Administrator

Administrator

Tuesday, 12 December 2023 20:25

ምንጊዜም አዲስ

      ማድረስ ሲባል አንድ ትእዛዝን በፌስታል አሽጎ ለደንበኛ ወርውሮ መምጣት ማለት አይደለም። በየጊዜው በየትእዛዙ ደንበኛዎን ማስገረም፣ ማስደነቅ እና ማስደሰት ማለት እንጂ።ትናንት ትእዛዝን በተቀበሉ ጊዜ የደረሱበትን መንገድ እና የሙያ ፍቅር ዛሬ ደግሞ ያሻሽሉት። ማሻሻልዎ የይዘትም የቅርጽም ይሁን። ደንበኛዎ ከሚገምትዎ ላቅ ብለው ይገኙ። ያን ጊዜ በደንበኛዎ ላይ አግራሞትን ይችራሉ። ደግሞ ነገ ከጠበቀው በላይ ሆነው ይገኙለት። ይህን ባደረጉ ቁጥር ደንበኛዎ በእርስዎ ላይ መተማመኑ ከፍ ያለ ይሆናል። ከዚህም ሲያልፍ እርስዎም በሙያዎ እና ብቃትዎ መታመንዎ እና የማይሸረሸር ስም መገንባትዎ እየጨመረ ይሄዳል። ታዲያ የዚህ ሁሉ ድምር ውጤት እርስዎ በበጎ የሚነሳ መለያ ጠባይን ከዕለት ዕለት እያዳበሩ መሄድዎ ነው። ይህ ወደ ስኬት የሚያደርስዎ ተግባራዊ የስኬት መንገድ ነው።ኃይሌ ገብረ ስላሴ በኦሎምፒክ ሊሳተፍ በቦሌ አየር ማረፊያ በኩል ስንሸኘው ይዞት የወጣው ልብስ ብቻ ይዞ የሚመለስ እንዳልሆነ እምነትን እንድናሳድር አድርጎናል። ኃይሌ ሲመለስ ወርቅ፣ ከወርቅ የላቀ የሪኮርድ ክብር፣ ብሎም ዛሬ ብዙኃኑን ማስተዳደር የቻለ ሀብት ይዞ ይመጣል። ማረስ ማለት ይህ ነው። ሁሉን በሰዓቱ፣ ግን በፍጥነት እና በጥራት።


አራትቅንጅትበመስተንግዶ ኢንዱስትሪ ውስጥ ነጠላ አገልግሎት ወይም የአገልግሎት ምንጭ የለም። አንድ ሆቴልን እንውሰድ ለምሳሌ። ደንበኛው አንድ አገልግሎትን ብቻ ፈልጎ መጣ እንበል። ያገኘው አንድ አገልግሎት ይሁን እንጂ ያአገልግሎት በተቀናጀ መንገድ የተገኘ እንጂ አንድ ግለሰብ ወይም አንድ ክፍል ብቻውን የሰጠው ሊሆን አይችልም።
ምግብ ተመግቦ የሄደ ደንበኛ፤ የጽዳት፣የጥበቃ፣ የኪችን፣ የመስተንግዶ፣ የሒሳብ አገልግሎት እና ሌሎችንም ክፍሎች ቅንጅት የሚጠይቅ አገልግሎት ነው ያገኘው። ምግብ ስለተመገበ ብቻ የአብሳይ አገልግሎት ብቻ አግኝቶ ሄደ ልንል አንችልም።
ስለዚህ እርስዎ ሊለዩ ወይም ሊታወቁ ከሚገቡባቸው ጠባያት አንዱ የተቀናጀ ሥርዓት መከተል ነው። ቅንጅቱ ከግለሰብ ግለሰብ፣ ከግለሰብ ክፍል፣ ከክፍል ክፍል፣ ከክፍል ግለሰብ መሆን አለበት።በቀዳሚዎቹ ክፍሎች እንዳየነው ኃላፊነትን መወጣት የሁሉም ድርሻ ነው። ኃላፊነትን መወጣት ታማኝነትን ለማግኘት የሚረዳ ጠባይ ነው። ስለዚህም አንድ ግለሰብ ወይም ክፍል ኃላፊነትን ወሰደ ማለት ሽልማቱንም ወቀሳውንም ይወስዳል ማለት ነው። ይህ እንዲሆን ደግሞ ግለሰቦች እና ክፍሎች ተናበው ተቀናጅተው መሥራት
ይገባቸዋል። በምግብ ደስተኛ የሆነ ደንበኛ በመኝታም ደስተኛ እንዲሆን የክፍሎች የተቀናጀ አግልግሎት ያስፈልጋል። ይህንን ጠባይ ገንዘብዎ እንዲደርጉ የሚያስችሉ ስልቶች የሚከተሉት ናቸው።


ኃላፊነትን መውሰድ የተቀናጀ አገልግሎትን ለማቅረብ ኃላፊነትን መውሰድ የመጀመሪያው ስልት ነው። እርስዎ የራስዎን ክፍል ኃላፊነት ከወሰዱ ሌላውም ሰው የራሱን ክፍል ኃላፊነት ለመውሰድ አይሰስትም።ስለዚህ ኃላፊነትን ይወሰዱ፤ እንደ ግለሰብ ወይም እንደ ክፍል ኃላፊነትን ሲወስዱ ሌሎችም በየደረጃቸው ኃላፊነታቸውን ይወስዳሉ።ሀቀኝነት አንድ የተቀናጀ ስራ እንዲቀጥል ወይም እንዳይቀጥል ወሳኙ ቁም ነገር የሚመነጨው ጉዳዩ ከሚመራበት የሀቀኝነት ልክ ላይ ነው። ሀቀኝነት በሌለበት የተቀናጀ እና የተሰናሰለ
አሰራር ሊኖር አይችልም። “የማይተማመን ባልንጀራ በየወንዙ ይማማላል” የሚለው አባባል ለዚህ አስረጅ መሆን ይችላል።በሀቀኝነት ላይ የተመሠረተ የተቀናጀ አሠራር በየዕለቱ እያደገ የሚመጣ ነው። በየዕለቱም ወደ ስኬት እየተለወጠ የሚሄድ ነው። ሀቀኝነት ከሌለበት ግን በየዕለቱ እየፈረሰ የሚመጣ ነው።ሀቀኝነት ከላይኛው ኃላፊነትን ከመውሰድ ጋር የሚመጣ ነው።


የምንከውነው ክዋኔ፣ የምናደርገው ድርጊት፣ የምናስበው እሳቤ ሀቅ ላይ ያልተመሰረተ ከሆነ እርስ በእርስ የተሰናሰለ ውጤትን ልናገኝ አንችልም። ይልቁንም የዛሬው ተግባር ከነገው ጋር የሚቃረን ይሆናል። የነገው ዕቅድ ከትናንቱ ጋር የሚፋረስ ይሆናል።ከሥራው አለመቀናጀት አልፎ ደንበኞቻችን እምነት እንዲያጡብን ሊያደርግ የሚችል ይሆናል። አንድ ደንበኛ ኮሪደር ላይ ካገኘው ሠራተኛ የሚያገኘው መረጃ ፍሮንት ዴስክ ላይ ከሚያገኘው መረጃ የሚምታታበት ከሆነ እስካሁን ስናነሳቸው የነበሩ በጎ ጠባያት ሁሉ ከንቱ ይሆናሉ። ታማኝነት እናጣለን። የነበረን የሥኬት መንገድ ጥርጣሬ ውስጥ የሚወድቅ ይሆናል። ሀቀኝነት እውነት ሆኖ ጊዜያዊ ከሆነም እርስ በእርሱ ሊቃረን የሚችል ውጤትን የሚያስከትል ይሆናል።
በሁኔታዎች ላይ የሚንጠለጠል እውነታ ከሆነ ያ እውነታ መሠረቱ ጥቅመኝነት ነው። ነገር ግን ለዘላቂ እውነት፣ ለዘላቂ ደንበኝነት ማገልገል ነው ሀቀኝነት። ደንበኛችን ኪስ ውስጥ ያለውን ገንዘብ አራግፈን እኛ ድርጅት ውስጥ ለማስቀረት ብዙ አመክንዮ ብንደርድርም የዛሬ አመክዮ
ለነገም የማይሠራ ከሆነ ጊዜያዊ ጥቅም እንጂ ሀቀኝነት ሊሆን አይችልም። ሀቅ የመታመን የጀርባ አጥንት ነው።


ግልጽነትከሀቀኝነት ብዙ የራቀም ባይሆን ያለንበትን ነገር ወደ ተግባር ከመለወጣችን በፊት በግልጽ ስለማስቀመጥ የሚያልም ጠባይ ነው። በግልጽ ያልተወራ፣ በግልጽ ያልተደረገ፣ በግልጽ ለውይይት ያልቀረበ ይዋል ይደር እንጂ ቂምን፣ አለመግባባትን ብሎም ውድቀትን ይዞ ሊመጣ የሚችል ነገር ነው። አንድ ተቋም በተቀናጀ አካሄድ ይመራ፣ ይሥራና ለውጥ ያምጣ ከተባለ፣ ነገሮች ከመጀመሪያው ጀምሮ በግልጽ
መመራት አለባቸው። “ይህ ባይነገርም ችግር የለውም”፤ የሚባል ነገር የተቀናጀ ሥርዓትን በመፍጠር ላይ ዋጋ የሌለው ነገር ነው። ነገሮች በግልጽነት ከተጀመሩ ወደ ሀቀኝነት ብሎም ወደ ተቀናጀ ሥርዓትነት ይለወጣሉ።
ምግባራዊነትየትኛውም ሙያ የራሱ ምግባር አለው። በሙያችን የተነሳ የምናውቃቸው በርካታ ምሥጢሮች አሉ። ምስጢሮችን መጠበቅ የሙያ ስነ ምግባር ነው።አንዳንዴ ገጥሟችሁ ያውቃል?
ባለሥልጣናት ወይም ባለሃብቶች ወይም ዝነኞችን አየን፤ እንዲህ አደረጉ… እንዲሁም አደረጉ ተብሎ ሲወራ? ይህ ምሥጢር በየት ወጣ? በአብዛኛው በአገልግሎት ሰጪዎች በኩል አይደለምን? የእነዚህን ዝነኞች ምሥጢር መያዝ ያላስቻለ፤ ሙያ ሊሆን አይችልም። “የሺህ ፍልጥ ማሰሪው ልጥ” እንደሚባለው የሁሉም ነገር መጠቅለያው የሙያ ሥነ-ምግባርን ማክበር ነው። የወል ምግባርም ሳይረሳ።
አምስትጽናትጽናት ኃይል ከሚለይቸው ጠባያት ዋነኛው ነው። ያለ ጽናት ወደ የትኛውም ውጤት መድረስ አይቻም። ጽናት የሥነ
ልቡና የአካል፣ የአዕምሮ፣ የሥሜት ዝግጁነትን የሚጠይቅ ነው።ትናንት በሞከርነው ላይ ዛሬ ተጨማሪ ሙከራ ማካሄድን ይጠይቃል። ምናልባት ትናንት ከደረስንበት አንጻር ስኬትን ለማረጋገጥ አንድ ስንዝር ብቻ መራመድ የዛሬ ኃላፊነታችን ይሆናል። ኪሎሜትሮችን
ሮጠን አንድ የማጠቃለያ ስንዝር ጽናት አጥተን ለሽንፈት ልንዳረግ እንችላለን።በሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ውስጥ የአንድ
ብሎን አንድ ዙር መጥበቅ እና መላላት የራሱ ትርጉም አለው። በዓለም ላይ ታላላቅ የፈጠራ ሰዎች ከጽናት ማነስ የተነሳ የአንድን ብሎን
አንድ ክርክር አዙሮ ባለማጥበቅ፣ ለዘመናት የለፉባቸው የምርምር ሥራዎች ውጤት ባለቤት ሳይሆኑ ቀርተዋል። ተመራማሪዎቹ
ዕድሜ ዘመናቸውን የለፉባቸውን ልፋቶች ምናልባት ለሽርፍራፊ የጊዜ መለኪያ ያህል ጸንቶ መሞከር ስለአቃታው ከእነሱ ቀጥለው ጥቂት የሞከሩት የፈጠራው ወይም የአሸናፊነቱ ባለቤት እንዲሆኑ ያስችላቸዋል። ጽናትን ልንለማመድባቸው የምንችላቸው ቁምነገሮች የሚከተሉት ናቸው፡-- ቀጣይነት፡- የምንሞክረውን ነገር ቀጣይነት ማረጋገጥ። ለጊዜው ብልጭ ብሎ የሚጠፋ እንዳይሆን መጠንቀቅ።


