Administrator

Administrator

 ሌላ የልጅ ልጃቸውም በድብደባ ወንጀል ተከስሶ ነበር
   የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንትና የጸረ አፓርታይድ ታጋይ የኔልሰን ማንዴላ የልጅ ልጅ የሆነው ማንዴላ፣ አንዲትን ደቡብ አፍሪካዊት የ15 አመት ልጃገረድ አስገድዶ በመድፈር ወንጀል ተከስሶ ባለፈው ሰኞ ፍርድ ቤት መቅረቡን ዘ ጋርዲያን ዘገበ።
ልጃገረዷን ጆሃንስበርግ ውስጥ በሚገኝ አንድ መጠጥ ቤት ውስጥ አስገድዶ ደፍሯል በሚል በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለው የ24 አመቱ ቡሶ ማንዴላ፤ ባለፈው ሰኞ  ለመጀመሪያ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን በሳምንቱ መጨረሻ በጆሃንስበርግ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርቦ ጉዳዩ እንደሚታይ ይጠበቃል፡፡
ቡሶ ማንዴላ ከሁለት ሳምንታት በፊት ልጃገረዷ በመጠጥ ቤቱ መጸዳጃ ቤት ውስጥ ሳለች ተከታትሏት ሄዶ አስገድዶ ደፍሯታል መባሉን የጠቆመው ዘገባው፣ ጥቃቱ የደረሰባት ልጃገረድ ክስ መመስረቷን ተከትሎ ባለፈው ሳምንት በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉንም አስታውሷል፡፡
ተጠርጣሪው የማንዴላ የልጅ ልጅ ስለሆነ ብቻ ከሌሎች ወንጀለኞች ተለይቶ የሚታይበት ምክንያት የለም ያለው የጆሃንስበርግ ፖሊስ፤ እንደማንኛውም ተጠርጣሪ እንደሚያዝና ጉዳዩ በፍርድ ቤት ተጣርቶ የአገሪቱ ህግ ባስቀመጠው መሰረት ተገቢው ውሳኔ እንደሚሰጠው አስታውቋል፡፡
ተከሳሹ ማንዴላ ከሶስቱ ሚስቶቻቸው የመጀመሪያዋ ከሆነችው ኤቭሊን ማሴ ከወለዷቸው ልጆች ከአንዷ እንደተወለደና አያቱ ማንዴላ በህይወት ሳሉ በተናዘዙለት መሰረት 300 ሺህ ዶላር እንደወረሰ ያስታወሰው ዘገባው፤ ማንድላ ማንዴላ የተባለው ሌላ የኔልሰን ማንዴላ የልጅ ልጅም ከወራት በፊት አንድን የ40 አመት ደቡብ አፍሪካዊ ደብድቧል በሚል ተከሶ ፍርድ ቤት ቀርቦ እንደነበርም አክሎ ገልጿል፡፡

  ባለፈው ሳምንት ለገበያ የቀረበው ሌላው መፅሐፍ በደራሲ ተስፋዬ ገብረሥላሴ የተደረሰው “ጣፊናስ” የተሰኘ ልብወለድ ነው፡፡ አሁን በህይወት የሌለው ደራሲና ሃያሲ መስፍን ኃብተማርያም በመጽሐፉ የጀርባ ሽፋን ላይ በሰጠው አስተያየት፤ “…በታሪኩ ሂደት ለጥቅም የቆሙና ከአገርና ከህዝብ እንቅደም ያሉ ኢትዮጵያውያን የመኖራቸውን ያህል ለአገራቸው የሚሟገቱና መስዋዕትነት ለመክፈል የቆረጡ ውድ የኢትዮጵያ ልጆችም ስሜትን ወጥረው ይይዛሉ…” ብሏል፡፡ የቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ ያሳተመው “ጣፊናስ”፤ 308 ገፆች ያሉት ሲሆን ዋጋው 68 ብር ነው፡፡

የጥበብ መጀመሪያ ነገሮችን በትክክለኛ ስማቸው መጥራት ነው፡፡
የቻይናውያን አባባል
ሃቀኛ ዜጋ በራሱአገር ስደተኛ ነው፡፡
የአሜሪካውያን አባባል
ላንተ ሲል የዋሸ፣ ባንተ ላይም መዋሸቱ አይቀርም፡፡
የቦስንያ አባባል
ተረት ወደ እውነታ የሚያሻግር ድልድይ ነው።
የአረቦች አባባል
የእውነት ባሪያ የሆነ ሰው ነፃ ነው፡፡
የአረቦች አባባል
ሁልጊዜ እውነትን በቀልድ መልክ ተናገር፡፡
የአርመናውያን አባባል
ከሚያቆስል እውነት የሚፈውስ ውሸት ይሻላል፡፡
የቼኮች አባባል
እውነት ሁልጊዜ ቤት አልባ ናት፡፡
የዳኒሾች አባባል
ያለጊዜው የሚነገር እውነት አደገኛ ነው፡፡
የግሪካውያን አባባል
እውነትን አለመግለፅ ወርቅን መደበቅ ነው።
የግሪካውያን አባባል
እውነትን በራሷ ድምፅ ታውቃታለህ፡፡
የይሁዳውያን አባባል
ከዋሾ ጓደኛ ሃቀኛ ጠላት ይሻላል፡፡
የጀርመናውያን አባባል
የጎረቤትህን ሃቀኝነት በራስህ አትለካ፡፡
የአሜሪካውያን አባባል
እግዚአብሔር በሃቀኛ ልብ ውስጥ ይኖራል።
የጃፓናውያን አባባል

[የመጽሐፍ ቅኝት በአብነት ስሜ ]

