Administrator

Administrator

የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር በአገር አቀፍ ደረጃ የንባብ ባህል እንዲዳብር “ከመንግሥት እና ከባለድርሻ አካላት ምን ይጠበቃል?” ለሚለው ጥያቄ መልስ ለመስጠት የሚያስችል አውደ ጥናት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ሥነ - ፅሁፍና ፎክሎር ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር በትላንትናው ዕለት በብሄራዊ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መፃህፍት ኤጀንሲ አዳራሽ አውደ ጥናት አካሂዷል፡፡ በአውደ ጥናቱ ላይ አቶ ደረጀ ገብሬ (ረ/ፕ) “የንባብ ባህልን ለማዳበር የባለድርሻ አካላት ሚና” በሚል ርዕስ እንዲሁም ዶ/ር ሙሉ ሰው አስራቴ፤ “የልሳነ ብዙ የቋንቋ ትምህርትና ፖሊሲ የንባብ ባህልን ለማዳበር የሚኖረው ተግዳሮት እና ዕድል” በሚል ርዕስ የውይይት መነሻ ሃሳቦችን ማቅረባቸው ታውቋል፡፡

  በአሌክስ አብርሐም በተፃፈው “ዶ/ር አሸብር” የተሰኘው የወግ ስብስቦች መፅሃፍ ላይ በነገው ዕለት ከ8 ሰዓት ጀምሮ በወ-መዘክር አዳራሽ ውይይት ይካሄዳል፡፡ ለውይይት መነሻ የሚሆን ሃሳብ የሚያቀርበው ደራሲና ጋዜጠኛ አለማየሁ ገላጋይ ነው ተብሏል፡፡
የመፅሃፍ ውይይቱ እናት ማስታወቂያ፣ የጀርመን የባህል ማዕከልና ወመዘክር በጋራ የሚያዘጋጁት እንደሆነ ታውቋል፡፡

በሰለሞን ተሾመ ባዬ የተዘጋጀው “ፎክሎር ምንነቱና የጥናቱ የትኩረት አቅጣጫ” የተሰኘ መፅሃፍ የፊታችን ሐሙስ ከቀኑ 10 ሰዓት በብሄራዊ ሙዚየም እንደሚመረቅ ተገለፀ፡፡ በምረቃ ሥነ - ሥርዓቱ ላይ የተለያዩ ምሁራን የውይይት ሃሳብ የሚያቀርቡ ሲሆን ምሁራኑ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ፣ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዘሪሁን አስፋው፣ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራና አቶ እንዳለ ጌታ ከበደ እንደሆኑ ታውቋል፡፡ የመፅሀፉ ይዘት፡- የፎክሎር ፅንሰሀሳብን በሳይንሳዊ መንገድ ማብራራት፣ በአገራችን የሚገኙ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ያላቸውን ቃላዊ፣ ቁሳዊና መንፈሳዊ ባህሎችን መሰረት ያደረገ ትንተና መስጠት እና ሌሎችን ያካትታል ተብሏል፡፡ በ335 ገፆች የተዘጋጀው መፅሀፉ፤ በ120 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

ነፃነት ኪዳነማርያም የተፃፈው “የአሥመራው ታዳኝ” የተሰኘ ታሪካዊ ልብወለድ መፅሃፍ በነገው ዕለት ከጠዋቱ 3 ሰዓት ላይ መስቀል አደባባይ በሚገኘው ኢዮሐ ሲኒማ ይመረቃል፡፡ የመፅሀፉ ዋጋ 60 ብር እንደሆነ ታውቋል፡፡ ደራሲው ከዚህ ቀደም “ዋሻው” የተሰኘ ለአገሪቱ የመጀመሪያ የሆነውን የአኒሜሽን ፊቸር ፊልም ሰርቶ ለተመልካች ማቅረቡ ይታወሳል፡፡  