ብልጭ ብሎ እንዲጠፋ ባደረግን ቁጥር ሐሳቦቻችንን ሜዳ ላይ እየበተንን እንገኛለን። ስለዚህ ሙከራችን፣ ጥረታችን እና ትግላችን ቀጣይነት ያለው፣ የማይቋረጥ መሆኑን ማረጋገጥ ያስፈልጋል። ለምሳሌ ለልባችን ደኅንነት በየጠዋቱ ገመድ መዝለል ታዝዞልን ከሆነ የልብ ምታችን እስኪስተካከል ብቻ አይደለም በገመድ ዝላዩ ላይ መትጋት ያለብን። ይልቁንም የእድሜ ዘመን ተግባራችን አድርገን አጽንተን መያዝ አለብን እንጂ።- ምግባር፡- ታጋሽነት፣ አድማጭነት፣ አንባቢነት፣ ፈታሽነት ወዘተ ሀብቶቻችን ሊሆኑ ይገባል። ምግባር የሌለው ሰው የሚጓዘው ርቀት በጣም አጭር ነው። ምግባር ባጣ ቁጥር በመንገዱ ላይ የሚያጋጥመው እንቅፋት እየበዛ፣ የሚፈትነው እና የሚጣላው እየበረከተ ይሄዳልና ወደ ስኬት ሳይሆን ወደ ውድመት ይመራል። ስለዚህም ጽናት ይኖረን ዘንድ ምግባር ያስፈልጋል። በምግባሩ የተመሰገነ ሰው በጉዞው ሁሉ የሚያበረታው፣ የሚያግዘውና የሚረዳው ሰው ስለሚያገኝ እስከ መጨረሻ ድረስ ጸንቶ ለመታገል የሚያስችለውን ስንቅ እያገኘ ይሄዳል።- ልህቀት፡- ጥረት ብቻውን ድንጋይ የመግፋት ያህል ነው። ጥረት የምናደርግበትን መንገድ መመርመርም ይገባል። በምንሠራበት ሥራ በተሠማራንበት ሙያ ምንጊዜም የላቅን ሆነን መገኘት ይገባል። እዚህ ድረስ የመጣንበት መንገድ ወደ ቀጣዩ ጎዳና ላያሻግረን ይችላል። ስለዚህም የጉዳዩ ልሂቅ ሆነን ለመቀጠል መታተር ያስፈልጋል። ኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶችና ሰርቶ የመቆም ሕልም አይደለም ጉዞው፤ የዘርፉ የልህቀት ማዕከል ሆኖ የመገኘት እንጂ። ይኸንንም እያስመሰከረ ይገኛል።

በበርካታ ከተሞች ቅርንጫፎችን ከመክፈትም ባለፈ ሁሉም ቅርንጫፎች የሙያው የሥልጣኔ ልክ መታያ ወይም የልህቀት መገለጫ እየሆኑ መጥተዋል። ስለዚህ በምንሰጠው አገልግሎት ውስጥ ልቆ መገኘት ወይም እየላቁ መገኘት የጽናት ጉልበትን ያስታጥቃል።- ቁርጠኝነት፡- ጽናት አለመሸነፍ ነው። ላለመሸነፍ ደግሞ ብርቱ ትግል ያስፈልጋል፤ እየወደቁ መነሳት፣ እየተነሱ መታገል ያስፈልጋል። ስለዚህ የትኛውም ፈተና ቢመጣ ፈተናውን ለመፋለም ቁርጠኛ ሆኖ መገኘት ይጠይቃል።- ጽናት ታሪክን ይቀይራል። ታሪካቸውን የማናውቃቸው፤ ከየትነታቸው የማይታወቅ፣ አዳዲስ ዝነኞች በየጊዜው በዓለማችን ላይ ብቅ ይላሉ። ስኬታማ የተባሉትን ሰዎች ታሪክ መለስ ብለን ስንመለከት የሁሉም ለማለት በሚያስችል ደረጃ ብዙ ፈተናዎችን መውጣት የጠየቀ ስኬት ነው ያላቸው።- ነገሮች ሁሉ አልጋ በአልጋ ሆነውለት ወይም እድሜውን በሙሉ በሎተሪ ስኬት ላይ የደረሰ የለም። መነሻውን ሎተሪ ያደረገ እንኳ ቢሆን ያንን የሎተሪ ዕጣ ለማስተዳደር ብዙ ፈተናዎችን ማለፍ እና በጽናት መሥራት ጠይቆት እናገኛለን። ያለ ጽናት ለረጅም ጊዜ የዘለቀ ስኬት የለም።ይህ ለየዘርፉ የሚሰራ ነው። በዓለም ላይ አንደኛ የተባሉ ሳይንቲስቶችን ተመልከቷቸው። “ትምህርት የማይገባቸው” ተብለው ከትምህርት ቤት የተባረሩ ሁሉ አሉበት። በዓለም ላይ ምርጥ የተባሉትን ደራሲዎች ተመልከቷቸው። “ ስራዎቻቸው ለአቅመ ህትመት አልደረሱም” ተብለው በተደጋጋሚ በአሳታፊዎች የተገፉ ናቸው።
በዓለም ላይ ስኬታማ የሆኑ ስፖርተኞችን ተመልከቷቸው። አጋዥ አጥተው በባዶ እግራቸው በብርድና ቁር ሲለማመዱ የነበሩ ናቸው። ይህ ሁሉ የሚያመላክተው ጽናት የስኬት መጠቅለያ መሆኑን ነው።(ምንጭ፡- “ሆኖ መገኘት” ከሚለው
አዲስ መፅሐፍ የተቀነጨበ)

 

አሸናፊዎች ከ100 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር ተሸልመዋል ዳሽን ባንክ በተለያየ የስራ ፈጠራ ክህሎት ባለ ሀሳቦችን አወዳድሮ የሚሸልምበት “ዳሽን ከፍታ” የሁለተኛ ዙር ተወዳዳሪዎች ባለፈው ማክሰኞ ህዳር 25 ቀን 2016 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በሸራተን አዲስ ሆቴል ተሸለሙ፡፡ ከ1ኛ-10ኛ የወጡት ስራ ፈጣሪዎች ከ100 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር ሽልማት ወስደዋል፡፡ ተወዳዳሪዎች በእለቱ ከባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ዓለሙና ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ከአቶ ንጉሱ ጥላሁን እጅ ሽልማታቸውን ተቀብለዋል፡፡

ባንኩ፤ ስታርች በጋራ ሆነው በመስራት አንደኛ ለወጡ ወጣቶች የ500ሺህ ብር፣ የአይነ ስውራን የትምህርት መርጃ መሳሪያ ብሬል በመፍጠር ሁለተኛ ለወጣው 400 ሺህ ብር በጋራ ሆነው የግብርና ቴክኖሎጂ ለፈጠሩት ወጣቶች 300 ሺህ ብር፣ በግሉ ከወዳደቁና በአካባቢው ከሚገኙ ቁሳቁሶች ጫማ በማምረት ለፈጠረው ስራ 200 ሺህ ብር እንዲሁም ሄይዝ ሲቲንግ ማሽን የሚባል የትምህርት መረጃ መሳሪያ ፈጥሮ አምስተኛ ለወጣው ወጣት የ150 ሺህ ብር ሽልማት በማበርከት ውጥናቸው እንዲሰምርና ወደ ስራው በስፋት እንዲገቡ
የሚደግፋቸውን ገንዘብ አበርክቶላቸዋል፡፡ከ6ኛ-10ኛ ለወጡትና የበቆሎ መፈልፈያ ማሽን፣ የግብርና ቴክኖሎጂ፣ ሶላር ኩከር፣ የህፃናት የዳይፐር መቀየሪያ እዲሁም የትምህርት መርጃ መሳሪያ ለፈጠሩ ባለህልሞች ለእያንዳንዳቸው የ100 ሺህ ብር ሽልማት አበርክቷል፡፡

በእለቱ በተለይ ከ1ኛ-5ኛ የወጡት ወጣት ስራ ፈጣሪዎች አጭር የህይወት ታሪክ እንዲሁም “ዳሽን ከፍታ” ከጅምሩ እስካሁን የደረሰበትን ጉዞ የሚያሳይ አጭር ዘጋቢ ፊልም ለእይታ ቀርቧል፡፡በሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ሽልማቱን ላሸናፊዎች ከሰጡ በኋላ ባደረጉት ንግግር፤ “ዳሽን ባንክ የሚሰራው ስራ መንግስትንም ሀገርንም በቀጥታ የሚደግፍና ችግር ፈቺ ባለሀሳብ ወጣቶች በብዛት እንዲፈጠሩ የሚያደርግ በመሆኑ መመስገን አለበት” ሲሉ አወድሰው ስራ ፈጣሪ ተወዳዳሪዎችን በርትተው በመስራት የሀገራቸውን ችግር እንዲፈቱ አሳስበው፣ ሚኒስትር መስሪያ ቤታቸው ለስራ ፈጣሪዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ በመግለፅ ቃል ገብተዋል፡፡ በሁለተኛው ዙር የ”ዳሽን ከፍታ” የስራ ፈጠራ ውድድር 2 ሺህ 500 ሰዎች
ተመዝግበው እንደነበረና ወደ መጨረሻው ዙር ያለፉት 10 ተወዳዳሪዎች መሸለማቸውም ታውቋል፡፡ለውድድሩ በየክልሉና በየከተሞቹ ከ40 በላይ ዳኞች መሳተፋቸው የተገለፀ ሲሆን በዕለቱ በዳኝነት ለተሳተፉና የውድድሩ አጋር ለሆኑ ተቋማትና ግለሰቦች የምስጋናና የእውቅና ሽልማት ተሰጥቷል፡፡ በተያያዘ ዜና፤ የዲጂታል የባንክ አገልግሎትን ቀድሞ በማዘመን የሚታወቀው ባንኩ ባለፈው ሳምንት ህዳር 22 ቀን 2016 ዓ.ም ከኩሪፍቱ ሪዞርት ጋር በመተባበር የስጦታ ካርድና በእጅ የሚሰራ የክፍያ መፈፀሚያ (Co-Branded Gift card
and Wirst Band ) በኩሪፍቱ ወተርፓርክ በይፋ አስተዋውቋል፡፡


