Administrator

Administrator

- የተናዘዙት ኃጢያት ለሸክም አይከብድም፡፡
የህንዶች አባባል
- ሃዘንህ ከጉልበትህ ከፍ እንዲል አትፍቀድለት፡፡
የስዊዲሽ አባባል
- ወጣትነት በየቀኑ የሚሻሻል ጥፋት ነው፡፡
የስዊዲሽ አባባል
- የተረታ ሰው የተሰጠውን አሜን ብሎ ይቀበላል፡

የሰርቢያኖች አባባል
- ምሳሌያዊ አባባሎች የታሪክ ቤተ መፃህፍት
ናቸው፡፡
የቤልጂየሞች አባባል
- ማንንም እንዲያገባ ወይም ወደ ጦርነት እንዲሄድ
አትምከር፡፡
የዳኒሽ አባባል
- እንቁላልና መሃላ በቀላሉ ይሰበራሉ፡፡
የዴኒሽ አባባል
- በባህር ላይ ሃብታም ከመሆን ይልቅ በመሬት
ላይ ድሃ መሆን ይሻላል፡፡
የዴኒሽ አባባል
- አንደኛው እጅ ሲገነባ፣ ሌላኛው ያወድማል፡፡
የኢራቃውያን አባባል
- የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም፡፡
የኢራቃውያን አባባል
- እናት ስትሞት፣ ጎጆውም ይሞታል፡፡
የኢራቃውያን አባባል
- ውበት የሴቶች ጥበብ ነው፡፡ ጥበብ የወንዶች
ውበት ነው፡፡
የቻይናውያን አባባል
- የቅፅበት ንዴትን ከታገስክ የ100 ቀናት ሃዘንን
ታመልጣለህ፡፡
የቻይናውያን አባባል
- አይጦችን ለማጥፋት ቤትህን አታቃጥል፡፡
የአረቦች አባባል
- መሸለም ቢያቅትህ ማመስገን አትርሳ፡፡
የአረቦች አባባል
- ፀሐይ ምንጊዜም ቢሆን መጥለቋ አይቀርም፡፡
የአረቦች አባባል
- ልጆች የሌሉበት ቤት መቃብር ነው፡፡
የህንዶች አባባል
- ከአዲስ ሃኪም የቆየ በሽተኛ ይሻላል፡፡
የህንዶች አባባል



በወጣቷ ገጣሚ ፅጌረዳ ጌታቸው የተፃፉ የእንግሊዝኛ ግጥሞች የየዘ “The Unspoken Outlook” የተሰኘ የግጥም መድበል በዛሬው ዕለት ከ10፡30 ጀምሮ ቦሌ ኤርፖርት መዳረሻ ጋ በሚገኘው ቲኬ ህንፃ፣ 8ኛ ፎቅ ላይ ይመረቃል፡፡ በምረቃው ሥነ -ሥርዓት ላይ የስነ ፅሁፍ ባለሙያ ሂሳዊ ዳሰሳ ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
በ84 ገፆች የተቀነበበው የግጥም መድበሉ፤ በ38 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ገጣሚዋ ዘንድሮ በሲቪል ኢንጂነሪንግ ከአምስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ እንደምትመረቅ ታውቋል፡፡

በደራሲ ገነት አዲሱ የተፃፈው “የማንነት አደራ” የተሰኘ የረዥም ልብወለድ መጽሐፍ ባለፈው እሁድ በራስ አምባ ሆቴል የተመረቀ ሲሆን ከሳምንቱ መጀመሪያ አንስቶ በመሸጥ ላይ እንደሆነ ታውቋል፡፡
“ከዓመታት ጀምሮ በርካታ ሃሳቦች በውስጤ ከወዲያ ወዲህ ሲሉ ኖረዋል፤ እነሆ ዘመናቸው መጥቶ በአምላክ እርዳታ ቃሎች ከጥበብ ጋር እንደመዋደድ ያሉልኝ ሲመስለኝ ዛሬ ሃሳቦቼ ጽሑፍ ሆነው ሊወለዱ ደፈሩ” ብላለች፤ ደራሲዋ በመፅሀፉ መግቢያ ላይ ባሳፈረችው ሃሳብ፡፡
በ376 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ፤ ለአገር ውስጥ በ94 ብር፣ ለውጭ በ25 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ደራሲዋ በኢንተርናሽናል ቴኳንዶ በአፍሪካ የመጀመሪያውን 4ኛ ዲግሪ ያገኘች የማርሻል አርት አስተማሪ ስትሆን “አላዳንኩሽም” እና “ምርቅዝ በቀል” የተሰኙ ፊልሞች ላይ በመተወንም ትታወቃለች፡፡

