንም። ስለዚህ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላትም ለሙያና ብዙኃን ማህበራት ትኩረት ሰጥተው አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ አለባቸው፡፡ የብዙኃንና የሙያ ማህበራት ያላቸውን ምርጥ ተሞክሮ ቀምሮ ማስፋፋት ያስፈልጋል፡፡ የሀገር ውስጥም ሆነ ያደጉ ሀገራት ተሞክሮዎችን ከሀገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ጋር አጣጥሞ ማስፋፋት፣ ለነገ የማይባል ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ተግባር ሊሆን ይገባል:: እንደ ሀገር የሙያም ሆኑ የብዙኃን ማህበራት፣ በዜጎች መብት ነክ ጉዳዮችና የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ሂደት ውስጥ በንቃት መሳተፍ የሚያስችላቸው አሰራር መዘርጋት አለበት እንላለን፡፡
የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት ኤጀንሲ
ኢሜይል አድራሻ - This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

‹‹የፍራየርስ ክለብ ኢንሳይክሎፒዲያ ኦፍ ጆክስ›› ካካተታቸው ቀልድ አከል ቁምነገሮች ውስጥ  የሚከተለው ይገኝበታል፡፡
ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ሚስተር ሁበርት ሐምፍሬይ የተባሉ ምሁር ለአንድ የዩኒቨርስቲ ተማሪ የመጨረሻ የጥናት ወረቀት መካር (advisor) ሆነው ይቀጠራሉ፡፡ የመካርነቱን ሥራ በታላቅ ደስታ ነበር የተቀበሉት፡፡ እንዲህ ብለው፡-
‹‹በዕውነቱ ወጣት ምሁራን ለወግ ማዕረግ ይበቁ ዘንድ የመጨረሻ የጥናት ወረቀታቸውን ሲያቀርቡ ማገዝና ሙያዊ ክህሎታቸውን ማብቃት፣ ለእኔ ታላቅ ደስታና ዓይነተኛ ክብር ነው፡፡ በተቻለኝ አቅም ዕውቀቴን ላጋራው ፍቃደኛ መሆኔን እገልፃለሁ!›››
ሚስተር ሐምፍሬይ ተማሪውን መርዳት ቀጠሉ፡፡ ተማሪውም በትጋት መሥራቱን ቀጠለ፡፡
ወረቀቱን የማቅረቢያው ወቅት ሲደርስ ተማሪው በቆንጆ ሁኔታ የተጠረዘ ፅሑፉን ይዞ ሚስተር ሐምፍሬይ ዘንድ ከች አለ፡፡
‹‹ሚስተር ሐምፍሬይ፤ በወረቀቴ ላይ አስተያየትዎን ይሰጡኝ ዘንድ ይሄው መጥቻለሁ፡፡ ምን ይሉኝ ይሆን?››
ሚስተር ሐምፍሬይም፤
‹‹መልካም፡፡ አየውና መልስ እነግርሃለሁ›› አሉና አሰናበቱት፡፡ ተማሪው አመስግኖ ከቢሮአቸው ወጣ፡፡
ሁለት ወር አለፈ፡፡ ከሚስተር ሐምፍሬይ በኩል ምንም የተሰማ ነገር የለም፡፡ ስለዚህ ተማሪው ቢሮአቸው ሄደ፡፡
ከዚያም፤ ‹‹ሚስተር ሐምፍሬይ፤ ወረቀቴን እንዴት አገኙት?” ሲል ጠየቃቸው፡፡
ሚስተር ሐምፍሬይም፤
