Administrator

Administrator

የጀግና ሰው መልኩ ሁለት ብቻ ነው፤ አንድ ፊት መስዋዕት በአንድ ፊት ድሉ ነው፤ የሁሉም ማሰሪያ ማተቡ ብቻ ነው፡፡ (“የአሲምባ ፍቅር” ገፅ 140) ካህሳይ አብርሃ ወይም በበረሀ ስሙ አማኑኤል ተብሎ ይጠራል፡፡ መስከረም 27ቀን 1968 ዓም የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ሰራዊትን ለመቀላቀል ወደ ትግል ወጣ፡፡ ሰኔ 27ቀን 1968 ዓም ወልዲያ ለተልዕኮ የወጣ የሠራዊቱ ቡድን ወደ አሲምባ በተመለሠበት ዕለት በተፈጠረ የጦርነት አጋጣሚ ከይመር ንጉሴ ጋር ተገናኘ፡፡

በ1970 በኤርትራ አድርጎ ሱዳን በመግባት ከሠራዊቱ ተለየ፡፡ ኑሮውም በአሜሪካ ሆነ፡፡ የደርግ አገዛዝ ሲገረሰስ ይመር ንጉሴን ለማግኘት እንዲሁም የመጀመሪያ የሴት ፍቅረኛው የተሠዋችበትን ቦታ ለማየት ወደ ኢትዮጵያ መጣ። በሰራዊቱ ውስጥ ስላሳለፈው የትግል ህይወት የሚተርክ “የአሲምባ ፍቅር” የተሰኘ መፅሀፍ ባለፈው ቅዳሜ የቀድሞ የኢህአፓ አባላትና ሌሎች እንግዶች በተገኙበት አስመርቋል፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ኤልሳቤት እቁባይ በአሜሪካ ከሚኖረውና በፋርማሲ ባለሙያነት ከተሰማራው ካህሳይ አብርሃ ጋር ስለ መፅሀፉ እና የትግል ህይወቱ አነጋግራዋለች፡፡

                                                    ***

በየትኛው ስም ልጠቀም---- አማኑኤል በሚለው ወይስ በበረሀ ስምህ ካህሳይ? በፈለግሽው መጠቀም ትችያለሽ፡፡ ወደ አሲምባ የገባህበትን የመጀመሪያዎቹን ቀናት እንዴት ታስታውሳቸዋለህ? ስሜቱን ልገልፀው አልችልም፡፡ ለመብት ከሚታገል ድርጅት ጋር መቀላቀል ደስታ ፈጥሮብኝ ነበር፡፡ ኑሮው ውጣ ውረድ ያለበት መሆኑ አልከበደህም? ረሀቡ፣ ጥማቱ እና ውጣ ውረዱ ያለ መሆኑን ገምቼ ስለገባሁበት እንቅፋት አልሆነብኝም፡፡ የታጠቁትን መሳሪያ ሳይ ደግሞ በጣም ደስ አለኝ። እዛ ያሉትን ጓዶች ሳያቸው የበለጠ ተደሰትኩ፡፡ በጣም አዋቂ ሰዎች ነበሩ፡፡ ከሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢ የመጡ፡፡ የኢህአፓ አባል የሆንከው ቆይተህ ነው፡፡ ለረጅም ጊዜ የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ሠራዊት (ኢህአሠ) አባል ነበርክ፡፡ ስለፓርቲው ምን ያህል እውቀት ነበረህ? ፓርቲው የበላይ አካል እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ የፓርቲ አባል ባልሆንም የሚደረጉትን ነገሮች በሙሉ አውቅ ነበር፡፡

ለምሳሌ የፓርቲው አባሎች ስብሰባ ሲያደርጉ ለፀጥታ ጉዳይና ለደህንነት በሚል መሪዎች ይነግሩናል፡፡ ስለዚህ ኮሚሳሩ “እገሌ እገሌን ይዘን እንሄዳለን” ካለኝ የፓርቲ ስብሰባ እንዳለ እናውቃለን ማለት ነው፡፡ የሆነ መመሪያ በሚወጣበት ጊዜ በመጀመሪያ የፓርቲ አባሎች ይወያዩበታል፤ ከዛ ወደ ሠራዊቱ ይመጣል፡፡ የፓርቲ አባል ስሆን በህይወት እቆያለሁ የሚል ሀሳብ አልነበረኝም፡፡ በማንኛውም ወቅት ግዳጄን ስወጣ ህይወቴ ሊያልፍ እንደሚችል ነበር የማምነው፡፡ እስቲ ይመር ንጉሴ ከተባለው የገበሬ ሚሊሻ ጋር የተገናኛችሁበትን አስገራሚ ገጠመኝና ከዛ በኋላ የሆነውን ነገር ንገረኝ … ወሎ ግዳጅ ወጥተን ጉራወርቄ በምትባል ቦታ እየሄድን የሁካታ ድምፅ ሰማን፡፡ የገበሬ ታጣቂ ሚሊሽያዎች ከኋላችን እየተከተሉን ነበር፡፡ አጠገባችን ሲደርሱ ተኩስ ከፈቱ፡፡ አንዳንድ ጓዶች ጥይት ጨርሰዋል፡፡ አንዱ በመጥረቢያ ተመትቶ ወድቋል፤ ሌላው በጩቤ ተወግቷል፡፡