    መቅድም
ወሪሳ በሚል ርእስ በሐምሌ ወር መጨረሻ ላይ 240 ገጾች ያሉት የአማርኛ ልቦለድ ታትሟል። የልቦለዱ ደራሲ ዓለማየሁ ገላጋይ ይባላል። ይህ ብእሮግ የዚህ መጽሐፍ ቅኝት ነው። ቅኝቱን የማደርገው ልቦለድን-እንደ-ህልም-መፍታት በሚል ጽንሰ-ሐሳባዊ ማእቀፍ ውስጥ ነው። አንድ ደራሲ ከግለሰብ፣ ከቤተሰብና ከማህበረሰብ አልፎ የኅብረተሰብንም ህልም የሚያልምበት ጊዜ አለ። ይህ ሲሆን ደግሞ ደራሲ እንደ ህልም ዓላሚ፣ ድርሰት እንደ ህልም፣ ኀያሲ ደግሞ እንደ ህልም ፈች ይታያል።
ህልም እና ልቦለድ
የሰው ልጅ ሆኖ ህልም የማያልም የለም ይባላል። ችግሩ ምን ያህሉን ያስታውሰዋል ነው እንጂ ሁሉም ሰው ያልማል። ህልም ለጤናችንም ወሳኝ ነው ይባላል። የበቂ እንቅልፍ እጦት ጤናን እንደሚያቃውስ ይታወቃል። የዚህ ችግር ሁነኛው መንስዔ የእንቅልፍ ጊዜ ማጣቱ ሳይሆን እንዲያውም የህልም ጊዜ ማጣቱ እንደሆነ ከቅርብ ጊዜ ጥናትና ምርምሮች መረዳት ይቻላል። የህልም አስፈላጊነት እስከዚህም ይደርሳል።
በመስኩ ያሉ ባለሙያዎች ህልምን በየጊዜው መመዝገብ መቻል ጠቀሜታው የትየለሌ ነው ይላሉ። ከህልም ጥቅሞች ውስጥ አንዱ ላይ ብቻ እናትኩር። የሰው ልጅ በዕለት ተዕለት ህይወቱ በውጣ ውረዶች ውስጥ ያልፋል፤ ከአስጨናቂ ጉዳዮችና ጣጣዎች ጋር ይጋፈጣል። ታድያ አንዳንዴም ቢሆን ችግሩንና ህመሙን በግላጭ አፍርጦ ለማየት ጊዜ ያጣል። ያንን ስውሩ አእምሮ የሚባለው መዝግቦ ይይዝለታል።  ከጊዜ ማጣት ሌላ ድፍረትም የሚጠፋበት ጊዜ አለ።  የሰው ልጅ ጭንቁን፣ ጣሩንና  ሰቆቃውን ሆን ብሎ ለመርሳትና ከህይወቱ መዝገብ ውስጥ ለመሰረዝና ላለማስታወስ የሚጥርበትም ጊዜ አለ። ንቁው የአእምሮ ክፍል የሸሸውንና ያሸሸውን ስውሩ አእምሮ ደብቆ ይይዘዋል። ስለዚህ ችግሩ ይሸሸጋል እንጂ ጠፍቶ አይጠፋም፤የተረሳ ይመስላል እንጂ ተረስቶ አይረሳም።
ቀላሉንም ሆነ ከባዱን (አንዳንዴ ሰቅጣጩንም) ችግር ማታ አረፍ ባልን ጊዜ እየተግተለተለ ከፊታችን ይደቀናል። በዚህ ወቅት ሐሳብን እናመነዥካለን። የቻልነውን እንቆቅልሽ እንፈታለን፤ያልቻልነውን ለጊዜውም ቢሆን እናልፈዋለን። የፈራነውን ደግሞ እንሸሽገዋለን፤እንርቀዋለን።
በእውን ያልፈታነውን የህይወትና የኑሮ እንቆቅልሽ በህልም እናገኘዋለን። ለችግራችን መፍትሔ ስለምናገኝበት ነው ህልማችንን የምንመረምረው። አንዳንዱ ህልም ፊት ለፊትና ግልጽ ስለአልሆነ ህልም-ፈቺ እንፈልጋለን። የእእምሮ ጤና ችግር ያጋጠማቸውን ህሙማንም በህልማቸው ለመርዳት የሚደረግ የህክምና ሳይንስ አለ።
በህልም ውስጥ ትውስታ አለ። ትውስታው የትላንት፣ የበቀደም ብቻ ሳይሆን ያምና እና የካችአምና ሊሆን ይችላል። ከዚያም አልፎ ሀያና አርባ ዓመት ወደ ኋላ  የምንጓዝበት አጋጣሚ አለ። ይህ እንግዲህ በህይወት ዘመናችን ስለሆነው ነው። ትውስታ ከህይወት ዘመን ያለፈም እንደሚሆን በዘርፉ ጥናቶች በተደጋጋሚ ተጠቁሟል።
ይህ ምን ማለት ነው? አንድ ሰው የራሱን ብቻ ሳይሆን የአያቱን፣ የቅድመ አያቱንና  በጣም ወደ ኋላ ሔዶ የዘርማንዘሩን ወይም የነገዱን የጥንት ውሎና ክራሞት የሚያስታውስበት አጋጣሚ የትየለሌ ነው። ታዲያ ትውስታው ከሚገለጥባቸው መንገዶች ውስጥ ህልም አንዱና ዋነኛው ነው።
አሁን የህልምና የድርሰትን ቁርኝት እንይ። አንድ ደራሲ በፈጠራ ጽሑፉ ላይ በሚያተኮርበት ጊዜ ተመስጦው ህልምን ከማየት ጋር ይመሳሰላል። በዚህ አተያይ ደራሲው በድርሰቱ የሚያቀርብልን ህልሙን ነው ማለት ይሆናል። ህልሙ ደስ የሚልና ግልፅ የሚሆንበት ጊዜ አለ። በዚህ ጊዜ ፍችና ትንታኔ ውስጥ አንገባም። የአንዳንዱ ደራሲ ህልም ግን ከተራ ህልም ያለፈ ይሆናል። እንደዚህ ያለው ደራሲ የሀገሩን ህልም ነው የሚያልመው። በሌላ አነጋገር ደራሲው “ነቢይ” ነው፤ድርሰቱም “ትንቢት” ነው።
የአእምሮ ጤና ችግር ያጋጠመውን ግለሰብ ለማከም ህልሙ እየተመዘገበ ይመረመራል። የችግሩ ነቅ የት ነው? ህመሙን ያመጣው እሾህ የተተከለው ከምን ስፍራ ነው? በሌላ አነጋገር ሰንኮፉ ይፈለጋል። ሰንኮፉ ሲነቀል ብቻ ነው ቁስሉ ሙሉ በሙሉ ሊሽርና ህመሙም ሊድን የሚችለው።
የግለሰቦች ስብስብ ነችና ሀገርም እንደ ግለሰብ ትጨነቃለች፤በሰቆቃ ውስጥ ታልፋለች፤ ትቃትታለች፤ትጓጉራለች። በአንድ ቃልም ትታመማለች። ወይም ደግሞ ሁላችንም እንደ ሀገር እንደ ኅብረተሰብ እንታመማለን። ሁሉም ሰው ግን ሊታመም አይችልም። የሀገርን ህመም የሚታመም ደራሲ አለ። እንዲህ ዓይነቱ ደራሲ ህመማችንን ይታመማል፤ ህመማችንን ያልማል። ህልሙ ውስጥ ህመሙ አለ። ድርሰቱ ውስጥ ደግሞ ህልሙ አለ። ድርሰቱ የሀገር ህልም ነው። የሀገርን ችግርና ህመም ደግሞ በድርሰቱ ህልም ውስጥ መመርመር አለብን። የድርሰቱን ፍችና አንድምታ ትርጓሜ መውጣት ማለት ህመማችንን መመርመር ማለት ነው፤ መድኃኒትም ከዚያ ይገኛል። እኛ አልታመም ያልነውን ህመም ደራሲው ይታመማል። እኛ አላልም ያልነውን ህልም ደራሲው ያልማል። ህልሙን መስማትና መፍታት የኛ ፈንታ ነው። መፍታቱ ቢቸግረን እንኳ መስማቱን ግን መስማት አለብን። መፍታቱ ባስቸገረ ጊዜ ኀያሲ የዚህን ሥራ መስራት አለበት። ይህ የሒስ አንዱ ፈርጅ ነው።
በሀገራችን ተንሰራፍቶ ያለው የልቦለድ ሒስ ስልት በአብዛኛው መዋቅራዊ ነው። የትልም፣ የግጭት፣ የገፀባህርያት አሳሳል፣ የቋንቋ አጠቃቀምና የትረካ ቴክኒክ በመሳሰሉት ላይ ያተኩራል። ከዚህ የሚያፈነግጠው አልፎ፣ አልፎ ነው።
በቀደሙት ዘመናት በነበሩ አንዳንድ የአማርኛ ልቦለዶች ውስጥ ማኅበራዊ ሕፀፆች በተምሳሌታዊ አካሔድ ተገልጠዋል። በቅድመ-ሳንሱርና በድኅረ-ሳንሱር (አንዳንዱ የብዙኃኑ ሳንሱርና ትርጓሜ ነው) ይኼ ንጉሡን ለመንካት ነው፤ይኼ ፕሬዚደንቱን ለማሽሟጠጥ ነው እየተባለ ተነግሯል። የልቦለዱ ደራሲ ከዋናው ገፀባህሪ ጋርም እየተነፃፀረ ሲታይ ቆይቷል። በበዓሉ ግርማ ኦሮማይ ውስጥ ያሉ ገፀባህርያትም በወቅቱ ከነበሩ ባለሥልጣናት ጋር ያላቸው ተመሳስሎ በየደረጃው ተተንትኗል። ሒስ ግን ከዚህም በላይ መሄድ አለበት። ለምሳሌ በዳኛቸው ወርቁ አደፍርስ ውስጥ በመጨረሻ ወደ ገዳም የምታመራው ፂወኔ፤በሀገር ደረጃ ደራሲው እንደ ኢትዮጵያ ሳያያት አልቀረም ተብሎ እንደተገመተው ዓይነትና ከዚያም ያለፈ የአንድምታ ትርጓሜ ያስፈልገናል።
የዓለማየሁ ገላጋይ ወሪሳ
ወሪሳ በአንደኛ መደብ የተተረከ ልቦለድ ነው። ተራኪው የአማርኛ አስተማሪ ነኝ ይላል፤ ሊቅነቱ ግን ተረት ላይ ነው። በታሪኩ ውስጥ በቅርቡ ከክፍለሀገር ወደ አዲስ አበባ የተቀየረ አስተማሪ ነው። የተራኪው የአክስት ልጅ እስር ቤት ገብቷል። አክስት ስትሞት፣“ልጇ ከከርቸሌ እስኪወጣ ቤቱን እንድጠብቅላት ተናዘዘችብኝ” ይላል ተራኪው። ተራኪው በዚህ አኳኋን ነው ወሪሳ የሚባል ሰፈር የገባው። ወሪሳ ከእሪ በከንቱ የሚጎራበት የ“ወሮበሎች” ሰፈር ነው። እንዲህ የሚባል ሰፈር አዲሳባ ውስጥ ይኑር-አይኑር አላቅም። ከሌለ  የደራሲው ምናባዊ ፈጠራ ነው። የሰፈሩ የአስፈሪነት ገለፃ በመጽሐፉ የመጀመሪያ ዓረፍተ ነገር ይጀምራል። ተራኪው ገና ሲጀምር፣ “እኔ እንደ ኢየሱስ በወንበዴዎች መካከል ተቸንክሬአለሁ”ይለናል። ሰፈሩ ባጭር ቃል ሲዖል ነው፤ያስፈራል፤በጣም ያስፈራል። ተስፋ ያስቆርጣል።
ወሪሳ ተከታታይነትና ተለጣጣቂነት ያላቸው አስፈሪ ህልሞች የታጨቁበት ማህደር ነው። ህልሞቹ የተዘፈቅንበት ማኅበራዊ ውጥንቅጥ ነፀብራቅ ናቸው። ምን ያህል ወርደናል! ምን ያህል ተዋርደናል! ምን ያህል በክተናል! ያስብላሉ። የወሪሳ ህልሞች “እገሌ የጎዳና ተዳዳሪውን፣እገሌ የተማረውን፣ እገሌ ካድሬውን፣ እገሌ ተቃዋሚውን፣ እገሌ ገዥውን ፓርቲ፣ እገሌ ቤተክህነቱን ይወክላል” በሚል ብዙም ረብ በሌለው ፈሊጥ መፈታት ያለባቸው አይደሉም።
ህልሞቹ በትእምርታዊነት (ሲምቦሊዝም) የተሞሉ ናቸው። ተራ ቅዥት አይደሉም። በቅጡ ሊተነተኑ ይገባል። በትንተናው ደግሞ ደራሲው እንዲህ ሊል ፈልጎ ነው የሚለውንም አካሄድ ለጊዜውም ቢሆን ወደ ጎን ገፋ ማድረግ አለብን። እኔ እንደሚመስለኝ ደራሲው ምንም ሊል አልፈለገም። ህልሙን ነው የጻፈው። ህልሙ ደግሞ የሀገርና የኅብረተሰብ ህልም ነው። እኛ ማድረግ የሚገባን ህልሙን ማንበብና  መፍታት፣አንድም እንዲህ ማለት ነው እያልን ከሦስትና ከአራት የዘለሉ ትርጓሜዎች ማውጣት። ህልሙ ውስጥ ያገር ህመም አለ። ያን ያገር ህመም ሰንኮፍ መመርመር፣ ማመልከትና መንቀልም አለብን። ሌላው አማራጭ ሸፋፍኖ መተው ነው። ወይም ደግሞ ህመማችንን የታመመልንን ደራሲ ማንቋሸሽና ማውገዝ። ሌላ ደራሲ እስኪታመምልን መጠበቅ።
የወሪሳ ጥቂት አንድምታዎች