‹‹እርግጠኛ ነህ ይሄ የመጨረሻውና ያለቀለት ሥራህ ነው? ዕውቀትህ ይሄ ብቻ ነው?›› ሲሉ ትኩር ብለው እያዩት ጠየቁት፡፡
ተማሪው  ቅር ያላቸው ነገር እንዳለ በመገመት፤
‹‹አንዴ ወስጄ ልየው?›› አለ፡፡
‹‹ይሻላል›› አሉት፡፡
ተሜ፤ በድጋሚ መሥራቱ እየከፋው የወረቀቱን ጥራዝ ተቀብሎ ሄደ፡፡ ፕሮጄክቱን አንዴ ሊከልሰው ነው፡፡
ከሁለት ወራት በኋላ ተማሪው የከለሰውን ወረቀት አጠናቅሮ፣ ቀንብቦ፣ ለሚስተር ሐምፍሬይ አምጥቶ አስረከባቸው፡፡ ሁለት ወር አለፈ፡፡ ከሚስተር ሐምፍሬይ በኩል ምንም ወሬ የለም፡፡ ስለዚህ ‹‹ቢሮአቸው ብሄድ ይሻላል›› ብሎ ወደዚያው አመራ፡፡ እንደደረሰም፤
‹‹እንዴት ሆነልኝ፤ ሚስተር ሐምፍሬይ?›› ሲል ጠየቀ፡፡
ሚስተር ሐምፍሬይ ግን፤
‹‹በቃ ይሄው ብቻ ነው ችሎታህ? እንደገና ቢሠራ ይሻላል›› አሉት፡፡
‹‹እሺ፤ የመጨረሻ ሙከራ ላድርግ›› አለና ተሜ፤ እየከፋው ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ በጣም ቅር እያለው በነጋታው ጥናት ክፍሉ ገብቶ ለሶስተኛ ጊዜ ወረቀቱን ፃፈና፤
‹‹አሁንስ ‹አልቀበልም› ቢሉኝ፤ የራሳቸው ጉዳይ፤ እተወዋለሁ!›› እያለ ወደ ሚስተር ሐምፍሬይ ቢሮ ሄደና አስረከባቸው፡፡
ሚስተር ሐምፍሬይም፤
‹‹በቃ ይሄ ነው የመጨረሻ ሥራህ?›› አሉት፡፡
‹‹አዎ፤ ከዚህ በላይ ምንም የምጨምረው ነገር የለም›› አላቸው፤ ፍርጥም ብሎ፡፡
ቀጥሎም
‹‹አንዴ ብቻ ሳይሆን ሁለት ሶስቴ ተመራምሬበታለሁ፡፡ ሁለት ሶስት ዓይነት ትንተና ተንትኛለሁ፡፡ ደጋግሜም ፅፌዋለሁ፡፡ ይኸው ነው!››
ሚስተር ሐምፍሬይ ትኩር ብለው ካስተዋሉት በኋላ፤
‹‹ጥሩ! እንግዲያው ከሰጠኸኝ ወረቀቶች ሁሉ ለመጀመሪያ ጊዜ ይሄኛውን አነበዋለሁ!›› ብለው አሰናበቱት፡፡ ተሜ ወጣና፤
‹‹ወይኔ! እስከ ዛሬ አንዱንም ሳያነብቡ ነበር ለካ የሚያፈጉኝ!›› እያለ ሄደ፡፡
                                                          *    *    *
የሰውን ድካም ማቃለል የሚችሉ አመራሮችና ኃላፊዎች የየተቋማቱ ምሰሶዎች ናቸው፡፡ በአንፃሩ የሰው ድካም የማይሰማቸው ሰዎች፤ ሙሉ ልብ እንዳይኖራቸው የማያግዙ፣ የራሳቸውን መንገድ ብቻ የሚያሰላስሉና የመልካም አስተዳደር አካላት ያልሆኑ ግለሰቦች አሉ፡፡ ያልተገነዘቡት ነገር አለ፣ ለውጥ አሮጌውን ጥሎ አዲስ ይዞ እንደሚራመድ አዳዲስና ወጣት ኃይሎችን ያላቀፈ ዕድገት ወንዝ አይሻገርም፡፡ ከዚህም ጎን ለጎን የሲቪክ ማህበራትን ያላጠናከረና አዳዲስ እንዲፈጠሩ ያላገዘ የለውጥ ጉዞ፤ አገራዊ መግባባቶች፣ አገራዊ እርቆች፤ ቀና ውይይቶችና ሽምግልናዎች  የሚሰምሩት ሲቪል ማህበራት እንደ ልብ ሲንቀሳቀሱ ነው፡፡ አመራሮች ስለ ዕቅዳቸው የሚናገሩትና የሚገቡት ቃል የግብር-ይውጣ እንዳይደለ ማረጋገጥ ተገቢ ነው፡፡ የአመራር ለውጦች ሲደረጉ ከነበሩ ተጨባጭ የህዝብ ችግሮች ጋር በቅጡ የተሳሰሩና እነዚያን ችግሮች የሚፈቱ መሆን አለባቸው፡፡ አለበለዛ ‹‹ትሻልን ትቼ ትብስን አገባሁ›› የሚል ሥጋት ይፈጠራል፡፡ በተለይ ከሙስና ጋር ቁርኝነት ያላቸው የኃላፊነት ቦታዎች ብርቱ ጥንቃቄ ይጠይቃሉ። የቢሮክራሲና የደላሎች፣ የኤጀንሲዎች፣ የአስመጪና ላኪዎች ግንኙነት፣ ዛሬ ባገራችን ብዙ የተወራለት ስስ-ብልት ነው፡፡ ‹‹ዛር ልመና ሳይያዙ ገና›› ይሏል አበው፡፡ ከወዲሁ የነገሮችን አካሄድ ማጤንና መንቀሳቀስ ብልህነት ነው። ለትላንትና መልስ ለመስጠት፣ ዛሬም የቆምንበትን ሁኔታ አምርሮ መመርመር፣ የአዳዲስ ሹማምንት ሁሉ ብርቱ ኃላፊነት ነው፡፡
 አንዳንድ ፀሐፍት ስለ አንዳንድ ቢሮክራቶች መመሪያ ይህን ይላሉ፡፡
 ‹‹ ሀ-ኃላፊ ስትሆን ጠያቂና ተመራማሪ ምሰል
   ለ- ችግር ሲፈጠር የበታችህን ወክል (delegate)
   ሐ- ስትጠራጠር የማይገባ ነገር አጉተምትም፤ አነብንብ
   መ- የቢሮክራትነት ዋና ጥበብ ይሄው ነው››
ከዚህ ይሰውረን! ስንት ቢሮክራቶች ይህን አባዜ ተሸክመው ይሆን? ብሎ መጠየቅ የአባት ነው፡፡
በሌላ ወገን ደግሞ ስለ ፕሮጄክት ልዩ ልዩ ደረጃዎች ሲፅፉ ፡- ‹‹ አንደኛው የፕሮጄክት ደረጃ ወይም ምዕራፍ/
           ስለ ፕሮጄክቱ ሥራ መጓተት ነው፡፡ ሁለተኛው/
           ከግራ-መጋባት ነፃ መሆን ነው፡፡ ሦስተኛው/
           መሸማቀቅና መጨናነቅ መጀመር ነው፡፡
አራተኛ/ ጥፋተኛውን ፍለጋ መግባት ነው፡፡ የማነው ጥፋቱ? መባባል ነው፡፡ አምስተኛው/ ምንም ያላጠፋውን የዋህ ሰው እንዲቀጣ ማድረግ ነው፡፡ ስድስተኛውና የመጨረሻው በፕሮጄክቱ ሥራ ምንም ያልተሳተፉ ሰዎችን ማሞገስና ክብር ሰጥቶ ማወደስ ነው፡፡››
ከላይ የተጠቀሱት ጉዳዮች እኛም ጋ አሉ የምንል እራሳችንን መፈተሽ ነው፡፡ ሹማምንቶቻችን አገርና ህዝብን ያስቀድማሉ ወይ? ካላስቀደሙስ? ከዚህም ይሰውረን እንበል፡፡ ምክንያቱም የተለያዩ እርስ በርስ የሚግባቡ፣ የሚሞዳሞዱ ወዳጅ አመራሮች፤ የሆድ ለሆድ መርህ ኔት-ወርክ፤ አላቸው፡፡ መደጋገፊያ መረብ ነው፡፡ በዚያም ክፉኛ ይጠቃቀማሉ፡፡ ሀቀኛና ምስኪን ሠራተኞች ግን ላባቸውን አፍስሰው ሥራዎች እንዲሳኩና አገራችን ከድህነት እንድትወጣ ዕለት-ሰርክ ደፋ-ቀና ይላሉ፡፡ ዛሬ ሁኔታችን ይሄን መሳይ ነው፡፡ ‹‹ሹም ለሹም ይጎራረሳሉ፤ ድሀ ለድሀ ይላቀሳሉ›› የሚባለው ለዚህ ነው! ሹመትና ሽረት የተለመደ ነው፡፡ ትልቁ ቁም-ነገር የተሾመው ሹም፤ ብቁና ከተሻረው ሹም ስህተትና ጥፋት ምን ተማረ፤ የሚለው ነው! ‹‹ትላንትና ማታ ቤትህ ስትገባ የመታህ የድንጋይ እንቅፋት፣ ዛሬ ማታም ከደገመህ፤ ድንጋዩ አንተ ነህ›› የሚለውን የቻይናዎች አባባል አለመርሳት ነው! ሹመት የብቃት ማረጋገጫ ይሁን!!

   መንግስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች በዓመት ሦስት ጊዜ ፓርላማ ገብተው በውይይት እንዲሳተፉ ለማድረግ ማኑዋል እየተዘጋጀ መሆኑን የገለፀ ሲሆን ተቃዋሚዎች በበኩላቸው፣ ሳይወከሉ በፓርላማ ውይይት ህገ መንግስታዊ አይደለም ሲሉ ተችተዋል። ተቃዋሚዎች ለምን አላማ ከመንግስት ጋር በዚህ መንገድ እንዲወያዩ እንደተፈለገ አይገባንም ያሉት የአረና ም/ሊቀመንበር አቶ ጎይቶም ፀጋዬ፤ ውይይቱ በፓርላማ መደረጉ ምናልባት ኢህአዴግ ብቻውን ተቆጣጥሮታል የሚለውን ሃሜት ለማስቀረት ካልሆነ በቀር ሌላ ፋይዳ አይኖረውም ብለዋል። “የተቃዋሚዎች የመወሰን ሚና ጨርሶ በሌለበት ሁኔታ የሚደረጉ ውይይቶች ጥቅማቸው እምብዛም ነው” ይላሉ አቶ ጎይቶም፡፡
የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ም/ሊቀመንበር አቶ ሙላቱ ገመቹ በበኩላቸው፤ ተቃዋሚዎች የህዝብ ውክልና ሳይኖራቸው በፓርላማ መገኘታቸው በምን አግባብ ነው? ሲሉ ይጠይቃሉ፡፡ “ፓርላማው ላይ መገኘት የሚቻለው በህዝብ ሲወከሉ ብቻ ነው” ያሉት አቶ ሙላቱ፤ ተቃዋሚዎች የመወሰን ሚና ሳይኖራቸው የሚያደርጉት ውይይት ምንም ፋይዳ አይኖረውም ብለዋል፡፡
“መንግስት ከተቃዋሚዎች ምክር የሚፈልግ ከሆነ፣ በፓርላማው መሆን የለበትም” ያሉት አቶ ሙላቱ፤ ሌሎች ልዩ መድረኮች መዘጋጀት አለባቸው ይላሉ፡፡ ተግባራዊ ይደረጋል ብለው እንደማያምኑ የተናገሩት ም/ሊቀመንበሩ፤ ከዚህ በፊት መሰል የውይይት መድረኮች ይዘጋጃሉ ተብሎ መቅረቱን ያስታውሳሉ፡፡ አሁን መንግስት ማድረግ ያለበት ለህዝብ ጥያቄ መልስ መስጠት ነው ብለዋል - አቶ ሙላቱ፡፡
የፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባል የሆነው የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ (ኢራፓ) ፕሬዚዳንት አቶ ተሻለ ሰብሮ በበኩላቸው፤ “መንግስት ከተቃዋሚዎች ጋር ይወያያል የተባለው ከ2002 ምርጫ ማግስት ጀምሮ ነው፤ ሆኖም ተፈፅሞ አያውቅም፤ የአሁኑም የፓርላማው ውይይት የተስፋ ቃል ነው” ይላሉ፡፡
የመንግስትና የተቃዋሚዎች ውይይት እስካሁን ተግባራዊ ሲሆን አለማየታቸውን የገለፁት አቶ ተሻለ፤ “በእውን የሚደረግ ከሆነም፣ “በምን አግባብ ይከናወናል? መቼ ነው የሚጀምረው? እንዴት ነው ተቃዋሚዎች የሚሳተፉት? የሚሉትን ጥያቄዎችን መመለስ አለበት” ብለዋል፡፡ “የውይይት መድረኩ እውን ይሆናል ብለን እንድናምንና ምልክቶች መታየት አለባቸው ብለዋል” - ሲሉ አክለዋል፡፡
“የተቃዋሚዎች በፓርላማ መሳተፍ ምንን መርህ አድርጎ ነው? ህገ መንግስታዊ ነው? በአዋጅ የሚያሳትፍ ነው? የፖሊሲ አቅጣጫ አለው?” ሲሉ የጠየቁት የኢዴፓ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጫኔ ከበደ በበኩላቸው፤ “ተቃዋሚዎች በምን መንገድ፣ የትኛውን የህብረተሰብ ክፍል ወክለው  ነው በፓርላማ ሊሣተፉ የሚችሉት” ብለዋል፡፡
‹‹መንግስት ቅድሚያ መስጠት ያለበት ለህዝቡ ቀጥተኛ ጥያቄዎች መልስ መስጠት ላይ ነው ያሉት ዶ/ር ጫኔ፤ በአሁኑ ሰዓት ህዝብ ለተቃዋሚዎችም ለመንግስትም ፍላጎት ባላሳየበት ሁኔታ ተቃዋሚዎች በምን አግባብ ነው ፓርላማ ገብተው ሊነጋገሩ የሚችሉት ሲሉ ጠይቀዋል፡፡  ኢዴፓ ተቃዋሚዎችን ፓርላማ አስገብቶ በመወያየት ብቻ ችግሮች ይቀረፋሉ የሚል እምነት  እንደሌለው የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፤ ፓርቲያቸው የፖሊሲ አቅጣጫዎች እንዲሻሻሉና ህግ ሙሉ ለሙሉ እንዲከበር እንደሚፈልግ ገልፀዋል፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስና የፌደራሊዝም መምህር አቶ ናሁሠናይ በላይ የፓርላማውን ውይይት በተመለከተ ተጠይቀው ሲመልሱ፤ በፓርላማው ለየት ያለ ሃሳብ እንዲንፀባረቅ መፈለጉ መልካምና ጠቃሚ መሆኑን ገልፀው፤ የተቃዋሚዎች ሚና የሚለካው ከገዥው ፓርቲ ጋር በመገናኘታቸው ብቻ አይደለም፤ ገዥው ፓርቲ በተቃዋሚዎች ሚና የሚያምን ከሆነ፣ እንደ ፖለቲካ ፓርቲ የሚንቀሣቀሱበትን የመጫወቻ ሜዳ ምቹ ማድረግ አለበት ብለዋል፡፡
“ኢህአዴግ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገንቢ ሚና አላቸው ብሎ ማመን መጀመሩን ለማሳየት ከፈለገ፣ በፖለቲካ እንቅስቃሴያቸው ላይ እንቅፋት ከመሆን መቆጠብ ይኖርበታል፤ በአመት ሶስት ጊዜ ተቃዋሚዎችን በፓርላማ አሳትፋለሁ ማለት ብቻውን በቂ አይደለም፤ የተለያዩ መድረኮች መዘጋጀት አለባቸው” ያሉት ምሁሩ፤ “አሁን የሃገሪቱ ሁኔታ እንደ ቀድሞ የኔ ሃሳብ ብቻ  ይሰማ የሚባልበት ባለመሆኑ፣ ኢህአዴግ ከልቡ ተምሮ ከሆነ፣ ይህን ውጥኑን ተግባራዊ ሊያደርግ ይችላል” ሲሉ እምነታቸውን ገልፀዋል፡፡

