Administrator

Administrator

Saturday, 20 June 2015 10:13

‹‹እውነት!?››

‹‹እውነት!?››
አንድ የገዢው ፓርቲ አባል ‹‹ምርጫ በማሸነፉ›› ደስ ተሰኝቶ ሚስቱ ጋ ደወለ አሉ፡፡
‹‹ሄሎ ማሬ!›› ‹አቤት ውዴ! ‹‹ምርጫውን እኮ አሸነፍኩኝ!›› አለ ደስታ ባመጣው ፈገግታ ታጅቦ፡፡ ‹‹እውነት!?›› እሷም ደስታ የሚያደርጋትን አሳጥቷት ባለማመን ጠየቀች፡፡ ጥያቄዋ ግን ባልን አስቆጣው፤ ‹‹እ!? ምን አልሽ አንቺ!›› ‹‹እውነት አሸነፍክልኝ ወይ?› ነው ያልኩት፡፡›› አሁንም ደስታዋ አላባራም፡፡
‹‹አንቺ ሴት ከፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር መዋል ጀመርሽ ማለት ነው!?›› ንዴት የሚያደርገውን እያሳጣው፡፡
‹‹ምን እያልክ ነው ውዴ?›› ግራ ቢገባት ጠየቀች፡፡
‹‹እዚህ ጋ ‹እውነት› የሚለውን ቃል ምን አመጣው!? ‹አሸነፍኩ› ማለት፤ ያው አሸነፍኩ ነው! አይገባሽም እንዴ!››
(ከበኃይሉ ገ/እግዚአብሄር ፌስቡክ)

     ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በወጣው የአዲስ አድማስ ዕትም ላይ በብዙዎች የተዘነጋውንና ከህወሓት 10 መስራቾች አንዱ የነበረውን የታጋይ አብጠው ታከለን ታሪክ ጋዜጣችሁ ለህዝብ ለማስተዋወቅ ያደረገውን ጥረት እናደንቃለን፤ምስጋናችንንም  እናቀርባለን፡፡ምንም እንኳን የአባታችን የትግል ታሪክ ተገቢውን ዕውቅና እንዲያገኝ ለሚመለከታቸው የፓርቲና የመንግስት ባለሥልጣናት ለማስታወስ  ከጎንደር አዲስ አበባ በመጣን ጊዜ የሚያነጋግረን አጥተን ብንከፋም፣ ጉዳያችንን ለማስረዳት የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ (ነፍሳቸውን ይማርና) ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ቢሮ በሄድንበት ወቅት በታላቅ ክብር፣ ከመቀመጫቸው
ተነስተው በመቀበል  ስላስተናገዱን ልናመሰግናቸው እንወዳለን፡፡ ይሄም ብቻ አይደለም።  ወይዘሮ
አዜብ “ጉዳያችሁ ጉዳዬ ነው” ብለው ታጋይ አብጠውን በተመለከተ የሚቻለው ሁሉ እንዲደረግ የበኩሌን ያለሰለሰ ጥረት አደርጋለሁ በማለት በእጅጉ አበረታተውናልና በድጋሚ ከልብ እናመሰግናለን፡፡ አባታችን አቶ አብጠው ታከለ፤ ከህውሓት የትግል ጥንስስ ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈችበት 2000 ዓ.ም ድረስ ከኢህአዴግ የትግል መስመር ያልወጣና በያዘው አቋም የፀና እንደነበርም በዚህ አጋጣሚ እንዲታወቅልን እንፈልጋለን፡፡
ቤተሰቦቻቸው 

