Administrator

Administrator

ጥቅምት 22 ቀን 1923 ዓ.ም

በዛሬዋ_ዕለት

ከ 93 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የንግሥ በዓል ዋዜማ ፤ የታላቁ ንጉሠ ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለበዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ የተመረቀበት ዕለት ነበር።

የዳግማዊ አጤ ምኒልክ መታሰቢያ ሀውልት የቆመው/የተተከለው ከዛሬ 93 ዓመታት በፊት ጥቅምት 22 ቀን 1923 ዓ.ም ነበር፡፡

ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ምኒልክ የአባታቸውን የዳግማዊ አጤ ምኒልክን ስራና ውለታ ቀጣዩ ትውልድ ያስበውና ይዘክረው ዘንድ … ማስታወሻ የሚሆን የመታሰቢያ ሐውልት ለማሰራት አሰቡ፡፡

ሐውልቱንም በጀርመናዊው መሃንዲስ ሙሴ ሄንትል አማካኝነት አስጠንተው፤ ከጀርመን ተቀርፆ እንዲመጣ አዘዙ፡፡ ሀውልቱ የተመደበለት ቦታ ተደልድሎ ከተዘጋጀ በኋላ ገና ሳይተከል/ሳይቆም ንግሥቲቱ መጋቢት 22 ቀን 1922 ዓ.ም አረፉ፡፡

በመሆኑም የንግሥቲቱን እረፍት ተከትሎ ንጉሰ ነገሥት ለመሆን እየተዘጋጁ የነበሩት አልጋ ወራሽ ንጉሥ ተፈሪ መኮንን፣ ከዛሬ 93 ዓመታት በፊት (ጥቅምት 22 ቀን 1923 ዓ.ም) ሐውልቱ በታላቅ ክብረ በዓል እንዲተከል አደረጉ፡፡

በሐውልቱ ላይ አፄ ምኒልክ ካባ እንደለበሱ አንባር አጥልቀው በእጃቸው ጣምራ ጦር ይዘው በፈረሳቸው በ‹አባ ዳኘው› ላይ ተቀምጠው በግርማ ሞገስ ይታያሉ፡፡ የሐውልቱ ቁመት ከተፈጥሮ አካላዊ መጠን በላይ ሲሆን ‹አባ ዳኘው› ፊቱን ወደ ሰሜን መልሶ በኋላ እግሮቹ ቆሞ፣ የፊት እግሮቹን ወደላይ አንስቶ ይታያል፡፡ ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን በወረረችበት ወቅት በ 1929 ዓ.ም ወድቆ/ፈርሶ ነበር፡፡

የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት


ብርሃኑ ድንቄ የ 5ቱን የመከራ ዓመታት አጭር ታሪክ በሚለው መጽሐፋቸው ጣሊያኖች የአፄ ምኒልክን ሐውልት እንዴት እንዳፈረሱት እንደሚከተለው ገልፀውታል፡፡ …በቅድሚያ ሐውልቱ ያለበትን አካባቢ ረጅም እንጨት እየማገሩ በቆርቆሮ ሲያጥሩ ሰነበቱ….ይህንን ያየው የአዲስ አበባ ሕዝብ ሊያፈርሱት ነው ብሎ እርስ በእርሱ በሐዘን መነጋገሩን ቢሰሙ ‹‹ልናድስ›› ነው ብለው አስወሩ፡፡ ሁሉንም ነገር ካመቻቹ በኋላ ግን በየበሩ በታንክ ጭምር ጥበቃ አጠናክረው… ወደ ማታ የአራዳን አካባቢ በታንክ አጥረው በባውዛ ሌሊቱን ከተማውን እየተቆጣጠሩ በሌላ ኃይል ደግሞ ሐውልቱን ሲያፈርሱ አድረው ሲነጋጋ ወደ አልታወቀ ቦታ ወስደው ቀበሩት፡፡ ሕዝቡ እድሜና ፆታ ሳያግደው ሐዘኑን ይገልጽ እንደነበር አዛውንቶች ይመሰክራሉ።