    በህፃናት ላይ የሚሰራው ዊዝ ኪድስ፣ በ7 ሃገርኛ ቋንቋዎች የተለያዩ የህፃናት መፅሃፍትን ለማዘጋጀት ማቀዱን ገለጸ፡፡ መፅሃፎቹ በአማርኛ፣ በትግርኛ፣ በሃዲያ፣ በሶማሊኛ፣ በሲዳሞኛ፣ በኦሮምኛና በወላይትኛ ቋንቋዎች የሚዘጋጁ ሲሆን በቀጣይ ሳምንት በሚያካሂደው የ7 ቀናት ወርክሾፕ ላይ የመፅሃፎቹ ዝግጅት ይከናወናል ተብሏል፡፡
ከመስከረም ወር ጀምሮም መፅሃፎቹ ለገበያ እንደሚቀርቡ ተጠቁሟል።  የዊዝ ኪድስ ወርክሾፕ ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ብሩክታዊት ጥጋቡ፤ ድርጅታቸው በአዲሱ ትውልድ ልብ ውስጥ የንባብ ልማድና ፍቅርን ለማስረጽ በማለም ወደ መፅሃፍት ዝግጅት መግባቱን ጠቁመው፣ የህፃናትና  ታዳጊዎች ንባብ መጎልበት ሃገሪቱ ለምትሻው የትምህርት ጥራት አጋዥ ይሆናል ብለዋል፡
በሰባቱ ሃገርኛ ቋንቋዎች የሚዘጋጁት መፅሃፍቱ፤ህፃናትን የሚያነቃቁ የተለያዩ ታሪኮችና ርዕሰ ጉዳዮችን የሚያካትቱ  ይሆናሉ፤ የህፃናቱን እድሜ የሚመጥኑ እንዲሆኑም ይደረጋል ተብሏል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር የዘርፉ ተግዳሮቶች ብሎ ከጠቀሳቸው መካከል አስፈላጊ የሆኑ አጋዥ መፅሃፍት እንደልብ አለመገኘት አንዱ መሆኑን የጠቀሱት ወ/ሮ ብሩክታይት፤ ድርጅታቸው ይህን እጥረት ለመቅረፍ ከትምህርት ስርአቱ ጋር የተጣጣሙ ጥራት ያላቸውን ተነባቢ መፅሀፍት በተለያዩ የሃገሪቱ ቋንቋዎች ማዘጋጀቱን ይቀጥላል ብለዋል፡፡
ዊዝ ኪድስ በአሁን ወቅት እድሜያቸው ከ3-17 ዓመት ለሆናቸው ህፃናትና ታዳጊዎች 3 የቴሌቪዥን ፕሮግራሞችን እያዘጋጀ ሲሆን ከዚህ ቀደም በ5 ሃገርኛ ቋንቋዎች፣ከ35 በላይ የህፃናት መፅሃፍት አሳትሟል፡፡

የታዋቂው ፖለቲከኛ ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም“አዳፍኔ” ፍርሃትና መክሸፍ” የተሰኘ “መጽሐፍ
ባሳለፍነው ሣምንት ለንባብ በቅቷል፡፡ደራሲው ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም “ሐውልት”በሚል ርዕስ ባሠፈሩት የመታሰቢያ ገፅ ጽሑፋቸው፤ለደጃዝማች ሃይሉ ከበደ፣ ዋጋቸውን ላላገኙለኢትዮጵያ አርበኞች፣ የፋሽስት ኢጣሊያን ወረራለመቋቋም በእንግሊዝ አገርና በአውሮፓ በሙሉየተደረገውን የፖለቲካ ትግል የነጭ ዘረኛነትን አጥሮችሁሉ ተሻግረው ሰው በመሆን በፊታውራሪነትለመሩት ይዘሮ ሲሊቪያ ፓንክረስት፣ የዜግነትግዴታቸውን በአውሮፓ በተለያዩ መንገዶች ለፈፀሙለፀሐፊ ትዕዛዝ አክሊሉ ሃብተወልድ፣ ለአብዲሣ አጋእና ለዘርአይ ደረስ ይሁን ብለዋል፡፡መጽሐፉ የተለያዩ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እናታሪካዊ ጉዳዮችን የሚተነትን ሲሆን በ280 ገፆችተዘጋጅቶ በ69 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

