Administrator

Administrator

ቶሞካ ቡና ኃ.የተ.የግል.ማህበር በንኮማድ ኮንስትራክሽን ኃ.የተ.የግል ማህበር (ደንበል ሲቲ ሴንተር) ላይ የ48.2 ሚሊዮን ብር ክስ መመስረቱ ታወቀ፡፡
ከሳሽ ቶሞካ ቡና ጥር 7 ቀን 2011 ዓ.ም ስፋቱ 137 ካሬ ሜትር የሆነውንና በደንበል ሲቲ ሴንተር ህንፃ ላይ የሚገኘውን ቦታ እስከ ጥር 6 ቀን 2021 ዓ.ም ለአስር ዓመት ለቡና መሸጫ ካፊቴሪያነት አገልግሎት ለማዋል ከንኮማድ ኮንስትራክሽን ጋር የኪራይ ውል መዋዋሉን የክስ ጭብጡ ያስረዳል፡፡ ከሳሽ በዚሁ ውል መሰረት በመጋቢት ወር 2011 ዓ.ም በተፈፀመ የግንባታ ውል ቦታው ለቡና መሸጫነት ምቹና ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን 1 ሚሊዮን 491 ሺህ 403 ብር ወጪ በማድረግ አድሶና አሳምሮ ስራውን መቀጠሉን ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ ልደታ ምድብ ችሎት፣ የውል ጉዳዮች ችሎት የቀረበው የክስ መዝገብ ያመለክታል፡፡
ይሁን እንጂ ተከሳሽ ጥቅምት 19 ቀን 2016 ዓ.ም በተፃፈ ደብዳቤ የኪራይ ውሉ መቋረጡን በመግለፅ  ካፌው የሚጠቀምበትን የኤሌክትሪክ የመብራት መስመር በማቋረጥና አገልግሎት እንዳይሰጥ በማድረግ በድርጅቱ ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ማድረሱን ከሳሽ ለፍ/ቤቱ ባቀረበው ክስ አመልክቷል፡፡
ተከሳሽ     ውሉን ያቋረጠባቸው ምክንያቶች ከህግና ከስነስርዓት ውጪ በመሆናቸውና ለኪሳራ ስለዳረገኝ ፍርድ ቤቱ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ተከሳሽ 48 ሚሊዮን 272 ሺህ 360 ብር እንዲከፍለኝ እንዲወስንልኝ ሲል መጠየቁን የክስ ዝርዝሩ ያስረዳል፡፡
በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡን በስልክ የጠየቅናቸው የንኮማድ ኮንስትራሽን ኃ.የተ.የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ አበበ መንገሻ “በስልክ ምንም አይነት ምላሽ አልሰጥም” በማለታቸው ምላሻቸውን ማካተት አልቻልንም፡፡

 (የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ጋዜጣዊ መግለጫ)

          የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)፤ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣በጉራጌ ዞንና በቀቤና ልዩ ወረዳ መካከል የነበረውን አለመግባባት ተከትሎ ጥቅምት 2 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ የተከሰተውን የጸጥታ መደፍረስና ያስከተለውን ጉዳት ከአካባቢው ነዋሪዎች በቀረበለት አቤቱታ መነሻነት ከጥቅምት 20 እስከ 25 ቀን 2016 ዓ.ም.በቦታው በመገኘት ጭምር ምርመራ ያከናወነ ሲሆን፣ አሁንም በአካባቢው ያለውን አጠቃላይ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታም በመከታተል ላይ ይገኛል፡፡ ኮሚሽኑ ከተጎጂዎችና ምስክሮች ጋር 22 ቃለ-መጠይቆች አድርጓል፤ ከጉራጌ ዞን፣ ከወልቂጤ ከተማ አስተዳደርና ከቀቤና ልዩ ወረዳ የሥራ ኃላፊዎች፣ በዞንና በልዩ ወረዳ ደረጃ ከሚገኙ የመንግሥት ኃላፊዎች እንዲሁም በአካባቢው የሚገኘውን የኮማንድ ፖስት ኃላፊዎችን አነጋግሯል፤ ከሃይማኖት መሪዎችና ከሀገር ሽማግሌዎች ጋር 2 የቡድን ውይይቶች አካሂዷል፡፡ በተጨማሪም ዘረፋና ውድመት ደርሶባቸዋል የተባሉ የግልና የመንግሥት ተቋማትን ተዘዋውሮ ጎብኝቷል፤ተጎጂዎች ሕክምና ካገኙባቸው የሕክምና ተቋማት ማስረጃዎችን ጨምሮ የተለያዩ የሰነድ ማስረጃዎችን አሰባስቧል።
በጉራጌና በቀቤና ማኅበረሰብ መካከል ከዚህ በፊትም የተለያየ መጠን ያለው ግጭትና የሰላም ስምምነት ጥረት የነበረ ሲሆን፤ በተለይ ከቀቤና የልዩ ወረዳነት ምሥረታ ጋር በተያያዘና የልዩ ወረዳው መቀመጫን በተመለከተ በሁለቱ ማኅበረሰቦች አስተዳደሮች መካከል አለመግባባቱ እየተካረረና የግጭት አደጋው እየጨመረ መጥቶ እንደነበር መረዳት ተችሏል።
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ፤ “በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች አሁንም ዘላቂ መፍትሔ ያልተሰጣቸው የመዋቅርና የአስተዳደር ጥያቄዎች ለሰላምና ደኅንነት እጦት እንዲሁም ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት ምክንያት ሆነው መቀጠላቸው እጅግ አሳሳቢ ስለሆነ፤ የፌዴራልና የክልል መንግሥታት ኃላፊዎች ቅሬታና ጥያቄ የቀረበባቸውን አካባቢዎች ሁሉ ተዓማኒ በሆነና ተቀባይነት ባለው ሂደት በማሳተፍ ዘላቂ መፍትሔ ሊያመቻቹ ይገባል” ብለዋል፡፡
ዋና ኮሚሽነሩ አክለውም፤ “በወልቂጤ ከተማ ጥቅምት 2 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ የተከሰተውን ሁከትና የደረሰውን ጉዳት በተመለከተ የክልሉና የፌዴራል መንግሥት በመቀናጀትና ተገቢውን ማጣራት በማድረግ ተጠያቂነትን ማረጋገጥና ተጎጂዎችን መካስ ይገባል” ብለዋል፡፡



‘Fly Now Pay Later’


 ዳሽን ባንክና የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ደንበኞች የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቅመው ክፍያውን ቆይተው የሚከፍሉበትን ‘ጉዞዎ ይቀድማል ክፍያው ይደርሳል’ የሚል  አዲስ የክፍያ አማራጭ በዛሬው ዕለት አስተዋወቁ።

የዳሽን ባንክ ዲጂታል ባንኪንግ ዋና መኮንን አቶ ዮሐንስ መኮንን እንደገለጹት፤ ‘ጉዞዎ ይቀድማል ክፍያው ይደርሳል’ የተሰኘው አዲሱ  የክፍያ አማራጭ  በደንበኞች ምርጫ መሰረት በ6 ወር ወይም በ12 ወር የብድር ክፍያ የሚሰጥ ነው፡፡

 ደንበኞች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆን በዳሸን ባንክ የሂሳብ ቁጥር መክፈት እንደሚገባቸውና በተጨማሪም በባንኩ ቢያንስ ለሦስት ወራት አገልግሎት ያገኙ መሆን እንደሚገባቸውም አመልክተዋል፡፡

አዲሱን አገልግሎት ለመጠቀም አንድ ደንበኛ አስፈላጊ ቅድመ-ሁኔታዎችን ካሟላ በኋላ በቅርንጫፉ የተፈቀደለትን የብድር መጠን የሚወስድ ሲሆን፤ የተፈቀደለትን ገንዘብ ለመጠቀም የሚያስችል የአንድ ጊዜ መለያ ቁጥር መልዕክትም በተንቀሳቃሽ ስልኩ የሚደርሰው ይሆናል። በመቀጠልም ደንበኛው የተሰጠውን መለያ ቁጥር በአየር መንገዱ የሞባይል መተግበሪያ ላይ በማስገባት ትኬት መቁረጥና የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ይችላል።