ማኅበረ ቅዱሳንን በመወንጀል ‹‹ወጣቶቹን ሰብስባችሁ እሰሩልን›› ያሉ አስተዳዳሪዎች የፖሊስ እና
የደኅንነት አካላትን በተባባሪነት ወቀሱ‹‹ማኅበረ ቅዱሳንን እንደተቋም መወንጀል አትችሉም፤ ፖሊስ የእናንተ ብቻ አይደለም፤ መጀመሪያ ራሳችኹን ፈትሹ›› /ዶ/ር ሺፈራው ተክለ ማርያም
     በሙስና መንሰራፋት፣ በመልካም አስተዳደር እና በፍትሕ ዕጦት ሳቢያ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እየተደረገ ካለው የአገልጋዮች እና የምእመናን መነሣሣት ጋር በተያያዘ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የቤተ ክርስቲያኒቱን አካላት ማነጋገር ጀመረ፡፡ ብልሹ የሰው ኃይል አስተዳደር እና የፋይናንስ አሠራር በተከታዩ ዘንድ የሚፈጥረው የተከማቸ ቅሬታ፣ የሃይማኖት ተቋማቱ እምነት እንዲያጡ ምክንያት እየኾነ እንዳለ በሥልጠና ሰነዶቹ የሚገልጸው ሚኒስቴሩ፣ በቅርቡም የወሳኝነትና የተሳትፎ ድርሻ ያላቸው የተለያዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ የአስተዳደር እና የአገልግሎት አካላት የሚሳተፉበት ተከታታይ ውይይት እንደሚያካሒድ ተጠቁሟል፡፡በሚኒስቴሩ ጥያቄ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የተመረጡ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ከትላንት በስቲያ ከቀትር በኋላ ከሚኒስትሩ ዶ/ር ሺፈራው ተክለ ማርያም እና ከሚኒስትር ዴኤታው አቶ ሙሉጌታ ውለታው ጋር የውይይቱ ቅድመ ዝግጅት ነው የተባለ ምክክር አድርገዋል፡፡በዋና ሥራ አስኪያጁ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የተመሩ የኻያ አምስት አድባራት አስተዳዳሪዎች በተካፈሉበት በዚኹ ምክክር፣ ‹‹በማኅበራት ሰላማችንን እያጣን ነው፤ ሰንበቴ ሲከበን እናንተም የላችኹም፤ መንግሥትም የለም፤ አልደገፋችኹንም፤ አልረዳችኹንም›› የሚሉ ክሦች እና አቤቱታዎች ከአንዳንድ አለቆች መቅረቡ ተጠቅሷል፡፡ካለፈው ሚያዝያ ወር መጨረሻ ጀምሮ የሀገረ ስብከቱ ሰንበት ት/ቤቶች ፥ ሙስና እንዲወገድ፣ መልካም አስተዳደርና ፍትሕ እንዲሰፍን፣ እምነትና ሥርዐት እንዲጠበቅ በሰልፎችና በስብሰባዎች
የሚያካሒዱት እንቅስቃሴም ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን ልብሱን ለውጦ የመጣበት ነው›› ብለዋል - አስተዳዳሪዎቹ፡፡
