Administrator

Administrator

Saturday, 07 January 2017 00:00

የዘላለም ጥግ

(ዝነኞች በመሞቻቸው ሰዓት የተናገሩት)

- “እርስ በርስ ተዋደዱ”
    ጆርጅ ሃሪሰን (እንግሊዛዊ ሙዚቀኛ)
- “መሄድ እፈልጋለሁ፤ እግዚአብሔር ይወስደኛል”
    ድዋይት ዲ. አይዘንሃወር (የአሜሪካ ፕሬዚዳንት)
- “እንቅልፌን ልተኛ ነው፤ ከአሁን በኋላ አልጠራችሁም፡፡ እናንተም ወደ መኝታችሁ መሄድ ትችላላችሁ”
     (ለጠባቂ ወታደሮቹ የተናገረው) ጆሴፍ ስታሊን (የሶቭየት ህብረት መሪ)
- “እንዳላሰለቸኋችሁ ተስፋ አደርጋለሁ”
    ኤልቪስ ፕሪስሊ (አሜሪካዊ ዘፋኝና ተዋናይ)
- “እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን፡፡ በክፍል ውስጥ አስቂኙ ሰው መሆን ሰልችቶኛል”
    ዴል ክሎዝ (ኮሜዲያን)
- “ለእኔ አታልቅሺ፤ ምክንያቱም የምሄደው ሙዚቃ የተወለደበት ሥፍራ ነው”
     (ለሚስቱ የተናገረው) ጆሃን ሴባስትያን ባች (ጀርመናዊ ሙዚቃ ቀማሪ)
- “ያሳዝናል፤ ያሳዝናል፤ በጣም ዘገየ!”
       (ያዘዘው የወይን ጠጅ በሰዓቱ ባለመድረሱ የተናገረው) ሉድዊግ ቫን ቤትሆቨን (ጀርመናዊ ሙዚቃ ቀማሪ)
- “እኔ ፒያኖ ተጫዋች ነኝ”
      (“ፕሮቴስታንት ነህ ካቶሊክ?” ተብሎ ሲጠየቅ የመለሰው) ጆን ፊልድ (አየርላንዳዊ ሙዚቃ ቀማሪ)
- “ዛሬ ለመሞት ጥሩ ቀን ነው፡፡ ሁላችሁንም ይቅር ብያችኋለሁ፡፡ እግዚአብሔርም ይቅር እንደሚላችሁ ተስፋአደርጋለሁ”
     ቤንጃሚን መርፊ (ቅጥር ነፍሰ ገዳይ)
- “ለመሞት አልፈልግም፡፡ እባካችሁ ከሞት ታደጉኝ”
     ቻቬዝ ሁጎ (የቬኔዝዋላ ፕሬዚዳንት)
- “የለም፤ እርቃኔን አይደለም፡፡ ዩኒፎርሜን እለብሳለሁ”
     ቀዳማዊ ፍሬድሪክ ዊሊያም (የፕረሽያ ንጉስ)