በሁለቱ ተቋማት ስምምነት በቀረበው በዚህ አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን የሚፈቀደው የብድር ገንዘብ መጠን እስከ ስድስት መቶ ሺ ብር የሚደርስ ነው። የሚፈቀደው ብድር ወለድ የሚታሰብበት ሲሆን፤ ይህም ደንበኛው በመረጠውና ብድሩን በወሰደበት የጊዜ ገደብ ከብድሩ ጋር አብሮ የሚከፈል መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና የንግድ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ለማ ያዴቻ በበኩላቸው፤ “የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኛ ተኮር አሰራርን እንደመከተሉ የተለያዩ ዘመናዊና ለመጠቀም ቀላል የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን እያስተዋወቀ ይገኛል። የምናበለጽጋቸው ቴክኖሎጂዎች ለደንበኞቻችን ምቹ መሆናቸው እንደተጠበቁ ሆኖ የአገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት ጋርም የተጣጣሙ እንዲሆኑ እናደርጋለን። ዛሬም አጋራችን ከሆነው የዳሽን ባንክ ጋር በመተባበር ለደንበኞቻችን ያቀረብነው አዲስ የክፍያ አማራጭ ተግባራዊ እንዲሆን የሞባይል መተግበሪያችን ከአዲሱ የክፍያ አገልግሎት ጋር የተቀናጀ እንዲሆን አድርገናል” ብለዋል።

ደንበኞች የተፈቀደላቸው የብድር መጠን ሲያልቅ ማደስ የሚችሉ ሲሆን፤ በአንዴ የወሰዱትን ብድርም ለተለያዩ በረራዎች ከፍለው መጠቀም እንደሚችሉ ታውቋል፡፡  አገልግሎቱ በተለይም በንግድ ስራ ላይ ለተሰማሩ፣ ለጅምላ አስመጪዎችና ለዕረፍት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ ውጭ ለሚሄዱ ደንበኞች አመቺ ነው ተብሏል።

2ኛው ሀገር አቀፍ የህገወጥ ንግድ መከላከል ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተካሄደ ሲሆን፤ በመድረኩ ላይ ህገወጥ የቁም እንስሳ ንግድ ከፍተኛ ኪሳራ ማስከተሉ ተጠቁሟል፡፡

በጉባኤው ላይ በቁም እንስሳት፤ በመድኃኒትና ሌሎች የንግድ ዘርፎች ላይ በሚታይ ህገወጥ ንግድ ላይ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጓል፡፡

በንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ስርዓትና ፈቃድ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፍሰሀ ይታገሱ  እንደተናገሩት፤ ህገወጥ ንግድን ለመከላከል በዘመናዊ መልኩ የንግድ ስርዓቱን ማስኬድና ከጎረቤት ሀገራት ጋር በትብብር መስራት አስፈላጊ ነው ብለዋል።

በሀገር ደረጃ ጤናማ የንግድ ስርዓት እንዲኖር፤ የግሉን ዘርፍ መብት በጠበቀ መልኩ መንግስትም ተገቢውን ግብር እንዲያገኝ የሚያስችሉ መመሪያዎች እየተዘጋጁ እንደሚገኙ ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ የንግድ ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ኢንጂነር መላኩ እዘዘው በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በቁም እንስሳት በአፍሪካ አንደኛ ብትሆንም፣ ወደ ጎረቤት ሀገራት በሚደረግ  ህገወጥ ንግድ  ምክንያት ተጠቃሚ መሆን አልቻለችም ብለዋል፡፡

 “በመድሃኒት ንግድ አንድ ቢሊዮን ዶላር ግብይት የሚካሄድ ቢሆንም፣ በዘርፉ ባለው ህገወጥነትና ብልሹ አሰራር ምክንያት የሚፈለገው ገቢ አልተገኘም” ብለዋል፤ ፕሬዚዳንቱ፡፡

በሃዋሳ ከተማ በምሥራቅ ክፍለ ከተማ በ280 ሚሊዮን ብር ወጪ በ700 ካ.ሜ ቦታ ላይ የተገነባው ባለ 3 ኮከቡ ፌኔት ሆቴል፣ በዛሬው ዕለት የክልሉ የሥራ ሃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ተመረቀ፡፡

የዕለቱ የክብር እንግዳ የሲዳማ ክልል ፕሬዚዳንት አማካሪ አቶ ተሰማ ዲማ በምርቃት ሥነስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ "ሃዋሳ የቱሪዝም ከተማ እንደመሆኗ ሆቴሉ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረክታል" ብለዋል።

አዳዲስና ዘመናዊ አገልግሎቶችን ያካተተው ፌኔት ሆቴል፤ የኮንፍረንስ ቱሪዝሙን መደገፍ የሚችሉ የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሰጡ ክፍሎች ጭምር የያዘ ነው ተብሏል፡፡

 ለ41 ቋሚና 10 ጊዜያዊ ሰራተኞች የሥራ ዕድል ፈጥሯል የተባለው ሆቴሉ፤ የከተማዋን የቱሪስት እንቅስቃሴና ገቢ ለማሳደግ የላቀ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ተነግሯል፡፡

በ1992 ዓ.ም በሃዋሳ ከተማ ጥቂት ሰራተኞችን ይዞ በ50ሺ ብር በጀት በኪራይ ቤት የተጀመረው ሥራ፣ ለረዥም ዓመታት በከተማዋ ተወዳጅ ሆኖ ወደዘለቀው ፌኔት ክትፎ ቤት እንዳደገና  ዛሬ  የተመረቀውን ባለ 3 ኮኮብ ሆቴል ማዋለድ እንደቻለ በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ ተጠቁሟል፡፡

 ፌኔት ሆቴል፤ በቀጣይ በከተማዋ ባለ 4 ኮኮብ ሆቴል ለመገንባት ያቀደ ሲሆን፤ ለክልሉ የመሬት ጥያቄ አቅርቦ ምላሽ እየጠበቀ እንደሚገኝ የሆቴሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጤናዬ ዋርጌ ተናግረዋል፡፡

የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞና  ሌሎች ከፍተኛ የክልሉ የሥራ ሀላፊዎች ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በዛሬው ዕለት በመሐል ሐዋሳ ፒያሳ ላይ አስገንብቶ ያስመረቀውን ሁለገብ ሕንጻ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

 የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር አቶ  ደስታ ሌዳሞ ከጉብኙቱ በኋላ ባደረጉት ንግግር፤ ''ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በሲዳማ ክልልም ሆነ በሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ተጨማሪ ኢንቨስትመንት ማስፋፋት ለሚያቅዱ ሌሎች አካላት ምሳሌ መሆን የሚችል ተግባር እያከናወነ ነው'' ብለዋል።

''ባንካችሁ ለከተማችን ተጨማሪ ውበት ያጎናፀፈ ዘመናዊ ሕንጻ አስገንብቶ ለምረቃ በማብቃቱ እንኳን ደስ አላችሁ” ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ''ንብ ባንክ እንደ ስሙ ጥራት ያለው ስራ የሚያከናውን ባንክ ነውም'' ሲሉ አክለው ተናግረዋል፡፡



በሐዋሳ ከተማ የተሟላ የባንክ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ 20 ዓመታትን ያስቆጠረው ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ፤ በከተማዋ የዲስትሪክት ፅ/ቤት ያለው ሲሆን  የቅርንጫፎቹንም ቁጥር 8 አድርሷል።