በጊዜው የአዲስ አበባ ነዋሪ የነበረው የሃንጋሪው ዶክተር ላዲ ስላስ ላቫ እንደፃፈው፣ ሐውልቱ ከፈረሰበት ቦታ ቆመው ያለቅሱ የነበሩትን ሰዎች የጣሊያን ወታደሮች በኃይል ይበትኑ እንደነበር ገልጿል፡፡

በሌላ ዘገባ ደግሞ አንድ ሕፃን ልጅ ሲያለቅስ ጣሊያኖች ደርሰው ለምን እንደሚያለቅስ ቢጠይቁት ‹‹የንጉሱን ምልክት ስላወረዳችሁ ነው›› ብሎ እንደመለሰላቸውና ጣሊያኖችም ከሙሶሊኒ ሌላ ንጉሥ እንደሌለው በመንገር ልጁን ገርፈው እንዳባረሩት ተገልጿል፡፡ ጣሊያኖች ሐውልቱን ካፈረሱ በኋላ ሰው ሳያይ ሸፍነው በመውሰድ በታላቁ ቤተ-መንግሥት አዳራሽ ጀርባ ቀበሩት…

የወራሪው ኃይል ከኢትዮጵያ ከተባረረ በኋላም ሐውልቱ ከተቀበረበት ቦታ ወጥቶ እንደገና ታድሶና ተጠግኖ ሚያዝያ 27/ 1934 ዓ.ም ቀድሞ በነበረበት ቦታ እንዲቆም ተደረገ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም፣ በ 1988 ዓ.ም የአድዋ ድል መቶኛ ዓመት ሲከበር ሐውልቱ ጥገና ተደርጎለት እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

ታሪክን_ወደኋላ

????የእንጆሪ የጤና ጥቅሞች | Health Benefits Of Strawberries
????????????
????????የደም ግፊታችንን ያመጣጥናል፡፡
????????የቅድመ-ወሊድ ጤናን ይጨምራል፡፡
????????በሽታ የመከላከል ሥርዓትን ወይም አቅምን ይጨምራል፡፡
????????የአይናችንን ጤና ያሻሽላል፡፡
????????መጥፎ ኮሌስትሮልን ይዋጋል፡፡
????????ፀረ-ኢንፍላሜሽን ነው ወይም ኢንፍላሜሽንን ይካላከላል።
???????? ፀረ-ባክቴሪያ ባህሪ አለው ወይም ባክቴሪያን ይከላከላል።
???????? ፀረ-ካንሰር ባህሪ አለው ወይም ካንሰርን ይከላከላል።
???????? ፀረ-ቫይረስ ባህሪ አለው ወይም ቫይረስን ይከላከላል።
???????? ፀረ-እርጅና ባህሪ አለው ወይም እርጅናን ይከላከላል።

ከ100 ሺ በላይ ጎብኝዎች የሚታደሙበት ሃይል ቁጠባ አረንጓዴ አፍሪካ የተሰኘ የኤሌክትሪሲቲ ኤግዚብሽን ሊካሄድ ነው።
3A ኤቨንትስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪካል መሃንዲሶች ማህበር ጋር በመተባበር  " ሃይል ቁጠባ አረንጓዴ አፍሪካ " በሚል መሪ ቃል 4ኛውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪሲቲ ኤግዚብሽን ከየካቲት 13 እስከ የካቲት 16/2016 ዓ.ም ድረስ በታላቅ ድምቀት በሚልንየም አዳራሽ ለማካሄድ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ አስታወቁ።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኤልክትሪካል መሃንዲሶች ማሀበር 25ኛ አመቱን በታላቅ ድምቀት ያከብራል ተብሏል።
በኤግዚቢሽኑ ከ 300 በላይ የሚሆኑ በሃገር ውስጥ ያሉና ከውጭ የሚመጡ በኤሌክትሪሲቲ ዘርፍ
፣ላይ የተሰማሩ አምራቾች አስመጪዎችና አቅራቢዎች  ከ100,000 በላይ የሚሆኑ ጎብኚዎች የሚሳተፉ ሲሆን በዝግጅቱ ላይ የተለያዩ ሲምፖዚየሞች፣ ሴሚናሮች እና ጥናታዊ ፅሁፎች ይቀርቡበታል ተብሏል።
የ3A ኢቨንትስ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አብዱልፈታህ  አሊ እንደገለጹት በኤግዚቢሽኑ ላይ የሚሳተፉ ድርጅቶች ምርትና አገልግሎታቸውን የሚያስተዋውቁበት የሚያሳዩበት፣ በዘርፉ የካበተ ልምድ ያላቸውን መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በማግኘት  የልምድ ልውውጥ ለማድረግ፤ ለቀጣይ ስራ አጋርነት ለመፍጠር እንደሚያስችል እና እንደሚረዳ ገልጸዋል።


ከ100 ሺ በላይ ጎብኝዎች የሚታደሙበት ሃይል ቁጠባ አረንጓዴ አፍሪካ የተሰኘ የኤሌክትሪሲቲ ኤግዚብሽን ሊካሄድ ነው።
3A ኤቨንትስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪካል መሃንዲሶች ማህበር ጋር በመተባበር  " ሃይል ቁጠባ አረንጓዴ አፍሪካ " በሚል መሪ ቃል 4ኛውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪሲቲ ኤግዚብሽን ከየካቲት 13 እስከ የካቲት 16/2016 ዓ.ም ድረስ በታላቅ ድምቀት በሚልንየም አዳራሽ ለማካሄድ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ አስታወቁ።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኤልክትሪካል መሃንዲሶች ማሀበር 25ኛ አመቱን በታላቅ ድምቀት ያከብራል ተብሏል።
በኤግዚቢሽኑ ከ 300 በላይ የሚሆኑ በሃገር ውስጥ ያሉና ከውጭ የሚመጡ በኤሌክትሪሲቲ ዘርፍ
፣ላይ የተሰማሩ አምራቾች አስመጪዎችና አቅራቢዎች  ከ100,000 በላይ የሚሆኑ ጎብኚዎች የሚሳተፉ ሲሆን በዝግጅቱ ላይ የተለያዩ ሲምፖዚየሞች፣ ሴሚናሮች እና ጥናታዊ ፅሁፎች ይቀርቡበታል ተብሏል።
የ3A ኢቨንትስ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አብዱልፈታህ  አሊ እንደገለጹት በኤግዚቢሽኑ ላይ የሚሳተፉ ድርጅቶች ምርትና አገልግሎታቸውን የሚያስተዋውቁበት የሚያሳዩበት፣ በዘርፉ የካበተ ልምድ ያላቸውን መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በማግኘት  የልምድ ልውውጥ ለማድረግ፤ ለቀጣይ ስራ አጋርነት ለመፍጠር እንደሚያስችል እና እንደሚረዳ ገልጸዋል።


ይህን ያውቁ ኖሯል.....?

በአድዋ ተራራዎች ላይ የአንባገነኑ መሪ የቤኒቶ ሙሶሊኒ የፊት ቅርፅ ሐውልት ቆሞ እንደነበር......