 የስጦታ ካርዱና በእጅ የሚታሰረው የክፍያ መፈፀሚያ በኩሪፍቱ፣ በቢሸፍቱ በቦስተን ዴይ ስፓና በተመረጡ የዳሽን ባንክ ቅርንጫፎች ማለትም በቢሾቱ ንዑስ ቅርንጫፍ፣ በአፍሪካ ጎዳና፣ ቦሌ ኖክ፣ ድል በር፣ ጊዮንና አሙዲ ቅርንጫፎች የሚገኙ ሲሆን በየትኛውም
የዳሽን ባንክ ቅርንጫፍ በመቅረብ ገንዘባቸው ሲያልቅ መልሰው እንደሚሞሉ የዳሽን ባንክ ቺፍ ዲጂታ ኦፊሰር አቶ ዮሃንስ ሚሊዮን በይፋ ማድረጊያ ስነ ስርዓቱ ላይ ተናግረዋል፡፡ የኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓ ማናጀር አቶ እስክንድር ጌታቸው በበኩላቸው፤ ኩሪፍቱም በሀገራችን
የመጀመሪያውን ስፓ በመክፈት ዳሽንም ዲጂታል ባኪንግን በማስተዋወቅ ቀዳሚ በመሆናቸው የሚያመሳስላቸው ነገር መኖሩን ገልፀው ከዚህ ቀደምም በአሞሌና በሌሎቹም ሁለቱ ተቋማት አብረው ሲሰሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡ በእጅ የሚታሰረው ሰዓት መሰል
የክፍያ መፈፀሚያ አንድ ሰው ዋና ውስጥ ሆኖ የፈለገውን ለማዘዝ ውሃ የማያበላሸው ቀላልና ቀልጣፋ አሰራርን የተከተለ ነው ተብሏል፡፡
በስጦታ ካርዱም ሆነ በእጅ በሚታሰረው የክፍያ መፈፀሚያ መገበያየት የ10 በመቶ የዋጋ ቅናሽ ያስገኛልም ተብሏል፡፡