 ባንኩ በሐዋሳ ፒያሳ ያስገነባውን ባለ 12 እና ባለ 14 ወለል መንትያ ሕንጻ በዛሬው ዕለት የተለያዩ የመንግሥት የሥራ ሀላፊዎች፣ የባንኩ የቦርድ ከፍተኛ የስራ አመራር፣ ማኔጅመንትና የከተማዋ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ማስመረቁን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያው ነው የተባለለት የአንጎል የደም ስር ክሊፒንግ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

ይህ ህክምና የተደረገላት ታካሚ ከአዲስ አበባ በጥቂት ርቀት ላይ የምትኖር ሲሆን፤ ድንገት በዕለት ሥራዋ ላይ ሳለች ከፍተኛ የራስ ህመም ይሰማት እንደጀመረና ከዚያም እራስዋን ስታ መውደቋን ታሪኳ ያስረዳል።

ህክምና ተቋም እንደደረሰችም በተደረገላት ምርመራ በአንጎልዋ ውስጥ የደም ቧንቧ መፈንዳት ምክንያት የደም መፍሰስ እንደተከሰተና የፈነዳው የደም ቧንቧ በቀዶ ጥገና ህክምና ባስቸኳይ ካልተስተካከለ ለሞት የሚዳርጋት መሆኑን ይነገራታል።

በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በኒውሮሰርጀሪ ዲፓርትመንት አስተባባሪነትና የአንጎል ደም ቧንቧ ቀዶ ጥገና ህክምና ከፍተኛ ልምድ ባካበቱት ዶ/ር ቶማስ ቦጋለ የሚመራ የህክምና ቡድን፣ ታህሳስ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ሶስት ሰዓት ከግማሽ በወሰደ የቀዶ ጥገና፣ የተስተካከለ የአንጎል የደም ዝውውር እንዲኖራት ማድረግ ተችሏል።

ታካሚዋ በተደረገላት ህክምና እጅጉን እንደተደሰተች ገልጻ፥ ባሁኑ ሰዓት ከህመምዋ አገግማ ወደ ቤትዋ ተመልሳለች፡፡  ይህ ህክምና ከዚህ ቀደም በሀገር ውስጥ  በመንግስት ሆስፒታሎች ሲሰራ የአሁኑ  የመጀመሪያው ነው ተብሏል።

በጉብኝቱ ወቅት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ኢንጅነር) ስለኢንስቲትዩቱ ሥራዎች ገለጻ አድርገዋል፡፡ በውይይቱ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂን ለማልማት በኢንስቲትዩቱ የሚሰሩ የምርምር ተግባራት ለሀገር የሚበጁ መሆናቸውን እንደተገነዘቡ ተመራማሪዉ ተናግረዋል።
ሳይንቲስቱ የሰዉሰራሽ አስተዉሎት ቴክኖሎጂ ለሰዉ ልጅ የሚያበረክተውን ሚና እንዲሁም በጠፈር ምርምር የቴክኖሎጂዉ አበርክቶ ጉልህ መሆኑን ገልፀዋል።
የሰዉሰራሽ አስተዉሎት ቴክኖሎጂ ቸግር ፈቺ የምርምር ዘርፍ በመሆኑ ወጣቶቸና በውጪ የሚኖሩ የዲያስፖራ አባላት በንቃት አንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።
ብርሃኑ ቡልቻ (ዶ/ር) በጨረቃ ላይ ዉሃ መኖር አለመኖሩን የሚመረምር መሳሪያ የፈጠሩ የናሳ ተመራማሪ ናቸዉ።

 ዘጠኝ ሞት ጥንቅቅ ተደርጎ የተሰራ ስነልቦናዊ ድራማ ነው። ይዞ የተነሳው ዓለማቀፋዊ ጭብጥ፣ የገጸ ባህርይ አሳሳልና የተዋንያኑ ብቃት እንዲሁም የሲኒማው የላቀ ደረጃ ተወዳጅ አድርገውታል። በዚህ ዳሰሳበፊልሙ የተነሳው ስነ-ልቦናዊ ጭብጥ ላይ በማተኮር ስለ ሞት፣ ስለ ሀዘን፣ እውነታን በመካድ ራስን ስለ መደለልና ስለ ለቅሶ ባህላችን በወፍ በረር እንመለከታለን።
          ዶ/ር ዮናስ ላቀው፤ የአእምሮ ህክምና ስፔሻሊስትና የአማኑኤል ሆስፒታል ታሪኮች መጽሐፍ ደራሲ