   በእስራኤል በዶክትሬት ዲግሪ የተመረቁ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ናቸው
    ኢትዮጵያዊው ምሁር ዶ/ር አንበሴ ተፈራ በእስራኤል የመጀመሪያው ከፍተኛ የዩኒቨርሲቲ መምህርና የፋካልቲ አባል በመሆን በቴል አቪቭ ዩኒቨርሲቲ ስራ መጀመራቸውን ጂዊሽ ኒውስ ድረገጽ ሰሞኑን ዘገበ፡፡
ዶ/ር አንበሴ በቴል አቪቭ ዩኒቨርሲቲ የእብራይስጥ ባህል ጥናት የትምህርት ክፍል የሴሜቲክ ቋንቋዎች ከፍተኛ መምህር ሆነው እያስተማሩ እንደሚገኙ የጠቆመው ዘገባው፣ ምሁሩ ከ15 አመታት በፊት የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ሲያገኙም በእስራኤል የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ እንደነበሩ አስታውሷል፡፡
በ1962 የተወለዱት ዶ/ር አንበሴ፤ የመጀመሪያና የሁለተኛ ዲግሪያቸውን በሊንጉስቲክስ በተቀበሉበት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለአምስት አመታት ያህል በመምህርነት ማገልገላቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ እየሩሳሌም ውስጥ ከሚገኘው ሂብሩ ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን መቀበላቸውንና በዩኒቨርሲቲው አማርኛ ቋንቋን ሲያስተምሩ እንደቆዩም አክሎ ገልጿል፡፡  
ዶ/ር አንበሴ፤ ሶስት መጽሃፍትንና ከ20 በላይ ጥናታዊ ጽሁፎችን ለህትመት ያበቁ ሲሆን፣ ከማስተማርና ከጥናትና ምርምር በተጨማሪም ለ13 አመታት ያህል ለእስራኤላውያን የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች አማርኛ ቋንቋን በማስተማርና በትምህርት ሚኒስቴር የአማርኛ ጥናቶች ብሄራዊ ሱፐርቫይዘር ሆነው በማገልገል እንደሚታወቁ ዘገባው ጠቁሟል፡፡

Saturday, 01 August 2015 14:06

በሚቀጥለው ቅዳሜ …

ወደ ኢትዮጵያ ጠቅልዬ ልመለስ ነው ስል በአሜሪካ ያሉ ሚዲያዎች መጥተው ነበር ቺካጐ ትሪቡን “አዲስ አበባ ዎን፤ ቺካጐ ሎስት” ብሎ ፅፏል በኢትዮጵያ በደቡብ በሸዋ፣ በጐንደር ገጠሮች 30 ት/ቤቶች አሠርቷል
በአያት አካባቢ ሪል ኢስቴት እየሠራ ነው “አይዞን” የተባለ 12 ዘፈን የያዘ አዲስ አልበሙን በቅርቡ ያወጣል
ጋንግስተሮች በ30 ሞተርሳይክሎች እያባረሩ ሊገሉት ሲሉ አምልጧልከአርቲስት ዘለቀ ገሠሠ ጋር ያደረግነውን ግሩም ቃለ ምልልስ በሚቀጥለው ሳምንት ያንብቡት  