     የታዋቂው ሞታውን ሪከርድስ ኩባንያ ፕሬዚዳንትና የአለማችን ትልቁ ሙዚቃ አሳታሚ ኩባንያ የዩኒቨርሳል ሚዩዚክ የኧርባን ሚዩዚክ ፕሬዚዳንት የሆነችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኩባንያ ስራ አስኪያጅ ኢትዮጵያ ሃብተማርያም፣ በቢልቦርድ የ2016 የአለማችን ምርጥ 100 የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ስራ ስኪያጅ ሴቶች ዝርዝር ውስጥ ተካትታለች፡፡
በአለማችን የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ የተሳካ ተግባራት የፈጸሙ የዘርፉ ኩባንያዎችን የሚመሩ ሴት የስራ አስፈጻሚዎችንና ማናጀሮችን እየመረጠ በየአመቱ ይፋ የሚያደርገው ቢልቦርድ፣ ሰሞኑንም ኢትዮጵያ ሃብተማርያምን ጨምሮ በአሳታሚነት፣ በአከፋፋይነትና በሌሎች ተያያዥ መስኮች የተሰማሩ ኩባንያዎችን የሚመሩ የአመቱ 100 ምርጥ ሴቶችን ዝርዝር አውጥቷል፡፡ የ37 አመት እድሜ ያላት ኢትዮጵያ ሃብተ ማርያም በምትመራቸው የሙዚቃ ኩባንያዎች አማካይነት በአመቱ ባከናወነቻቸው ተግባራት፣ ከአለማችን ምርጥ የሙዚቃ ኩባንያ መሪ ሴቶች ተርታ መሰለፏን ቢልቦርድ በድረገጹ ባስነበበው መረጃ ገልጧል፡፡ እ.ኤ.አ በ2011 የታላቁ የአለማችን የሙዚቃ ኩባንያ ሞታውን ሪከርድስ ከፍተኛ ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆን የተሾመችው ኢትዮጵያ፤ ስቲቪ ዎንደርን ጨምሮ ከአለማችን ታላላቅ ድምጻውያን ጋር ስኬታማ ስራዎችን በማከናወን ወደ ፕሬዚዳንትነት ማደግና በዩኒቨርሳል ሚዩዚክ ኩባንያ የኧርባን ሚዩዚክ ፕሬዚዳንት ሆና መስራት መቻሏ ተነግሯል፡፡
ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2014 በዚሁ የቢልቦርድ የአለማችን ምርጥ 100 የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ሴቶች ዝርዝር ውስጥ ተካትታ እንደነበርም መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