በወሪሳ ታሪክ ውስጥ ተራኪውን በብዙ ሺህ ትብታቦች አስረው የቁም ስቃዩን የሚያሳዩት አንድ ገፀባህሪ አሉ። አምበርብር ይባላሉ። በአባትም ሆነ በእናት ከሰው ልጅ የተወለዱ አይመስልም። ዋናውን አስማዲዮስ ቁጭ ነው። ለነገሩ የሰው ልጅ ከዲያብሎስ ተንኮልና ክፋት በላይም እንደሄደ እናውቃለን። አምበርብር ሥጋ የለበሰውን ዲያብሎስ ያስንቃሉ። አንደበታቸው ውስጥ ሀምሳ ሺህ እባብ ያለ ይመስለኛል። እንደዚህ ዓይነቱ ሰው በምድራችን ላይ ይኖራል ወይ ብዬ ለመገመት አልቸገርም፤ሞልቷል። ሁላችንም ወደዚያው እያመራን ይመስለኛል። አንበርብር የሁላችንም ወኪል ናቸው። ለነገሩ የወሪሳ ሰፈር ሰዎች ሁሉ ከሰውነት ክብር ወርደዋል። ሁሉም ደግሞ የኅብረተሰባችን ነፀብራቅ ናቸው። ገሀዱን እውነታ ነው በወሪሳ ህልም ውስጥ የምናየው።
ተራኪው የአማርኛ አስተማሪ የገባበት ውጥንቅጥ በጣም፣ እጅግ በጣም የሚያስፈራ ብቻ አይደለም። የሚሰቀጥጥና የሚዘገንን ነው። መጽሐፉን ሳነብ ከአስፈሪ ህልም ውስጥ ለመባነን እንደሚጓጉር ሰው ሆኜ ነው። እንደዚህ ስል በዕድሜ ገፋ ያልኩ ጎልማሳ እንደሆንኩ ልብ በሉ። ተራኪው ታምሟል፤ ይጓጉራል፤ ዛር እንደሰፈረበት ሰው መውጫ ቀዳዳ አጥቷል። ህመሙ የሁላችንም ህመም ነው። ተራኪው የታመመውን ህመም ሁላችንም ታምመናል። አምበርብር ተራኪውን እንደ ክፉ ዛር ተቆራኝተውታል። ተራኪው የገባበት ጣጣ በክፉ ዛር ተይዞ ባርያና አገልጋይ ከሆነ ሰው ጋር ይመሳሰልብኛል። የተራኪው ታላቅ ተስፋ የሚያንሰራራው አምበርብር ታመው ለሞት የተቃረቡ በመሰሉ ጊዜ ነው። ሰውዬው የበደሏቸውን ሰዎች እየጠሩ ይቅርታ ይጠይቃሉ። የይቅርታቸው መቋጫ ግን እርግማን ነው። ተበዳዩን መልሰው አጥፊና ተፀፃች ያደርጉታል። ይባስ ብለው ሊጠይቃቸው የተሰበሰበውን የጎረቤት ሰው ራእይ አየሁ ይሉታል። የእሪ በከንቱ ሰው አምበርብርን ታመው ባለመጠየቁ ምክንያት እግዚአብሔር እንዲህ ይላችኋል፤ “የእሪ በከንቱ ሰው ታምሜ ጠየቅኸኝ? ተርቤ አበላኸኝ? ታርዤ አለበስኸኝ? ይላል እግዚአብሔር” በዚህ ሳቢያ የሰፈሩ ሰው አምበርብርን ምግብ እየያዘ መጠየቅና መንከባከብ ይጀምራል። በሦስት ቀን ውስጥ እሰበሰባለሁ ያሉት ሰውም ዕድሜያቸው እየረዘመ ይሔዳል።
እኔ ህልም ነው ባልኩት የወሪሳ ልቦለድ ውስጥ ያሉት የአምበርብር ባህሪ በብዙ መልኩ ሊተረጎም የሚችል ነው። አምበርብር የአንድ በሽታ ትእምርት ናቸው። ይኼ በሽታ ክብራችንን የገፈፈ የትንሽነት፣ የአጭበርባሪነት፣ የተንኮል፣ የሤራ ነቀርሳ ነው። አምበርብር በሽታችን ናቸው። ጣጠኛው ተራኪ፣እንደዚሁም የወሪሳና የእሪበከንቱ ሰው አምበርብርን ሊገላገላቸው አልቻለም። ይባስ ብሎ እሳቸው ባጠፉት ጥፋተኛ፣ እሳቸው በበደሉት በደለኛ ሆነ። በኩነኔያቸውም ተኮነነ፤ ተፀፀተ። ከሞት ደጃፍ ነኝ ያሉትን ሰው (ይኸ ሌላው ተንኮላቸው ነው) እድሜ ሊቀጥልላቸው ይሮጥ ገባ።
ይኸ ቀድሞ የገባንበትና አሁን የምንዳክርበት ጣጣ ነው። ለዘመናት የነበሩንን ገዢዎች ጥፋትና ኀጢአት እኛው ተሸክመናል። ክፉ መሪ ሲነሳ አምላክ ስለ ጥፋታችን ያመጣብን ቅጣት ነው እንላለን። ስለ አረመኔ መሪዎቻችን እንማልዳለን፤ እንፀልያለን። የእግዚአብሔር ሥዩም ነኝ ካለ ለዲያቢሎስም እንሰግዳለን። መቼም ዲያብሎስማ፣ ዲያብሎስ ነኝ ብሎ አይመጣም።
ሶሻሊዝም የሚባል ሥርዓት አምጥተን መከራችንን በላን። አይ፣ ጥፋቱ የኛ ሆነ እንጂ “ሶሻሊዝም” የተባለ ሥርዓትማ እንከን አይወጣለትም ነበር ብለን ሙሾ ተቀመጥን። መንግሥቱ ኃይለማርያም “ጥሎን ጠፋ፤ ጥሎን ፈረጠጠ” ብለን እስከ አሁንም ድረስ የምናላዝን አለን። ሌሎችም፣ “ጥሏችሁ ጠፋ” እያሉ ሆድ ያስብሱናል። ኃይለሥላሴ ከሞቱ ፀሐይ ትጨልማለች፤ መንግሥቱ ሥልጣን ከለቀቀ ኢትዮጵያ ትፈርሳለች እያልን ዘምረናል። ሰው እንዴት ከበሽታው መገላገልን ይፈራል? በሽታ ተውሳክ ነው፤ ተደራቢ ነው፤ ይበላናል። ቀስ በቀስም ያጠፋናል። ከበሽታ አምጪ ተውሳኮች ውስጥ ቫይረስና ባክቴሪያ የሚባሉ አሉ ሲባል እሰማለሁ። ታዲያ በሽታ አምጪ ለሆኑ (ሰላማዊዎችም አሉ ይባላል) ባክቴሪያዎችና ቫይረሶች የምናዝን ህዝቦች አይምሮአችን ጤነኛ ነው? ለሚያሳድዱኣቸው ጅቦች የሚፀልዩ አህዮች ጤነኞች ናቸው? ሙጀሌን መንግሎ ማውጣት እንጂ ማስታመም ያስፈልጋል? ለሙጀሌ ይፀለያል?
የዛሬ አስር ዓመት ገደማ የኤችአይቪ ምርመራ አድርገው ነፃ የተባሉ ሴት “ባይልልኝ ነው” ብለው እንዳዘኑ በቀልድ መልክ የተነገረ እውነተኛ ታሪክ ሰምቻለሁ። ይኸ ነገር የብዙዎቻችን አባዜ እንደሆነ እገምታለሁ። ለሌላው ከማዘን ተቸግረን እንዲታዘንልን የምንፈልግ ብዙ አለን። በዘመኑ ቋንቋ የተረጂነት መንፈስ የሚሉት ይኸ ሳይሆን አይቀርም። በእዚሁ በእኛ አገር ባህታዊያንና መናኞች ዓለምን የናቁ ናቸው። ገላቸውንና ልብሳቸውን አያጥቡም፤ ቅማልም አይገድሉም። ዓለምን ያልናቅን ደግሞ ሌሎች የቅማል ዓይነቶችን ነው ይዘን የምንዞር።ይኸ ነገር በሁሉም የሰው ልጅ ውስጥ ያለ የባህሪ እንከን ነው። ፈረንጅና ሀበሻ አይልም። በሥነልቦና ትንተና ውስጥ የስኬታማነት ፍርሀት የሚባል ነገር አለ። ስኬታማ መሆንን፣ ማሸነፍን፣ መበልፀግን የሚፈሩ ሰዎች አሉ። ፍርሀታቸው ከነሱ በላይ ያሉ ሰዎች እንዳይጠሏቸው ነው። እነዚህ ስኬታማ ከሆኑ የሌላ ባርያ መሆናቸው ያቆማል። የባርያ አሳዳሪዎችም ይታመማሉ። ነገሩ፣“ሞኝን ማን ይጠላዋል” ዓይነት ነው።
አንድ የዛሬ ሀያ አምስት ዓመት ገደማ ያነበብኩት መጽሐፍ አለ። “Flowers for Algernon” ይባላል። የሳይንስ ልቦለድ ነው። ዋናው ገፀባህሪ የአእምሮ ዕድገት ዝግመት አለበት። ተራኪው እሱ ራሱ ነው።  በአንድ ዳቦ ቤት ተላላኪ ሆኖ ይሠራ ነበር።  የሰውን ልጅ የአእምሮ ችሎታ በህክምና ከፍ ማድረግ ይቻላል ብለው የተነሱ ሳይንቲስቶች፣በተራኪው አእምሮ ላይ የቀዶ ጥገና ያደርጋሉ። የልጁ የአእምሮ ችሎታ ሰማይ ጥግ ይደርሳል። በዚያው ልክ ደግሞ ቁጡ ይሆናል። ብቸኛ ይሆናል። ልቦለዱ የዚህ ሰው የዕለት ማስታወሻዎቹ ስብስብ ነው። ታዲያ በአንደኛው የዕለት ማስታወሻው ላይ ከዚህ ቀጥሎ ያለውን የሚመስል ሐሳብ ይጽፋል፤ “ድሮ “ሞሮን” እያለሁ ሰዎች ይወዱኝ ነበር። ዙሪያዬን ከበው ይስቃሉ። እኔም ደስተኛ ነበርኩ። አሁን ግን ብቻዬን ነኝ። ይከፋኛል። ሰው እንደ ድሮው አይወደኝም፤ አይጠጋኝም።”
እንግዲህ መወደድ የፈለገ ሰው ከሰውነት ተራ ይወጣል። ዝቅ ይላል። ትንሽ ይሆናል። ፍቅርና ሀዘኔታ አይጠገብም። ሱስ ይሆናል። ትንሽ ያደርጋል። ሁሌም ህፃን ሆኖ የመቅረትን አደጋ ይጋርጥብናል። ስንኩል ያደርገናል። ለማኝ እንሆናለን።
ኢትዮጵያ ክፋትና ክፉ ሰው አሸንፎ የሚኖርባት አገር ነች። ጀግና ነን እንላለን እንጂ እንደኛ ያለ ፈሪ ህዝብ የለም። ትንሽ ክፋትና ትንሽ ድፍረት ያለው ሁሉ ነው እያርበደበደ ሲገዛን የኖረው። ጀግና ብንሆንማ ሁላችንም እንነግሥ ነበር፤ ሁሉም ወንድ ንጉሥ፣ ሁሏም ሴት ደግሞ ንግሥት ትሆን ነበር። ጀግና ብንሆንማ መሪነት የሥራ ድርሻ ብቻ ይሆን ነበር። ጀግና ብንሆንማ መሪያችን ደመወዝ የምንከፍለው አገልጋይ ብቻ ይሆን ነበር። ጀግና ጠቢብም ነው፤እኛ ጥበብ የሚባል ነገርም አልነበረን። ክርስትናን ከማንም ቀድመን ተቀበልን እንላለን። ሁለት ሺህ ዓመት ግን ሰይጣን ነው በእግዚአብሔር ስም ሲገዛን የኖረው። ይህ ጥበብ ቢኖረን ኖሮ እንዲያ አይሆንም ነበር። አሜሪካ ጀግና ናችሁ ብትል ጠላትዋን እንድንወጋላት ነው። አምበርብርም መጣባቸው የተባለውን ባላንጣቸውን እንዲገድልላቸው ሲሉ ተራኪውን ያልሆነውን ጀግንነት ያላብሱታል። ፈረንጆች ጥበበኞች ናችሁ ቢሉን ሸቀጣቸውን ለመሸጥ ነው። ከተራበ ልጁ አፍ ቀምቶ ወተት የሚሸጥና መጫወቻ ቆርቆሮ የሚገዛ ህዝብ ሞኝና ተላላ እንጂ ጥበበኛና ጀግና አይደለም። ከባድ የሆነውን የምድር ወገብ የፀሐይ ግለት እንዲከላከልበት ተፈጥሮ የቸረችውን አፍሪካዊ ጥቁርነትና ከርዳዳ ፀጉሩን፣ የምድር ዋልታ ሰዎች የብርድ መከላከያ ወደሆነው ፈረንጃዊ ነጭና ለስላሳ ፀጉር የሚቀይርለት ቀለምና ቅባት ለመግዢያ ሲል መሬቱን፣ ክብሩንና ነፍሱን የሚሸጥ ህዝብ፤ጥበበኛና ጀግና አይደለም። እርስ በራሱ እየተፈጃጀ የፈረንጅ ታንክና ጠመንጃ የሚያሻሽጥና የሚሸምት፣በርሱም የሚፎክር ህዝብ ጥበበኛና ጀግና አይደለም። ነብር ሲያይ ፍየል፣ ጅብ ሲያይ አህያ፣ ፍየል ሲያይ ቅጠል፣ ድመት ሲያይ አይጥ፣ ተኩላ ሲያይ በግ፣ እሳት ሲያይ ገለባ የሚሆን ህዝብ ጥበበኛና ጀግና አይደለም። ዲሞክራሲን፣ ልማትንና ትምህርትን በልመና አገኛለሁ የሚል ህዝብ ጥበበኛና ጀግና አይደለም።
ይኸ ሸፍነንና ደብቀን የምናባብለው ቁስላችን ነው።  ይኸ ቁስል መገለጥ አለበት። መታጠብ አለበት። መታከም አለበት። መሻር አለበት። ቁስላችን በተነካ ቁጥር የምንጮህ ከሆነ ግን ምን ግዜም አንድንም። ምናልባት አንዱ ጀግንነታችን ቁስላችንን በነካውና በገለጠው ላይ ይመስለኛል። ለዚያ ጊዜ እንበረታለን። ውዳሴ ከንቱ ለሚመግበን ብቻ የምናጨበጭብ ተላላዎች ነን።
(ይቀጥላል)