ዚያ ልክ በምስራቃውያን የተመስጦ ብርሃን የሚመላለስ መናኒ፥በዚህ ልክ አድሎአዊ እንዴት ሊሆን ይችላል? ሊገባኝ አልቻለም! ያዕቆብ ብርሃኑ “የፍምእሳት ማቃመስ” በሚለው 5ኛው መጽሐፉ የታሪክ ክፍሉ ላይ ያነሳቸው የታሪክ ሰበዞችሚዛናቸውን የሳቱና የግል አሉታዊሥሜት የተንጸባረቀባቸው፣ በመሰለኝና በደሳለኝ መንፈስየተጻፉ መሆናቸው የመጽሐፉን መንፈስ ይረብሸዋል። የመጽሐፉ የሕትመት ወረቀት ጥራትና
የሥነ ጽሑፍ ውበቱ እጅግ ግሩም ነው። በምሥራቃውያን ብህትውናዊ የሕይወት ፍልስፍና ላይ ያለው ንባብና ተመስጦ በእጅጉ ያስቀናል። ዳሩ ግን የመጽሐፉ የእርስ በእርስ የሃሳብ ግጭትና ያለ በቂ መረጃ የሚደመድመው ነገር የመጽሐፉን ትልቅነት የሚቀንሰው ይመስለኛል። አንዳንድ ጊዜ ግልጽ ተቃርኖዎችን በንጹህ ሕሊናህ ለማስታረቅ ወይም ለማቀራረብ ዳኛ ስታጣ ስለ ፍትህ ብለህ የራስህን ብይን ትሰጣለህ። በእኔ ትንሿ የታሪክ ንባቤ፥ ያዕቆብ ብርሃኑ የታሪክ ትንተናውን ቢተወው የመጽሐፉን ዋጋ ያንረዋል ብዬ አስባለሁ። ስለ አንድ ሁነት ከታሪክ ተነስቶ ብይን ለመስጠት ታሪክን
በከፍተኛ ጥንቃቄ በወጉ የግድ ማወቅ ይኖርበታል። ታሪክ በነጠላ ጥራዝ ነጠቅ ጥቅስ ድምዳሜ ላይ አይደርስም። “ማኒ” አክሱም ኃያል ነች ስላለ ብቻ ኃያል ነች ብለን ስናወድስ፣ “ኤዲዋርዶ ጊበን” ደግሞ የመካከለኛው ዘመን ጨለማ ነው ስላለ ብቻ ጨለማ ነው ብለን ስንረግም መኖርየለብንም። እንደ ሀገርና እንደ ማኅበረሰብም የጎዳን ይህ አይነቱ የጠቅላይ ድምዳሜ አካሄድ ነው። ይህ ስለ አክሱምና መካከለኛው ዘመንበዶ/ር ዳኛቸው አሰፋና በብሩህ አለምነህ የተደረገው ስሁት የታሪክ ድምዳሜ እንደገና ከታሪክ መነሻው መታየት ያለበት ጉዳይ ሆኖሳለ እንደገና ያዕቆብ ብርሃኑ ደግሞ ጥናት
ሳያደርግ ሲደግመውታሪክ ከባለሙያ ውጭ ሲታይ የሚያመጣውን የተዛነፈ ድምዳሜን ያረጋግጥልናል። አክሱምን በጥልቀት ሳያውቁ ስለአክሱም ድምዳሜ መስጠት፣ መካከለኛውዘመንን በጥልቀት ሳያጠኑ ስለ መካከለኛው ዘመን ስሁት ድምዳሜ መስጠት እንዴት ይቻላል? ይህ አይነቱ አካሄያድ ምንድነው ጥቅሙ? ማንንስ ነው የሚጠቅመው? ለምሳሌ ያዕቆብ እንዲህ ይላል፤...”ለነገሩ እስከ አፄ ቴዎድሮስ ዘመን ያለውየኢትዮጵያ ታሪክ በሙሉ ትረካው ተረትቅልቅል ነው” (ገጽ 7) ይላል። የትኛውታሪክ ነው ተረቱ? በንጽጽር የመካከለኛውዘመን ከየትኛውም ጊዜ በላይ ለኢትዮጵያየታሪክ ጥናት በቂ የጽሑፍና የቁሳቁስ ምንጮች ያሉበት በመሆኑ ከተረት የጸዳ ታሪክ መጻፍ የሚቻልበት አቅም አለው። በዚህም የተነሳ እነ ፕሮፌሰር ሥርግው
ኃብለ ሥላሴ፣ ፕሮፌሰር ታደሰ ታምራት፣ ፕሮፌሰር መርዕድ ወልዳረጋይ፣ ተክለጻዲቅ መኩሪያ፣ ዳንኤል ክብረት፣ ፕሮፌሰርሀብታሙ መንግሥቴ፤ ከውጭ የታሪክ ጸሐፊያን ደግሞ ኤድዋርድ ኡሉንዶርፍ፣ ትሪሚንግሃም፣ ኮንቲ ሮሲኒና ሌሎችም የዘመናዊ የታሪክ ጥናት መንገድን በመከተልከተረት በላይ የሆነ ታሪክ በማስረጃ ጽፈዋል! ነገር ግን ለታሪክ ምንጭነት እንደ ግብዓት የሚያገለግሉ ዜና መዋዕልን፣ ገድላትን፣የተለያዩ ድርሳናትን፣ ሚት ነክ
እና የዘውጌ ትርክቶችን እንደ መደበኛ ታሪክ ማየት እጅግ አደገኛ ነው። እነዚህ ከላይ የዘረዘርናቸው ድርሳናት በየትኛውምሀገር ያሉ ሁነቶች ናቸው።ይልቁንም በበቂመረጃ ያልደገፈውና መካከለኛው ዘመንንያነቃቃው፣ ያዕቆብ ስለ ንግሥተ ሳባናስለ አክሱም የጻፈው ተረክ ነው። በጣም
የሚገርመው ለሚፈልገው ዓላማ ሲሆን ተረት የተባለውን እንደ እውነት መጠቀም ደስ ያላለውን ዘመን ደግሞ በመደበኛ የታሪክ ባለሙያዎች የተጻፈውን ኃቃዊ ታሪክ እንደ ተረት መቁጠር ምን የሚባል ሳይንስ ነው?
“በአባቷ እግር የተተካችው ንግሥተ ሳባ ግን ቅድመ አክሱም ኢትዮጵያን ታላቅ አደረገች” ይላል (ገጽ 8) ላይ። ንግሥተ ሳባ መቼ እና የት ቦታ እንዴት ባለ ንግሥና ነገሰች? የሚለው ተረክ ግን በበቂ ማስረጃ ማሳየት አይቻልም። ያዕቆብም አንዲትምየእናት መዝገም ማስረጃ አላቀረበም።
ቅድመ አክሱም ንግሥተ ሳባኢትዮጵያንኃያል አደረገች የሚለው ተረክ በእምነትና በሚትእንጅ ተጨባጭ ማስረጃ ማቅረብ “በአባቷ እግር የተተካችው ንግሥተ ሳባ ግን ቅድመ አክሱም ኢትዮጵያን ታላቅ አደረገች” ይላል (ገጽ 8) ላይ። ንግሥተ ሳባ መቼ እና የት ቦታ እንዴት ባለ ንግሥናነገሰች? የሚለው ተረክ ግን በበቂ ማስረጃ ማሳየት አይቻልም። ያዕቆብም አንዲትም የእናት መዝገም ማስረጃ አላቀረበም። ቅድመ አክሱም ንግሥተ ሳባኢትዮጵያን ኃያል አደረገች የሚለው ተረክ በእምነትና በሚትእንጅ ተጨባጭ ማስረጃ ማቅረብ አይቻልም። ዳሩ ግን መረጃ የለም ብለንተረኩ ውሸት ነው የሚል ድምዳሜ ላይ አንደርስም። ይቀጥልና ከአክሱም መውደቅ በኋላ፤ “ከዚያ በፊት ያልነበሩት የእርስ በርስ ጦርነቶች እንደ አሸን ፈሉ” (ገጽ11) ይለናል። ለዚህ ሃሳብ መነሻው ምንድ ነው? በጥንት ጊዜ የርስበርስ ጦርነት ያልነበረበት ጊዜ አለ ወይ? በአክሱማውያንዘመን ስለተደረጉት ጦርነቶች ምን ያህል ያውቃል? የኢዛና የድንጋይ ላይ ጽሑፎች እንኳን የተጻፈበት ከበርካታ ጎሳዎች ጋር ስላደረገው ጦርነት ድል ነው። በአክሱም
ዘመን የኢትዮጵያ ጂኦግራፊካል ግዛት ምን ያህል ነበር? ሚጢጢዬ? ወይም ሰፊ?እንደሆነ እንኳን በእርግጠኝነት መናገር የሚችል አካልየለም።መረጃ ካለ በበቂ መረጃ መሞገት ይችላል። መካከለኛው ዘመን ግን በተለይም የዓምደ ጽዮንና የዘርዓ ያዕቆብ ዘመን በጣም ትንሽ የነበረችውንየአክሱም ኢትዮጵያግዛት ለማስፋፋት ትላልቅ ዘመቻዎችን አከናውነዋል ይሁንና ይኸ ዘመቻ የኢትዮጵያን የሃገረ መንግሥት ግንባታ ከፍታን ያሳያል እንጅ የውድቀት አንድምታ የለውም። ፕሮፌሰር ኡሉንዶርፍና ፕሮፌሰር ታደሰ ታምራት በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛ እምርታ የታየበት ዘመን እንደነበር ጽፈዋል። በተለይም ዳንኤል ክብረት “ከእቴጌ ዕሌኒ እስከ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ” በሚለው መጽሐፉና ፕሮፌሰር ሀብታሙ መንግሥቴ”በረራ-ቀዳሚት አዲስ
አበባ”በሚለው መጽሐፍ የመካከለኛውን ዘመንን ከፍታ በእናት መዝገብ በመታገዝ በዝርዝር አስቀምጠዋል! እስካሁን ይኸንን ያስተባበለ ምሁር አልመጣም።
ያዕቆብ ይቀጥልና፤ “የአክሱም ሥልጣኔ ግን አንድ ሥልጣኔ ሊኖረው የሚገባው ቅንጣቶች ሁሉ ነበሩት ...የተደራጀ ሥነ መንግሥት፣ የጽሕፈት ቋንቋ፣ ሃይማኖት፣ ባህል፣ ዕደ ጥበብ፣ የንግድ ግንኙነት፣ፈጠራ፣ ከተሞች ...” ሲኖሩት የመካከለኛው ዘመን እንደሌለው ይናገራል። የአክሱም መንግሥት የነበሩት የእድገት ምልክቶች የዛጉዌም፣ የሸዋም ሆነ የጎንደር የአፄ ግዛት ነበሯቸው። እነዚህ የአክሱም ቀጥታዊ ወራሽ በመሆናቸው የአክሱም የሥልጣኔ አብዛኛው ቅንጣቶች ነበራቸው። እዚህ ድምዳሜ ላይ ከመድረሳችን በፊት በመካከለኛው ዘመን የነበረውን የሀገረ መንግሥት ግንባታ፣የዕውቀት ግስጋሴ፣ የዲፕሎማሲ ጉዞ፣ የከተማ ግንባታዎች፣የሥነ -ጽሁፍ፣ የውይይት እድገት እና መሰል ታሪኮችን ቁጭ ብለን ከበዛው መረጃ ማጥናት
ይጠበቅብናል። ደግሞም የገብረሕይወት ባይከዳኝን፣ የዳንኤል ክብረትን፣የኤድዋርዶ ኡለንዶርፍን፣ የሀብታሙ መንግሥቴን ጥናት እና እጅግ ብዙ ያልተጠኑ የጽሁፍ ስራዎችን ማፈራረስ ያስፈልጋል። አለበለዚያ እንደዚህ የማለት ሞራል ሊኖር አይችልም።
ያዕቆብ፥ የደቂቀ እስጢፋኖሳውያንን እንቅስቃሴ የፕሮቴስታንታዊ የለውጥ አቀንቃኝ አድርጎ ማቅረብ ይታይበታል! (ገጽ 22)። ደቂቀ እስጢፋኖሳውያን እኮ ዋናው አጀንዳቸው ይህን ዓለም ንቆና ጥሎ በባሕታዊነት መመነን መሆኑን ማየት ለምን እንዳልተቻለ ትልቅ ጥያቄ ነው? ስለ ደቂቀ
እስጢፋኖሳውያን ዋና አጀንዳ በአማን ነጸረ በ”ወልታ ጽድቅ” መጽሐፉ በእናት መዝገብ አማካኝነት ይኸን የውሸት መረጃ አልባ ትርክት አፈራርሶታል!
ያዕቆብ ይቀጥልና”በዚያ በኢሮፓ ሼክስፒር...በጻፈበት ዘመን በኢትዮጵያ ደብተሮች የአጼ ልብነ ድንግልንና የአጼ ገላውዲዎስን ዜና መዋዕል እና ገድሎች
መልካመልኮች ይደርቱ ነበር” ገጽ 28 እና ገጽ 47 ይላል። ዜና መዋዕል፣ገድልና መልክ በዚያ ዘመን መጻፍ እኮ ያስደንቃል እንጅ“ይደርቱ” ነበር ተብሎ አያሰድብም ነበር። ትልቁ ችግር በዚህ በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን እነዚህን የጽሁፍ ሥራዎችን እንኳን በወጉ የሚያጠና ኢትዮጵያዊ ሰው አለመኖሩ ነው። እነዚህን ሥራዎች እንኳን በማድነቅ የተራቀቁባቸው ፈረንጆቹ የመሆናቸውን ጉዳይ ስናጠና አንድ ኢትዮጵያዊ ተነስቶስለማያውቀው ድርሳናት የመናገር ሞራል ማግኘቱ ኢ-ፍትሃዊ ነው። በጣም የሚገርመው ደግሞ ይኸ አገላለጽ ነው።”ሀገር የሚሰራው በትርክትነው ይልና...እኛ ግን በጠጅ ከሚወራረድየአባቶቻችን ገድል ከታከከ ፉከራ በቀርበአትሮኖሳችን ምንም ትርክት አልነበረም”(ገጽ 57 እና ገጽ 62) ይላል። በዚያን ዘመን
በዓለም ላይ ኢትዮጵያውያን አባቶች እኛታላቅ ሕዝብ ነን ብለው ክብረ ነገሥትንያህል መጽሐፍ ከመጻፍ የበለጠ ትርክት ምንሊያመጡ ይችላሉ? ኢትዮጵያውያን በጊዜውአሁን ኃያላን የሆኑት ሀገራት ከፈጠሩትትርክት የሚበልጥ ትርክት ፈጥረው ነበር።ዳሩ ግን ያንን ታላቅ ትርክ(Grandnarration ) የሁሉ በማድረግ ማስቀጠልናማሻሻል ባለመቻሉ ትርክት አልባ ሀገርናትውልድ ፈጥረናል። ይህ የአባቶች ችግር
ሳይሆን የኛ ችግር ነው። ኢትዮጵያውያንበፈጠሩት ጠንካራ የበላይነትን የሚያላብስትርክት የተነሳ ታላላቅ መንፈሳዊ ነገሥታትተፈጥረውም ነበር። በዚህም የተነሳ በአውሮፓውያን እንኳን ሳይቀር ‘የካህኑ ዮሐንስ’ ሀገር የሚል ገነታዊ ተምኔት የተላበሰ ግሩም ትርክት ፈጥረውልን ነበር፤ ይኸንንም
መጠቀም አልቻልንም። እንደውም ቀደምት ኢትዮጵያውያን የሚታሙት ለራሳቸው የተጋነነ ትርክት በመፍጠራቸው ነው እንጅ
ትርክት ባለመፍጠራቸው አይደለም።አንዳንድ ጊዜ ስለ ሰው ልጅ ንጽህና፣ ቅድስናና ተፈጥሮአዊነት በሚያስደንቅተመስጦ፡ሲጽፍምሳሌዎቹንባህር ተሻግሮ እነ ቅዱስ”ፍራንሲስኮ አሴሲ”እና”ቅድስት ቴሬዛን” ሲጠቅስ ጸሐፊው “ያዕቆብ ብርሃኑ” በምን ያህል ደረጃ ከኢትዮጵያውያን የመናኒያን ድርሳናት
እንደራቀ ይጠቁመናል። ምናልባት የኢትዮጵያ ቅዱሳንን ተመስጦና ከተፈጥሮ ጋር ያላቸውን ኅብረት አይቶት ቢሆን ኖሮ ምሳሌ ለመጥቀስ ባሕር አይሻገርም ነበር። ኢትዮጵያ አንዱ የምትተችበት እኮ ቁሳዊ ሥልጣኔን ትታ በርካታ መናኒያንና ጻደቃንን ያፈራች መንፈሳዊት ሀገር መሆኗ ነው። ከኢትዮጵያ ርቆ ስለ ኢትዮጵያ መጻፍ አንዱና ዋናው ችግራችን ነው።
ደራሲው ያዕቆብ ብርሃኑ በአንድ በኩል የኢትዮጵያ በቁስ አለመሰልጠኗ እጅግ እያሳስበው ትችት ያቀርባል፤ በሌላ መለኩ ደግሞ የምዕራባውያንን ሥልጣኔ “ስይጠና”(ሠይጣንነት) ይለዋል፤ አክሎም የሰው ልጅ ወደ ተፈጥሮአዊነት መመለስ አለበት ብሎ ይከራከራል።”የሰው ልጅ ወደ ዋሻው፣ ወደ
ምንጩ፣ ወደ ሥነ ተፈጥሮው ወደ ንጽሕና ልጅነት መመለስ እንዳለበት አስባለሁ” ይላል ገጽ 84። ይህ የመጽሐፉን ጭብጥ እርስበርሱእንዲጋጭ ያደርገዋል! በአንድ ወገን አውሮፓውያን ሲሰለጥኑ ኢትዮጵያ ምንኩስና ላይ ነበረች በማለት ይተቻል፣ በሌላ መንገድ ደግሞ በጥልቅ መመሰጥንና
ከተፈጥሮ ጋር ኅብረት መፍጠርን እሴቱ ያደረገውን ምንኩስናን በጥልቅ መቃተት ይናፍቀዋል፤ እንደገና ደግሞ የአውሮፓ ሥልጣኔ “ሥይጠና” ነው በማለት ያጣጥለዋል። ታዲያ እርስበርሱ የሚቃረን ሃሳብ ካቀረበ የጸሐፊው ጭብጥ ምንድነው? ይልቅ በዚህ በኩል ሺህ ጊዜ ቢጽፍ ሺህና ሺህ ጊዜ የሚያነቡት ደቀመዛሙርት ሲያፈራ እንደሚኖር አልጠራጠርም። ያዕቆብ ብርሃኑ እንዲህ ይለናል፡- “የሆነ ሰው ... ይሄን ሁሉ ዘመን ምን ስታደርግ ነበር ? ቢለኝ በእብዶች ጉባኤ በታወከች ከተማ፣ ሀገር፣ ዓለም መሃል ነፍሴን የማስጠልልባት የሆነች የጽሞና ጥጋት ሳስስ ነበር” ገጽ 108። ይቀጥልና”ሌላ ሰው ደግሞ አንተ ማነህ ቢለኝ መልሴ “የጽሞና አሳሽ ነኝ” ማለት ይከጅለኛል” ገጽ 111።“ ቢሆንም የጽሞናው አሳሽ ነኝ፣እስኪይዘኝ መሄድ እፈልጋለሁ፣ ነፍሴን የማስጠልልባት የፀጥታ ጥጋት እስካገኝ ወደ ምንም መራመድ ያምረኛል” ገጽ 113። ይህ የጽሞና አሳሽ ከሰውና ከኳኳታው እየሸሸ፣ በአካይ ሌሊት ከተማዋን በጽሞና የሚታዘብ! ከጸጥታው ጋር ቅጽበቶችን የሚዋረስ! ታዲያ ይኸ ሰው በታሪክ ላይ የሚያዳላ አንጀትን ከየት አመጣው? ከተፈጥሮ ውብ ምስጢራት ጋር እና ከዚያ ባሻገር ካለው ኃይል ጋር ኅብረት ለመፍጠርና ለመነጋገር የሚያደርገውን
መፍገምገም በድንቅ ቃል እንዲህ ሲናገረው ያምራል! እግዚአብሔርን ስትሹ፥”ከእያንዳንዷ ቢራቢሮ ጋር ለመቅበጥበጥ፣ ከእያንዳንዷ አበባ ጋር ለመሽኮርመም.... እናም ወደ ተራሮች የመሸሽ ምኞት እንዳልሆነ እወቁት...በፍጹም እዚያ ተፈጥሮ ነው፤ እዚያ ንጹህ ትንፋሽ፤ ወደ ተራሮች መውጣት
የሚያርበተብት መሻት ነው፣ ወደ ተፈጥሮ የመመለስ ፍንደቃ፣ በኦና የብርሃን ንኝት የመስከር፣ ፀሐይ እንዳኮረፈች ልጃገረድ ከተራሮች ጀርባ ስትጋረድ፣ ጨለማ ከሸለቆዎች ጥልቅ እየዳኸ ወጥቶ መላውን ፍጥረት ሲቆጣጠር የመመልከት መቋመጥ...ራሮች ወንድሞቻችን ናቸው። አዎ ከደመና
ለመተቃቀፍ፣ ከጉም ለመሳሳም፣ ጨረቃን ለማሽኮርመም፣ ፀሐይን ለማሞር፣ በእግዜር ችሎት ላይ ለመታደም ከፍታውን እፈልገዋለሁ” ይላል። (ገጽ 146)። ይኸኛው አይነት ሮማንቲክ አጻጻፍ መቼም ቢሆን ወረቱ የማይቀዘቅዝ ኪነ ጥበባዊ አጻጻፍ ስለሆነ ይበል የሚያሰኝ ነው። የተፈጥሮን ህልቆ መሳፍርት ምስጢር እያሰሱ መኖር አለፍም ሲል ሕብረታዊ መቃመስን በመፍጠር ሁኔታው በብዕር እንዲህ መሰደር ይታደሉታል እንጅ አይሸከሙትም። ያዕቆብ ብርሃኑ በዚህ በኩል በጻፈ ጊዜ ቀልብን ሰቅዞ ይይዛል! ያዕቆብ ብርሃኑ በዚህ መጽሐፍ ተተኳሪነት በ”ዐውደ ፋጎስ የውይይትክበብ” ላይ”ኢትዮጵያውያን ከእሳት ዳርሥልጣኔ ምን አተረፍን? ምን አዋጣን? ምንስ አጎደለብን?” በሚል ርዕስ ቁጭትንየሚፈጥር ምርጥ የውይይት መነሻ ገለጻ አድርጎ ሰፊ ውይይት ተደርጎበት ነበር። ምን አልባትም የታሪክ ክፍሉ ውይይት ላይ ቀርቦ ቢሆን ኑሮ ትላልቅ ግልጽ ግብአት ይገኝበትነበር። ሌላው በመጽሐፉ የመጨረሻምዕራፍ “በፍም እሳት ማቃመስ” በሚለውርእስ ስር የቀረበው የአልኬሚ ትንታኔመሰረቱን ምን አድርጎ እንደሚተነትን ግልጽ
አይደለም። ሃሳቡ የፈጠራ ይሁን የመገለጥወይም የግል አስተውሎት ምንም ግልጽ አይደለም። ለኃቃዊ ምልከታ ትችት በሰፊውየተጋለጠ ጽሁፍ እንደሆነ ይሰማኛል። እንደ ማጠቃለያ:- ያዕቆብ ብርሃኑ በታሪክ ዙሪያ ያነሳው ሃተታና ብያኔ ሚዛናዊነት የጎደለውና የግል ስሜት የተጫነው በመሆኑ በሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የተመሰጠባቸው ረቂቃን የሚስቲሲዝም ጉዳዮች ላይ አሉታዊ ጥላ ያጠላባቸዋል! በዚያ ልክበጥልቀት የሚመሰጥና ከተፈጥሮ
ውበት ጋር ሊቃመስ የሚፍጨረጨር ባህታዊ አከል ደራሲ እንዴት ኢ-ፍትሃዊ ፖለቲካ ቀመስ የሚመስል የፕሮፓጋንዳ የታሪክ ብይን ሊጽፍ ይችላል?

Sunday, 10 December 2023 20:56

‘ጆሮ በሊዝ እንስጥ እንዴ!'

እንዴት ሰነበታችሁሳ!
ስሙኝማ… እንግዲህ አየሩም ‘ቀዝቀዝ' እያለ ነው፡፡ “ያወቁ ተሟቁ” ማለት ይሄኔ ነው፡፡ ልጄ አዋዋልና አመሻሻችሁን… አለ አይደል… ክረምት-ተኮር ካላደረጋችሁት በኋላ “ወጋኝ…ቆረጠኝ” ማለት ዋጋ የለውም፡፡ ስኳር እንኳን ከወርቅ ጋር ‘የውድነት' ፉክክር በያዘችበት ዘመን… “እድሜ ለሃኪም” ማለት እንኳን አስቸግሯል፡፡ [ስሙኝማ… ደህናው ነገር ሁሉ እየተወደደ… ‘ረከሰ' የሚለው ቃል እንደናፈቀን 2000 ዘመን ልትደፍን! ለነገሩ እዚያስ ድረስ ‘ቁልጭ' ብሎ… “አይ አያ ጊዜ ማለት ተገኝቶ ነው!]  
በነገራችን ላይ አዋሳዎች ብራቮ! ‘ሚሊዮን በሚሊዮን' በጀት የለም… እንደ አራስ ሶስት መቶ ስድሳ ምናምን ቀን መታረስ የለም… ‘ሙያ በልብ' ማለት እንደናንተ፡፡
ስሙኝማ… እንደገና ዬ‘ኳስ ሰሞን' መጣ አይደል፡፡ አንድ ወዳጄ የነገረኝን ስሙኝማ፡፡ ‘ቱባ' ሰው ናቸው አሉ፡፡ እናላችሁ ይሄ የፈረደበት ቡድናችን ጎሉን ሲቅም አዩና ምን አሉ መሰላችሁ… “የቡድናችን መሰረታዊ ችግር አጨዋወቱ ጎል-ተኮር አለመሆኑ ነው፡፡” አሪፍ አይደል!
ጋዜጠኞች አንድ አለ ፍሬንቻ መንገድ የምናሳብርባት ‘ብልሃት' አለችን፡፡ እዚችም እዚያችም ከነካኩን በኋላ “የዛሬ አነሳሳችን እንኳን ስለዚህ ለማውራት ሳይሆን…” ብሎ ከመጋቢት መንገድ ወደ አስፋልት ብቅ ማለት ነዋ! እና… ተግባባን መሰለኝ፡፡
አድ ወዳጃችን አለ “የፈለገ ነገር ቢመጣ ስቄ ነው የምቀበል…” የሚል፡፡ የምርም ተዋጥቶለት ነበር፡፡ ታዲያላችሁ በቀደም “አሁንስ ለማንስ አቤት ይባላል!” ብሎ ምርር ሲል ነበር፡፡ መስሪያ ቤት በሆነ ባልሆነ ‘አበሳውን' እያሳዩት ነበር፡፡
ምን መሰላችሁ… እየበዛ ሲሄድ… አለ አይደል ነቃ ብሎ… “የሄ ሁሉ ምሬት ከየት መጣ!” ማለት ደግ ነው፡፡ አሃ… ልክ ነዋ! አለበለዚያ ዘፈኑ ‘የድሮ'… ዳንሱ ‘አሁን' ይሆንና ነገርዬው ብልሽት ነው የሚለው፡፡
የምር'ኮ …. አለ አይደል… ግራ እየገባን ነው፡፡ ‘ጉልበተኝነት'… በሰርኩላር ይፈቀድ ይመስል… ትንሹም ትልቁም ሰውን “አሁንስ ለማን አቤት ይባል!” እያሰኘው ነው፡፡
በቀደም… አንድ እድሜው ከስምንት ወይ ከዘጠኝ የማይበልጥ ልጅ ማስቲካ ሲሸጥ አንድ የቀበሌ ዘብ ያስቆመዋል፡፡ [ኮሚኩ ነገር ምን መሰላችሁ… እዛው አካባቢ ሌሎች ተለቅ ያሉ ካልሲ፣ ጢም መላጫ ምናምን የሚሸጡ ነበሩ፡፡ “ማንን ታሸንፋለህ ቢሉት ሚስቴን አለ” የሚሉት ይሄን ነው እንዴ!]
እናላችሁ ልጁ ማስቲካዎችን በሙሉ ሰብስቦ እንዲያነሳው አደረገና ምን አደረገው መሰላችሁ… የደረደረበትን ካርቶን በጫጭቆ ጣለበት፡፡ ‘ጉልበት የሌለው' ህፃን ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ፡፡ በልጅ እንባው “ለማን አቤት ይባል?” እያለ ነው፡፡ እንዲህ አይነት ነገር… “ነገ'ኮ…” ምናምንም አሰኝቶ ‘ቴረር ቢጤ አይለቅባቸውም! ለቀበሌው ዘብ የሰው ንብረት የማበላሸት ‘ጉልበት'… ያፀደቀለት የፀጥታው ምክር ቤት ነው?
ምን ግርም ይልሃል አትሉኝም… ለምንድነው ‘ኮምፕሌይን' ባደረግን ቁጥር… የግድ ‘የጀርባ አላማ' የሚፈልገው? “ስራችሁ አላማረኝም” ለማለት የግድ ‘ብክኪ' መኖር አለበት!! እናስ “አሁንስ ለማን አቤት ይባል!” የሲ.ኤን.ኤን ላሪኪንግ ድምፅ ቀነስ አድርጎ… ‘ከአጥር ውጪ የምንጮኸው እኛን መስማት ግድ ነው፡፡ የምር… በተለይ እራሳቸውን መከላከል የማይችሉ ሰዎች…‘ጉልበት መፈተኛ' ሲሆኑ አያሳዙንዋችሁም!
አንድ ሁለት ወር ገደማ ይሆናል፡፡ ሴትዬዋ ጠዋሪ ቀባሪ የሌላቸውን በጣም የደከሙ አሮጊት ናቸው፡፡ በአሮጌ ሳህን ሀያም የማይሞላ ሙዝ አድርገው መንገድ ዳር ተቀምጠዋል፡፡ አንድ ‘የስነስርአት አክባሪ' ልብስ የለበሰ የሚመስል ሰው መጣና ሳህናቸውን በእርግጫ መትቶ ሙዙን በተነባቸው፡፡ እናላችሁ ልክ መቶ ጋሻ የማያጠጣ ቦይ የቀደደ ይመስል በትእቢት ተነፋፍቶ መንገዱን ቀጠለ፡፡ ተላላፊዎች ሙዙን ሲሰበስቡላቸው… አሮጊቷ ምንም ሳይንቀሳቀሱ እንባቸው ኮለል ይል ነበር፡፡ የሚማቸው የለም እንጂ “ለማን አቤት ይባል!” እያሉ ነው፡፡
እኔ የምለው… ዘቡ ንብረታቸውን በእርግጫ በትኖ አለጠያቂ የሄደበት ‘የነፃነት ስሜት' አያስፈራቸውም፡፡ ወይ “የማሳርፍበት ልጣ!” የሚል አይነት የሚወዘውዘው ዱላ ሲሰጡ… የ“ስትፈልግ ቅደድ… ስተፈልግ እርገጥ…” ልዩ መብት ተሰጥቶታል እንዴ!
‘በደንብ ልብስ' ሽፋን… ‘ጉልበተኝነት' እንዳልታየ ሲያልፍ… አለ አይደል… “ጉልበተኝነት እንማን ጋር ሲደርስ ነው የሚቆመው?” ትላላችሁ፡፡ አሀ ልክ ነዋ… አለበለዚያ ‘አርጩሜ የሚያዝብን' ይበዛና… መመለሻ አይኖረወም፡፡
እኔ እምለው… ዘንድሮ'ኮ ጡንቸኛ መስሪያ ቤቶች… ‘ጉልበተኛ' ያደርጋቸዋል፡፡ “ይሄ ሰው የሚሆነው ምንድነው?... አቅም አለው ወይ?... የቤተሰቡ ኑሮ አይናጋም ወይ?” ብሎ በሚጠይቅ የለ፡፡ ብቻ በዚህም በዛም “አምጣ…” “ጨምር…” እንደገና “ጨምር…” ነው፡፡ ይሄኔ ሰው በየኮሊደሩ ሆነ በሚፀልይበት ቦታ “ለማን አቤት ይባላል?” ይላል፡፡  ምን ይደረግ… ሰሚ የለ! ‘ማሳመን' … እንኳን የለም፡፡ በቃ “ወይ ክፈል… ወይ ዞር በል” አይነት ነገር ነው፡፡
ስሙኝማ… በቴሌቪዥን እንኳ አቤት እንዳንል… የኛ ቴሌቪዥን ለ‘እኛ ብቻ' ነው የተተወው፡፡ አሀ… ‘ውሳኔ ሰጪዎች' በ‘ዲሽ' ነዋ አለምን የሚቃኙት፡፡ እንደውም ሃሳብ አለኝ… በቃ ብሶታችንን ሁሉ ሄደን ለላሪ ኪንግ እንንገረው፡፡ ልክ ነዋ… ‘አለቆች' እንደኛ “የላንጋኖ ሃይቅ…” የ“ሰሜን ተራራዎች…” አይነት ‘ሚዩዚካል' [ቂ…ቂ…] የለባቸውም፡፡ ስለዚህ በላሪ በኩል “ለማን አቤት ይባላል…” የሚል እየበዛ ስለሆነ መላ ፈልጉ ይባልልን፡፡
ሶስት ቀን ቢሆነን ነው፡፡ ሚኒባሱ ሶስት ሰከንድ እንኳን ሳይቆም አንድ ተሳፋሪ አውርዶ ሲንቀሳቀስ ከቆመበት የሚንቀሳቀስ መኪና መንገድ ይዘጋበት እና ሊያሳልፈው ቆም ይላል፡፡ ብዙም እንደ ጆሴፍ እስታሊግ ሪዝ የለውም እንጂ መኮሳተሩ እሱን የሚያስመስለው የ‘ፓርኪን' ሰራተኛ “ቆመሃልና ልክፈል አለው፡፡ አሽከርካሪ… ረዳቱ… ፊት የተቀመጡ ተሳፋሪዎች ሊያስረዱ ሞከሩ፡፡ ወይ ፍንክች፡፡ ሾፌሩ ለረዳቱ ምን አለው መሰላችሁ “ንጉሱ እሱ ነውና ስጠው፡፡” እንዲህ አይነቱ ሰራተኛ ነገር ማርሽ ለማቀዝቀዝም ጎተት ያለ ታክሲን “ቆመሃልና ክፈል…” ቢል ‘ለማን አቤት ይባላል፡፡'
እናላችሁ… በየደረጃው የደንብ ልብስ የለበሰ ‘ቆመጥ የያዘው' ለአምስት ሰው የሚባቃ ቆዳ ወንበ “የሚንጪለለው” “ተቀባይነት ያለው የኔ ቃል ብቻ ነው…” በሚል እንደ ልቡ ሲሆን… እኛ የዜግነታችን ደረጃ እየወረደ የመጣው “ለማን አቤት ይባል!” በንል ምን ይገርማል! ነው… መናገራችን አንሶ ለመደመጥ ጆሮ በሊዝ እንስጥ!
ደና ሰንብቱልኝማ!