 ምርጫው አገሪቱ በዴሞክራሲ መራመዷን ያሳያል ብለዋል
               - የዋነኛው ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ሌላ ምርጫ እንዲካሄድ ጠይቀዋል
   አወዛጋቢውና ደም አፋሳሹ የብሩንዲ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ባለፈው ማክሰኞ የተካሄደ ሲሆን ለመምረጥ ከተመዘገቡት 3.8 ሚሊዮን የአገሪቱ ዜጎች መካከል 74 በመቶው ድምጻቸውን እንደሰጡ የብሩንዲ የምርጫ ኮሚሽን ፕሬዚደንት ፔሪ ካልቬር ዳይካሬ ባለፈው ረቡዕ መናገራቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
ህገ መንግስቱ ከሚፈቅድላቸው ውጪ ለሶስተኛ ዙር የስልጣን ዘመን በምርጫ ለመወዳደር መወሰናቸው ከፍተኛ ተቃውሞ ያስነሳባቸው የብሩንዲው ፕሬዚዳንት ፔሪ ንኩሩንዚዛ፣ ሃሳባቸውን እንዲቀይሩ ጫና ቢደረግባቸውም በእምቢተኝነት በተወዳደሩበት ምርጫ ድምጽ የሰጡ ሲሆን ምርጫው ብሩንዲ በዲሞክራሲ አንድ እርምጃ ወደፊት መራመዷን የሚያሳይ ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡
የአገሪቱ ቀንደኛ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ የሆኑት አጋቶን ርዋሳ በበኩላቸው፣ አገሪቱ እንደ አገር እንድትቀጥልና የከፋ ደም መፋሰስ እንዳይከሰት ከተፈለገ፣ የምርጫው ውጤት ይፋ በተደረገ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ብሄራዊ የአንድነት መንግስት ሊያቋቁሙ ይገባል ሲሉ ለፕሬዚዳንት ንኩሩንዚዛ ጥሪያቸውን እንዳቀረቡ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
ምርጫው የአገሪቱ ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ራሳቸውን ባገለሉበት ሁኔታ የተከናወነ በመሆኑ አሳታፊ አይደለም ያሉት ርዋሳ፣ የሚቋቋመው ጊዜያዊ የብሄራዊ አንድነት መንግስት በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ሌላ ምርጫ እንዲያካሂድም ጠይቀዋል፡፡
አሜሪካ የመንግስት ሃይሎች ተቃዋሚዎችንና የሲቪክ ማህበራትን በሚያዋክቡበት፣ መገናኛ ብዙኃን በተዘጉበትና መራጮች በሚገደዱበት ሁኔታ የተደረገው የብሩንዲ ምርጫ ተዓማኒነት የለውም ማለቷን የዘገበው አሶሼትድ ፕሬስ፣ ካለፈው ሚያዝያ ወር ጀምሮ ምርጫው ባስነሳው ብጥብጥ ከ100 በላይ ዜጎች መሞታቸውንና ከ170 ሺህ በላይ የሚሆኑትም አገር ጥለው እንደተሰደዱ አስታውቋል፡፡
የተመድ ዋና ጸሃፊ ባንኪ ሙን በበኩላቸው፤የብሩንዲ የፖለቲካ ሃይሎች አገሪቱንና ህዝቧን ወደ ከፋ ጥፋት የሚያስገቡና በአካባቢው አለመረጋጋትን የሚያስከትሉ ተግባራትን ከመፈጸም እንዲታቀቡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በመዲናዋ ቡጁምቡራና በሌሎች የአገሪቱ አካባቢዎች በተቃዋሚዎችና በመንግስት ወታደሮች መካከል ግጭት በቀጠለበት ሁኔታ ማክሰኞ ዕለት የተከናወነው ምርጫ የድምጽ ቆጠራ ረቡዕ መጠናቀቁን የዘገበው አልጀዚራ፣ ፕሬዚዳንት ፔሪ ንኩሩንዚዛ በሰፊ ልዩነት ያሸንፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክቷል፡፡

  እ.ኤ.አ በ2050 ሮቦቶችንና ሰዎችን ኳስ ለማጋጠም ታቅዷል
    በቻይና በተከናወነውና 40 የአለማችን አገራት ቡድኖች በተካፈሉበት የዘንድሮው የአለም ሮቦቶች የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር ጃፓን ማሸነፏን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
በጃፓኑ ቺባ ኢንስቲቲዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ የተሰሩ ሮቦቶችን የያዘው ዘ ብሬንስ ኪድስ የተባለው የጃፓን የሮቦቶች ቡድን፣ የቻይናውን ዚጁዳንሰር አቻውን አንድ ለባዶ በማሸነፍ ነው ዋንጫውን ለመሳም የበቃው፡፡
የአለማችን ሮቦቶች የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር እ.ኤ.አ ከ1997 ጀምሮ በየአመቱ ሲከናወን እንደቆየ ያስታወሰው ዘገባው፣ በውድድሩ የሚሳተፉ አገራት ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱንም ጠቁሟል፡፡
የአለማችን ሮቦቶች የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር በሮቦቲክስ ዘርፍ የተሻለ ፈጠራን የማበረታታትና የማስፋፋት አላማ እንዳለው የጠቀሰው ዘገባው፣ እ.ኤ.አ በ2050 በሮቦቶችና በሰዎች መካከል የእግር ኳስ ውድድር የማካሄድ  እቅድ መያዙንም አክሎ ገልጧል፡፡