       ሞት-ታላቁ ምስጢር
በዘጠኝ ሞት ላይ የተነሳው  ጭብጥ  የሁሉንም ሰው ልብ የሚያንኳኳ፣ ሁሉም ሰው ላይ የሚደርስ ነገር ስለሆነ “ይሄ ጉዳይ አይመለከተኝም” የሚል ሰው አይኖርም።  ሁላችንም የምንወዳቸውን ሰዎች በአንድ ወይም በሌላ ጊዜ ማጣታችን አይቀርም።  በጅምላ ዋናውን ከመሞታችን በፊት ደግሞ ትንንሽ የችርቻሮ ሞቶች ሁልጊዜ ዙሪያችን አሉ። ከሚወዱት ሰው መለየት፣ ከሀገር መሰደድ፣ ጤና የሚነሱ ህመሞች፣ ተቀብረው የቀሩ እምቅ ችሎታዎች… ወዘተ። ዘጠኝ ሞት እነዚህን ሁላችንም አዳፍነን ይዘናቸው የምንዘራቸውን ጥያቄዎች የሚቆሰቁስ ፊልም ነው።  በነባሪያዊ የስነ-ልቦና ህክምና (ጽንሰ ሀሳብ) መሰረት፤ ሰዎች ሁሉ አራት መሰረታዊ ጥያቄዎች ጭንቀት ይፈጥሩብናል። እነዚህም ብቸኝነት፣  ነፃነት፣ የህይወት ትርጉምና ሞት ናቸው። ሞት ቢያስቡት ቢያስቡት የሚገባ ነገር አይደለም። እንደውም አተኩረው ካዩት እንደ ቀትር ጸሀይ ማጥበርበርና ግራ ማጋባት  ይጀምራል።
በአንድ መንደር የሚኖር ልጅ እናቱ ትሞትና ለብዙ ሳምንታት አምርሮ ያለቅስ ነበር። ቤተሰቦቹና ጎረቤቶቹ ሊያጽናኑት ሞክረው አልሆን ሲላቸው ለሃይማኖት አባት ይናገራሉ። እሳቸውም ልጁን፤ “ሀዘን ማብዛት ደግ አይደለም። ፈጣሪም አይወደውም” ይሉና  ይገስጹታል። ልጁም ተግሳጹን ፈርቶ ማልቀሱን ይተዋል። ከተወሰነ ጊዜ በኋላ የእሳቸው እናት ሞቱና እሳቸው አልቅሰው አልቅሰው አላቆም አሉ። ልጁ ሄዶ፤ “ምነው ሀዘን ማብዛት ደግ አይደለም ብለውኝ አልነበር?” ሲላቸው፤ “የኔ ልዩ ነው” አሉት ይባላል። ስለሞት ሲወራ ብንሰማም በኛ  ከደረሰብን ግን ልዩ ነው። ህዳር አበጋዝን እየመከረችው ነበር። “ለብሌን ንገራት፤ መዋሸት ጥሩ አይደለም” ስትለው ነበር። በራሷ ሲደርስ ግን “ልዩ” ሆነባት።
ሀዘን እና  እርም ማውጣት
ሁሉም ሀዘኖች የተለያዩ ናቸው። ሁለት ሰዎች የፈለገ ቢመሳሰሉ የሚያዝኑበት መንገድ አንድ አይነት አይሆንም። የምናዝንበት መንገድ እንደየመልካችን የተለያየ ነው።
ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ የሞት ጥናት (Thanatology)  ፈር ቀዳጅ የሆነችው  Elisabeth   Kiibler- Ross የነደፈችው ባለ 5 ደረጃዎች ንድፈ ሀሳብ አለ።
1.  ድንጋጤዎች ሞትን አለመቀበል  (shock and denial)
2. ንዴት (anger)    
3. ድርድር ( Bargaining)
4. መቀበል (Acceptance)
5. መከፋት (Deperasion)
 ይሄ ንድፈ ሃሳብ በቅደም ተከተል የተቀመጠ ይሁን እንጂ ሰዎች በእያዳንዱ ደረጃ ላይ የሚያሳልፉት ጊዜና ከአንዱ ደረጃ ወደ ሌላኛው የሚሻገሩበት ፍጥነት እንደሁኔታውና እንደግለሰቡ ይለያያል።
እውነታው ከባድ ሲሆን አእምሯችን ራስን መደለያ ስልቶችን  በመጠቀም ከሀዘኑ (ለጊዜውም ቢሆን) ይጋርደናል። የምንወዳቸው ሰዎች መሞታቸውን ስንሰማ እንደነዝዛለን። እውነታውን አንቀበለውም። ለቅሶ ሊደርሱ የሚመጡ ሰዎች እንኳን “አልሰማሁም! አልሰማሁም!” እያሉ ቢሆንም በርግጥ ሰምተዋል። ነገር ግን የሰሙትን ነገር ምን ያህል  መቀበል እንደከበዳቸው እየገለጹ ነው።
የህዳርን ሀዘን ያወሳሰቡ የተወሰኑ ነገሮች አሉ። የመጀመሪያው ድንገተኛ ሞት መሆኑ ነው። ጠዋት “በኋላ እንገናኛለን” ብላ በሰላም ተለይታ፣ ከስራ ስትወጣ ድንኳን ተደኩኖ መድረስ ከባድ ነው። ሰው ሲታመም አስታሞ፣ ሲሞት ወግ ነው።
ሰዎች ለሀዘኑም አእምሯቸው ስለሚዘጋጅ፣ ሞት ሲከሰት ለመቀበል ብዙ አይከብዳቸውም። ድንገት የሚከሰት ሞት ግን የገነገነ ሀዘን (Hypertrophied grief) ስለሚፈጥር ለመቀበል ከባድ ነው።
ፊልሙ ሲጀምር አካባቢ ህዳር  አበጋዝን፤ ”እናቴ ለኔ እናት ብቻ አይደለችም፤ ሚስጥረኛዬ፣ ጓኛዬም ናት።” ስትለው ይታያል። እናቷን ሚዜ ለማድረግ በቀልድ መልክም ቢሆን ስትናገር ታይቷል።  ጓደኛዋም እህቷም ነበሩ። ለእሷ ብለው ብዙ ዋጋ ከፍለዋል። በየፍርድ ቤቱ  ተከራክረዋል። የቆዳ ፋብሪካውን ክበብ ምግብ እንዳትበላ፣ ሌሊት ተነስተው ምሳ የሚቋጥሩላትን  እናቷን ስታጣ ምነው መቀበል አይከብዳት?
ህዳር “እናቷን ይኸውልሽ አግቢ አግቢ ብለሽኝ ብኋላ ብቻሽን እንድትቆራመጂ” ስትላቸው “ጽድቁ ቀርቶብኝ በወጉ በተኮነንኩኝ” ሲሏት፣ አእምሮዋ ላይ  መጥፎ ይሆን? የክበብ ምግብ ስትበላ  እናቷ የሚቋጥሩላት ትዝ እያላት አልበላ ብሏት ይሆን? ለእናቷ ቃል የገባችው፤ “የብረት መዝጊያ”  አማች ማምጣት እሳቸው ከሞቱ በኋላ ትርጉም የለሽ ነገር ሆኖባት ይሆን? የባኞ ቤቱን ገንዳ ባለማስተካከሌ፣ እኔ ነኝ እናቴን የገደልኳት ብላ ራሷን  እየወቀሰች ይሆን? ምስኪን ህዳር! እውነታውን መቀበል ቢከብዳት አይገርምም።
ፊልሙ ሊያልቅ ሲል ህዳር የእናቷን ሞት መቀበሏን አይተናል። ሆኖም እስክትወጣ ግን ብዙ የሚቀራት ይመስለኛል። ደስ ሲላት ለእናቷ ለመንገር ስልክ ታወጣ ይሆናል። ሰርግ ለማድረግ ከወሰነች ሰርጓ መሃል የምትተክዝ ይመስለኛል። በአል ሲመጣ  ሆድ ሳይብሳት አይቀርም ሀዘን እረጅም ሂደት ነው።