በቻይናዎች ዘንድ የሚታወቅ አንድ ተረት አለ፡፡ አንድ ብልጥ ብርቱካን - አዟሪ አመቱን ሙሉ ያጠራቀመውን ብርቱካን ባወጣ ሰዓት ሰው ሁሉ እንደጉድ እየተሻማ በእጥፍ ዋጋ ይገዛዋል፡፡ ብርቱካን ለመግዛት የሚሻማውን ሰው ያስተዋለ፤ አንድ፤ የከተማውን ሀብት ዘርፈዋል በመባል የሚታሙ ትልቅ ሰው፤ ወደ ብርትኳን - አዟሪው መጥተው በርከት አድገው ይገዛሉ፡፡
ቤታቸው ገብተው ልጠው ሲበሉ ግን በእዛኞቹ ብርቱካኖች የበሰበሱና የደረቁ ሆነው ያገኙዋቸዋል፡፡ በዚህም ተናደው የበሰበሱትን ብርቱካኖች ይዘው ወደ ብርቱካን - አዟሪው ይመጡና፤
“ስማ የሚያማምሩ ብርቱካኖች ናቸው እያልክ ለአገሩ ሁሉ የሸጥካቸው ብርቱካኖች የበሰበሱ ሆነው አግኘሁዋቸው፡፡ እኮ ልበላቸው እንጂ ለአማልክት መስዋእት ላቀርባቸው አልገዛሁዋቸውም!”
ብርቱካን - አዟሪው፤
“እኔ እንግዲህ ለአመታት የኖርኩት እነዚህን አይነት ብርቱካኖች በመሸጥ ነው፡፡ ማንም ደምበኛዬ አጭበረበርከኝ ብሎኝ አያውቅም፡፡ ለመሆኑ በእኔ ላይ ስህተት ፍለጋ የተነሱት እርሶ ራስዎ ማነዎት? እስከዛሬ ሲበሉት የኖሩት ብርቱካን ዛሬ እንዴት መበስበሱ ታየዎት? ብዙ ትላልቅ የሚመስሉ ሰዎች ከተማችንን ለአደጋ እያጋለጧት ነው፡፡ የሚያስታርቁ መስለው የሚያጣሉ ሽማግሌዎች አሉ፡፡ መዝባሪዎችን የሚያወግዙ ግን ራሳቸው መዝባሪ የሆኑ የተከበሩ ሰዎች አሉ፡፡ በሚያማምሩ ፈረሶች ላይ የሚቀመጡ በየጉራንጉሩ ጥፋት ሲያደርሱ የሚገኙ በርካታ ሰዎች አሉ፡፡ በአጠቃላይ የእኔን ብርቱካን የሚመስሉ ብዙ ሰዎች ሞልተዋል፡፡ እነዚያ ትላልቅ ሰዎች ማጋለጥ ሲገባዎት ወደ እኔ ትናንሽ ብርቱካች መምጣትዎ ተገቢ ነው? አንድ ነገር ልብ ይበሉ፡፡ በሰው ላይ ጥቃቅን ስህተት ሲፈልጉ የራስዎን ተራራ የሚያህል በደል እንዳያጋልጡ ይጠንቀቁ! ከተማችን እስከዛሬ የኖረችው በዚህ ዘዴና ጥንቃቄ መሆኑንንም አድርሱ” አላቸው፡፡ ትልቁ ሰው ነገሩ ገብቷቸው፤ የበሰበሱትን ብርቱካኖች ይዘው ድምፃቸውን አጥፍተው ወደቤታቸው ተመለሱ፡፡   
***
የትናንሽ ሰዎች ስህተት በማሳየት የራሳቸውን አሣር የሚህል ጥፋት የሚሸፋፍኑ ትላልቅ ሰዎች ያሉባት አገር ወደ ብልፅግና ሳይሆን ወደ ከፋ ድህነት መሄዷ አሌ አይባልም፡፡ እንዲህ ያለ ሽፍጥ የተጠናወታት አገር ልማቷ ልፋት ይሆንባታል፤ “ሣር ስትፈልግ ውላ አሣር የማያጋጥማት” ትሆናለች፡፡ ለስህተታቸው ምሁራዊ መጎናፀፊያ የሚያጠልቁ፤ ውስጡን - ለቄስ መሆናቸውን በታዋቂነት ካባ በመሸፈን የሚኖሩ፤ እስከጊዜው አዎን አዎን ይላሉ እንጂ አገርን ለፍሬ፤ ህዝብን ለተደላደለ ኑሮ አያበቁም፡፡ እንቅፋትም ሲመታቸው “ፖለቲካ ድረሽ!” የሚሉና ለወደቀው ዕቃ ሁሉ ፖለቲካን ዋስ የሚያደርጉም በልቶ ለማደርና የሰላም እንቅልፍን ለሚመኝ ህዝብ ፋይዳ አይፈይዱለትም፡፡ የሚያወሩ አፎች እንጂ የሚሰሩ እጆች የላቸውምና!
“ቄስ ካናዘዘው እድሜ ያናዘዘው ይበልጣል” ይሏልና ሀገራችን ካሳለፈቻቸው ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ሂደቶች አያሌ ነገሮችን አይታለች፡፡ ከባለአፍ ባለጤግ፣ ከባለሰይፍ ባለእርፍ፤ እንደሚበጃት አስተውላለች፡፡ ከድንፋት ብልሃት እንደሚበጃት ተገንዝባለች፡፡ ከጡጫ ምንጫ እንደሚሻላት አውቃለች፡፡ በሸንጎ ከሚወራረፋና በዐላማ ከሚጠላለፍ የፖለቲካ መሪዎች ይልቅ፤ ከልብ የሚወቃቀሱ፣ መልካም ስራን የሚያወድሱ ግልፅ መሪዎች እንደሚያድኗት አጢናለች፡፡ ከለበጣ አስብሰባና እሰጥ -አገባ ይልቅ አጎንብሶ አፈሯን መማስና ፍሬዋ ማፈስ፤ አውሎ እንደሚያሳድራት ጠንቅቃ አውቃለች፡፡ ከሁሉም በላይ የሚናገሩለት ሳይሆን የሚናገር፣ በስሙ የሚሰራለት ሳይሆን ራሱ የሚሰራ ህዝብ እንዲሚኖራት ማስፈለጉን ከታሪክም፣ ከተግባርም ተምራለች፡፡
ያለንበት ወቅት ወሳኝ ነው- በፖለቲካዎችም በኢኮኖሚያዊም ገፁ፡፡ መፈክሮች አፍአዊ ሳይሆኑ ልባዊ መሆናቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡ የወቅቱ ጥሪዎቻችን (order of the day) በአግባቡ የታመነባቸው መሆን እዳለባቸው ሁሉ ተግባራዊ ትርጓሜያቸውም የህሊና ታማኝነትንና ልባዊ ፅናትን ይጠይቃ፡፡ ዲሞክራሲያዊነትን ከዲፕሎማሲያዊነት ጋር በብስለት ማቀናጀትን ወቅቱ ግድ ይላል፡፡ ያም ሆኖ በዲፕሎማሲያዊነት ስም ማጎብደድና እጅ - መስጠት እንደማይገባ ሁሉ፤ “ድርድር ለምኔ” ብሎ በልሂቅ በደቂቁ ላይ ዘራፍ ማለትም ፍፁም አደገኛ ነው፡፡ ብዙ በጮህን ቁጥር የተደመጥን መምሰሉ ለግብዝነት እንዳይዳርገን ሰብሰብ ብሎ  ማሰብ ተገቢ ነው፡፡