Saturday, 07 January 2017 00:00

የፖለቲካ ጥግ

- ጥሩ ኳስ ተጫዋቾች፤ ጥሩ ዜጎች ይወጣቸዋል፡፡
    ቼስተር አርተር
- የፕሬዚዳንት ከባዱ ሥራ ትክክለኛውን ነገር ማከናወን አይደለም፤ ትክክለኛውን ነገር ማወቅ ነው፡፡
    ሊንዶን ጆንሰን
- መፍራት ያለብን ነገር ቢኖር ራሱን ፍርሃትን ነው፡፡
    ፍራንክሊን ዴላኖ ሩዝቬልት
- ሃቁን ተናገር፣ ጠንክረህ ሥራ፣ እናም ለእራት በሰዓቱ ድረስ፡፡
    ጌራልድ አር.ፎርድ
- ፖለቲከኞች ሥልጣን ይወዳሉ፡፡ እኔ ነፃነት እወዳለሁ፡፡ ለዚያ ነው ፖለቲከኛ ያልሆንኩት፡፡
    ቪክቶር ፒንቹክ
- ፖለቲከኞች መምራት አይችሉም፡፡ እነሱ የሚችሉት ማውራት ብቻ ነው፡፡
    ዶናልድ ትራምፕ
- ፖለቲከኞቻችን ከማንዴላ ብዙ ይማራሉ ብዬ አስባለሁ፡፡
    ክሊንት ኢስትውድ
- ሲጋራ ማጨስ ያረጋጋኛል፡፡ ለህይወቴ ደስታ የሚሰጠኝን ነገር ፖለቲከኞች እንዲወስኑልኝ አልፈልግም፡፡
    ዴቪድ ሆክኔይ
- ፖለቲካ ውስጥ እውነትን ከጨመርክ፣ ፖለቲካ አዲዮስ!
    ዊል ሮጀርስ
- ፖለቲከኞቻችንን በጣም ከመጥላታችን የተነሳ መዋሸታቸውን ቢነግሩን እንኳን አናምናቸውም፡፡
    ፒተር ኒውማን
- አገርህን ውደድ፤ መንግስትን ግን ፍራ፡፡
    ኤን.ኢ.ፎክ ዊዝደም
- እኒያ መርሆቼ ናቸው፡፡ ካልወደድካቸው ሌሎች አሉኝ፡፡
    ግሮቾ ማርክስ
- ነፃነት የዕድገት እስትንፋስ ነው፡፡
    ሮበርት ኢንገርሶል
- ሙቀቱን የማትችለው ከሆነ ከወጥ ቤት ውጣ፡፡
    ሃሪ ትሩማን (የአሜሪካ ፕሬዚዳንት)
- አፍንጫ ስር ያለውን ለማየት የማያቋርጥ ትግል ይጠይቃል፡፡
   ጆርጅ ኦርዌል
- መንግስት ሲሳሳት፣ ትክክል መሆን አደገኛ ነው፡፡
   ቮልቴር

870 ሚሊዮን ብር ተመድቦለት፣ 5.6 ቢሊዮን ብር ፈጅቷል

በአፋር ብሄራዊ ክልል ከ11 አመታት በፊት የተጀመረውና ግንባታው በ3 አመታት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ታቅዶለት የነበረው የተንዳሆ የመስኖ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ከታቀደለት ጊዜ በ8 አመታት ዘግይቶ፣ ከተያዘለት በጀት 5 እጥፍ ያህል ፈጅቶ ተጠናቅቋል፡፡
በ1997 ዓ.ም የተጀመረው የተንዳሆ የመስኖ ግድብ ፕሮጀክት፣ ግንባታው ለ8 አመታት ከመጓተቱ በተጨማሪ፣ 870 ሚሊዮን ብር ይፈጃል ተብሎ ቢታቀድም፣ ወጪው በአምስት እጥፍ ያህል በማደግ 5.6 ቢሊዮን ብር መድረሱን የውሃ፣ የመስኖና የኤሌክትሪክ ሚኒስትር አስታውቋል፡፡
የተቋራጮች የልምድና የአቅም ማነስ፣ በፕሮጀክቱ ላይ በቂ ጥናቶች አለመደረጋቸውና ከፋይናንስ ጋር የተያያዙ ችግሮች፣ የመስኖ ግድቡ ከተያዘለት ጊዜ ዘግይቶ ለመጠናቀቁ ምክንያት መሆናቸውንም የውሃ፣ የመስኖና የኤሌክትሪክ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ከበደ ገርባ ገልጸዋል፡፡
1.8 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ የማጠራቀምና 60 ሺህ ሄክታር መሬት የማልማት አቅም ያለው የተንዳሆ የመስኖ ግድብ፣ በአሁኑ ወቅትም 25 ሺህ ሄክታር የሸንኮራ አገዳና የ6 ሺህ አባወራዎችን የእርሻ ማሳዎች በመስኖ እያለማ እንደሚገኝም ተነግሯል፡፡