ስልጠናና የቴክኒክ ድጋፍ እንሰጣለን ብለዋል

   በዓለም ታዋቂና ቀዳሚ ከሆኑት የኬክና ዳቦ አምራች ድርጅቶች አንዱ የሆነው ቤከልስ በቅርቡ ከተከፈተው ራማዳ አዲስ ሆቴል ጋር በመተባበር፣ ደረጃውን የጠበቀ ኬክና ዳቦ ለአዲስ አበባ ነዋሪ ሊያቀርብ ነው፡፡
ታዋቂው ጀርመናዊ ሼፍ ባስቲያን ኤቬርሰማን ትናንት በራማዳ አዲስ ሆቴል፣ ትክክለኛ ኬክና የዳቦ መጋገሪያ ቁሶችን (ዱቄት የተለያዩ ዓይነት ቸኮሌቶች…) በማቅረብ፣ ከተለያዩ ሆቴሎች ለተጋበዙ እንግዶች በመጋገር አሳይቷል፡፡
አዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ከተማ በመሆኗ ጥራት ያለውና ደረጃውን የጠበቀ ኬክና ዳቦ ማቅረብ አለብን ያሉት ሚ/ር ባስቲያን፤ ከ5 ኮከብ ሆቴሎች ጀምሮ አነስተኛ ኬክና ዳቦ መጋገሪያዎች፤ ትክክለኛውን ቁስ እንዲጠቀሙ፣ ለሁሉም የኬክና ዳቦና ዘርፍ ኢንዱስትሪ የቴክኒክ ድጋፍ፣ ጥራት ያለውት ምርት….. እናቀርባለን ብለዋል፡፡
ማንኛውም ሆቴልና ኬክና ዳቦ መጋገሪያ ትክክለኛውን ጥሬ ዕቃ ከራማዳ አዲስ ሆቴል ጋር በመነጋገር ሊያገኝ እንደሚችል ተገልጿል፡፡

     የሆላንድ ካር ኩባንያ ግማሽ ባለሀብት የሆኑት ኢ/ር ታደሰ ተሰማ፤ በኩባንያቸው ላይ እየተደረገ ያለውን ምርመራ በተመለከተ ለጠ/ሚኒስትሩና ለፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አቤቱታ አቀረቡ፡፡
ባለሀብቱ ህዳር 27 ቀን 2009 ዓ.ም ለዋና ጠቅላይ አቃቤ ህግ አቶ ጌታቸው አምባዬና ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በፅሁፍ ባቀረቡት አቤቱታ፤ “በፍ/ቤት የኪሳራ ውሳኔ የተላለፈበትን ሆላንድ ካር ኩባንያ በተመለከተ የኪሳራውን ሂደት እንዲያከናውኑ በተሾሙት መርማሪ ዳኛ ላይ እምነት አጥቻለሁ›› ብለዋል፡፡
ባለሀብቱ እየተፈፀመ ነው ያሉት በስልጣን አለአግባብ መጠቀምና ሙስና እንዲጣራላቸው ጠይቀዋል - በአቤቱታቸው፡፡
በዘጠኝ ነጥቦች ዘርዝረው እየተፈፀሙ ናቸው ያሏቸውን ስህተቶች ያቀረቡት ባለሀብቱ፤ ኪሳራ አጋጥሞታል የተባለው ኩባንያቸው በአንድ ወቅት በሀገሪቱ ካሉ ኩባንያዎች ከፍተኛ ግብር ከፋይ የነበረና ታማኝ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ተብሎ የተሰየመ ድርጅት እንደነበር አስታውሰዋል፡፡  ሆላንድ ካር፤ ዶክ፣ አባይ፣ አዋሽ፣ ተከዜና ናኦሚ የተሰኙ አውቶሞቢሎችን በአገር ውስጥ በመገጣጠም ይታወቅ እንደነበር ይታወሳል፡፡