ደረጃው ይመጥንም አይመጥንም የጥያቄ  መብዛትና፤ በስብሰባ ያለመርካት ጉርምርታ ቢያይል፤ እውነትነቱን ተገንዝቦ በሆደ-ሰፊነት መቀበል የመልካም አመራር መለኪያ ነው፡፡ የሃያላን መንግስታት ጫና ብራኳችንን መስበር የለበትም፡፡ የእነርሱ መልእክተኞችና ጉዳይ አስፈፃሚ መሆም ወደራስ ህልውና መሸርሸርና ከተረጂነት ወደ ፍፁመተ ተገዢነት (absolute servitude) ወደ መሸጋገር እንዳይዘልቅ ማመዛዘን ያባት ነው! የምናወሳው ግልፅነተ ፣ ከግልብነት እንዳይምታታ ከአፋችን የማይጠፋው ተጠያቂነት ከተጠቂነት ጋር እንዳይደባለቅ መጠንቀቅ በጣም ተገቢ ነው፡፡ የተደከመበት ሁሉ ፍሬው ሳይታይ ሌላ አዲስ እቅድ በላይ በላዩ በማከል አንዱም ሳይጨበጥ ቀርቶ የወረት ልማት እንዳየሆን በቅርብ መከታተል ይገባ፡፡ አለበለዚያ “መሞኝ ጠምቃ አስቀም፣ ውሃ ትጠጣለች” እንደሚባው እዳይን መጀመራችንን እያወደስን፣ መጨረሻችንን ሳናስረግጥ እንዳንቀር ልብ ብሎ መጓዝ ያሻል፡፡ እሺ እሺ የሚሉ አያ ናቸውና ሀሳዊውን እሺታ ከእሙናዊው እሺታ መለየት ያስፈልጋ፡፡


ከቶውንም ግትርነት ለማንም አይበጅም፡፡ ጊዜንም ቦታንም ሳያስተውሉ ግትር መሆን ከግብዝነት አይለይም፡፡ ስናስተምር እየተማርንም መሆን አለበት፡፡ ሹም፤ ዜጋ የሚሆንበት ጊዜ እንዳለና ዜጋም ሹም የሚሆንበት ሰአት እንደሚኖር ማስተዋል ደግ ነው፡፡ ተለዋዋጭ ሂደቶች ተለዋዋጭ ክስተቶችን ሊያመጡ እንደሚችሉ ከልብ ማመን ለመቻቻል ችግሮችን በውይይት ለመፍታትና ፅንፈኛ-አክራሪነትን ለመግታት ያመቻል፡፡ ለምንም ነገር ግንባራችንን አናጥፍም ብሎ መፈጠም አላግባብ አቅም ይፈጃል፡፡ ብልሃትን ያመነምናል፡፡ በባዶ ሜዳ ዘራፍን ያበዛል፡፡ ትንፋሽ ይጨርሳል፡፡ የመንገኝነት ስሜት የሚጎዳንን ያህል የጀሌነት ስሜትም በሳል-እይታን (critical) ይጋርዳል፡፡ የየግል እድገትን ያቀጭጫል፡፡ የመሪነት ክህሎት (leadership quality) እንዳይኖረን ያደርጋል፡፡ እነዚህን ሁሉ በአግባቡ መርምረን በአግባቡ ለመጠን መገኘት ያሻል፡፡ በዚህኛው ዘመን አንድ እርምጃ ለመራመድ እንዳንችል የሚደርጉ ከአመት አመት የማይለወጡ፣ በትልቅነት ካባ ትንንሾችን እያወገዙ የሚኖሩ ከእድሜ እድሜ ቅንጣት የማይሻገሩ ቢቀሰቅሷቸው የማይነቁ ቢጭሩባቸው የማይነዱ እንደነበሩ ያሉ ግለሰቦች ቡድኖችና ፓርቲዎች ከቶም ለለውጥ ጋሬጣ ናቸው፡፡ ለእድገት እንቅፋት ናቸው፡፡ ለመረጃና ለእውቀትም የተዘጋ በር መሆናቸው ይታወቃ!
ያም ሆኖ በየአደባባዩ - አውቃለሁ ተምሬያለሁ፣ በቅቻለሁ፣ ስሜና ማዕረጌ የስራዬ ምስክር ነው የምናገረው ቢገባወም ባይገባውም ህዝብ ሊከተለኝ ይገባል እያ መድኩን ባገኙና፣ የቴሌቪዥን “ካሜራ - ማን” ባውዛ ባዩ ቁጥር እየተስተካከሉ ብዙ ብዙ ማውራትን የማይታክቱ መበርከታቸው ዛሬ ገሀድ ነው፡፡ ዞሮ ዞሮ ግን ድርጊታቸው “ገበሎ ራሱን ሲነቀንቅ ንግግ የሚያውቅ ይመስላል” ከሚለው ተረት አይዘልም፡፡
 

 በሻለቃ አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ የህይወት ፍልስፍና መነሻነት የተሰናዳውና ስለ መለወጥና ለመለወጥ ስለ ሚያስፈልጉ ዘርፈ ብዙ ቁርጠኝነቶች የሚያትተው “ሆኖ መገኘት” መፅሀፍ ለንባብ በቃ፡፡ ከኢትዮጵያ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት እውቅናናፈቃድ ባለው በሆቴል ማኔጅመንት ከፍተኛ ብቃትባለውና በስትራቴጂ ልማት ብሎም በተቋማዊአመራር ከፍተኛ ልምድ ባዳበረው እንዲሁም በሀይሌሆቴሎችና ሪዞርቶች አመራር ብቃቱ አንቱታንባተረፈው መልካሙ መኮንን እና በተቋማዊ ልማትእንዲሁም በዘላቂ የትምህርት ዘርፍ ባለራዕይ መሪበሆነው ፋሲል መንግስቴ የተሰናዳው ይሄው መፅሀፍመለወጥ ለሚፈልጉ ባለ ሀሳቦች እጅጉን ጠቃሚእንደሚሆን ሻለቃ አትሌት ሀይሌ ገብረ ስላሴበመፅሀፉ ጀርባ በሰጠው የጀርባ ማስታወሻ ገልጿል፡፡ “ምንም እንኳ የመጽሀፉ መነሻ ሀሳብ ከእኔ የህይወትፍልስፍና የተቀዳ ቢሆንም እኔ ግን እንደሌላ ሰውሆኜ ነው ያነበብኩት እኔ በግል ህይወቴ የምኖራቸውየህይወት መርሆዎችና ፍልስፍናዎች በተለያዩ ቢዝነሶች ውስጥ ሊተገበር የሚችል የፍልስፍናመፅሀፍ እንደመነሻ ሀሳብ ሆነው መቅረባቸው ታላቅ የደስታ ስሜት ጭሮብኛል……፡፡ ይህ የደስታስሜት የሚመነጨው ከተራ ግብዝነት አይደለምይልቁንም እንደ ሀገርና እንደህዝብ መድረስ ይገባን ነበር እያልኩ የምቆጭባቸው ብዙ ነገሮች ስላሉ ነው፡፡

እንደ ሀገርና እንደ ህዝብ የምንኮራባቸው በርካታ ሀብቶች ቢኖሩም ልናስተካክላቸውና ልናርማቸውየሚገቡን ደግሞ ብዙ ጉዳዮች ወይም “ቢሆን”የምለውን ምኞቴን በዚህ መፅሀፍ አይቻለሁ…”በማለት አስተያየቱን ሻለቃ አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴአስፍሯል፡፡ በሀይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች በሁሉምቅርንጫፎች የሚሰጠው ወጥ እና ተመሳሳይየአገልግሎት ጥራት “እኔም ሀይሌ ነኝ”….. ይቻላልበሚል መርህ ላይ የተመሰረተና በአገር ልጅ ችሎታናብቃት ላይ የተመሰረተ ፍልስፍና መሆኑ እንደሀገር ተግባር ላይ ሊውል የሚገባው ትልቅ ተግባርመሆኑም በመፅሀፉ ተካትቷል፡፡በ5 ምዕራፍ ተከፋፍሎ በ198 ገጽ የተቀነበበው“ሆኖ መገኘት” መፅሀፍ በ350 ብር ለገበያ የቀረበ
ሲሆን በቅርቡ ለምርቃት እንደሚበቃም ከደራሲያኑእና “ከእሺ” ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃያመለክታል፡፡ የመፅሀፉ አርታኢ ደግሞ ደራሲና
ጋዜጠኛ ደሳለኝ ስዩም መሆኑም ታውቋል፡

በመንግስትና በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት መካከል በዳሬ ሰላም ሲካሄድ የነበረው ድርድር እንዳይሳካ የተደረገው በመንግስት ነው ሲሉ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንደኦ ገለፁ፡፡ መንግስት በሁለቱ ወገኖች መካከል የተፈጠረውን ችግር በውይይት ለመፍታት ፍላጎት የለውም
ሲሉም ለቢቢሲ በሰጡት ቃለ ምልልስ ላይ ተናግረዋል፡፡


የሰላም ሚኒስትር ዴኤታና የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት (ጨፌ) አባል የሆኑት አቶ ታዬ ደንደአ ከትናንት በስቲያ ከቢቢሲ አፋን
ኦሮሞ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለፁት፤ በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለው ችግር በሰላም እንዲፈታ ከተወሰነ በኋላ በመንግስት በኩል ድርድሩ እንዳይሳካ ተደርጓል ብለዋል፡፡ በሁለቱ ዙር ውይይቶች ተስፋ ሰጪ ሁኔታዎች ታይተው እንደነበር ያመለከቱት አቶ ታዬ፤ “የኦሮሞ ነፃነትሰራዊትን የሚመራው ድሪባ ኩምሳ (ጃልመሮ) ለሰላም ካለው ቁርጠኝነት የተነሳ መንግስት ከፈለገ እርምጃ ይውሰድብኝ ብሎ
በመንግስት ቁጥጥር ስር በሆነው የአየር ክልል ውስጥ አልፎ ወደ ታንዛኒያ የሄደ ቢሆንም በመንግስት በኩል ግን ለሰላምና ችግሮችን በውይይት ለመፍታት ፍላጎት አልታየም” ብለዋል፡፡ የሰላም ድርድር ጉዳይ በሰላም ሚኒስቴር በኩል የሚከናወን መሆኑ በህግ የተሰጠ የስራ ሃላፊነት መሆኑን 
ያመለከቱት አቶ ታዬ፤ እኛ በማናውቀው ሁኔታ በሰላም ድርድሩ ከሰላም ሚኒስቴር ይልቅ የፍትህ ሚኒቴር ተሳታፊ እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል፡፡

ከህውሃት ጋርም ሆነ ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር በሁለት ዙር በተደረገው የሰላም ድርድር መስሪያ ቤታቸው የሰላም ሚኒስቴር አለመሳተፉንም

አመልክተዋል፡፡
በመንግስትና በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት መካከል የመጀመሪያው ዙር ድርድር ሲካሄድ ገብረጉራቻ ከተማ ውስጥ ህዝቡን በማወያየት ላይ እንደነበሩ