 የአንበሳ ጀግንነት ከአዳኝ ቀስት አያድነውም።
የአፍሪካውያን አባባል
ደስተኛ ህዝብ ታሪክ የለውም፡፡
የቤልጂየሞች አባባል
ጦርነት ላልቀመሱት ጣፋጭ ነው፡፡
የላቲኖች አባባል
ሽንፈት የሚመረው ስትውጠው ብቻ ነው፡፡
የቻይናውያን አባባል
እውነት የያዘን ሆድ በበላ እንኳን አይበሱትም፡፡
የሃውሳ አባባል
እሳት ያቃጠለው ሰው ሁልጊዜ አመድ ያስፈራዋል፡፡
የሶማሌያውያን አባባል
መጥበሻው ካልጋለ ማሽላው አይፈነዳም፡፡
የዮሩባ አባባል
ዝሆን ላይ የሚጮህ ሞኝ ውሻ ብቻ ነው፡፡
የአንጎላውያን አባባል
በግድ ድስት ውስጥ የገባ አጥንት ድስቱን መስመሩ አይቀርም፡፡
የቼዋ አባባል
አይጥ የገደለ ዝሆን ጀግና አይባልም፡፡
የካሜሩያውያን አባባል
ትዕግስት የገነት ቁልፍ ነው፡፡
የአልባንያውያን አባባል
ቤትህን ከመምረጥህ በፊት ጎረቤትህን ምረጥ፡፡
የሶሪያውያን አባባል
ፈረሱ ከሚጠፋ ኮርቻው ይጥፋ፡፡
የጣልያኖች አባባል
ምንም ዓይነት ምስጢርህን ከራስህ አትደብቅ፡፡
የግሪካውያን አባባል
የሥራ ፈት ምላስ ፈፅሞ ሥራ አይፈታም፡፡
የአፍሪካውያን አባባል

 መስራቹ ዙክበርግ የዓለማችን 9ኛው ባለጸጋ ሆኗል
    ታዋቂው የማህበራዊ ድረገጽ ፌስቡክ በአለማቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ትርፍ እያገኙ ካሉ 10 የዓለማችን እጅግ ትርፋማ ኩባንያዎች አንዱ መሆኑንና የኩባንያው መስራች ማርክ ዙክበርግም ከዓለማችን ቀዳሚ ቢሊየነሮች 9ኛውን ደረጃ መያዙን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘገበ፡፡
ኤስ ኤንድ ፒ በተባለው የአክሲዮን ገበያን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ 274 ነጥብ 95 ቢሊዮን ዶላር ሃብት ያካበተው ፌስቡክ፣ ከሰሞኑ የአክሲዮን ገበያ ትርፋማነቱ መጨመሩን ተከትሎ፣ ከአለማችን 10 እጅግ ትርፋማ ኩባንያዎች የስምንተኛ ደረጃን ይዟል፡
የኩባንያው ትርፋማነት መጨመሩን ተከትሎ፣ የኩባንያው መስራች የማርክ ዙክበርግ አጠቃላይ ሃብትም 42 ነጥብ 9 ቢሊዮን መድረሱን ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡
ከሳምንታት በፊት ይፋ የተደረገው የብሉምበርግ የአለማችን ቀዳሚ ባለጸጎች ዝርዝር ማርክ ዙክበርግን የዓለማችን 11ኛው ባለጸጋ ብሎት እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣አራት ቢሊየነሮችን ቀድሞ በ9ኛነት ደረጃ ላይ መቀመጡን ገልጧል፡፡