  አቢሲኒያ ባንክ በቅርቡ ባደረገው የባለአክሲዮኖች 20ኛ መደበኛና 11ኛ ድንገተኛ ጠቅላላ ጉባኤዎች ላይ ለግብረሰናይ ድርጅቶች እንዲለገስ የተወሰነውን የግማሽ ሚሊዮን ብር ድጋፍ ለተመረጡ 7 ግብረሰናይ ድርጅቶች ሰጠ፡፡
ባንኩ ባለፈው ሳምንት በቅርቡ ለተቀዳሚ ደንበኞች ማስተናገጃ በከፈተው ልዩ ሐበሻ ቅርንጫፍ በተደረገው የርክክብ ሥነ ስርዓት ላይ የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሙሉጌታ አስማረ ባደረጉት ንግግር፣ ባንካችን ከምስረታው ጀምሮ ላለፉት 20 ዓመታት ከበርካታ የግብረሰናይ ድርጅቶች ጋር አብሮ በመስራት ማኅበራዊ ግዴታውን ሲወጣ ቆይቷል ብለዋል፡፡
በዕለቱ ድጋፍ የተደረገላቸው 7 ግብረሰናይ ድርጅቶች፡- የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የ200 ሺህ ብር፣ መቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል የ100 ሺህ ብር፣ ለዓለም የሕፃናት ዕርዳታ ድርጅት 60 ሺህ ብር፣ ርዕይ ለትውልድ የ50 ሺህ ብር፣ ነህምያ ኦቲዝም ማዕከል የ40 ሺህ ብር፣ የጎንደር መልሶ ማቋቋምና ልማት ማኅበር የ25 ሺህ ብር፣ ፍሬገነት ኪዳን ለህፃናት የ25ሺ ብር ቼክ ከባንኩ የዲሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር ከአቶ መሰረት ታዬ እጅ ተቀብለዋል፡፡
“ከተመሰረትን አጭር ጊዜ ቢሆንም ይዘን የተነሳነው ራዕይ ትልቅ ነው፡፡ በ2020 ዓ.ም (ከ11 ዓመት በኋላ ማለት ነው) 10 ሺህ ህፃናት ራዕይ ኖሯቸው አገር የሚቀይሩ ትልቅ ቦታ የሚደርሱ ዜጎችን መፍጠር ነው” ያሉት የርዕይ ለትውልድ ፕሬዚዳንት፤ የድርጅቱ ዓላማ፣ ከተለያዩ ድርጅቶች ድጋፍ በመጠየቅ የድሃ ቤተሰብ ልጆች ምግብ እንዲበሉ ማድረግ፣ የትምህርት መርጃ መሳሪያዎችና ዩኒፎርምም ማቅረብ ነው ብለዋል፡፡