ሻይ አይጠጡ
ሻይ በሰውነታችን ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው አሲድ እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡ ይህ አሲድም በተመገብነው ምግብ ውስጥ ያሉ ፕሮቲኖች እንዲጠነክሩና አልፈጭ እንዲሉ ያደርጋቸዋል፡፡
አያጭሱ ምግብ ከተመገቡ በኋላ ወዲያውኑ ሲጋራ ማጨስ እጅግ አደገኛ ነው፡፡ ከምግብ በኋላ የሚያጨሱ ሰዎች በሳንባ ካንሰር የመያዝ እድላቸው ከፍተኛ ነው፡፡
ፍራፍሬ አይመገቡ
ከምግብ በኋላ ወዲያውኑ ፍራፍሬ መመገብ አንጀታችን በአየር እንዲወጠር ያደርገዋል፡፡ ፍራፍሬ መብላት ከፈለጉ፣ ምግብ ከመመገብዎ ከአንድ ሰዓት በፊት ወይንም ከተመገቡ ከአንድ ሰዓት ተኩል በኋላ ቢሆን ይመረጣል፡፡
ገላዎን አይታጠቡ
ምግብ እንደተመገቡ ወዲያውኑ ገላን መታጠብ በእግርና በእጃችን አካባቢ የደም ፍሰት (ዝውውር) መጠኑን እንዲጨምር የሚያደርግ ሲሆን ይህም በሆዳችን አካባቢ ያለውን የደም ፍሰት ይቀንሰዋል፡፡ በዚህ ምክንያትም የምግብ ስልቀጣ ስርዓቱ ይዳከማል፡፡
ቀዝቃዛ ውሃ አይጠጡ
ከምግብ በኋላ ቀዝቃዛ ውሃ መጠጣት በበላነው ምግብ ውስጥ የሚገኙትን ዘይት ነክ ነገሮች ወደ ጠጣርነት ይቀይራቸዋል፡፡ ይህ ደግሞ የምግብ መፈጨት ሂደቱን ከማጓተቱም በላይ ወደ ጠጣርነት የተቀየረው ዘይትና ቅባት ጨጓራ ውስጥ ከሚገኝ አሲድ ጋር በመገናኘት በፍጥነት ተሰባብሮ ወደ አንጀት ውስጥ እንዲገባ ያደርገዋል፡፡ ይህም ወደ ስብነት ተቀይሮ ለካንሰር መከሰት ሰበብ ሊሆን ይችላል፡፡ ስለዚህም በተቻለዎ መጠን ከምግብ በኋላ ቀዝቃዛ ውሃን ከመጠጣት ይቆጠቡ፡፡ በምትኩ ለብ ያለ ውሃ ቢጠጡ የምግብ መፈጨት ሥርዓቱ የተሳካ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡
የእግር ጉዞ አያድርጉ
ከምግብ በኋላ ወዲያውኑ የእግር ጉዞ ማድረግ የምግብ ስልቀጣ ሂደቱ በአግባቡ እንዳይከናወን ያደርገዋል፡፡
ወዲያውኑ አይተኙ
በልተን ወዲያውኑ ከተኛን የተመገብነው ምግብ በአግባቡ አይፈጭም፡፡ ይህ ደግሞ ለጨጓራ ህመምና ለአንጀት ቁስለት ይዳርገናል፡፡