በቅርቡ በኦሮሞ አባገዳዎች ም/ቤት የአባዱላነት ማዕረግ በተሰጣቸው ባለሀብቱ አቶ ድንቁ ደያስ የተቋቋመውና በስሩ 5 ድርጅቶችን ያቀፈው ‹‹ሶሩማ ፋን ቢዝነስ ግሩፕ››፤ በተለያዩ  ማህበራዊ ሚዲያዎች የስም ማጥፋት ዘመቻ እየተካሄደበት መሆኑን ገልፆ ጉዳዩን በህግ ለመፋረድ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።
ሶደሬ ሪዞርት ሆቴል፣ ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርስቲ፣ ሪፍት ቫሊ ሆስፒታል፣ ናፍያድ ት/ቤት፣ ኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ፤ ቀርሺ ማይክሮፋይናንስ የሚሉ የንግድ ድርጅቶችን በስሩ ያካተተው ቢዝነስ ግሩፑ፤ 10 ሺህ የሚደርሱ የሚደርሱ ሰራተኞችን እንደሚያስተዳድርም ተገልጿል፡፡
የቢዝነስ ግሩፑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ረታ በቀለ በፅ/ቤታቸው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ ድርጅቶቹ ከመንግስት ጋር መልካም ግንኙነት ያላቸው ቢሆንም በተለይ ሶደሬ ሪዞርትና ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ በመንግስት እንደተዘጉ ተደርጎ የተናፈሰው ዘገባ ሀሰተኛ መሆኑን ገልፀው ድርጅቶቹ መደበኛ አገልግሎታቸው እየሰጡ መሆናቸው ተናግረዋል፡፡
“ከመንግስት ጋር ጥሩ ግንኙነት አለን፣ ከቀረጥ ነፃ እቃዎችን በማስገባት ጭምር መንግስት ድጋፍ እያደረገልን ነው” ያሉት ስራ አስኪያጁ፤ የተናፈሰው ዘገባ ምንጩ እንደማይታወቅና ጉዳዩን የኩባንያው የህግ ባለሙያዎች እየመረመሩት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የድርጅቶቹ ባለቤት አቶ ድንቁ ደያስም፣ ሃገራቸውን እንዳልከዱና በውጭ ሃገር በህክምና ላይ መሠንበታቸውን ጠቁመው፣ በአሁን ወቅትም ህክምናቸውን አጠናቀው በአሜሪካ  ከሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ጋር ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርስቲ በትብብር በሚሠራበት ጉዳይ ላይ እየተመካከሩ እንደሆነ ዋና ስራ አስኪያጁ አስታውቀዋል፡፡
ተዘግቷል የተባለው ሶደሬ ሪዞርት ቀደም ሲል ግማሽ ድርሻው የመንግስት እንደነበር የጠቆሙት አቶ ረታ፤ በቅርቡ ባለሃብቱ ሙሉ በሙሉ ጠቅልለው መግዛታቸውንና አፈፃፀሙም እየተከናወን መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ከዕለታት አንድ ቀን፣ባልና ሚስት የገና በዓል ፌሽታ ወዳለበት አንድ አደባባይ በመኪና ይሄዳሉ፡፡