የለቅሶ ባህላችንና እውነታን መካድ
 ሞት አለማቀፋዊ ይሁን እንጅ የሀዘንና የለቅሶ ስነስርዓቶች በባህል የተቀኙ ናቸው። ምእራባውያን ጥቁር ሱፍና ከረባት አድርገው ጥቂት ሰዎች በተገኙበት ቀብር አስፈጽመው ወደየቤታቸው ይሄዳሉ። እንግሊዞች ጋ “እዬዬ” ብሎ ማልቀስ የለም። ኮምጨጭ ብለው (with stiff upper lip) ንግግር  ያደርጉ ይሆናል እንጂ ድምጽ አውጥቶ ማልቀስ የተለመደ አይደለም። የኛ ሀገር ሰው የእንግሊዞችን ቀብር ቢመለከት “ምን አይነት ልበ ድንጋዮች ናቸው?” ሳይል አይቀርም። በኛ አገር ደግሞ ሀዘን ሲያጋጥም ጎረቤት፣ የእድር ሰዎች፣ የስራ ባልደረቦች፣ * በጣም የሚቀርቡን  ስምንት መቶ ሰዎች ለማስተዛዘን ይመጣሉ።
*  የቀብር ስነስርዓት ላይ ሙሾ  ማውረድ፣ ደረት መምታት፣ አብሬ ካልተቀበርኩ ማለት ሊኖር ይችላል። አንድ እንግሊዛዊ የቀብር ስነ-ስርዓታችንን ቢመለከት፣ ብዙ ሰዎች ራሳቸውን ስተው (mass hysteria)ሊመስለው ይችላል።
ፊልሙ ላይ እንደተቀመጠው የዶርዜዎች የለቅሶ ባህል ደግሞ የሞተውን ሰው በጭፈራ መሸኘት ሊኖር ይችላል።
እድር፣ ጎረቤትና ዘመዶች በለቅሶ ጊዜ  የስሜት  እንዲሁም ተግባራዊ እገዛ ያደርጋሉ። ዋናው ሀዘንተኛ እንግዶችን “እንዴት  ላስተናግድ?” ብሎ አይጨነቅም። ሰጥ ለጥ  አድርገው ያስተናግዳሉ።
በሌላ መልኩ ሀዘን ላይ ያሉ ሰዎች እርም እንዳያወጡ የሚያደርጉ ክስተቶችም አሉ። ሰዎች  ስለሀዘናቸው ማውራት ሲጀምሩ አንዳንድ ሰዎች ስለሚጨንቃቸው “ያው  የፈጣሪ ስራ ነው።” ወይ “ሁላችንም ወደዚያው ነን። ምን ይደረጋል?”  የሚባሉት ጠቅለል ያሉት የማጽናኛ ንግግሮች ሀዘኑን ስለሚደፋፍኑት፣ ሀዘን ውስጥ ያለው ሰው ብቸኝነት እንዲሰማውና ስሜቱን አፍኖ እንዲይዝ ያደርጋል።  
አንዳንድ ጊዜ ሀዘን ውስጥ ያሉ ሰዎች “ግንባር ለማስመታት” መጥቶ  “ሀሙስ አይቻት አልነበር ምን አጋጠማት?” ከሚለው ሰው ሁሉ ጋር እየደጋገሙ መናገሩ ያታክታቸዋል። ከላይ  ከላይ የሆኑ ብዙ ንግግሮችን ከማድረግ የውስጥ ስሜታቸውን ከሚረዷቸው ጥቂት ሰዎች ጋር መወያየት ይመርጡ ይሆናል።
ብዙ ሺህ ህጻናትና ታዳጊዎች ልክ እንደ ብሌን  እናታቸውን እየጠበቁ ነው። አንዳንዶቹ  ሃያዎቹ ውስጥ ደርሰውም አሁንም መጠበቃቸውን ቀጥለዋል። ይህን የሚያደርጉ ወላጆች አንድም ለልጆቻቸው በማሰብ ሲሆን፣ ሁለትም እንዴት እንደሚነግሩ  ግራ ገብቷቸው ነው።
 አእምሯችን አስፈሪና አስጨናቂ ነገሮች ሲያጋጥሙት ከግንዛቤ ውጪ የተለያዩ የመከላከያ ስልቶችን በመጠቀም ጭንቀቱን ለጊዜውም ቢሆን፣ በመጠኑም ቢሆን ለማርገብ ይሞክራል። እነዚህ ነገሮች ከግለሰቡ ግንዛቤ ውጭ የሚካሄዱ ናቸው። በፊልሙ ላይ የተነሳው እውነትን መካድ ገሀዳዊውን ዓለም የምንመለከትበትን መንገድ ስለሚያዛባው እንዲሁም ግለሰቡንም በጣም ስለሚጎዳው ኋላ ቀር ራስን የመደለያ መንገድ ይባላል።
 በህክምና ውስጥ እውነታን መካድ በተለያየ መንገድ ያጋጥመናል። ለምሳሌ አንድን  ሰው እንዴት ነው ብዙ አልኮል ትጠጣለህ ብዬ ብጠይቀው፤  “በየቀኑ ብዙ አልኮል እጠጣለሁ” የሚለው እውነታ የሚያስጨንቅ ስለሆነ፣ ሳያስበው አልፎ አልፎ ከጓደኞቼ ጋር አንድ፣ ሁለት እንላለን። ሊል ይችላል። በተመሳሳይ ሱስ ውስጥ ያለ ሰው፣ ሱስ ስለማቆም ብናወራው “እኔ እኮ ሱስ የለብኝም። ከፈለግሁ ማቆም እችላለሁ።” ሊል ይችላል።
  የስኳር የደም ግፊት ህመምን መቀበል የሚያቅታቸው ሰዎች፤  መድሃኒት ከመጀመር በስፖርት እከላከለዋለሁ” ሲሉ ዜናው ስላስጨነቃቸው አእምሯቸው እውነታውን በመካድ እየደለላቸው ሊሆን ይችላል። ለማጠቃለል ዘጠኝ ሞት  በደንብ ጥናት ተደርጎ የተሰራ ስነ-ልቦናዊ  ፊልም ነው።  ለወደፊትም መታየቱ እንደሚቀጥል ጥርጥር የለኝም። የስነ-ልቦና ትምህርት ላይ እንደ ማስተማሪያ ሊያገለግል የሚችል፣ የስነ-ልቦና ህክምና ላይ ደግሞ ጠለቅ ያለ ሳይንሳዊ ጥናት እንዲደረግ  የሚጎተጉት ፊልም ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ከምንም በላይ ግን ሁላችንም ስለ ህይወትና ስለ መንታ ወንድሙ ሞት  እንድናስብ የሚያደርግ ፊልም ነው።
ስለሞትና ስለሀዘን ሁለት ስነ-ልቦናዊ  መጽሐፍትን እጠቁማለሁ።
 Mourning and Melamcholia by sigmund freud
On Death and Dying by Elisabeth  Kijbler-ross  እንዲሁም የተራዘመ (Prolonged) ወይም የተወሳሰበ (Complicated) ሀዘን ውስጥ  ላላችሁ ደግሞ ሁለት የመጽሐፍ ጥቆማ አለችኝ።
WHO DIES?  By stephen and Dndrea hevine
When bad things happen to good people by harolds. Kushner
ያለ አእምሮ ጤና፣ ጤና የለም!