በኒውዝላንድ እየተመረተ በአገራችን የሚቀነባበረውና ከ30 በላይ የንጥር ምግብ ይዘት አለው የተባለ የህፃናት የዱቄት ወተት ለገበያ ሊቀርብ ነው፡፡
በፋፋ ፋድስ እና በኒውዝላንድ ሞይሪ ከኦፕሬቲቭ ፎንቴራ የጋራ ትብብር ተመርቶ ለገበያ የሚቀርበው ይኸው የህፃናት የዱቄት ወተት የላቀ ጥራት ያላቸውና በስፈላጊ ንጥረ ምግቦች የዳበረ መሆኑንና ፕሮቲን፣ ካልሲየም ቫይታሚን ኤ እና ዲ፣ አይረንና ዚንክን ጨምሮ ከ30 በላይ የሆኑ ንጥረ ምግቦቹን የያዘ መሆኑን የኒውዝላንድ ሚልክ ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዚኮ ቃሲም ተናግረዋል፡፡
ምርቱ ከነሐሴ 16 እስከ ጳጉሜ 6/2007 ዓ.ም ድረስ በኤግዚቢሽን ማዕከል በሚካሄደው የአዲስ አመት ኤክስ9 ላይ በነፃ ለጐብኚዎች ይቀርባል፡፡