“የዘንድሮን ገና በደመቀ ሁኔታ ነው የምናከብረው” አለ ባል፡፡
“እንደሱ እንዳናደርግ እኔ ትላንት የገና ወጪ ስጠኝ ብልህ፣ እንደልማድህ ‹እሱን ለእኔ ተይው› አልከኝ” አለች ሚስት፡፡
“የልጆቹን ፍላጎት አንተ አታውቅም” ብልህ፣ “እንዴት? አባታቸው አይደለሁም?!” ብለህ ትቆጣለህ፡፡ አሁንም የገበያውን ነገር ካወቅኸው ገላገልከኝ”
ጥቂት መንገድ እንደሄዱ፣ አንድ የትራፊክ መብራት ጋ ይደርሳሉ፡፡ ባል ቀይ መብራቱን ጥሶ ይሄዳል፡፡
ትራፊክ ፊሽካ ይነፋል፡፡
ሹፌር ያቆማል፡፡
ለሚስቱ፤
“የዓመት ባል ገንዘብ ፈልጎ ነው እንጂ እኔ ምንም አላጠፋሁም!” ይላታል፡፡
“ቀይ መብራት ዘለህ መጥተህ፣‹እንዴት አላጠፋሁም› ትላለህ?”
“የአንቺን አላምንም፤ትራፊኩ የሚለኝን ልስማ!”
ትራፊኩ መጣ፡፡ ሹፌር መስተዋቱን ዝቅ አደረገ፡፡
ትራፊክ - “መንጃ ፍቃድ?”
መንጃ ፍቃዱን ጠየቀ፡፡
ሹፌር አሳየውና፤ “ምን አጠፋሁ ጌታዬ”
ትራፊክ፤ “ቀይ መብራት ጥሰዋል”
ሹፌር ፤“በጭራሽ አልጣስኩም!”
በመካከል ሚስት ትገባና፤
“እኔ ተው እያልኩት ነው የጣሰው፡፡ ግን ችግሩ እዚህ አገር፣ሰዎች ዶክተር ስለሆኑ የፈለጉትን ማድረግ የሚችሉ ይመስላቸዋል፡፡
ባል፤“ዝም በይ! አፍሽን ዝጊ! … እሺ ትራፊክ ይቅርታ አድርግልኝ”
ትራፊክ፤ “ጥፋትዎ ያ ብቻ አልነበረም፡፡ 30 ኪ.ሜ በሰዓት በሚነዳበት መንገድ፣50 ኪ.ሜ በሰዓት በመንዳትዎ ይጠየቃሉ፡፡”
ሚስት፤
“እኔ ቀስ ብለህ ንዳ ብዬው እምቢ ብሎኝ ነው - ነግሬዋለሁ!”
ባል፤ “አንቺ ሴትዮ፤አፍሺን ዝጊ ብያለሁ!!”
ትራፊኩም፤ “እመቤት፤ሁልጊዜ እንደዚህ ነው የምትወያዩት?”
ሚስት፤
“ኧረ ጌታዬ፤ሌላ ጊዜ ጨዋ ነው፡፡ እንዲህ ሲጠጣ ብቻ ነው እንደዚህ የሚናገረኝ!”
ትራፊክ፤
“አሃ!!”
*   *   *
 አውቃለሁ፣ በቅቻለሁ ብሎ ሁሉ እኔ እንዳልኩት መሆን አለበት የማለት ግትርነት ደግ አይደለም፡፡ የየትኛውም ሙያ ባለቤት እንሁን፡፡ ከህግ በላይ አይደለንም፡፡ በሙያ ክህሎት አገኘን ማለት ከሀገርና ከሀገሬው በላይ ሆንን ማለት አይደለም፡፡ ዝርዝር ጉዳዮች ለዐቢዩ ህግ ተገዢ መሆናቸውን በፍፁም መዘንጋት የለብንም፡፡ የትራፊክ ህግን ማክበር ከሙያችን በላይ የሆነውን ያህል፤ ለትራፊኩ የእኛን ሙያ ማክበር፣ ከሙያው በላይ መከበር እንዳለበት፣ አሊያም እኩል የሙያ አክብሮት ሊኖር እንደሚገባው መገንዘብ እንዳለበት ሊያስተውል ተገቢ ነው፡፡
በቤተሰብ ህግም የባል ሙያ መከበሩ እንዳለ ሆኖ፣ ሚስት የምትለውን አለማዳመጥ ወይም መናቅ ኪሳራ ነው!!