በማህበራዊና ትምህርታዊ ጉዳዮች ላይ በማተኮር የምትዘጋጀው “ተምሳሌት” መጽሔትና ዌብሳይት የምረቃ ሥነስርዓት ዛሬ ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በዋቢሸበሌ ሆቴል ሆቴል ይካሄዳል። መጽሔቷ ባለሙሉ ቀለም ህትመት መሆኗን የገለፁት አዘጋጆቹ፤ በአዲስ አበባና በዙሪያው ባሉት ከተሞች እንደምትሰራጭም ገልፀዋል፡፡ ተምሳሌት ዌብሳይት ከመጽሔቷ ጋር በተጓዳኝ አገልግሎት እንደሚሰጥም ታውቋል፡፡
በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ “ተምሳሌት” መጽሔት እና ዌብሳይትን የማስተዋወቅ ፕሮግራም እንዲሁም የፓናል ውይይት ይካሄዳል ተብሏል፡፡


በአብነት ስሜ የተጻፉት “የቋንቋ መሰረታዊያን” እና “ሳይኪና ኪዩፒድ” የተሰኙ ሁለት መጽሃፍት ካለፈው ረቡዕ ጀምሮ ለገበያ መብቃታቸውን ጸሃፊው በተለይ ለአዲስ አድማስ ገለጸ፡፡
በቋንቋ ምንነት፣ አመጣጥ፣ የመማር ሂደት፣ ተግባራትና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥነውና 407 ገጾች ያሉት መጽሃፉ፤ በ90 ብር ከ99 ሣ. በአዲስ አበባ እና በተለያዩ ክልሎች በመሸጥ ላይ ይገኛል፡፡ በስድስት ክፍሎችና በአስራ አራት ምዕራፎች የተከፋፈለው መጽሃፉ፣በቋንቋ እና እሳቦት፣ በቋንቋ ሳይንሳዊ ጥናት እንዲሁም በጽህፈት ታሪክ ዙሪያ በጥናት የተደገፉ መረጃዎችንና ትንተናዎችን አካትቷል ተብሏል፡፡
ለገበያ የቀረበው ሌላኛው የደራሲው ስራ “ሳይኪና ኪዩፒድ” የተሰኘ የህጻናት መጽሃፍ ሲሆን አስር ተረቶች፣ አራት መቶ እንቆቅልሾችና አንድ የእንግሊዝኛ ልቦለድ አካትቶ የያዘ ነው፡፡   
አብነት ስሜ ከዚህ ቀደምም “የኢትዮጵያ ኮከብ” እና “ፍካሬ ኢትዮጵያ” የተሰኙና በኮከብ ትንበያ፣ ትንተና እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥኑ መጽሃፍትን ለንባብ ማብቃቱ ይታወሳል፡፡