የሰንበት ት/ቤት አባላቱ የመለያ ልብሶቻቸውን (ዩኒፎርሞቻቸውን) ለብሰው በመውጣት በሚያደርጓቸው ሰልፎችና ስብሰባዎች መንግሥት የጸጥታ ርምጃ ሳይወስድ በዝምታ መመልከቱን የተናገሩት አስተዳዳሪዎቹ፣ የፖሊስ እና የደኅንነት አካላትን በተባባሪነት በመውቀስ፣ ‹‹ወጣቶቹን እሰሩልን›› ብለው ሲጠይቁ ተሰምተዋል፡፡የቤተ ክርስቲያንን ሀብት ለግላቸው በማካበት ከገቢያቸው በላይ የሚኖሩ አለቆች በሥነ ምግባርና በፀረ ሙስና ኮሚሽን እየተመረመሩ በሀገሪቱ ሕግ እንዲጠየቁ የሰንበት ት/ቤቶቹ የሚጠይቁ ሲኾን
ዋና ሥራ አስኪያጁ እና አንዳንድ አለቆች በአንፃሩ፣ ‹‹ዶልፊን እና ሃይገር የሚያቆሙ ናቸው፤ ቢዝነስ አድርገውታል” በማለት ይከሷቸዋል፡፡በምክክሩ ወቅት ብሶት ነው የሚያስጮኸኝ በማለት በከፍተኛ ድምፅ የተናገሩ አንድ አስተዳዳሪ፣ “ማኅበረ ቅዱሳን አባላቱን የሰንበት ት/ቤት ዩኒፎርም አስለብሶ መውጣት ጀምሯል፤ ሕንፃውን ከየት አምጥቶ ነው ያቆመው?” ሲሉ በሰንበት ት/ቤቶቹ መነሣሣት ማኅበሩን ተጠያቂ አድርገዋል፡፡ “ወጣቱን ዩኒፎርም እያስለበሱ ይልካሉ” ያሉ የሌላ ደብር አስተዳዳሪም፤ “እንዴት አድርገን
መከላከል እንዳለብን አሠልጥኑን እንጂ ስለሰላም ምን ያደርግልናል” በማለት የሚኒስቴሩን
ሓላፊዎች አስደምመዋል ይላሉ የስብሰባው ተሳታፊዎች፡፡ፖሊስ እና የጸጥታ አካላት የሕዝብን ሰላም እና ደኅንነት የሚጠብቁ መኾናቸውን የተናገሩት ሚኒስትሩ ዶ/ር ሺፈራው ተክለ ማርያም፣ ‹‹ፖሊስ ለእናንተ ብቻ ነው እንዴ?›› ሲሉ አለቆቹን ጠይቀዋቸዋል፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን በሲኖዶስ ዕውቅና የተሰጠው ሕጋዊ ማኅበር መኾኑን ሚኒስትሩ ጠቅሰው፣ ችግር ያለባቸው ግለሰቦች ይኖራሉ እንጂ ማኅበር እያችሁ በጅምላ መጥራት የለባችኹም፤ ተቋሙን በጅምላ መፈረጅ ወንጀል ነው፤›› ብለዋል፡፡ ሀገረ ስብከቱን ጨምሮ አስተዳዳሪዎቹ በሚመሯቸው አድባራት መልካም አስተዳደርን በማስፈን ለምእመናንና ለሰንበት ት/ቤቶቹ ወጣቶች ምሳሌ መኾን እንደሚገባቸው የተናገሩት ሚኒስትሩ፣ ‹‹ሰው እሰሩ ያላችኹት ሌላ ችግር ነው የሚፈጥረው፤ የምናስረው ሰው የለም፤ መጀመሪያ ራሳችኹን ፈትሹ›› በሚል ለአለቆቹ የእሰሩልን ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በሚኒስቴሩ ዕቅድ መሠረት ይካሔዳል የተባለውና በቤተ ክርስቲያኒቱ ከሚታየው የአገልጋዮችና የምእመናን መነሣሣት ጋር የተገጣጠመው ይኸው የቅድመ ውይይት ምክክር፣ በቤተ ክርስቲያኒቱ የአስተዳደር መዋቅር የወሳኝነት እና የተሳትፎ ድርሻ ያላቸውን የማኅበረ ካህናትን፣ የማኅበረ ምእመናንና የሰንበት ት/ቤቶች ተወካዮችን