ይህ ነገር በበዓል ሰሞን በጣም ግዘፍ ይነሳል! መደማመጥ በበዓል ሰሞን ምንዛሪው ብዙ ነው። በአንድ ወገን ባህል አለ፡፡ በሌላ ወገን ዘመናዊ ስሜት አለ፡፡ ለምሳሌ፣ በአውሮፓውያን የልደት ዛፍ (X-mas Tree) እና በእኛ ቄጤማና ነጭ አረቄ ስሜት መካከል እንደምንገነዘበው፡፡ በልጆቻችን ላይ የሚፈጠረው ስሜት፣ በወላጆቻችን ላይ የሚደረተው ስሜት፣ ማንም ስለ ምንም ማብራሪ ሳይሰጥ፣ በዘፈቀደ መከበሩና እንደፈረደብን ሳንወያይበት፣ በተድላና በደስታ ማለፋችን፤ የአልፋ - ኦሜጋ ሕግ መሆኑ ግራ ያጋባል፡፡
ባህልን መጠበቅ ግድ ነው፡፡ ባህልን መከለስ ምርጫ ነው፡፡ የሁለቱን ልዩነት ማወቅና ማስተዋል፣ ኃላፊነት የሚሰማው ዜጋ ግዴታ ነው!
የገና በዓልን ስናስብ የክርስቶስን ልደት እናስብ፡፡ የእኛን “ልደት”ን ግን በፍፁም፣ መርሳት የለብንም። በየቀኑ መወለድ፣ በየዕለቱ ማደግ መቼም ያስተዋልነው ጉዳይ ነው፡፡ የየዕለት ውልደታችን ውጤት እገና ዘንድ እሚደርሰው፣ የዓመት ውሎአችንን ጠቅልሎ ነው፡፡ ስለዚህም ከተወለድን አይቀር በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ባህላዊ መንፈሱ የተሟላ ልደት ይሆንልን ዘንድ እንመኝ! “ከሰማያተ - ሰማያት ወርጄ፣ ከድንግል ማሪያም ተወልጄ አድንሃለሁ” የሚለውን አስታውሶ፣ በስፋት መጠቀም ነው፡፡ “ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው!” ማለትም ያባት ነው፡፡
በየወቅቱ መወለድ የአዳጊ ልጅ ባህሪ ነው፡፡ እያንዳንዷን እድገት ሳይታክቱ መመርመር ታላቅ ዕድል ነው፡፡ ለመወለድ ሰብዓ ሰገሎችን ሳንጠብቅ፣ ለየራሳችን ስራ፣ ጥረት፣ ትግል፣ ዕምነት ቦታ መስጠት አገርንና ህዝብን ያሳብባል፡፡ በየዕለቱ ሁላችንም አራስ ነን፡፡ ነገ ግን ወጣት፣ ጎልማሳና አዋቂ እንሆናለን፡፡ በሁሉም ገፅታችን አገራችን ትፈልገናለች!!
የለውጥ አቅም ከለመድነው መፋታት ነው፡፡ ከለመድነው መላቀቅ፣ የአዲስ አዕምሮ ቅያስ ይፈልጋል፡፡ ቅያሱ መንገድ የት እንደሚያደርሰን ለማወቅ፣ የእንቅፋቶቹን ምንነት፣ የእኛን ምርጫና ግባችንን ማወቅ፣ የእኛን ቀጣይ - ዘዴ መቀየስ፤ የለውጥ ሙከራ ባይሳካ ደግሞ መዘጋጀት ዋና መሆኑን … ማስተዋል ብልህነት ነው፡፡ ያም ሲለመድ ደግሞ እንደ ህይወት ይኖራል፡፡ “ልማድ ሲሰለጥን ተፈጥሮ ይሆናል” የሚለው አባባል ግንዛቤ ውስጥ ይገባል የሚባለው ይሄኔ ነው!! ሁሉንም በቀናው ሂደት ይባርክልን፡፡ ራሳችንን ከአደጋ እንጠብቅ!
መልካም የገና በዓል
 ለክርስትና ዕምነት ተከታዮች!!