በ 2ተኛ የኢጣሊያን ወረራ ዘመን በአድዋ በሱሎዳ ተራራ ፊት ለፊት ላይ በፋሺስት ወታደሮች የተገነባው ይህ ሃውልት ቁመቱ 4.80 ሜትር ከፍታ የነበረው ሲሆን ፤ የጣሊያን ወታደሮች በወቅቱ የዚህ ሐውልት በቦታው የመገንባታቸው ዋንኛው ዓላማ እና ለማስተላለፍ የፈለጉት መልዕክት:-

➻ በ 1888 ዓ.ም ላይ የደረሰባቸውን ሽንፈት በውስጣቸው ለነበረው ቁጭት እና እፍረት ማካካሻ ይሆናል ብለው በማሰብ እንዲሁም በሃጉረ አፍሪካ ለነበሩት ለሌሎቹ የቀኝ ገዢዎች የአውሮፓውያን ሃገራት የጠንካራነት ማሳያ የሞራል ማበረታቻ ምልክት ይሆናል በማለት ነበር ከ 40 ዓመት በፊት ሽንፈታቸው ከተጎነጩባት ቦታ ላይ በወርሃ የካቲት 1928 ዓ.ም ላይ ገንብተው ያቆሙት።

ሆኖም ግን አሁን ሐውልቱ በቦታው የለም ሀገራችን ከፋሺስት ጣሊያን ነፃ ከሆነች በኋላ በቦታው ምንም አይነት የሐውልቱ አሻራ እና ፍርስራሽ እንዳይኖር ተደርጎ ሊፈረስ ችሏል።

ክብርና ሞገስ ከወራሪ ነፃ ሀገር ላስረከቡን ጀግኖች አርበኞቻችን

ይህን ያውቁ ኖሯል.....?

በአድዋ ተራራዎች ላይ የአንባገነኑ መሪ የቤኒቶ ሙሶሊኒ የፊት ቅርፅ ሐውልት ቆሞ እንደነበር......

በ 2ተኛ የኢጣሊያን ወረራ ዘመን በአድዋ በሱሎዳ ተራራ ፊት ለፊት ላይ በፋሺስት ወታደሮች የተገነባው ይህ ሃውልት ቁመቱ 4.80 ሜትር ከፍታ የነበረው ሲሆን ፤ የጣሊያን ወታደሮች በወቅቱ የዚህ ሐውልት በቦታው የመገንባታቸው ዋንኛው ዓላማ እና ለማስተላለፍ የፈለጉት መልዕክት:-

➻ በ 1888 ዓ.ም ላይ የደረሰባቸውን ሽንፈት በውስጣቸው ለነበረው ቁጭት እና እፍረት ማካካሻ ይሆናል ብለው በማሰብ እንዲሁም በሃጉረ አፍሪካ ለነበሩት ለሌሎቹ የቀኝ ገዢዎች የአውሮፓውያን ሃገራት የጠንካራነት ማሳያ የሞራል ማበረታቻ ምልክት ይሆናል በማለት ነበር ከ 40 ዓመት በፊት ሽንፈታቸው ከተጎነጩባት ቦታ ላይ በወርሃ የካቲት 1928 ዓ.ም ላይ ገንብተው ያቆሙት።

ሆኖም ግን አሁን ሐውልቱ በቦታው የለም ሀገራችን ከፋሺስት ጣሊያን ነፃ ከሆነች በኋላ በቦታው ምንም አይነት የሐውልቱ አሻራ እና ፍርስራሽ እንዳይኖር ተደርጎ ሊፈረስ ችሏል።

ክብርና ሞገስ ከወራሪ ነፃ ሀገር ላስረከቡን ጀግኖች አርበኞቻችን

ከካንሰር ህመም ሁሉ በብዛት የጡት ካንሰር በአንደኛነት ደረጃ የሚታይ በሽታ ነው:: ገዳይነቱም አያጠያይቅም ምክንያቱም የጡት ካንሰር በሴቶች ላይ ለሚከሰቱት የካንሰር ሞት መንስኤ ከሳንባ ካንሰር ቀጥሎ ሁለተኛው ነው።

ማሞግራም የጡት ኤክስሬይ ምስል ነው። ዶክተሮች የጡት ካንሰር የመጀመሪያ ምልክቶችን ለመፈለግ ማሞግራም ይጠቀማሉ። መደበኛ ማሞግራም ዶክተሮች የጡት ካንሰርን ቀድመው ለማግኘት የሚደረግ ምርመራ ነው፣ አንዳንዴም እስከ ሶስት አመት ድረስ አስቀድሞ የጡት ካንሰርን ለማወቅ ያስችላል::