Saturday, 23 December 2023 11:11

የሞት ቅኔ

ሚስቱን ማመን ካቆመ ቆየ ይህ ደግሞ የሆነው ስራ ተቀጥራ መስራት ከጀመረች ጀምሮ ነው ብሎ ነው የሚያስበው፡፡ ከዛን ጊዜ ጀምሮ የምታደርገው ነገር በሙሉ እየተከታተለ ጥልቀቱን ሊረዳው የማይችለው ቅናት ውስጥ ገባ፡፡ ቅናቱ ስር እየሰደደ ሄዶ ወደ ንዴትና ጥላቻ አደገ፡፡ ይህም የንዴት ስሜት ህይወት መስርቶ በጭንቅላቱ ውስጥ ታዛውን ከቀለሰ ቆየ፡፡ አሁን ላይ ከቁጥጥሩ ውጭ ሆኖበታል፡፡ አይኖቿ ያበግኑታል፣ ስትራመድ ማየት አይፈልግም፣ እየሳቀች ከሰማት ከዛ አካባቢ መራቅ ነው የሚፈልገው፣ እሱን መውደድ እንዳቆመች ነው የተረዳው፣ እንደ ወንድ የምታየው አይመስለውም፣ ምክንያት ፈልጋ ቤቱን ጥላለት መኮብለል እንደምትፈልግ ነው የሚገምተው፣ ቤተክርስቲያን ልሂድ ብላ ሰንበት ላይ ስትወጣ የገዛ ፈጣሪው ላይ መቅናት ይጀምራል፡፡ ሁሉም ነገር ከጤነኝነት ያፈነገጠ እና እያደገም ሲሄድ ወደ እብደት ሊከተው እንደሚችል ነው እየተረዳ ያለው፡፡
ቢንያም ይህን እያሰበ ቦሌ ካልዲስ ካፌ ውስጥ በትካዜ ውስጥ ሆኖ ተቀምጧል፡፡ ድንገት ግን አንድ ቻይናዊ እሱ ከተቀመጠበት ወንበር ጋር መጥቶ ቆመ፡፡ ዮሴፍ ቀና ብሎ ተመለከተው፡፡ ቻይናዊው ጥርት ባለ አማረኛ ያናግረው ጀመር፡፡
“ይቅርታ የኔ ወንድም አንድ ጊዜ እንዳናግርህ ፍቃደኛ ነህ?”
ቢንያም በደመነፍስ ውስጥ ሆኖ እንዲቀመጥ በአይኑ ምልክት አሳየው፡፡ ምንም ነገር ማውራት ባይፈልግም አሁን ካለበት ሀሳቡ የሚያላቅቀውን ማንኛውንም ነገር ከመሞከር ወደ ኃላ እንደማይል ስለገባው ለቻይናው እንግዳ ፈቀደለት፡፡
ቻይናዊውም አጠገቡ ከተቀመጠ በኃላ ወዲያው ወደ ጉዳዩ ገባ፡፡
“ዛሬ ላማክርህ ይዤልህ የመጣሁት ሀሳብ እጅግ ድንቅ ነገር ነው፡፡ በናዝሬት ከተማ ውስጥ አንድ የሜዲቴሽን ማዕከል አለን፡፡ የማዕከላችን ዋና አላማም የሰው ልጆችን ወደ ከፍተኛው ንቃታቸው እና የማንነት ጥጋቸው ድረስ ሄደው ራሳቸውን እንዲያገኙት ማድረግ ነው፡፡ በዚህ ሰዓት ላይ ብዛት ያላቸው ሰዎች በመመዝገብ ላይ ናቸው፡፡ በማዕከሉ ውስጥ ከሚሰጡ መንፈሳዊ እውቀቶች መካከል ነፍስን አውጥቶ መጓዝ (Astral projection) እና ነፍሰ ብርሀንን የመመልከት ጥበብ (Aura Reading) ዋነኞቹ ናቸው፡፡
ቢንያም ካቀረቀረበት ቀና ብሎ ተመለከተው፡፡ ጠበቅ ባለ ንግግርም ጠየቀው …”ነፍስን አውጥቶ መጓዝ ነው ያልከው?”
“በትክክል::” አለ ቻይናዊው፡፡ “ከጥንታዊቷ ቲቤት ውስጥ በተላለፉ አስደናቂ ጥበቦች ላይ መሰረት አድርገን ነው ትምህርቱን የምንሰጠው፡፡”
“ነፍስን አውጥቶ መጓዝ ስትል…ማለቴ ትንሽ ስለነገሩ አስረዳኝ?”
“አስትራል ፕሮጀክሽን ማለት አሁን ያለህበትን ስጋዊ ንቃትህን እንደያዝክ በነፍስህ ያሻህ ቦታ መጓዝን ያካትታል፡፡ አንድ ጊዜ ነፍስህን አውጥተህ መጓዝ ከቻልክ በአካልህ ልትደርስባቸው የማትችላቸው ቦታዎች በሀሳብ ፍጥነትህ ልክ በቦታው መገኘት ትችላለህ፡፡ ህይወትንም አሁን ከምታይበት እይታ ውጭ ሆነህ በአዲስ አይን መመልከት ትጀምራለህ፡፡ የማሰብ አቅምህም የት ድረስ መለጠጥ እንደሚችል በገዛ ጭንቅላትህ ብቻ ተጠቅመህ ትደርስበታለህ፡፡”  
“በሀሳብ ፍጥነት የፈለከው ቦታ መሄድ ትችላለህ ነው የምትለኝ? እንዴት እንዲህ ሊሆን ይችላል? ይህ እኮ ሊሆን የማይችል ሀሳብ ነው እያነሳህ ያለህው፡፡ ስለ ተሸከምኩት አካሌ ጥልቅ እውቀት የሌለኝ ሰው ነፍሴ የቱ ጋር ትሁን የት ሳላውቅ በእንዴት አይነት መልኩ ላዛት እችላለሁ?”
ቻይናዊው በእርግጠኝነት መንፈስ ፈገግ ብሎ ቢንያምን ካየው በኃላ ይህን ተናገረው…”ጥያቄህ በሙሉ ትክክል ነው፡፡ ነገር ግን ከመፈጠራችን በፊት እና ከሞትን በኃላ ያለውን ነገር ላይ ምንም እውቀት የሌለን ሰዎች ነበርን ሆኖም ባደግንበት ቦታ የሚነገሩንን መንፈሳዊ ሚስጥራቶች አድምጠን ያላየናቸውን አለማት አምነን ተቀምጠንም እናውቃለን፡፡ ይህም እውቀት እንደዛው ነው፡፡ ያልተመለከትከውን ሰው ሲጠይቅህ አላውቀውም እንደምትለው ሁሉ በውስጥህ ያለውንም ድንቅ ጥበብ በተመሳሳይ የእወቀት ቅርፅ ውስጥ ሆነህ ብትፈልገው ታገኘዋለህ፡፡”
ቻይናዊው ከተቀመጠበት እየተነሳ… “ጊዜ ኖሮኝ ስለያንዳንዱ ነገር ባስረዳህ ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ሆኖም በማዕከላችን መጥተህ በራስህ መንገድ እና ኢማጅኔሽ እውቀቱን ካላገኘህ በስተቀር እኔ ያልኩህን እያሰብክ ብቻ ነው የምትጓዘው፡፡ በዚህም ውሳኔህን እፈልገዋለሁና ይህች ቢዝነስ ካርዴን ይዘህ ልክ ስትወስን ደውልልኝ፡፡”
…ቢዝነስ ካርዱን ለቢንያም አቀብሎት አካባቢውን ለቆ ሄደ፡፡
ቢንያም የዛን ቀን እንቅልፍ ሳይተኛ አደረ፡፡ በየማህሉ ሚስቱ አቅሊስያን እየዞረ እያያት መናደዱን ግን አላቆመም፡፡ እንዲሁ ጠዋት ላይ ተነስታ ጥላው የምትጠፋ እየመሰለው ነው፡፡ ምን አድርጓት እንደሆነ ግን ሊገባው አልቻለም፡፡ በእርግጥም ነፍሱን አውጥቶ ያሻው ቦታ መብረር የሚችል ከሆነ አቅሊስያ የምትረግጠውን ምድር በሙላ እየተከተለ የምታደርገውን መመልከት ይችላል፡፡ ይህን ደግሞ ከሞት በላይ እረፍት እንደሆነ ተረዳ፡፡