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የአዕምሮ ህክምና ክፍል ተባባሪ ፕሮፌሰርና የትምህርት ክፍሉ ሃላፊ በሆኑት ዶ/ር ዳዊት ወንድምአገኝ ተፅፎ፣ ባለፈው ሳምንት ለንባብ የበቃው ‹‹አለመኖር›› የተሰኘ መፅሐፍ፤ ዛሬ ከቀኑ 9፡00 ጀምሮ ቦሌ ሩዋንዳ በሚገኘው ባታ የባህል ምግብ አዳራሽ እንደሚመረቅ የፕሮግራሙ አዘጋጅ ክላስ ፕላስ ኤቨንት አስታውቋል፡፡
በምርቃት ሥነስርዓቱ ላይ መፅሐፉ ለውይይት የሚቀርብ ሲሆን የአዕምሮ ሀኪሙ ዶ/ር መስፍን አርአያ፣ የፍልስፍና ምሁሩ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይና ወ/ሮ ሶሎሜ ታደሰ በመጽሐፉ ላይ ጥናታዊ ጽሁፍ እንደሚያቀርቡ ይጠበቃል፡፡  

Saturday, 31 December 2016 11:37

የፍቅር ጥግ

 (ስለ ቤተሰብ)

 · በዓለም ላይ ትልቁ ነገር ቤተሰብና ፍቅር ነው፡፡
    ጆን ውድን
· የእኔ ጥንካሬና ድክምቴ፤ ቤተሰቤ ነው፡፡
    አይሽዋርያ ራይ ባችቻን
· ህፃናት የገነት መግቢያ ቁልፎች ናቸው፡፡
    ኤሪክ ሆፈር
· ቤተሰብ ከተፈጥሮ ድንቅ ስራዎች አንዱ ነው፡፡
    ጆርጅ ሳንታያና
· ህፃናት ንስሮች፤ በቤተሰባቸው ክንፍ ፈጽሞ ሊበሩ አይችሉም፡፡
    ሊዩ ያንግ
· የእኔ ምክር፡- ዛሬ ለአንዲት ሰከንድ ቤተሰብህን አመስግን፡፡
     ጄና ሞራስካ
· የሴቶች ተፈጥሮአዊ ሚና የቤተሰብ ምሰሶ መሆን ነው፡፡
     ግሬስ ኬሊ
· ቤተሰብ የሥልጣኔ መሰረት ነው፡፡
     ዊል ዱራንት
· በቤተሰቤ ውስጥ ከትውልድ ወደ ትውልድ፣ ከሰባት ትውልድ በላይ፣ ለ200 ዓመታት ሲተላለፍ የቆየ አንድ ነገር ቢኖር - ተስፋ አለመቁረጥ ነው፡፡ ለሽንፈት እጅ አለመስጠት፡፡ በዚያ መንገድ ነው የምንኖረው፡፡
      ኒክ ዋሌንዳ
· የነበረኝን በሙሉ ሰጥቼአለሁ፡፡ አሁን ከቤተሰቤ ጋር ጥሩ ጊዜ ማሳለፍ እፈልጋለሁ፡፡
       ዲያጎ ማራዶና
· በጣም ሃይማኖተኛ የሆነ ቤተሰብ ውስጥ ነው ያደግሁት፡፡ በ5 ዓመቴ ቁራን በቀላሉ አቀራ ነበር፡፡
       አክህማድ ካድይሮቭ
· ቤተሰቤ አስቂኝ እንደነበር ተገንዝቤአለሁ፤ ምክንያቱም ማንም ሰው ከቤታችን መውጣት አይፈልግም ነበር፡፡
       አንቶኒ አንደርሰን
· በእኛ ቤተሰብ፣ ለአባቴ መልስ ከሰጠሁ፣ ችግር ውስጥ እወድቃለሁ፡፡
      ጆል ኮርትኔይ
· ቤተሰብህን አትመርጥም፡፡ ከእግዚአብሔር የሚቸርህ ስጦታ ነው፡፡
      ዴዝሞንድ ቱቱ
· ቤተሰብ የህይወት መሰረት ነው፡፡ የዘላለም ደስታ ቁልፍም ጭምር፡፡
      ሌ.ቶም ፔሪ