በምርመራው ወቅት በምስሉ ላይ እንደሚታየው ባለሙያው ጡትዎን በሁለት የፕላስቲክ ሳህን መሀል ያስቀምጣል. ሳህኖቹ ኤክስሬይ በሚወሰድበት ጊዜ ጡቱን ጠፍጣፋ ያደርጋሉ እናም አንዳንድ ጫናዎች እና ህመሞች ይሰማዎታል::

የጫናው ህመም መጠን በተወሰነ መልኩም ቢሆን ስለሚጨምር ይህን ምርመራ በወር አበበ ስዓት ማድረግ አይመከረጠርም:: በተጨማሪም ዲኦድራንት ወይም ሽቶ የመሳሰሉትን  ምርቶች መጠቀም በኤክስሬይ ላይ እንደ ነጭ ነጠብጣቦች በመፍጠር የምርመራውን ተዓማኒነት ስለሚቀንሱ አይመከሩም።

በእድሜ ከ40 በላይ የሆኑ ሴቶች በ1-2 አመት ልዩነት የማሞግራም ምርመራ ማድርግ ይኖርባቸዋል:: ማሞግራም ዋነኛ የቅድመ ካንሰር ምርመራ ቢሆንም ሌሎች አማራጮም መኖራቸውን መዘንጋት የለበትም:: በዳበሳ የሚደረግ የቅድመ ካንሰር ምርመራ በሀኪም ዘንድ ቀርቦ ወይም በ'ራስ በመዳበስ ገና እየጀመረ ያለ እጢ ማግኘት ሌላኛው አማራጭ ነው:: ልዩነቱ ማሞግራፊ በእጅ ላይ ለመሰማት በጣም ትንሽ የሆኑ እጢዎችን ሊያገኝ ይችላል። ይህም ማሞግራፊን ተመራጭና ተዓማኒ ያደርገዋል:: እድሜ ከ40 በታች ከሆነ የጡት አልትራሳውንድም 3ኛው አማራጭ ነው::

ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ ነውና ነገሩ ይህን የማሞግራፊ ምርመራ ማድርግ አስፈጊ ነው:: በኢትዮጵያ ቢያንስ በአዲስ አበባ ደረጃ የአገልግሎቱን ሁኔታ ለመግለፅ የክል በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ደረጃ  ክፍያው 360ብር ነው::

ይህ ምርመራ በተጨማሪም በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል እና በተለያዩ የግል ተቋማት ይሰጣል:: በእንሹራንስ በኩልም ምርመራውን በነፃ ማድረግ ይቻላል:: በአረብ ሀገር ያላቹ እህቶቼም በአቅራቢያ በሚገኝ የህክምና መእከል በመቅርብ ምርመራውን ማድርግ ጠቀሜታው የጎላ ነው::

Dr. Zerihun  Gelashe  Hailu

ከካንሰር ህመም ሁሉ በብዛት የጡት ካንሰር በአንደኛነት ደረጃ የሚታይ በሽታ ነው:: ገዳይነቱም አያጠያይቅም ምክንያቱም የጡት ካንሰር በሴቶች ላይ ለሚከሰቱት የካንሰር ሞት መንስኤ ከሳንባ ካንሰር ቀጥሎ ሁለተኛው ነው።

ማሞግራም የጡት ኤክስሬይ ምስል ነው። ዶክተሮች የጡት ካንሰር የመጀመሪያ ምልክቶችን ለመፈለግ ማሞግራም ይጠቀማሉ። መደበኛ ማሞግራም ዶክተሮች የጡት ካንሰርን ቀድመው ለማግኘት የሚደረግ ምርመራ ነው፣ አንዳንዴም እስከ ሶስት አመት ድረስ አስቀድሞ የጡት ካንሰርን ለማወቅ ያስችላል::