ሊያካትት እንደሚገባው አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ፡፡በዘመናዊ አሠራር፣ በመልካም አስተዳደር እና በሰላም ጉዳዮች ላይ የሚያተኩረው ዋናው ውይይት፤ በሚቀጥሉት ኹለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ እንደሚጀመር የሚኒስቴሩ ምንጮች አስታውቀዋል፡፡ የውይይቱን አቅጣጫ ለማመቻቸት በሚል ከትላንት በስቲያ በሀገረ ስብከቱ ሓላፊዎች ከተመሩት የአድባራት አለቆች ጋር ከተካሔደው ምክክር ፍጻሜ በኋላ ‹‹ዘመናዊ አሠራር ዴሞክራሲዊነት እና ብዝኃነት›› በሚል ርእስ በሚኒስቴሩ የተዘጋጀ የመወያያ ሰነድ እንደተሰጣቸውም ንጮቹ ገልጸዋል፡፡

 60 ዘጋቢ ፊልሞች ለተመልካች ይቀርባሉ
  ፌስቲቫሉ በክልል ከተሞችም ይቀጥላል
      በመላው ዓለም ከተሰሩ ምርጥ ዘጋቢ ፊልሞች የተመረጡ 60ዎቹ ለዕይታ የሚቀርቡበት “9ኛው አዲስ ኢንተርናሽናል ዘጋቢ ፊልም ፌስቲቫል” ትላንት በብሄራዊ ሙዚየም የቅርስ ጥናት እና ጥበቃ ባለስልጣን አዳራሽ ተከፈተ፡፡ ፌስቲቫሉ ለአምስት ቀናት እንደሚካሄድ የገለፁት የ“ኢንሺዬቲቭ አፍሪካ” ዋና ዲያሬክተር አቶ ክቡር ገና፤ በቀጣይ ዓመታት ፌስቲቫሉ የራሱን ውድድር አድርጎ ፊልሞችና ፊልም ሰሪዎችን ለመሸለም እንዲሁም ኢትዮጵያዊያን ፊልም ሰሪዎች በዘጋቢ ፊልሞች ስራ የተሻለ ተሳትፎ እንዲኖራቸው እንተጋለን ብለዋል፡፡ ፌስቲቫሉ የተከፈተው በሩት ኢሼል ዳይሬክተርነት በተሰራው “Shoulder Dancing” የተሰኘ ዘጋቢ ፊልም ነው፡፡ እስከ ሰኔ 9 በሚዘልቀው ፌስቲቫል፤ 60 የሚደርሱ ዘጋቢ ፊልሞች ለዕይታ የሚቀርቡ ሲሆን በአዲስ አበባ  በቅርስ ጥናትና ምርምር ማዕከል፤ በሀገር ፍቅር ትንሽዋ አዳራሽ፤ በብሪትሽ ካውንስል እና በአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሲዝ ለተመልካቾች ይታያሉ፡፡ የፊልም ፌስቲቫሉ ሰኔ 19 እና 20 ደግሞ በአዳማ፤ ባህርዳር፤ ሃዋሳ እና መቀሌ  ከተሞች እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡
በዘንድሮው ፌስቲቫል በዓለማችን አበይት የመነጋገሪያ አጀንዳዎች ላይ ተመርኩዘው የተሰሩ ዘጋቢ ፊልሞች ተመርጠው መቅረባቸውን በጋዜጣዊ መግለጫው የተናገሩት አቶ ክቡር ገና፤ ከ10 በላይ የፊልም ዳይሬክተሮችን ከተለያዩ አገራት በመጋበዝ በፊልሞቹ ዙሪያ ከተመልካች ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡበት መድረክ መመቻቸቱንም ገልፀዋል፡፡ ባለፈው ዓመት ከ10ሺ በላይ ታዳሚ የነበረው አዲስ ኢንተርናሽናል ዘጋቢ ፊልም ፌስቲቫል፤ ዘንድሮ ደግሞ በፊልሞቹ ብዛት፤ በሚቀርቡት ዘጋቢ ፊልም ሰሪዎች የብቃት ደረጃና አይነት እንዲሁም በሚያገኘው ተመልካች ብዛት በአፍሪካ ግዙፉ ፌስቲቫል ይሆናል ተብሎ ይገመታል፡፡ በፌስቲቫሉ ላይ ለመሳተፍከመላው ዓለም 500 ፊልሞች አመልክተው እንደነበር የገለፁት አዘጋጆቹ፤ ከግምገማ በኋላ 60 ዘጋቢ ፊልሞች ለዕይታ መመረጣቸውን ጠቁመው “አዲስ ኢንተርናሽናል ፊልም ፌስቲቫልን” በአፍሪካ ትልቁ መድረክ ለማድረግ በአበረታች አቅጣጫ ላይ ነን ብለዋል፡፡
ከዘጋቢ ፊልሞቹ ለዕይታ መቅረብ ባሻገር ከመላው ዓለም ከመጡ የፊልም ባለሙያዎች ጋር የጥያቄ እና መልስ እንዲሁም የውይይት መድረኮች ይካሄዳሉ ተብሏል፡፡
ኢትዮጵያውያን ፊልም ሰሪዎች በፌስቲቫሉ ላይ ያላቸው ተሳትፎ አነስተኛ መሆኑን ጠቁመው ዋናው ምክንያትም ዘርፉ ብዙም ንግድ የማይሰራበት በመሆኑ ስለማያበረታታቸው ነው ብለዋል፡፡
በፌስቲቫሉ ከሚቀርቡ ዘጋቢ ፊልሞች መካከል በኢትዮጵያዊያኑ ዳይሬክተሮች ትርሲት አግዝ እና ኃይሉ ከበደ የተሰሩት “የበሬው ውለታ” እና “ትስስር” የሚገኙበት ሲሆን “35 OWS AND A KALASHINIKOV”, “5 MINUTES Of FREEDOM”, “9999”, “At 60 Km/h” የሚሉና ሌሎችም ይታያሉ ተብሏል፡፡

 60 ዘጋቢ ፊልሞች ለተመልካች ይቀርባሉ
  ፌስቲቫሉ በክልል ከተሞችም ይቀጥላል
      በመላው ዓለም ከተሰሩ ምርጥ ዘጋቢ ፊልሞች የተመረጡ 60ዎቹ ለዕይታ የሚቀርቡበት “9ኛው አዲስ ኢንተርናሽናል ዘጋቢ ፊልም ፌስቲቫል” ትላንት በብሄራዊ ሙዚየም የቅርስ ጥናት እና ጥበቃ ባለስልጣን አዳራሽ ተከፈተ፡፡ ፌስቲቫሉ ለአምስት ቀናት እንደሚካሄድ የገለፁት የ“ኢንሺዬቲቭ አፍሪካ” ዋና ዲያሬክተር አቶ ክቡር ገና፤ በቀጣይ ዓመታት ፌስቲቫሉ የራሱን ውድድር አድርጎ ፊልሞችና ፊልም ሰሪዎችን ለመሸለም እንዲሁም ኢትዮጵያዊያን ፊልም ሰሪዎች በዘጋቢ ፊልሞች ስራ የተሻለ ተሳትፎ እንዲኖራቸው እንተጋለን ብለዋል፡፡ ፌስቲቫሉ የተከፈተው በሩት ኢሼል ዳይሬክተርነት በተሰራው “Shoulder Dancing” የተሰኘ ዘጋቢ ፊልም ነው፡፡ እስከ ሰኔ 9 በሚዘልቀው ፌስቲቫል፤ 60 የሚደርሱ ዘጋቢ ፊልሞች ለዕይታ የሚቀርቡ ሲሆን በአዲስ አበባ  በቅርስ ጥናትና ምርምር ማዕከል፤ በሀገር ፍቅር ትንሽዋ አዳራሽ፤ በብሪትሽ ካውንስል እና በአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሲዝ ለተመልካቾች ይታያሉ፡፡ የፊልም ፌስቲቫሉ ሰኔ 19 እና 20 ደግሞ በአዳማ፤ ባህርዳር፤ ሃዋሳ እና መቀሌ  ከተሞች እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡
በዘንድሮው ፌስቲቫል በዓለማችን አበይት የመነጋገሪያ አጀንዳዎች ላይ ተመርኩዘው የተሰሩ ዘጋቢ ፊልሞች ተመርጠው መቅረባቸውን በጋዜጣዊ መግለጫው የተናገሩት አቶ ክቡር ገና፤ ከ10 በላይ የፊልም ዳይሬክተሮችን ከተለያዩ አገራት በመጋበዝ በፊልሞቹ ዙሪያ ከተመልካች ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡበት መድረክ መመቻቸቱንም ገልፀዋል፡፡ ባለፈው ዓመት ከ10ሺ በላይ ታዳሚ የነበረው አዲስ ኢንተርናሽናል ዘጋቢ ፊልም ፌስቲቫል፤ ዘንድሮ ደግሞ በፊልሞቹ ብዛት፤ በሚቀርቡት ዘጋቢ ፊልም ሰሪዎች የብቃት ደረጃና አይነት እንዲሁም በሚያገኘው ተመልካች ብዛት በአፍሪካ ግዙፉ ፌስቲቫል ይሆናል ተብሎ ይገመታል፡፡ በፌስቲቫሉ ላይ ለመሳተፍከመላው ዓለም 500 ፊልሞች አመልክተው እንደነበር የገለፁት አዘጋጆቹ፤ ከግምገማ በኋላ 60 ዘጋቢ ፊልሞች ለዕይታ መመረጣቸውን ጠቁመው “አዲስ ኢንተርናሽናል ፊልም ፌስቲቫልን” በአፍሪካ ትልቁ መድረክ ለማድረግ በአበረታች አቅጣጫ ላይ ነን ብለዋል፡፡
ከዘጋቢ ፊልሞቹ ለዕይታ መቅረብ ባሻገር ከመላው ዓለም ከመጡ የፊልም ባለሙያዎች ጋር የጥያቄ እና መልስ እንዲሁም የውይይት መድረኮች ይካሄዳሉ ተብሏል፡፡
ኢትዮጵያውያን ፊልም ሰሪዎች በፌስቲቫሉ ላይ ያላቸው ተሳትፎ አነስተኛ መሆኑን ጠቁመው ዋናው ምክንያትም ዘርፉ ብዙም ንግድ የማይሰራበት በመሆኑ ስለማያበረታታቸው ነው ብለዋል፡፡
በፌስቲቫሉ ከሚቀርቡ ዘጋቢ ፊልሞች መካከል በኢትዮጵያዊያኑ ዳይሬክተሮች ትርሲት አግዝ እና ኃይሉ ከበደ የተሰሩት “የበሬው ውለታ” እና “ትስስር” የሚገኙበት ሲሆን “35 OWS AND A KALASHINIKOV”, “5 MINUTES Of FREEDOM”, “9999”, “At 60 Km/h” የሚሉና ሌሎችም ይታያሉ ተብሏል፡፡

 በዳንኤል ዓለሙ የተዘጋጀው “ይህን ያውቁ ኖሯል?” የተሰኘ የጠቅላላ ዕውቀት መጽሐፍ ሰሞኑን በገበያ ላይ ዋለ፡፡ በአምስት ምዕራፎች የተከፋፈለው መጽሐፉ፤ የዓለም አስደናቂ ሪከርዶች፣ የፖለቲካውና የስፖርቱ ዓለም አስገራሚና አስደናቂ እውነታዎች እንዲሁም በኢትዮጵያ ታሪክ ዙሪያ የሚያጠነጥኑ መረጃዎችን ይዟል፡፡ በ224 ገጾች የተሰናዳው መጽሐፉ፤ በ50 ብር ከ70 ሳ. ለገበያ ቀርቧል፡፡ ደራሲው ከዚህ ቀደም “ፈተናን የማሸነፍ ጥበብ”፣ “ስኬታማ የፍቅር ህይወት”፣“ገንዘብና ጭንቀት”፣ “ራስን የመለወጥ ምስጢር” እና “ይህን ያውቁ ኖሯል? ቁ.1” የሚሉ መጻህፍትን ማሳተሙን ጠቁሟል፡፡