Monday, 24 August 2015 09:49

የኪነት ጥግ

(ስለ ሙዚቃ)

- ማዜም የሚሹ ሁልጊዜ ዜማ አያጡም፡፡
የስዊዲሽ አባባል
- ለማዜም ምክንያት አያስፈልግህም፡፡
ማርቲ ሩቢን
- ነፍስህ ውስጥ ሙዚቃ ሲኖር፣ ሙዚቃህ ውስጥ
ነፍስ ይኖራል፡፡
ክሪስ ጃሚ
- ሙዚቃ ለነፍስ ጥንካሬ ያጎናፅፋል፡፡
ላይላህ ጊፍቲ አኪታ
- ማዜም እየቻልክ ለምን ታስባለህ?
ማርቲ ሩቢን
- እኔ ስፅፍ ነፍሴ ያዜማል፡፡
ሜሊሳ ማርሽ
- በትምህርት ቤት ከህፃናት ጋር ማዜሜ እጅግ
አስደሳች የህይወት ተመክሮዬ ነው፡፡
ፒቲ ሲገር
- ታላቅ ወንድሜ አሁንም ድረስ ከእኔ የተሻለ
ዘፋኝ እንደሆነ ያስባል፡፡
ሮድ ስቲዋርት
- ራሴን እንደ ሃገረሰብ ዘፋኝ አስቤ አላውቅም፡፡
ቦብ ዳይላን
- ሙዚቃ ሃይማኖቴ ነው፡፡
ጂሚ ሄንድሪክስ
- የዓለም እጅግ ዝነኛና ታዋቂ ቋንቋ ሙዚቃ ነው፡

PSY
- ሁሉም ሙዚቃ ውብ ነው፡፡
ቢሊ ስትራይሆርን
- በአሁኑ ጊዜ ፀጥታን የትም አታገኙም፡፡ ይሄን
ነገር አስተውላችኋል?
ብርያን ፌሪ
- የሆነ ጊዜ ላይ ልብህ ውስጥ ዜማ አይኖርም፡፡
እንዲያም ሆኖ ግን አቀንቅን፡፡
ኢሞሪ አውስቲን
- ልብህ ውስጥ ዛፍ አኑር፤ ምናልባት ዘማሪ ወፍ
ትመጣ ይሆናል፡፡
የቻይናውያን አባባል

ባለፉት አስር አመታት የተለያዩ ራስን የማበልጸግና የአመራር ስልጠናዎችን ለመካከለኛና ከፍተኛ አመራሮች በመስጠት የሚታወቀው SAK የስልጠና ማዕከል፤በዘንድሮ ክረምት 80 ለሚሆኑ ህጻናትና ወጣቶች እራስን የማበልጸግ (Personal Development)  ሥልጠና መስጠቱን አስታወቀ፡፡  
ስልጠናው በዋናነት ህጻናትና ወጣቶች ከትምህርት እውቀታቸው በተጨማሪ በባህሪያቸው ታንጸው በራሳቸው የሚተማመኑ፣አላማ መር ህይወት የሚመሩና ሃላፊነትን የሚቀበሉ የነገ አገር ተረካቢዎች እንዲሆኑ ለማስቻል ያለመ ነው ተብሏል፡፡
በሶስት ዙር በተሰጡት ስልጠናዎች ተሳታፊ የነበሩ ተማሪዎች እንዲሁም ወላጆች እርካታቸውን የገለጹ ሲሆን ስልጠናው በ10ኛው ቀን ሲጠናቀቅ የ“አልችልም አስተሳሰብ” የቀብር ስነስርዓት (“I can not do it; funeral) ይካሄዳል፡፡ የቀብር ስነስርአቱ ከመካሄዱ በፊት የሬሳ ሳጥን ይዘጋጅና ሁሉም ተማሪዎች ወደ ኋላ የሚያስቀሯቸው አስተሳሰቦች፣ ለምሳሌ - አልችልም፣ ይሉኝታ፣ ያበሻ ቀጠሮ፣ አይመለከተኝም፣ በጎ ነገሮችን ያለማድነቅ አባዜ፣ እኔ ብቻ ልጠቀም (win-Loss) ወይም ሁለታችንም አንጠቀም (Loss-Loss) ወዘተ---ተጽፈው በሳጥኑ ውስጥ ይገቡና ይቆለፍባቸዋል፡፡ በቀብሩ ስነስርዓት ወቅትም ተማሪዎች የደስታ ቀናቸው ስለሆነ፣ ሁሉም ነጭ ልብስ ለብሰው ወደ መቃብሩ ይሄዳሉ። በጉዞውም ላይ ቻው ቻው አልችልም፣ ባይ ባይ አልችልም የሚል መዝሙር ይዘምራሉ፡፡
የቀብሩን ጉድጓድ ተማሪዎች የሚያዘጋጁ ሲሆን የቀብሩም ቦታ ላይ የአልችልም አስተሳሰብ የቀብር ሥነስርዓት በንባብ ይሰማል፡፡ ከዚያም ሳጥኑ በጉድጓድ ውስጥ ገብቶ ይቀበራል፡፡ በቀብሩ ስነስርኣት ላይም ተማሪዎች እነዚህን የቀበሯቸውን ኋላ ቀር አስተሳሰቦች በድጋሚ እንዳያስቧቸው ቃል ይገባሉ፡፡ በቀብሩ ላይ የተነበበው ንባብ፣ በሰልጣኞች መኝታ ቤት ውስጥ እንዲለጠፍና ሁልጊዜ ተማሪዎቹ እንዲያዩት ይደረጋል፡፡
ሳይረፍድ በልጆቻችን አስተሳሰብ ላይ ለውጥ በማምጣት የወደፊት የህይወት መሰረታቸውን አብረን እንጣል የሚል ጥሪ ማስተላለፉን ያስታወሰው ማዕከሉ፤ጉዞውን በዘንድሮ ክረምት በስልጠና  መጀመሩን አመልክቷል፡፡ ስልጠናው መደበኛ ትምህርት በሚጀመርበት አዲሱ አመትም የሚቀጥል ሲሆን ቅዳሜና እሁድ እንዲሁም በየቀኑ የየእለቱ ትምህርት ከተጠናቀቀ በኋላ እንደሚሰጥ ማዕከሉ ጠቁሟል፡፡
የ SAK የስልጠና ማዕከል ራስን የማበልጸግ ስልጠናው እንደ ማንኛውም ትምህርት በአገራችን የትምህርት ስርአት ውስጥ ተካቶ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ተማሪ ከልጅነት ጀምሮ እንዲሰጥ ያለመ  ሲሆን ይህም ውጤቱ በእውቀትና በባህሪ የተገነባ ትውልድ ማፍራት ነው ይላል፡፡
የአልችልም አስተሳሰብ የቀብር ሥነስርዓት
እኛ ዛሬ እዚህ የተሰበሰብነው እራስን የማበልጸግ ሥልጠና የወሰድን ተማሪዎች፣ በዋናነት አልችልም የሚለውን አስተሳሰብና ሌሎችም እራስን ወደ ኃላ የሚያስቀሩ አስተሳሰቦችን ለምሳሌ፡-
እድለኛ አይደለሁም ብሎ ማሰብን
ለይሉኝታ መገዛትን
የአበሻ ቀጠሮ የሚባለውን ሰዓት የማርፈድ አስተሳሰብ
ሌላ ሰውን ለመምሰል የመፈለግ አባዜ
አይመለከተኝም የሚለውን አስተሳሰብ
አሉታዊ ጎኞች(Negative thinking) ላይ የማተኮር አስተሳሰብ
ድርድር ላይ መሸነፍ፣ መሸነፍ (Lose - Lose) የሚለውን ወይም የዜሮ ድምር አስተሳሰብ
ዛሬ ነሐሴ ----------/2007 ዓ.ም ከቀኑ 5 ሰዓት ላይ ቀብሬያቸዋለሁና ከዚህ በኋላ አነዚህ አስተሳሰቦች ከእኔ ጋር ቦታ የላቸውም፡፡ እነዚህ አሮጌ አስተሳሰቦች የአገራችን እድገት ጠንቅ በመሆናቸው በህይወት ዘመናችን ሁሉ ታግለን ከአገራችን ልናጠፋቸው ቆርጠን ተነስተናል፡፡ ዛሬ በቀበርናቸው አሮጌ አስተሳሰቦች ፋንታ የሚከተሉትን 10 አዲስ አስተሳሰቦች ለመተግበር ወሰነናል፡፡
እራሴን በቀጣይነት በእውቀት ለማሳደግ
እራሴን ተቀብዬ በማንነቴ ለመኩራት
በራሴ ለመተማመን
እችላለሁ በማለት በህይወቴ ለስንፍና ቦታ ላለመስጠት
በጎ አመለካከትን (Positive thinking) የህይወቴ መርህ ለማድረግ
የማድነቅ ባህልን የህይወት መመርያዬ ለማድረግ
ሃላፊነት መቀበልን ከህይወቴ ጋር ለማላመድ
የጋራ ተጠቃሚነትን ሁልጊዜ በህይወቴ ለመተግበር
ጊዜዬን በአግባቡ በመጠቀም ያበሻ ቀጠሮ የሚለውን አስተሳሰብ ለመሻር
ኑሮዩን በራይና በአላማ ለመምራት
ይህንንም የአልችልም አስተሳብ የቀብር ስነስርዓት ጽሁፍ፣ በመኝታ ቤቴ ግድግዳ ላይ ለጥፌ ሁልጊዜ ለማንበብ፤
ቃል እገባለሁ!
ቃል እገባለሁ!
ቃል እገባለሁ!