በምርመራው ወቅት በምስሉ ላይ እንደሚታየው ባለሙያው ጡትዎን በሁለት የፕላስቲክ ሳህን መሀል ያስቀምጣል. ሳህኖቹ ኤክስሬይ በሚወሰድበት ጊዜ ጡቱን ጠፍጣፋ ያደርጋሉ እናም አንዳንድ ጫናዎች እና ህመሞች ይሰማዎታል::

የጫናው ህመም መጠን በተወሰነ መልኩም ቢሆን ስለሚጨምር ይህን ምርመራ በወር አበበ ስዓት ማድረግ አይመከረጠርም:: በተጨማሪም ዲኦድራንት ወይም ሽቶ የመሳሰሉትን  ምርቶች መጠቀም በኤክስሬይ ላይ እንደ ነጭ ነጠብጣቦች በመፍጠር የምርመራውን ተዓማኒነት ስለሚቀንሱ አይመከሩም።

በእድሜ ከ40 በላይ የሆኑ ሴቶች በ1-2 አመት ልዩነት የማሞግራም ምርመራ ማድርግ ይኖርባቸዋል:: ማሞግራም ዋነኛ የቅድመ ካንሰር ምርመራ ቢሆንም ሌሎች አማራጮም መኖራቸውን መዘንጋት የለበትም:: በዳበሳ የሚደረግ የቅድመ ካንሰር ምርመራ በሀኪም ዘንድ ቀርቦ ወይም በ'ራስ በመዳበስ ገና እየጀመረ ያለ እጢ ማግኘት ሌላኛው አማራጭ ነው:: ልዩነቱ ማሞግራፊ በእጅ ላይ ለመሰማት በጣም ትንሽ የሆኑ እጢዎችን ሊያገኝ ይችላል። ይህም ማሞግራፊን ተመራጭና ተዓማኒ ያደርገዋል:: እድሜ ከ40 በታች ከሆነ የጡት አልትራሳውንድም 3ኛው አማራጭ ነው::

ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ ነውና ነገሩ ይህን የማሞግራፊ ምርመራ ማድርግ አስፈጊ ነው:: በኢትዮጵያ ቢያንስ በአዲስ አበባ ደረጃ የአገልግሎቱን ሁኔታ ለመግለፅ የክል በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ደረጃ  ክፍያው 360ብር ነው::

ይህ ምርመራ በተጨማሪም በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል እና በተለያዩ የግል ተቋማት ይሰጣል:: በእንሹራንስ በኩልም ምርመራውን በነፃ ማድረግ ይቻላል:: በአረብ ሀገር ያላቹ እህቶቼም በአቅራቢያ በሚገኝ የህክምና መእከል በመቅርብ ምርመራውን ማድርግ ጠቀሜታው የጎላ ነው::

Dr. Zerihun  Gelashe  Hailu

የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ አቶ አብነትገ/መስቀል እና 3 የመሬት አስተዳደር ሰራተኞችን ጨምሮ በአምስት ግለሰቦች ላይ የሙስና ወንጀል ክስ መስርቷል።
 
አቶ አብነት ገ/መስቀል በቂርቆስ ክ/ከ ወረዳ 2 የሚገኘውን ከሼክ አላሙዲን መሀመድ ጋር የጋራ ንብረታቸው የሆነውን የ1 ሺህ 971 ካሬ ሜትር ይዞታ በ83 ሚሊየን ብር በመሸጥ ለግል ጥቅም አውለዋል በሚል በተጠረጠሩበት ወንጀል በጊዜ ቀጠሮ ችሎት ሲቀርቡ እንደነበር አና ዐቃቤ ሕግ ከፌዴራል ፖሊስ የተረከበውን የምርመራ መዝገቡን ተመልክቶ ክስ ለመመስረት የ15 ቀን ይሰጠኝ ብሎ መጠየቁን ተከትሎ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ክስ የመመስረቻ ጊዜውን ለዐቃቤ ሕግ መፍቀዱን መዘገባችን ይታወሳል።
 