በፌስቡክ  ለአመታት የተለያዩ ጽሁፎችን በማቅረብ የሚታወቁ ጸሃፊያን በጋራና በተናጠል ያሳተሟቸውን የግጥም፣ የአጫጭር ልቦለዶችና የወጎች ስብስብ መጽሐፍትን ለንባብ እያበቁ ነው፡፡
የአምስት ገጣሚያንን ስራዎች ያሰባሰበው “መስቀል አደባባይ” የተሰኘ የግጥም መድበል ባለፈው ማክሰኞ ገበያ ላይ የዋለ  ሲሆን፣ በፌስቡክ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ሂሶችንና ወጎችን በማቅረብ ተወዳጅነትን ያተረፈችው  ህይወት እምሻውም “ባርቾ”በሚል ርዕስ  የአጫጭር ልቦለዶችና የወጎች ስብስብ መጽሃፍ አሳትማለች፡፡
በግጥም መድበሉ የአሌክስ አብርሃም፣ ዩሃንስ ሃብተ ማርያም፣ ረድኤት ተረፈ፣ ዮናስ አንገሶም ኪዳኔ እና ፈቃዱ ጌታቸው ግጥሞች የተካተቱ ሲሆን፣ ገጣሚያኑ እያንዳንዳቸው አስር ግጥሞችን አቅርበዋል፡፡ 150  ገጾች ያሉት የግጥም መድበሉ፣ በ45 ብር እየተሸጠ ይገኛል፡
የግጥም ስራዎቹን በማሰባሰብ ለህትመት ያበቃው ገጣሚና ደራሲ አሌክስ አብርሃም በተለይ ለአዲስ አድማስ እንደገለጸው፣ መስቀል አደባባይ በቀጣይም በቅጽ ተከፋፍሎ ለህትመት የሚበቃ ሲሆን፣ በፌስቡክም ሆነ በተለያዩ መድረኮች የሚታወቁ ወጣትና አንጋፋ ጸሃፊያንን የግጥም፣ የወግና የልቦለድ ስራዎችን የሚያካትት ይሆናል፡፡ የመስቀል አደባባይ ሁለተኛ ቅጽ ዝግጅት በከፊል መጠናቀቁንም አሌክስ አብርሃም ጠቁሟል፡፡
በሌላ በኩል ወጎችን፣ አጫጭር ልቦለዶችንና በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥኑ መጣጥፎችን  በፌስቡክ በስፋት በማቅረብ የምትታወቀውና በርካታ ተከታዮችን ያፈራችው ህይወት እምሻው፣ የመጀመሪያ ስራዋ የሆነውን ባርቾ የተሰኘ የወጎችና የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መጽሃፍ፣ ለህትመት አብቅታለች፡፡ 31 ወጎችን፣ 8 ልቦለዶችንና 13 የመሸጋገሪያ አጫጭር ልቦለዶችን ያካተተውና 256 ገጾች ያሉት መጽሃፉ፣ የመሸጫ ዋጋው 60 ብር እንደሆነ ደራሲዋ ለአዲስ አድማስ የገለጸች ሲሆን የፊታችን ሐሙስ  በዋቢ ሸበሌ ሆቴል እንደሚመረቅ ተናግራለች፡፡
በዕለቱ ከ11፤30 ሰኣት ጀምሮ በሚካሄደው የምረቃ ስነስርዓት ላይ በመጽሃፉ ከተካተቱት ታሪኮች አንዱ በአጭር ድራማ መልክ ለታዳሚዎች የሚቀርብ ሲሆን፣ የሙዚቃና የግጥም ስራዎችም ይቀርባሉ፡፡
ፌስቡክ ለበርካታ ወጣትና አንጋፋ ጸሃፍያን ስራዎቻቸውን ለአንባቢ ለማድረስ ሁነኛ አማራጭ እየሆነ የመጣ ሲሆን በማህበራዊ ድረገጹ ላይ በመጻፍ የሚታወቁ በርካቶችም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስራዎቻቸውን በመጽሃፍ መልክ እያሳተሙ በስፋት ለንባብ ማብቃት ጀምረዋል፡፡
በፌስቡክ ከሚታወቁና ከዚህ ቀደም ስራዎቻቸውን ለህትመት ካበቁ ጸሃፊያን መካከል፣ አሌክስ አብርሃም፣ በረከት በላይነህ፣ ሮማን ተወልደ ብርሃን፣ ዮሃንስ ሞላ፣ ሃብታሙ ስዩም፣ ቢኒያም ሃብታሙ፣ ትዕግስት አለምነህ፣ ሄለን ካሳ፣ ዮናስ አንገሶም ኪዳኔ፣ ሜሮን አባተ፣ ብሩክታዊት ጎሳዬ፣ ስመኝ ታደሰ እና ሌሎችም ይገኙባቸዋል፡፡