ያመለከቱት አቶታዬ፤ ህዝቡ የሰላም ድርድሩ በሰላም ተጠናቆ እፎይታን እናገኛለን የሚል ትልቅ ተስፋን ሰንቆ እንደነበር ገልፀው፤ በመንግስት በኩል
የሰላም ድርድሩ እንዲደናቀፍ ተደርጓል ብለዋል፡፡“እኔ ያለሀብት መንግስት ችግር ውስጥ ነን፣ ተወያይተን መፍትሄ እናመጣለን ብዬ ስጠይቅ ቤቱ ለውይይት ክፍት አይደለም፡፡ በማምታታትና በማደናገር ማለፍ ነው የሚፈልገው፡፡
የእኔ መንግሰት እንዲህ አይነት ፀባይ ነው ያለው” ሲሉ በቃለምልልሱ ወቅት ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በመንግስት ውስጥ ሙስና እና ብልሹ አሰራር በከፍተኛ ሁኔታ መንሰራፋቱን የገለፁት የሰላም ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ታዬ፤ ድሮ መሬት ይዘረፋል ከሚባለው በላይ አሁን ህጋዊ ሆኖ በቃላት መግለፅ በሚከብድ መልኩ እየተዘረፈ ከፍተኛ የአስተዳደር ቀውስ ፈጥሯል ብለዋል፡፡በአገሪቱ አሁን ለተፈጠረው ችግር መንግስት ትልቅ ተጠያቂነት አለበት ያሉት አቶ ታዬ፤ ራሳቸውም ቢሆኑ ለተጠያቂነት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡የሰላም ሚኒስትር ዴኤታው በዚህ ቃለ ምልልሳቸው ማጠቃለያም፤ ታጥቆ የሚታገለውም ሆነ አገር እያስተዳደረ ያለው መንግስት ችግሮቻቸውን በውይይት ለመፍታት ጥረት ማድረግ እንደሚገባቸው ጠቁመው፤ “ህዝቡ ከሚፈለገው በላይ ዋጋ ከፍሏል፤ ከዚህ በላይ ዋጋ እንዲከፍል መደረግ የለበትም፤ ለህዝቡ
ስትሉ ችግሮቻችሁን በውይይት ብትፈቱ መልካም ነው” ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የዐማራ ባንክ የዲሬክተሮች ቦርድ፣ ዋና ሥራ አስፈጻሚውን አቶ ኄኖክ አበበ ታደሰንና የኮርፖሬት አገልግሎት ዋና መኰንኑን አቶ ክንዴ አበበን፣ በአፈጻጸም ድክመት ከሓላፊነታቸው አነሣ።

የባንኩ ቦርድ ውሳኔውን ያሳለፈው፣ ዛሬ ዐርብ፣ ኅዳር 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ሲኾን፣ ኹለቱም ከፍተኛ ሓላፊዎች፣ ከተሾሙበት ዕለት ጀምሮ፣ በየጊዜው በሚሳዩት የሥራ አፈጻጸም ድክመት፣ የባንኩን ስትራቴጂያዊ ግቦች እና ቁልፍ የአፈጻጸም መመዘኛዎች ለማሳካት ያልቻሉና የማያስችሉ ናቸው፤ በሚል፣ ከሓላፊነታቸው እንዲነሡና ከባንኩ እንዲሰናበቱ መወሰኑን፣ ለኹለቱም በየስማቸው በአደረሳቸው ደብዳቤ አስታውቋል።

በ2014/15 ዓ.ም. ባንኩ ከ306 ሚሊዮን ብር በላይ ትርፍ ለማስመዝገብ ዐቅዶ የነበረ ቢኾንም፣ 460,286,000 ብር  ኪሳራ በማስመዝገብ፤ በሌላቸው ሥልጣን ባሳለፉት አስተዳደራዊ ውሳኔ፣ ከ89 ሚሊዮን በላይ ብር እንዲከፈል በማድረግ፣ የባንኩን ካፒታል ለብክነት የመዳረግ አደጋ ውስጥ በማጋለጣቸውና ሌሎችንም አጠቃላይ የአፈጻጸም ድክመቶችን በአስረጅነት የጠቀሰው የዲሬክተሮች ቦርዱ፣ ሓላፊዎቹ በቦታቸው መቀጠል እንደማይችሉ ገምግሞ አንሥቷቸዋል።

ከሓላፊነታቸው በተነሡት አቶ ኄኖክ አበበ ቦታ፣ የባንኪንግ አገልግሎቶች ከፍተኛ መኰንን አቶ ጫን ያለው ደምሴ፣ ከነገ ኅዳር 29 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በጊዜያዊነት የዋና ሥራ አስፈጻሚነቱን ቦታ  ደርበው እንዲይዙ እንደመደባቸው ታውቋል።

የቢኒያም ወርቁ "ትራንዚት" ትያትር ሊመረቅ ነው
የመግቢያ ዋጋ 1,000 ብር
በአይነቱ ልዩ የሆነው የቢኒያም ወርቁ "ትራንዚት" ትያትር ታሕሳስ 4/2016ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰአት ጀምሮ በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ሊመረቅ እንደሆነ አሜዜንግ ፕሮሞሽንና ኢቨንት ዛሬ ሕዳር 28/2016ዓ.ም በሃገር ፍቅር ቴአትር ቤት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል ።
አሜዚንግ ፕሮሞሽንና ኢቨንት ዳግም እየተናነቃቃ ያለውን የሀገራችንን የመድረክ ቴአትር ወደላቀ ከፍታ ለማሻገርና የተመልካቹን ፍላጎት ለማርካት በማሰብ በሀገራችን የትወና ታሪክ በተለይም አሁን ባለንበት ዘመን እጅግ ተወዳጅ የሆኑትን ተዋንያን
ሰለሞን ቦጋለ
ሳምሶን ታደሰ(ቤቢ)
* ሃና ዮሐንስ
* ሸዋፈራሁ ደሳለኝ በአንድ መድረክ የሚያሳትፍ ሲሆን የዚህ ትያትር
*ፕሮዲዩሰር= አሜዚንግ ፕሮሞሽንና ኢቨንት
*የክብር አጋር =ፀደይ ባንክ
*ደራሲና አዘጋጅ =ቢኒያም ወርቁ ነው።
የ"ትራንዚት ትያትር አጽመ-ታሪክ (SYNOPSIS) እነሆ
ካልደነገጥክ አትሰራም!
ካልሰራህ አትተባበርም!
ካልተባበርክ አታሸንፍም!
በጊዚያዊ ችግር አብሮነት ፍቅር ተስፋ እና የአላማ ጽናት ቢፈተንም እጅ ለእጅ በመያያዝ በየትኛውም መስክ አብሮ በጋራ በመቆም ሁሉንም ችግር ማሸነፍ እንደሚቻል የሚሳይ ትያትር ነው ።
የታሪክ ውቅር፤ ... የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍና የመጨረሻውን ጨዋታ ለማድረግ ወደ ቱኒዝያ ለመሄድ የ12 ሰዓት ትራንዚት ጣልያን ላይ ያደርጋል፡፡ እኩል መውጣት አልያም ማሸነፍ ብድኑን ያሳልፈዋል፡፡
የትያትሩ መቼት ላይ ...
ጣልያን ላይ አራት ተጫዋቾች ከቡድኑ ተነጥለው ይጠፋሉ፡፡ ሌሎች ተጫዋቾችም ሊጠፉ እየተዘጋጁ መሆኑ ተስፋ አስቆራጭ ስሜት ይፈጥራል፡፡ ከሚጠፉት ተጫዋቾች መካከል የቡድኑ አምበል ሲሳይ ረጋሳ ከቡድኑ አጥቂ መንሱር ጋር አንድ ክፍል ተጋርተዋል፡፡ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮቻችን ለስደት ምክንያት ሆነው ከአገራዊ ኃላፊነትና ከሀገር ፍቅር መስዋዕትነት ጋር በትያትሩ ይጋጠማሉ፤ ይፈተናሉ፡፡
የቡድኑ አምበል ሲሳይ ረጋሳ የቡድኑ አጥቂ መንሱር ከ40 ዓመት በፊት በአፍላ ወጣትነታቸው በፖለቲካ ስደተኝነት አውሮፓ ሄደው በሆቴል ውስጥ የፀጥታ ሠራተኛ የሆኑት ሻምበል ሺመላሽ፣ የኢኮኖሚ ስደተኛና የመንሱር የልጅነት ፍቅረኛ ንግሥት፣ በአካል መድረክ ላይ የምናያቸው ሲሆን የመንሱር ጎረቤት እርጊቲ፣ የሲሳይ አባት አቶ ረጋሳ፣ የንግሥት እናት እና አባት፣ የሻምበል የስደት ጓደኞች እንዲሁም የአዲስ አበባ አንድ አካል የሆነችው የቄራ መንደር ሕዝብ የዋናዎቹን ገፀ ባሕሪያት ያህል ሀሳባቸው፣ ሕይወታቸው፣ ፍልስፍናቸውና ትግላቸው በጥበባዊ እይታ ተተንትኖ ይቀርባል፡፡
መደምደሚያ
"ትራንዚት" ትያትር - በጥልቅ ፆታዊ ፍቅር በቤተሰብ መሰረት እና በልጆች አስተዳደግ እንዲሁም በየዘመኑ ያሉ የፖለቲካ አስተሳሰቦችና ሂደቶች በሳቅ እና ቁም ነገር እየተዋዛ የሚቀርብበት ትያትር ነው፡፡
የ"ትራንዚት ትያትር ደራሲና አዘጋጅ - ቢኒያም ወርቁ
ማነው?
በአሁን ሰዓት የኢትዮጵያ ትያትር ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት በመሆን በማገልገል ላይ ይገኛል።
በኢትዮጵያ የትያትር እና የፊልም ታሪክ ውስጥ በስፋት ከሚጠቀሱ ባለሙያዎች ይመደባል፡፡ በርካታ ፊልሞች ጽፏል፤ አዘጋጅቷል፤ በፊልሞቹም ላይ ተውኗል፡፡በተጨማሪም በትያትር ሥራዎቹም እናውቀዋለን፡፡
ደራሲና አዘጋጅ ቢኒያም ወርቁ፤ ከትያትር ሥራዎቹ መካከል ሜዳሊያ፣ የአልማዝ ቀለበት፣ ዱር ያደረ ፍቅር፣ ማን ለምን፣ ማበዴ ነው፣ መብረቅ ከበርካታ የመድረክ ሥራዎቹ መሃል ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
ከአርባ በላይ ከሆነው የፊልም ድርሰት እና ዝግጅት ሥራዎቹ ደግሞ አዲስ ሙሽራ፣ የትሮይ ፈረስ፣ ቫኬሽን ፍሮም አሜሪካ፣ የፍቅር መንገድ፣ 7ተኛው ሰው እና ሌሎችም በየዘመናቸው የበርካታ ሸልማት ባለቤቶች ናቸው።
 
Thursday, 05 October 2023 00:00

ሠዓሊ መዝገቡ ተሰማ

በ1972 ዓ,ም አራት ኪሎ በሚገኘው አለ የሥነ ጥበባት ትምህርት ኮሌጅ በዲፕሎማ ተመርቋል።
~በ1975 ዓ,ም በሩሲያ በሌኒን ግራድ ፔኒን የሥነ ጥበብ አካዳሚ ከአለማችን ታላላቅ ሠዓሊያን
ጋር ለ5 አመት ተምሮ በከፍተኛ ማዕረግ በማስተርስ ኦፍ ፋይን አርትስ ተመርቋል።
መዝገቡ ተሰማ ከ 40 አመት በፊት ጀምሮ በቡሩሹ የከተባቸው ሥዕሎቹ የኢትዮጵያን መልክአ ምድራዊ ገፅታዎች የሚያንፀባርቁ ናቸው።ምክንያቱን ሲጠየቅ የሚሰጠው ምላሽ ደግሞ እኔ የምስለው የማውቀውን የሀገሬን ትውፊታዊ አኗኗር ነው የሚል ነው።
~ በ1985 ዓ,ም በብሄራዊ ሙዚየም የመጀመረያውን ~በ1996 ዓ,ም በአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሲስ
~በ2004 ዓ,ም በብሄራዊ ሙዚየም "ንግስ" የተሰኘው አውደ ርዕይ እንዲሁም
~በ2008 ዓ,ም "የአዲስ አበባ ልጅ"የተሰኘውን የስዕል አውደ ርዕዩን አሳይቷል።