Saturday, 31 December 2016 11:41

የፀሀፍት ጥግ

 - ማንም ሰው እስኪሞት ድረስ ግለ ታሪኩን መፃፍ ያለበት አይመስለኝም፡፡
      ሳሙኤል ጎልድዊን
- የገጣሚ ግለ ታሪኩ ግጥሙ ነው፡፡ የቀረው ሁሉ የግርጌ ማስታወሻ ነው፡፡
      ዬቬጌኒ ዩቭቱሼንኮ
- ‹ህይወቴ› ግለታሪኬ አይደለም፤ ሙዚቃ ነው፡፡
      ሜሪ ጄ. ብሊግ
- ከባለቤቱ ይሁንታ ያላገኘ ግለ ታሪክ እየፃፍኩ ነው።
     ስቲቨን ራይት
- መፅሐፍ አንድም ግለ ታሪክ ነ ው፣ አ ሊያም ረዥም ልብወለድ ነው፡፡
     አይምሬ ኬርቴስዝ
- የወንድ ፊት ግለ ታሪኩ ነው፡ የሴት ፊት የልብ ወለድ ስራዋ ነው፡፡
     ኦስካር ዋይልድ
- የህይወት ታሪክህ ሲፃፍ ብዕሩን ማንም እንዲይዘው አትፍቀድ፡፡
     ሬቤል ትሪቨር
- ይሄ ግለ ታሪኬ አይደለም፡፡ የእስካሁኑን ጉዞዬን ብቻ የሚናገር ነው፡፡
     ሪቱ ቤሪ
- የህይወት ጉዞ አይገመቴ ነው፤ ማንም አስቀድሞ ግለ ታሪኩን ሊፅፍ አይችልም፡፡
     አብርሃም ጆሹዋ ሄሼል
- የህይወት ታሪክህን ስትፅፍ፣ እያንዳንዱ ገፅ ማንም ሰምቶት የማያውቀው ጉዳይ ማካተት አለበት፡፡
     ኤልያስ ካኔቲ

Saturday, 31 December 2016 11:32

የዘላለም ጥግ

 (ዝነኞች በመሞቻቸው ሰዓትየተናገሩት)

- “ወዳጆች ያጨብጭቡ፤ ኮሜዲው አልቋል”
    ሉድዊግ ቫን ቤትሆቨን (ሙዚቃ ቀማሪ)
- “እየሞትኩ ነው፡፡ ለረዥም ጊዜ ሻምፓኝ አልጠጣሁም”
   አንቶን ፓቭሎቪች ቼክኾቭ (ፀሐፊ)
- “ትክክለኛውን ነገር ለመስራት ተጣጥሬአለሁ”
   ግሮቨር ክሌቪላንድ (የአሜሪካ ፕሬዚዳንት)
- “መብራቱን አብሩት፤ በጨለማ ወደ ቤቴ መሄድ አልፈልግም”
    ኦ ኼንሪ (ደራሲ)
- “መብራቱን አጥፉት”
    ቴዎዶር ሩስቬልት (የአሜሪካ ፕሬዚዳንት)
- “ኢየሱስን አየዋለሁ፤ ኢየሱስን ለማየት እሻለሁ”
    ዊትኒ ሂዩስተን (ድምፃዊት)
- “መሞት አልፈልግም” (ሞታ ከመገኘቷ ከ2 ሰዓት በፊት በስልክ የተናገረችው)
    ኤሚ ዋይንሃውስ (ድምፃዊት)
- “ለማንበብ ወደ መታጠቢያ ክፍል እየሄድኩ ነው”
    አልቪስ ፕሪስሊ (ሙዚቀኛ)
- “አያችሁ፤ እንዲህ ነው የምትሞቱት”
    ኮኮ ቻኔል (ፋሽን ዲዛይነር)
- “ለእኔ ጠጡልኝ”
    ፓብሎ ፒካሶ (ሰዓሊ)
- “ዛሬ ማታ በደንብ እተኛለሁ››
    ሔነሪ ፎርድ (የአውቶሞቢል አምራች)
- “ብቻዬን ተዉኝ፡፡ ደህና ነኝ!”
     ባሪ ዋይት (ዘፋኝ)
- “ነገ ፀሐይ ስትወጣ እዚህ አልገኝም”
    ኖስትራዳመስ (ሀኪምና የክዋክብት ተመራማሪ)
- “ከሞት በስተቀር ምንም አልፈልግም”
     ጄን ኦዩስተን (ደራሲ)
- “ሰዓቴ የት ነው ያለው?”
    ሳልቫዶር ዳሊ (ሰዓሊ፣ ፀሐፊና ፊልም ሰሪ)

Saturday, 31 December 2016 11:31

አስገራሚ እውነታዎች!!!