Saturday, 04 July 2015 10:34

የኪነት ጥግ

(ስለ ፋሽን)
- ጎበዝ የሆነች ሞዴል ፋሽንን በ10 ዓመት
ልትቀድመው ትችላለች፡፡
ይቭስ ሴይንት ሎውሬንት
- እኔ ፋሽን አልሰራም፡፡ ራሴ ፋሽን ነኝ፡፡
ኮኮ ቻኔል
- ልብሶችን ዲዛይን አላደርግም፡፡ እኔ ዲዛይን
የማደርገው ህልሞችን ነው፡፡
ራልፍ ሎረን
- ፋሽን ያልፋል፤ ስታይል (ሞድ) ዘለዓለማዊ
ነው፡፡
ይቭስ ሴይንት ሎውሬንት
- ሴቶች የሚፈልጉትን አውቃለሁ፡፡ የእነሱ
ፍላጎት መዋብ ነው፡፡
ቫሌንቲኖ ጋራቫኒ
- ሽቶ የማትቀባ ሴት ተስፋ የላትም፡፡
ኮኮ ቻኔል
- ስታይል ሳትናገሩ ማንነታችሁን
የምትገልፁበት መንገድ ነው፡፡
ራሄል ዞ
- አንድ ሰው አይተኬ ለመሆን ምንጊዜም
ከሌላው መለየት ይኖርበታል፡፡
ኮኮ ቻኔል
- አለባበስ የኑሮ ዘይቤ ነው፡፡
ይቭስ ሴይንት ሎውሬንት
- እያንዳንዱ ትውልድ በድሮ ፋሽን ይስቃል፤
አዲሱን ግን የሙጥኝ ብሎ ይከተለዋል፡፡
ሔነሪ ዲቪድ ቶሬዩ
- የፋሽን ዲዛይነር ብሆንም ሻንጣዬን በብዙ
ቁሳቁሶች አልሞላም፡፡
ሪም አክራ
- ልብሶችን በማጥለቅና በወጉ በመልበስ
መካከል ልዩነት አለ፡፡
ዋየኔ ክሪሳ
- ግሩም ልብስ ከጥሩ ጫማ ጋር ያምራል፡፡
ሁለቱን መነጠል አትችልም፡፡
ዋይኔ ክሪሳ
- ምንም እንኳን የወንዶች ዓለም ቢሆንም
ሴት መሆኔን እወደዋለሁ፡፡ ወንዶች ቀሚስ
መልበስ አይችሉም፤ እኛ ግን ሱሪ መልበስ
እንችላለን፡፡
ዊትኒ ሂዩስተን
- ለልጃገረድ ተስማሚውን ጫማ ስጧት፤
ዓለምን ድል ትነሳለች፡፡
ማርሊን ሞንሮ
- የማስበው በጥቁር … ነው፡፡
ጋሬዝ ፑግ

Saturday, 04 July 2015 10:30

የፀሐፍት ጥግ

ኑርሁሴን
ሂሮዬ ሺማቡኩሮ
(ስለ ሃያስያን)
- ለማንም ሙገሳም ሆነ ወቀሳ ትኩረት አልሰጥም።
እኔ የምከተለው ስሜቴን ብቻ ነው፡፡
ዎልፍጋንግ አማዴዩስ ሞዛርት
- መፃፍ የሚችሉ ይፅፋሉ፤ መፃፍ የማይችሉ
ይተቻሉ፡፡
ማክስ ሃውቶርን
- አብዛኞቻችን ዘንድ ያለው ችግር በትችት ከመዳን
ይልቅ በሙገሳ መጥፋትን መምረጣችን ነው፡፡
ኖርማን ቪንሰንት ፒል
- ወጣቶች ሞዴሎችን እንጂ ሃያስያንን
አይፈልጉም፡፡
ጆን ውድን
- ሂስ የሚጠይቁ ሰዎች የሚፈልጉት ውዳሴ ብቻ
ነው፡፡
ሶመርሴት ሟም
- ልብህ ትክክል መስሎ የተሰማውን አድርግ፡፡
ትችት እንደሆነ አይቀርልህም፡፡
ኢልኖር ሩስቬልት
- አንድ ሰው ሌሎችን ለማውገዝ ከማሰቡ በፊት
ራሱን ለረዥም ጊዜ መመርመር አለበት፡፡
ሞሌር
- ሃያሲ ስንዝር ከሰጠኸው ተውኔት ልፃፍ ይላል፡፡
ጆን ስቴይንቤክ
- ሂስ የተወለደው ከኪነጥበብ ማህፀን ውስጥ
ነው፡፡
ቻርልስ ባውድሌይር
- ጠንካራ አስተያየቶች የሚሰነዘሩት በሚወዱህ
ሰዎች ብቻ ነው፡፡
ፌዴሪኮ ማዮር
- ሃያሲያን በሥነ ፅሁፍና በሥነ ጥበብ ዘርፍ
ያልተሳካላቸው ሰዎች ናቸው፡፡
ቤንጃሚን ዲስራኤሊ
- አንበሳም ቢሆን ራሱን ከዝንቦች መከላከል
አለበት፡፡
የጀርመናውያን አባባል
- የጎረቤትህን ቤት ብታቃጥል ያንተን ቤት የተሻለ
ገፅታ አያጎናፅፈውም፡፡
ሎ ሆልትዝ
- ሃያስያን ለሚናገሩት ትኩረት አትስጥ፡፡ ለሃያሲ
ክብር ፈፅሞ ሃውልት ቆሞለት አያውቅም፡፡
ዣን ሲቤሊዩስ