በደራሲ ድርቡ አደራ የተጻፈው “ሌባ ሻይ” ልብ ወለድ መፅሐፍም ለንባብ የበቃው ባሳለፍነው ሣምንት ነው፡፡ በ400 ገጾች የተቀነበበው መጽሐፉ፤ በ80 ብር እየተሸጠ ይገኛል፡፡ ጸሐፊው ቀደም ሲል “ሐምራዊት”፣ ሽንብሩት” እና “ዲና” የሚሉ መጽሐፍትን ማሳተሙ ይታወሳል፡፡
ለአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ስለ ህዋ ሳይንስ ግንዛቤ ለመስጠት ታስቦ የተዘጋጀውና “አስትሮኖሚ ለልጆች” የተሰኘው መጽሐፍም ከሳምንቱ የህትመት ትሩፋቶች አንዱ ሆኗል፡፡ በፊዚክስ የማስተርስ ድግሪ እንዳለው በጠቆመው አክመል ተማም የተሰናዳው መጽሐፉ፤ ዩኒቨርስ፣ጋላክሲዎችና ሶላር ሲስተም በሚሉ ሶስት ምዕራፎች ተከፋፍሎ የቀረበ ሲሆን በ28 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ የትምህርት ባለሙያው አክመል፤ ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ርዕሰ ጉዳይ ለሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችና ለሌሎች “ዩኒቨርስ” የተሰኘ መጽሐፍ አሳትሞ ማቅረቡም ታውቋል፡፡

የገጣሚ ደምሰው መርሻ በሙዚቃ የተቀናበሩ የግጥም ሥራዎች “ያልታየው ተውኔት” በሚል ርዕስ በሲዲ የተዘጋጀ ሲሆን የፊታችን ረቡዕ ከ11 ሰዓት ጀምሮ በሂልተን ሆቴል ይመረቃል፡፡
17 ግጥሞችን ታዋቂው ሙዚቀኛ ጆርጋ መስፍን ያቀናበረለት ሲሆን 1 ግጥም ደግሞ በጥላሁን ጊዮርጊስ (ፒጁ) መቀናበሩን ገጣሚው ጠቅሶ፣ኤርምያስ ዳኜ የሁሉንም ሚክሲንግ እንደሰራለት ተናግሯል፡፡
የሲዲውን ሽፋን ሰዓሊ ዳንኤል ታዬ ሰርቶልኛል ብሏል- ገጣሚው፡፡   
በሒልተን ሆቴል በሚካሄደው የግጥም ሲዲ የምረቃ ሥነሥርዓት ላይ አንጋፋው ሃያሲ አብደላ እዝራ በግጥሞቹ ላይ ሒሳዊ ዳሰሳ የሚያቀርብ ሲሆን ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ፣ ገጣሚ ኤፍሬም ስዩም፣ አርቲስት ፈለቀ አበበና ሌሎችም ለታዳሚያን የግጥም ሥራዎችን ያቀርባሉ ተብሏል፡፡ ደምሰው መርሻ በተለያዩ የጥበብ መድረኮች ላይ ግጥሞቹን አዘውትሮ በማቅረብ የሚታወቅ ተወዳጅ ገጣሚ ሲሆን የ“ግጥም በጃዝ” ቡድንም አባል ነው፡፡

Saturday, 13 June 2015 15:31

የፍቅር ጥግ

ልክ ነገ እንደሌሌ ያህል አፍቅር፡፡ ነገ ከመጣ ደግሞ እንደገና አፍቅር፡፡
ማክስ ሉሳዶ
መልካም ትዳር የደግነት ውድድር ነው፡፡
ዲያኔ ሳውዬር
ደስተኛ ትዳር ሁልጊዜ አጭር የሚመስል ረዥም ጭውውት ነው፡፡
አንድሬ ማውሮይስ
በጋብቻ ውስጥ ደስታን ማግኘት ሙሉ በሙሉ የዕድል ጉዳይ ነው፡፡
ጄን ኦዩስተን
(Pride & Prejudice)
“ፍቅር”፤ አንድ ሰው መጥቶ ትርጉም እስኪሰጠው ድረስ ተራ ቃል ነው፡፡