Monday, 24 August 2015 09:47

የፀሐፍት ጥግ

ስለታሪክ)
- ሰው የህይወት ታሪኩን ለሌላ ሰው የተናገረ ዕለት
ነው ታሪክ የተወለደው፡፡
አልፍሬድ ዲ ቪጅኒ
- ጀግና ፈፅሞ የታሪኩ ኮከብ አይደለም፡፡
ማሪሊም ማንሶን
- ዩኒቨርስ የተሰራው ከአቶሞች ሳይሆን ከታሪኮች
ነው፡፡
ሙርየል ፋክይሰር
- ያልተነገረ ታሪክን በውስጥህ እንደመሸከም ያለ
ስቃይ የለም፡፡
ማያ አንጄሉ
- ሁሉም የየራሱ የህይወት ታሪክ ጀግና ነው፡፡
ጆን ባርዝ
- የሰው ልጅ በቆዳ የተለበጠ ታሪክ ነው፡፡
ፍሬድ አሌን
- ልብ ወለድ ፎቶግራፍ አይደለም፤ የዘይት ቅብ
ሥዕል ነው፡፡
ሮበርትሰን ዲቪስ
- ሁሉም ግሩም ታሪኮች አስር በመቶ እውነት
ናቸው፡፡
ኮሎኔል ዴኒስ ፋኒንግ
- ህብረተሰብን የሚገዙት ታሪክ ተራኪዎች
ናቸው፡፡
ፕሌቶ
- እያንዳንዱ የምፈጥረው ታሪክ እኔን ይፈጥረኛል፡፡
የምፅፈው ራሴን ለመፍጠር ነው፡፡
ኦክታቭ ያ ኢ. በትለር
- እውነቱን ለማወቅ የሁለቱንም ወገኖች ታሪክ
ማግኘት አለብህ፡፡
ዋልተር ክሮንኪት
- እያንዳንዷ ሴት የራሷ ታሪክ ባለቤት መሆን
አለባት፡፡ ያለበለዚያ ሁላችንም የዝምታው አካል
ነን፡፡
ዛይናብ ሳልቢ
- አገራትና ቦታዎች ታሪክ፣ ተረክና ባህል አላቸው።
ሞሼ ሳፍዲ
- ይሄን ታሪክ በፊት ሰምታችሁት ከሆነ
አታስቁሙኝ፡፡ ምክንያቱም ደግሜ ልሰማው
እሻለሁ፡፡
ግሮውቾ ማርክስ