አንድ ጊዜ ዞሮ ተመለከታት፡፡ በህልም ውስጥ ሆና የምትማግጥበት መሰለው፡፡ ሊቀሰቀቅሳት ፈለገ፡፡ ቀስቅሶ አንቺ ጨካኝ ሊላት፤ ምን አድርጌሽ ነው ብቻዬን ልትጥዪኝ ያሰብሺው ብሎ ሊጠይቃት በንዴት ውስጥ ሆኖ ቋመጠ፡፡ ሆኖም እስካሁን አንድም ነገር ያላገኘባትን ሴት ምን ብሎ ዘሙተሸበኛል ይበላት፡፡ ምንም ነገር አይቶባት ባያውቅም እንዲሁ ግን ውስጡ እየደጋገመ ልታመልጥህ ነው ነው የሚለው፡፡ በጣም ይወዳታልና እርግጠኛ መሆን አለበት፤ ለአስራ ሶስት አመታት አብረው ህይወትን እንደመፅሀፍ እያነበቡ ኖረዋልና በድንገተኛ ስሜት ብቻ አመታቶቹን መናድ አልፈለገም፡፡
ሲነጋ ጠዋት ላይ አቅሊስያን ቀስቅሶ ለስራ ወደ ናዝሬት እንደተላከና የሶስት ወር ፕሮጀክት እንዳለበት ነገራት፡፡ ወዲያው አምናው ተስማማችለት፡፡ በፊት ግን ትታገለው ነበር፡፡ አብሬህ ካልሄድኩ ትለው ነበር፡፡ እንዴት ቀድመህ አትነግለኝም ብላው ታኮርፈው ነበር፡፡ ታለቅስ ነበር፡፡ የዛን ቀን ግን ባለው ነገር ያለማንገራገር ተስማማችለት፡፡ ይህም ደግሞ አናደደው፡፡ ምን ስለሆነች ነው ካጠገቧ ስለይ ምንም የማይመስላት ብሎ በውስጡ በገነ፡፡ ምን ያረጋጋት ነገር እንዳለ በፍጥነት ማወቅ አለበት፡፡ የዛን ጠዋት ላይ በቅጡ ሳይሰናበታት ቤቱን ጥሎ ሄደ፡፡
ናዝሬት ከደረሰ በኃላ የቻይናዊው ስልክ ላይ ደውሎ የሜዲቴሽን ማዕከሉ ጋር ከብዙ ፍለጋ በኃላ ለመድረስ ቻለ፡፡
ማዕከሉ ግዙፍ ግቢ ውስጥ የተበጀ ሲሆን በውስጡም ከቅጠሎች መገጫጨት ውጭ የሚሰማ አንዳችም ነገር አልነበረም፡፡ የሚተነፍሰው አየር ወደደው፡፡ የሚጠበቅበትን ምዝገባ ጨራርሶ አንድ ክፍል ለብቻው ተሰጠውና የመጀመሪያውን ምሽት አቅሊስያ ምን እያደረገች እንደሆነ እያሰበ አደረ፡፡
ነጋ፡፡
ብዙ ንጋቶችን ብቻውን መምህሮቹ የሚነግሩትን የአሰርምሞ ጥበብን እየተከተለ ሰነበተ፡፡
ቢንያም እጅግ የተረጋጋ መንፈስን ብቻ መተንፈስ ከሚችሉት የቡድሂስት አስተማሪ ስር ሆኖ ስለ ነፍስ አሰራር አጠና፡፡ ነፍስን ከቧት ስላለው ብርሀን (ነፍሰ ብርሀን) ምንነት ጥልቅ እውቀት ያዘ፡፡ በነፍስና በስጋችን መካከል ስላለው ድብቅ የንዝረት ህግ ጠንቅቆ ተረዳ፡፡ እንቅልፍ ሲወስደን ነፍሳችንን ይዞ ስለሚተመው ከሰውነታችን ጋር እንደ እትብት ተጣብቆ ስላለው ብርማው ገመድ ላይ እውቀቱ ተመነጠቀች፡፡ እሱና መላው አለም አንድ እንደሆኑና የእሱ እስትንፋስ አለም ላይ ህይወት እንደሚዘራ ተገለጠለት፡፡ በዚህ መሃል ግን ዋና አላማውን አልዘነጋም፡፡ በፍጥነት ይሄን ጥበብ አግኝቶ የሚስቱን መዳረሻ ነው ማወቅ የፈለገው፡፡
ለምን ሲናደድባት እንደምትረጋጋ፣ ለምን ተናዳለች ብሎ ሲያስብ እሷ ግን በተመረጡ አማርኞች ልታረጋጋው ትሞክር እንደነበር፣ የት ነህ…የት ነበርክ እያለች አስሬ የምትጠይቀው ሴት ለምን ድንገት መጠየቋን አቋርጣ በሚላት ነገሮች በሙላ መስማማት እንደጀመረች ማወቅ አለበት፡፡ አስራ ሶስት የትዳር አመታትን እንደቀልድ ማየት አልፈለገም፡፡ ብዙ ትግል ውስጡ አለበት፡፡ አቅሊስያን ነፍሱ ድረስ ወስዶ ተነቅሷታል፡፡ ራሱን ካላጠፋ በስተቀር ሊረሳት የማይችላት ሴት ናት፡፡  
ከብዙ ሙከራዎች በኃላ የመጨረሻው ቀን መጣና ይህ ተከሰተ፡፡
የቡድሂስቱ ጉሩ የማዕከሉን ሰልጣኞች ሰብስቦ ማናገር ጀመረ፡፡
“አሁን ሁላችሁም በዚህ ክፍል ውስጥ ያላችሁ ሰዎች ነፍሳችሁን አውጥታችሁ ለመጓዝ በቂ እውቀት አላችሁ፡፡ ዛሬ ላይም ስትናፍቁት የነበረው የነፍስ በረራ እና የአለማትን ጉብኝት የምትጀምሩበት ቀን ነው፡፡ ሆኖም ለጥንቃቄ ተብሎ የተነገራችሁን በሙሉ መተግበር አትዘንጉ፡፡ ምን ጊዜም ቢሆን ከዚህ አለም ውጭ ሆናችሁ የምታዩት እይታ አማሏችሁ በዛው እንድትቀሩ ሊያደርጋችሁ ይችላልና ወደ ስጋችሁ መመለሳችሁን አትዘንጉ፡፡  ሁላችሁም የተማራችሁትን ተግባር ላይ ለማድረግ በክፍላችሁ ውስጥ መግባት ይጠበቅባችኃል፡፡ በእያንዳንዳችሁ ክፍል ውስጥ ባለውም ድምፅ ማጉያ ለዚሁ ምትሀታዊ ተግባር ተብሎ የተዘጋጀላችሁን የፍሪኩዌንሲ ሞገድ ይለቀቅላችኃል፡፡ መልካም እድል ለሁላችሁም እየተመኘሁ አሁን ሁላችሁም ወደ ክፍላችሁ እንድትሄዱ በትህትና እጠይቃለሁ፡፡
ቢንያም የሚያደርገው ነገር የእብደቱን ልክ ገና መገንዘብ ሳይጀምር ነፍሱን አውጥቶ እንዲበር እየጠየቁት ነው፡፡ ሆኖም የሰው ልጅ ጥልቅ ፍላጎት መፍጠር የማይችለው ነገር እንደሌለ አድርጎ የሚያስብ የሰው አይነት ነበርና የአቅሊስያን ሁኔታዎች በሙላ ለመረዳት እና የሀሳቧ ጥጋት ስር ለመድረስ የሚራመደውን ያህል ለመራመድ ወስኗል፡፡
በክፍሉ ውስጥ ገብቶ  እንደተባለው በጀርባው ተኛ፡፡ ነፍስን እየጎተተ አለማትን በሚያስጎበኘው የሞገድ ድምፅ የሰመመን ስሜት ውስጥ ገባ፡፡ እንደተባለው አተነፋፈሱን እየቆጠረ በሰውነቱ ላይ ያውን ሀይል በሙሉ እኩል ለማድረግ ሞከረ፡፡ ሰውነቱ እንደ እፉዬ ገላ እየቀለለው መጣ፡፡ ሰውነቱ የከተመበት የስሜት ዳገት እንደ ህልም የሚመስለው ነው፡፡ ነገር ግን ህልም አይደለም፡፡ በሰውነቱ ላይ ከባድ የሆነ የኤሌክትሪክ ንዝረት ተሰማው፡፡ ልክ ይህ እንደተሰማው በፍጥነት ነፍሱ ስጋውን ለቃ ወጣች፡፡
የምትንሳፈፈው ነፍሱ ብቻ ናት እያሰበች ያለችው፡፡ ከስጋው ጋር ተዳብሎ የነበረው እውቀት አሁን ላይ የለም፡፡ በነፍስ አካሉ ውስጥ ሆኖ ዞሮ የገዛ አካሉን በአልጋው ላይ ተኝቶ ተመለከተው፡፡ ድንጋጤ ውስጥ ገባ፡፡ የሚያየውን ማመን አቃተው፡፡ የምር ሞትን ሳይሞት ሞትን እየሰለጠነው መሰለው፡፡ በህይወትም በሞትም ውስጥ ሆኖ እንዴት ራሱን ማግኘት እንደቻለ ለወራት ሰልጥኗልና እዚህ ሀሳብ ላይ በመፈላሰፍ ጊዜውን መፍጀት እንደሌለበት አውቋል፡፡ አሁን ላይ ከአዲሱ አካሉ ጋር ለጥቂት ጊዜም ቢሆን መላመድ ነው ያለበት፡፡ በክፍሉ ውስጥ ሆኖ እንደ እንግዳ ሰው በአልጋው ላይ ተኝቶ ያለው ራሱን ተመለከተው፡፡ አስቀያሚ ሰው ነኝ ብሎ ማሰብ ጀመረ፡፡ እስከዛሬ ሲያፈጥበት የነበረው መስታወት ሲዋሸው እንደከረመ ደረሰበት፡፡ ለካ እስካሁን መልኩ ምን አይነት እንደሚመስል ራሱ በራሱ አይን ነው ማየት የነበረበት፡፡