ያልታወቀ ደራሲ
አንዱ ጉንጭ ይሰጣል፤ ሌላው ይስማል፡፡ አንዱ ገንዘብ ይሰጣል፤ ሌላው ያጠፋል፡፡
ጆርጅ በርናርድ ሾው
ጋብቻ ግራ የሚያጋባ ነው፡፡ ባለቤታቸውን (ግማሽ ጐናቸውን) እንዲቆጣጠሩ ህጋዊ መብት ለግለሰቦች የሚሰጥ ዓይነት ፈቃድ ነው፡፡
ጄስ ሲ ስኮት
ሁሉም ጋብቻዎች ትዳሮች መንግስተ ሰማያት ነው ይላሉ፡፡ ግን እኮ ነጐድጓድና መብረቅም የሚፈጠሩት እዚያው ነው፡፡
ክሊንት ኢስትውድ
ሰዎች በትዳር የሚዘልቁት ስለፈለጉ እንጂ በሮች ቁልፍ ስለሆኑባቸው አይደለም፡፡
ፖል ኒውማን
ማንም ሴት፤ እናቱን የሚጠላ ወንድ ፈጽሞ ማግባት እንደሌለባት በደንብ አውቃለሁ፡፡
ማርታ ጌልሆርን
ትዳር የተሃድሶ ትምህርት ቤት አይደለም፡፡
ኦን ላንደርስ
ደስተኛ ወንድ የወደዳትን ሴት ያገባል፡፡ የበለጠ  ደስተኛ ወንድ ደግሞ ያገባትን ሴት ይወዳል፡፡
ሱዛን ዳግላስ
የደስታን በሮች የሚከፍተው እናት ቁልፍ ፍቅር ነው፡፡
ኦሊቨር ዌንዴል ሆልሜስ
ትዳር ደስተኛ አያደርግህም፤ አንተ ነህ ትዳርህን ደስተኛ የምታደርገው፡፡
Drs. Les and Leslie Parrott 

  ለደራሲው 10ኛው መጽሐፉ ነው
   “ዴርቶጋዳ” በተሰኘው የመጀመሪያ ልብ ወለድ መፅሃፉ ከፍተኛ ተነባቢነትና ዕውቅናን የተቀዳጀው ወጣቱ ደራሲ ይስማዕከ ወርቁ፤ “ሜሎስ” የተሰኘ አዲስ ልብ ወለድ መጽሐፍ ሰሞኑን ለንባብ ያበቃ ሲሆን 10ኛ መጽሃፉ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል፡፡ በ280 ገፆች የተቀነበበውን መጽሐፍ፤የዲዛይንና ህትመት ሥራ ያከናወነው ራሱ ደራሲው ያቋቋመው ዴርቶጋዳ ማተሚያ ድርጅት ነው፡፡ “ሜሎስ” በ60 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
ይስማዕከ ከዚህ ቀደም “የወንድ ምጥ”፣ “ዴርቶጋዳ”፣ “የቀንድ አውጣ ኑሮ”፣ “ራማቶሓራ”፣ “ተልሚድ”፣ “ተከርቸም”፣ “ዣንቶዣራ”፣ “ክቡር ድንጋይ” እና “ዮራቶራድ” የተባሉ መጽሐፍትን ያሳተመ ሲሆን  አብዛኞቹም በከፍተኛ ቅጂ በመሸጥ ለአሳታሚውም ሆነ ለጸሃፊው ዳጎስ ያለ ገቢ ማስገኘታቸው ይታወቃል፡፡ በተለይ “ዴርቶጋዳ” በጠቅላላው ወደ 200ሺ የሚጠጉ ቅጂዎች በመታተም በኢትዮጵያ የሥነጽሁፍ ህትመት ታሪክ አዲስ ሪከርድ ማስመዝገቡን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ አንዳንድ የሥነጽሁፍ ባለሙያዎችና ሃያሲያን፣ ደራሲው ከመጀመሪያው ሥራው በኋላ ያወጣቸው ተከታታይ  መጻህፍት እያሽቆለቆሉ መምጣታቸውን ቢናገሩም እስካሁን በሥራዎቹ ላይ የሰላ ሂስ የሰነዘረ ወይም ሂሳዊ ጽሁፍ ያቀረበ የለም፡፡