ይሁንና ዐቃቤ ሕግ ከተፈቀደለት የክስ መመስረቻ ጊዜ አስቀድሞ ዛሬ አቶ አብነትን ጨምሮ በአምስት ግለሰቦች ላይ የሙስና ወንጀል ክስ መስርቷል።
ክሱ የቀረበለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ክሱን ለመመልከት ለፊታችን ዓርብ ቀጠሮ ይዟል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ አቶ አብነት ገ/መስቀል ባሳለፍነው 2015 ዓ.ም በ2 ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት የቦሌ ታወር ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ጅምር ግንባታ ያለበት 3 ሺህ 383 ካሬ ሜትር ይዞታን ያለአግባብ ባለመብት በመሆን ይዞታው ላይ ካርታ በማውጣት ከ321 ሚሊየን ብር በላይ እንዲሸጥ አድርገዋል ተብለው ከሌሎች ከመሬት አስተዳደር ሰራተኞች ጋር ተከሰው ነበር።
 
ይሁንና በአቶ አብነት ላይ ቀርበውባቸው ከነበሩ ሶስት ክሶች መካከል ሁለቱ ክሶች በችሎቱ ዳኛ ከአንድ ሳምንት በፊት እንዲቋረጡ ተደርገዋል።
(ኤፍ ቢ ሲ)
የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ አቶ አብነትገ/መስቀል እና 3 የመሬት አስተዳደር ሰራተኞችን ጨምሮ በአምስት ግለሰቦች ላይ የሙስና ወንጀል ክስ መስርቷል።
 
አቶ አብነት ገ/መስቀል በቂርቆስ ክ/ከ ወረዳ 2 የሚገኘውን ከሼክ አላሙዲን መሀመድ ጋር የጋራ ንብረታቸው የሆነውን የ1 ሺህ 971 ካሬ ሜትር ይዞታ በ83 ሚሊየን ብር በመሸጥ ለግል ጥቅም አውለዋል በሚል በተጠረጠሩበት ወንጀል በጊዜ ቀጠሮ ችሎት ሲቀርቡ እንደነበር አና ዐቃቤ ሕግ ከፌዴራል ፖሊስ የተረከበውን የምርመራ መዝገቡን ተመልክቶ ክስ ለመመስረት የ15 ቀን ይሰጠኝ ብሎ መጠየቁን ተከትሎ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ክስ የመመስረቻ ጊዜውን ለዐቃቤ ሕግ መፍቀዱን መዘገባችን ይታወሳል።
 
ይሁንና ዐቃቤ ሕግ ከተፈቀደለት የክስ መመስረቻ ጊዜ አስቀድሞ ዛሬ አቶ አብነትን ጨምሮ በአምስት ግለሰቦች ላይ የሙስና ወንጀል ክስ መስርቷል።
ክሱ የቀረበለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ክሱን ለመመልከት ለፊታችን ዓርብ ቀጠሮ ይዟል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ አቶ አብነት ገ/መስቀል ባሳለፍነው 2015 ዓ.ም በ2 ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት የቦሌ ታወር ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ጅምር ግንባታ ያለበት 3 ሺህ 383 ካሬ ሜትር ይዞታን ያለአግባብ ባለመብት በመሆን ይዞታው ላይ ካርታ በማውጣት ከ321 ሚሊየን ብር በላይ እንዲሸጥ አድርገዋል ተብለው ከሌሎች ከመሬት አስተዳደር ሰራተኞች ጋር ተከሰው ነበር።
 
ይሁንና በአቶ አብነት ላይ ቀርበውባቸው ከነበሩ ሶስት ክሶች መካከል ሁለቱ ክሶች በችሎቱ ዳኛ ከአንድ ሳምንት በፊት እንዲቋረጡ ተደርገዋል።
(ኤፍ ቢ ሲ)