ጊዜውን ማባከን የለበትም፡፡ በፍጥነት የነፍሱ የህይወት ትንፋሽ ወደሆነችው ባለቤቱ አቅሊስያ በሮ እየሆነ ያለውን ነገር ማወቅ አለበት፡፡
በነፍሱ ውስጥ ያለውን ንቃት ተጠቅሞ አቅሊስያ ያለችበት ቦታ እንዲሰደው የገዛ እውቀቱን በሀሳብ ቃላቶች ጠየቀው፡፡ በሀሳብ ፍጥነት በአንድ ሆስፒታል ውስጥ ራሱን አገኘው፡፡ የተከሰተው ክስተት ስለፈጠረበት ድንጋጤ እኔ ደራሲውም ብሆን ለማስረዳት ይቸግረኛል፡፡ ሆኖም ቢንያም አሁን ሆስፒታል ውስጥ ባለ አንድ ክፍል ውስጥ ነው ያለው፡፡ ከፊት ለፊቱ አንድ ዶክተርና ከሱም በተቃራኒ አቅሊስያ ተቀምጣ እያያቸው ነው፡፡ የፈራው ነገር እንዳይከሰት በነፍሱ ንቃት ውስጥ ሆኖ ለፈጠሪው ቅፅበታዊ ፀሎት አደረሰ፡፡
ዶክተሩ በሀዘኔታ አቅሊስያን ሲያናግራት ተመለከተና ፀሎቱን አቋርጦ ትኩረቱን ወሬያቸው ላይ አደረገው፡፡
“አቅሊስያ አሁን በሀዘን ህይወትሽን መግፋት የለብሽም፡፡ ያለሽን ጊዜ ከምትወጂያቸው ሰዎች ጋር በደስታ ማሳለፍ ነው ያለብሽ፡፡ ብዙ የሚወዱሽና የሚያከብሩሽ ሰዎች አሉ….
አቅሊስያ አቋርጣው መናገር ጀመረች፡፡
“ባለቤቴ ቢንያምን ምን ልለው እችላለሁ? እንዴት አድርጎ ያምነኛል? ምን ያህልስ ሊያዝን ይችላል?” ቢንያም ይህንን ሲያደምጥ ከዛ አካባቢ ጥፋ ጥፋ የሚል ስሜት ውስጥ መግባት ጀመረ፡፡ ሆኖም እሱ ራሱ ያልተረዳው ሀይል ባለበት ቆሞ የባለቤቱን ንግግር እንዲያደምጥ ያዘው ጀመር፡፡ እሱም እንደዛው አደረገ፡፡
አቅሊስያ ከተከዘችበት ቀና ብላ ዶክተሩን መጠየቅ ጀመረች፡፡  “አንተ እኔን ብትሆን ምን ብለህ ነው ለቢንያም የምትነግረው?”
ዶክተሩ በሀዘኔታ እያያት መለሰላት “ መሞታችን በተፈጥሮ የተሰጠን ግዴታችን ነው፡፡ መች እንደምንሞት ማወቃችን ምናልባት በምድር ላይ ቀሩብን የምንላቸውን ነገሮች እንድናደርግ ይረዱን ይሆናል… ሆኖም አንቺ ብቻ አይደለም የምትሞቺው…ሁላችንም መንገዳችን ወደዛው ነው፡፡ ቢንያምም ቢሆን፡፡”
“ካንሰር እንዳለብኝ እኮ እስካሁን አያውቅም፡፡ ለመሞት ሁለት ወራቶች እንደቀሩኝ እስካሁን አያውቅም፡፡ እሱ የሚያውቀው ከልጅነቱ በምኞቱ ፀንሶት ያለውን ዮሴፍ ብሎ በቅድሚያ ስም ያወጣለትን ወንድ ልጁን እንደምወልድለት ነው፡፡ እሱ የሚናፍቀው አሁን ካለንበት ቤት ወጥተን የተሻለ ኑሮ መኖራችንን ነው፡፡ እሱ እየለፋ ያለው እኔ ምንም ሳልለፋ እንደልዕል እንድኖርለት በማሰብ ነው፡፡ የትኛው ድፍረቴ ነው ከሱ ፊት አቁሞኝ የዛሬ ሁለት ወር እሞታለሁ እንድለው እድል የሚሰጠኝ? የትኞቹ አይኖቼ ናቸው አይኖቹን እያዩ እስካሁን የለፋህው ልፋትህን ሞት የተባለው እርግማን ተረጋግቶ ሊያወድምብህ ነው ብዬ በድፍረት ውድቀቱን እንድተርክለት የሚሰብኩኝ፡፡ ፈራሁ እኮ ዶክተር…ገና ሳልሞት የሞትና የፍቅር ሀይል በቁሜ አሰቃየኝ፡፡ ባህሪዬን ቀይሬበትም በፀጥታው ውስጥ ያወራኝ፡፡ መውደዱን መናፈቁን ይነግረኛል፡፡ በምድር ላይ ብቻችንን ነን፡፡ ለኔም ለሱም ያለነው አንደኛችን ለአንደኛችን እየተሳሰብን ነው፡፡ አሁን ለስራ ወደ ፊልድ ሄዷል፤ ከስራ ሲመጣ ከሚለፋላት ሚስቱ ጋር ሳይሆን ጨክና ከሞት ጋር ካመለጠችው ጨካኟ ባለቤቱ ጋር ነው የሚገናኘው፡፡ ሳልነግረው ስሞትበት ምን ይለኛል፡፡ ለምን ሀዘኑን ከማይ ብዬ እውነቱን ልደብቅበት፡፡ ለምን ጨከንኩበት፡፡ አሁን እየከበደኝ ነው፡፡”
ዶክተሩ ተስፋ በመቁረጥ ባለበት ሆኖ አቀረቀረ፡፡ አቅሊስያ በቀጣይ ለማውራት ሞክራ የገዛ የእንባዋ ሳግ ስለተናነቃት ክፍሉን ለቃ ወጣች፡፡
ይህ ሁሉ ሲሆን ማልቀስ በማይችለው ነፍሱ፣ መጮህ በማይችለው አንደበቱ፣ መሮጥ በማይችለው እግሩ ከክፍሉ ሰማይ ላይ ተንሳፎ የሚያየው ቢንያም የሚያደርገው ጠፍቶት እየጠፋች ያለችውን አቅሊስያ በአይኑ ብቻ ሸኛት፡፡
እስካሁን ሚስጥር የሆነበትን ነገር ምላሹ ነፍስን በሚሸረካክት መንገድ ደረሰበት፡፡ አቅሊስያ ልትሞት ሁለት ወር ነው የቀራት፡፡ አቅሊስያ ካንሰር ይዟታል፡፡ አቅሊስያ እየዘሞተች አልነበረም፡፡ አቅሊስያ ቢንያምን ትወደዋለች፡፡ አቅሊስያ ልትሞት ነው….እነዚህ አረፍተነገሮች እንደ ፈረስ እየጋለቡ ነፍስያውን ይዞሩት ጀመር፡፡ በነፍሳዊ ንቃት ውስጥ ሆኖ መሞትን ተመኘ፡፡ ሆኖም የማይሞተውን ማንነቱን ይዞ ነው ከዚህ እውቀት ጋር የተዋወቀው፡፡ ሁሉም ነገር አስፈራው፡፡ ሆኖም ድንገት አንድ ሀሳብ ብልጭ አለለት፡፡ ወደ አካሉ ካልተመለሰ በዛው መቅረት ይችላል፡፡ ይህንንም የቡድሂስቱ ጉሩ አስተምረውታል፡፡ አዎ…ወደ ስጋው መመለስ አይፈልግም፡፡ ምን ቀረኝ ብሎ፡፡ የምትሞተው ሚስቱን ሞቶ ይጠብቃታል፡፡ የምትሞተው ሚስቱ ጋር አብረው ሞተው ልትበትናቸው ያለችውን ህይወት ድል ይነሷታል፡፡
ከዛን ቀን አንስቶ ቢንያም በነፍሱ እየበረረ በየቤተክርስቲያ ደጃፍ እየዞረ ከአቅሊስያ ጋር አብሮ አለቀሰ፡፡ ሙሾን አወረደ፡፡ ጥሎት የሄደውን የገዛ ስጋውን ረስቶት የሚናፍቃትን ነፍስ ከነፍስ እቅፉ ውስጥ እስክትመጣለት ድረስ አብሯት ሰነበተ፡፡ የምትሞትበት ቀናት ድረስ ሞቶ ተከተላት፡፡ የጠረጠራት ድረስ አስታውሶ እየደጋገመ ወደዳት፡፡ ህይወት በግሳንግስ ትርምሶቿ የቀማቻቸው እምነት እና ፍቅራቸውን በሞት ቅኔ ውስጥ አስመለሱት፡፡