 (ከዝነኞች ህይወት)
ዝነኛው የፊልም ተዋናይ ጃኪ ቻን፤ በ1954 (እ.ኤ.አ) ከድሃ ጥንዶች ነው የተወለደው፡፡ ወላጆቹ ያጡ የነጡ ድሃ ስለነበሩ ለሆስፒታል የሚከፍሉት ገንዘብ አጥተው ልጃቸውን (ጃኪ ቻንን) ለመሸጥ ሁሉ ዳድተው ነበር፡፡ በመጨረሻ ግን ተግተው ሰሩና ለሆስፒታሉ ክፍያ በቂ  ገንዘብ አገኙ፡፡ ዛሬ ጃኪ ቻን የሆሊውድ ተከፋይ ነው፡፡  
ታዋቂው አሜሪካዊ ኮሜዲያን ጂም ኬሪ፤ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን አቋርጦ የወጣው በ16 ዓመቱ ነበር፡፡ ለምን? ትኩረቱን ኮሜዲ ላይ አድርጎ ለመሥራት፡፡  
“Rocky” የተሰኘውን የፊልም ስክሪፕት የጻፈው ዝነኛው ተዋናይ ሲልቪስተር ስታሎን ነበር- ራሱ። ነገር ግን ስክሪፕቱን ሲጽፍ የሚኖርበት ቤት እንኳን አልነበረውም፡፡ ስክሪፕቱን ከመሸጡ ከአንድ ሳምንት በፊት በጣም ተቸግሮ ውሻውን በ50 ዶላር ሸጧት ነበር፡፡ በኋላ ግን መልሶ ገዛት - በ3ሺ ዶላር!! ገንዘብ ከየት ፈሰሰለት? ከስክሪፕት ሽያጩ ነዋ!!
የፊልም ተዋናዩ ሳን ዊሊያም ስኮት፤ ሴቶች ሲያፍርና ሲሽኮረመም አይጣል ነበር፡፡ እንስቶች በአካባቢው ካሉ በጭንቀት ላብ በላብ ይሆናል። በዚህም የተነሳ 30 ዓመት እስኪሞላው ድረስ የሴት ጓደኛ ወይም ፍቅረኛ አልነበረውም፡፡
የፊልም ተዋናዩ ጃክ ኒኮልሰን፤ ዓይናፋርነት አይነካካውም፡፡ ከልጅነቱ ጀምሮ ያሳደጉት  አያቶቹ ነበሩ፡፡ እሱ ግን እውነተኛ ወላጆቹ እንደሆኑ ነበር የሚያውቀው፡፡ እ.ኤ.አ በ1973 ዓ.ም ከ”ታይም” መፅሄት ጋዜጠኛ የሰማው መረጃ ዱብዕዳ ነው የሆነበት፡፡  “እህቱ” እንደነበረች የሚያውቃት ጁን፤ እውነተኛ እናቱ ሆና ተገኘች። በ37 ዓመት ዕድሜው!! ክፋቱ ደግሞ ይሄን እውነት ከመስማቱ በፊት እናቱም ሴት አያቱም ሞተዋል፡፡  
ጄምስ ቦንድን ሆኖ የሚተውነው የፊልም ባለሙያው ዳንኤል ክሬይግ፤ በትወናው ከፍተኛ ዝናና ተወዳጅነት፣ እንዲሁም በሽበሽ ገንዘብ አግኝቷል፡፡ ይሄ ብቻ ግን አይደለም፡፡ በፊልሙ ላይ ሲተውን የሚያሽከረክራትን Aston Martin የተሰኘች አውቶሞቢል የሚያመርተው ፋብሪካ፤ የህይወት ዘመን ስጦታ (መብት) አሽሮታል፡፡ በማንኛውም ጊዜ ደስ ያለውን መኪና (አስቶን ማርቲን ጨምሮ) አስነስቶ መፈትለክ ነው - በቀሪው ህይወቱ ሁሉ፡፡
“ሚስተር ቢን”ን ሆኖ የሚተውነው እንግሊዛዊው ኮሜዲያን ሮዋን አትኪንሰን፤ እንደ አሜሪካዊው ኮሜዲያን ጂም ኬሪ በ16 ዓመቱ ትምህርት አላቋረጠም፡፡ እንደውም ወደ ትወና የገባው በኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ የማስተርስ ዲግሪውን ከተቀበለ በኋላ ነው-  ከእንግሊዙ ኒውካስትል ዩኒቨርሲቲ፡፡