የአባ ባሕርይ መዝሙር /3/ በግጥም መልክ በግዕዝ ቋንቋ የፃፉት የሚከተለው ምሣሌ ይገኝበታል፡፡ እንዳመቸ አቅርበነዋል፡፡
በአንድ ዘመን እንዲህ ሆነ፡፡ አንድ ሰው በመንገድ እየሄደ ሳለ፣ በድንገት ከየት መጣ ሳይባል አንድ አውራሪስ ከተፍ አለበት፡፡ ሰውዬው እግሬ አውጪኝ ብሎ ፈፋውን ጉድባውን እየዘለለ፣ ጫካውን እያቋረጠ መጭ አለ፡፡ ፍርሃቱ የትየለሌ ሆነ፡፡ ነብሱን ሳያውቅ ሸሸ፡፡ በመጨረሻ ገደል ገጠመውና ወደ ገደሉ ሲወድቅ አንድ የዛፍ ቅርንጫፍ ፈፋውን ታኮ ተዘርግቶ ኖሮ፤ ያን ሲያይ ሰውዬው አፈፍ አድርጐ ተንጠለጠለበት፡፡ እዚያው ተንጠልጥሎም ሳለ፤ ከጐኑ በኩል አራት እባቦች እየተሳቡ ሲመጡ አየ፡፡ ይብስ ብሎም ከበታቹ አንድ ዘንዶ አየ፡፡ ያ ዘንዶ ሰውዬውን ለመዋጥ አፉን ከፍቶ ወደ እሱ እየተንጠራራ ይጠብቀዋል፡፡
ቀን ያመጣው አይቀሬ ነውና ሁለት ጥቁርና ነጭ አይጦች ደግሞ፤ ሰውዬው የተንጠለጠለበትን የዛፍ ቅርንጫፍ ተጐምዶ እንዲወድቅ እየገዘገዙ የበኩላቸውን እኩይ ተግባር እየፈፀሙ ይገኛሉ፡፡ እኒህንም አየ፡፡
በዚህ ሁሉ መሃል፣ ሰውዬው በፍርሃትና በጭንቀት ተውጦ እያለ፣ ከዚያ ዛፍ ቅርንጫፍ ላይ የሚንጠፈጠፍ የማር ወለላ አየ፡፡ ሰውዬው አፉን ከፈተና ማሩ ወደ አፉ ይፈስለት ዘንድ ጠበቀ፡፡ የማር ወለላው ጥቂት በጥቂት ፈሰሰለት፡፡
ከቶውንም በምን ዘዴና ብልሃት ላመልጣቸው እችላለሁ ያላቸውን ፍርሃቶች፤ ከባዶቹን የእባብ፣ የዘንዶና የአይጥ ፈተናዎች በምን መንገድ አልፋቸዋለሁ? የሚሉትን ጭንቀቶች፤ በወለላው ጣዕም ምክንያት ለጥቂት ጊዜ ሊረሳቸው ቻለ፡፡
                                                   *   *   *
የሰው ልጅ እጅግ አስከፊ በሆነ መከራና ጣጣ አረንቋ ውስጥ ወድቆ እንኳ አንዳች ፋታ የሚያገኝባትን ቅንጣት ቅፅበት ይፈልጋታል፡፡ በእሷም ረክቶ ህይወቱን የሚታደግባትን ተስፋ ይጠነስሳል፡፡ ገደል የከተተውን አውራሪስ መሸሹ እኩይ ዕጣው ነው! ሙሉ በሙሉ ገደል ገብቶ እንዳይንኮታኮት ያ ቅርንጫፍ ተዘርግቶ መጠበቁ ሰናይ ዕጣው ነው፡፡ ከዚህ ዙሪያ ደግሞ እባብና ዘንዶ አሰፍስፈው መንጠራራታቸው፣ ለሰውዬው የታዘዙ እኩይ ዕጣዎች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ጠብታዋ ወለላ ማርም የሰውዬው ሰናይ ዕጣ ናቸው! መከራዎቻችን የተስፋ ዕልባት አላቸው፡፡ በብዙ ድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ነጥብ ብርሃን የማየት ችሎታ መኖር መታደል ነው!
አያሌ ውጣ - ውረዶችን ባየንባት አገራችን፤
“ኧረ እናንተ ሰዎች ተውኝ እባካችሁ
እንኳን የመሶቡን የጄን ተውኩላችሁ”
…ስንል ኖረናል፡፡ ለማን ነው የምንተወው? ለምንድን ነው የምንተወው? እስከመቼስ የምንተወው? የሚሉትን ጥያቄዎች አላነሳንም፡፡ በዚህ ውስጥ መታሰብ ያለባቸውን ኃላፊነታችንን የመወጣትና መብታችንን የማስከበር ፍሬ - ጉዳዮች ምን ያህል አስበንባቸዋል? በምን ያህል ዕቅድና የረዥም መንገድ ትግበራስ ውጤታማ እንደምንሆን እርግጠኞች ነን? ማለት የአባት ነው፡፡
ተጨባጭ ችግሮቻችንን በተጨባጭ መንገድ መፍታት አለመቻል አንዱ ተጨባጭ ችግራችን ነው፡፡ በሀሳብ አንደጋገፍም፡፡ ሀሳብ ካቀረብን ስለችግር እንጂ ስለመፍትሄ አይደለም፡፡ ስለሆነም በችግራችን ላይ ሌላ ችግር ጨምረን ነው የምንለያየው፡፡
የኮሚቴ መብዛት ችግር አለ ተብሎ፣ ያን የሚፈታ ኮሚቴ እናቋቁም ብለው ተለያዩ እንደተባለው  ነው፡፡ አንዱ መሰረታዊ ዕጣችን ስለጊዜ ያለን አስተሳስብ ነው፡፡ ሊቀ-ጠበብት አክሊለ ብርሃን የደረሱትን ማህሌት ልብ እንበል፡-
“በሰላማ ጊዜ የረጋ ወተት
ተንጦ ተንጦ ቅቤው ወጣለት”
ጊዜ የወሰደ ሰው አንድ ቀን ቅቤው ይወጣለታል ነው ነገሩ፡፡ ጊዜን አርቀን ለማሰብ ግን የአዕምሮም የልቡናም አቅም የለንም፡፡ (ለምሳሌ የሃያ ዓመት ዕቅድ አይገባንም፡፡)
ከቀደምት ዘመናት ጀምሮ በአገራችን ብዙ አጋጣሚዎችን አጥተናል፡፡ በተለይ ቀለም የቀመሰው ክፍል ብዙ ዕድሎችን አጥቷል፡፡ አንድም አንፃር በማብዛት፣ አንድም ከሥርዓቱ ጋር አብሮ የመሥራት ባህል ስለሌለው፡፡
“አገራችን የዕድል ሳይሆን የታጡ - ዕድሎች አገር ናት” ይላል አንድ ፈላስፋ (A land of missed opportunities not of opportunities) የእኛም ምሁራን እንዲሁ ቢሉ እንዴት መልካም ነበር! ዶክተር ጌታቸው ኃይሌ ከፃፉት ውስጥ “ጌታ ዲነግዴ የሳምንት ገበያ ሲደርስ ከከብቶቻቸው አንዱን በሬ ለመሸጥ ገበያ ይወስዳሉ፡፡ ግን አንዳንድ ጊዜ ገበያ እስኪፈታ እዚያው ውለው በሬውን ሳይሸጡት ይቀሩና መልሰው ያመጡታል፡፡ አባቴ፤ “ጌታ ምነው በሬውን መለሱት? ገዢ አጡ እንዴ?” ሲላቸው፤ “የለም ልጄ ገዢስ ሞልቶ ነበር፤ ግን ስጠይቃቸው፤ በቀዬው ለበሬዬ የሚበቃ የመስኖ ሣር ያለው አንድም ሰው አላገኘሁም፡፡ ለእነሱ ሸጬ በሬዬን ረሀብ ላይ እንዳልጥለው ብዬ መልሼ አመጣሁት” ይሉታል… የሚል ይገኝበታል፡፡ ይህንንም በምግብ ራስን መቻል ከሚለው የዛሬ ትግላችን ጋር አዛምዶ ማየት ደግ ነው! በሬው ተሸጦ የሚበላው እንዳያጣ የሚታሰብበትም ዘመን ነበር - ያኔ፡፡
በተደጋጋሚ ከሚነሱት የምሁር አምባ ችግሮች ወሳኙ፤ “ጠባብነትና ትምህክተኝነት የምሁሩ አባዜዎች መሆናቸውን አለመርሳት ነው!” የሚለው ነው፡፡ በሁለቱም ፅንፍ የተቸከልን ብዙ ምሁራን አለን! አምላክ ደጉን ያምጣልን!!
አበሻ “ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኸ” ይለናል፡፡ ችግሮቻችን መፍትሄ ሳያገኙ ሰንብተው ካንሠር አከል (Cancerite) ከሆኑ በኋላ ብንጮህላቸው ከንቱ መባዘን ነው፡፡ “ቀድሞ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ አሁን ምን ያደርጋል ድስት ጥዶ ማልቀስ” የተባለውን ማጤን ነው፡፡
አገር እንደ ፅጌረዳ አበባ ብንመስላት፤ “ፅጌረዳዋ ከደረቀች በኋላ፣ ጎርፍ የሆነ ዝናብ ምን ይበጅ?!” የሚለው ይገባናል፡፡ ቀድመን እንዘጋጅ!!