Monday, 05 December 2016 10:02

የፍቅር ጥግ

 · አንድ ላይ መሆን የቱንም ያህል አስቸጋሪ ቢሆን ግዴለኝም፤ ለብቻ ከመሆን በላይ የከፋ ነገር የለም፡፡
    ጆሴፊኔ አንጄሊኒ
· የትም ብሄድ ልዩነት የለውም፤ ሁልጊዜ ወዳንተ መመለሺያ መንገዱን አውቀዋለሁ፡፡ አንተ አቅጣጫ ማመላከቺያ ኮከቤ ነህ፡፡
   ዲያና ፒተርፍሬዩንድ
· “እወድሻለሁ” - የሁሉም ነገር መጀመሪያና መጨረሻ ይኸው ነው፡፡
   ኤፍ. ስኮት ፊትዝጌራልድ
· ሁለመናዬ ሁሉመናሽን ይወደዋል፡፡
   ጆን ሌጀንድ
· ፍቅር፤ ለሰው ልጅ ብዙዎቹ ህመሞች ድዌዎች ፈውስ ነው፡፡
   ዊሊያም ሜኒንገር
· እውነተኛ የፍቅር ታሪኮች መጨረሻ የላቸውም፡፡
   ሪቻርድ ባች
· ፍቅር እሳት ነው፡፡ ነገር ግን ልብህን ያሙቀው አሊያም ቤትህን ያቃጥለው መገመት አትችልም፡፡
   ጆአን ክራውፎርድ
· በዓይኖችህ ሳይሆን በልብህ አፍቅር፡፡
   ድሬክ
· በፍቅር ስሜት ብቻ ነው የማምነው፡፡
   ካርሴና ካፑር ክሃን
· መፈቀር ብ ቻ አ ይደለም የ ምሻው፤ መ ፈቀሬም እንዲነገረኝ ጭምር እንጂ፡፡
   ጆርጅ ኢሊዮት
· በህይወት ውስጥ አንድ ደስታ ብቻ ነው ያለው- ማፍቀርና መፈቀር፡፡
   ጆርጅ ሳንድ

Monday, 05 December 2016 09:59

ስናውቃቸው የሚገርሙን!!

 · አንድ ፓውንድ (453.6ግራም) ማር ለማምረት፣ አንድ ንብ 2 ሚሊዮን አበቦችን መቅሰም ይኖርበታል፡፡
· የዓለም የህዝብ ቁጥር እ.ኤ.አ በ2080 ወደ 10.8 ቢሊንዮ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
· በህይወት ዘመናችን ሁለት የዋና ገንዳዎች የሚሞላ ምራቅ እናመርታለን፡፡
· መዝለል የማይችል ብቸኛው አጥቢ እንስሳ ዝሆን ነው፡፡
· እንደ ጣት አሻራ ሁሉ እያንዳንዱ ሰው የተለያዩ የምላስ አሻራዎች አሉት፡፡
· የሲጋራ መለኮሽያ ላይተር የተፈለሰፈው ከክብሪት በፊት ነው፡፡
· የተራራ አንበሶች ማፏጨት ይችላሉ፡፡
· ቢራቢሮዎች ምግባቸውን የሚቀምሱት በእግሮቻቸው ነው፡፡
· ዶልፊኖች የሚተኙት አንድ ዓይናቸውን ገልጠው ነው፡፡
· የጥርስ መቦረሽያ ‹‹ኮልጌት›› በስፓኒሽ ቋንቋ ‹‹ሂድና ራስህን ስቀል›› ማለት ነው፡፡
· አንድ አማካይ ሰው በህይወት ዘመኑ 6 ወራትን ቀይ የትራፊክ መብራት ወደ አረንጓዴ እስኪለወጥ ይጠብቃል፡፡
· የሰው ልጅ ተኝቶ ሳለ፤ በአማካይ 70 የተለያዩ ነፍሳትንና
10 ሸረሪቶችን ይበላል ወይም ወደ ሆዱ ያስገባል፡፡
· ሰው እስትንፋሱን በመግታት ነፍሱን ማጥፋት
አይችልም፡፡

Monday, 05 December 2016 09:57

የማሰላሰያ ጥግ

 ለመጨረሻ ጊዜ አዲስ ነገር የሞከራችሁት መቼ ነው?
መኖር የምትችሉት ለ1 ዓመት ብቻ ቢሆን፣ ምን ለማሳካት ትፈልጋላችሁ?
ዓይናችሁን ስትጨፍኑ ምን ታልማላችሁ?
ስለራሳችሁ እጅግ አድርጋችሁ የምትወዱት ምንድን ነው?
ህይወታችሁን እንደ ፊልም ብትቆጥሩት፣ ርዕሱን ምን ትሉታላችሁ?
ራሳችሁን በ5 ቃላት እንዴት ትገልጹታላችሁ?
በጣም የምትኮሩበት ነገር ምንድ ነው?
ህይወት ትላንት ምን አስተማረቻችሁ?
ምን መጥፎ ልማዶችን ማቆም ትፈልጋላችሁ?
እናንተን ልዩ የሚያደርጋችሁ ምንድ ነው?
በጣም የምትፈልጉት ነገር ምንድን ነው?