ሁኔታዎች ከቁጥጥራችን ውጪ ሆነዋል፡፡ በዚህ መሀል ያነጣጠርኩበትን ገበሬ ያለምንም ጥቅም እንደምገድለው እርግጠኛ ነበርኩ። በዚያ ሁኔታ ውስጥ ነፍስ ማጥፋት ዋጋ እንደሌለው ተሰማኝ፡፡ በመተኮስና ባለመተኮስ መሀል ሳመነታ ገበሬው ሰፈረብኝ፣ ተያያዝን ወደቅን፡፡ “ጥይት አልጨረስክም፤ ለምን ተኩሰህ አልገደልከኝም” ሲለኝ “እንኳን አልገደልኩህ” አልኩት፡፡ ምን መለሰልህ? በጣም ገርሞት “ምን ማለትህ ነው” አለኝ፡፡ “አንተ ምናልባት የምታስተዳድራቸው ብዙ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ፣ እኔ የለኝም፡፡ ብትገድለኝ አንድ ብቻዬን ነኝ” ስለው በተኛሁበት በያዘው ገመድ እጆቼን ማሰሩን ተወው፡፡ የሞቱትን ጓዶቻችንን ከቀበርን በኋላ፣ ጠመንጃውን አውርዶ ወደ ሰማይ እየተኮሰ ወደእኔ መጣ፡፡ “ይህን ሰው አላስይዝም፤ መሄድ ወደሚፈልግበት እሸኘዋለሁ” ብሎ ወደቤቱ ወሰደኝ፡፡ ከዛስ? የመጀመሪያው ሌሊት እንቅልፍ የሚባል በአይኔ አልዞረም፡፡

ምክንያቱም ጠዋት ምን ሊፈጠር እንደሚችል እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ይገድለኛል? ያስረኛል? አሳልፎ ይሰጠኛል የማውቀው ነገር የለም። ስለዚህ ጠዋት ማምለጥ የምችልበትን ሁኔታ እያሰላሰልኩ ነበር፡፡ ነገር ግን ወዲያው እሱ እኔን ይዞ ሲመጣ ፈጥኖ ደራሽ መጥቶ “ይመር ንጉሴ” እየተባለ ሲጠራ ሰምቻለሁ፡፡ እሱ ግን “ምንም አትሆንም አሳልፌ አልሰጥህም፤ ወደዚህ የሚመጡና የምንታኮስ ከሆነ ወደ ደኑ ማምለጥ ትችላለህ፡፡ እኔ በህይወት ካለሁ መጥቼ እፈልግሀለሁ” ሲለኝ እሱን ከማመን ውጪ ምንም ምርጫ እንደሌለኝ አወቅሁኝ፡፡ በዚህ ወቅት ምን ተሰማህ? እኔና ይመር በህይወት ተቀያይረናል፡፡ እሱን እኔ አልገደልኩትም፤ እሱም በተራው የእኔን ህይወት አትርፏል፡፡ ከዛ ወደ ሚስቱ ዘመዶች አገር ወስዶኝ ተመልሼ አሲምባ ገባሁ፡፡ አሲምባን ስናስብ የሚመጣብን የጦርነት ታሪክ ነው፡፡ መፅሀፍህ “የአሲምባ ፍቅር” ይላል፡፡

እስቲ ስለ አሲምባ እና ፍቅር ግንኙነት ንገረኝ? አሲምባ የኢህአሰ የመጀመሪያው ቤዝ ነው። አሲምባ ላይ ብዙ ነገሮች ተካሂደዋል፡፡ ሰዎች ተገድለውበታል፡፡ ግን እኔ የማየው ከዛ በላይ ነው። ምክንያቱም የጓዶች ፍቅርና መተሳሰብ … ከብዙ የተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የተውጣጡ ግን የአንድ ቤተሰብ ያህል የሚተሳሰቡና የሚዋደዱ ነበሩ። ሠራዊቱ ከህዝቡ ጋር ህዝቡም ከሠራዊቱ ጋር ያለውን ፍቅር ያሳያል፡፡ ህዝቡ ባይፈቅድ ኖሮ እዛ መኖር አንችልም ነበር፡፡ ሌላው የአገሩ ፍቅር ነው። ጋራው፣ ሸንተረሩ፣ ወንዙ ይናፍቃል፡፡ ትግራይ፣ ወሎ፣ በጌምድር ሁሉም የሚናፈቅ ፍቅር አላቸው፡፡ የመጀመሪያ የሴት ፍቅረኛዬ እና ጓዴ የድላይ ፍቅር አለ፡፡ አንተ የፍቅር ጓደኝነት በጀመርክበት ጊዜ ፓርቲው ያንን ይፈቅድ ነበር? አይፈቅድም እንደዚህ ዓይነት ግንኙነት ተፈጽሞ ቢገኝ እርምጃው ምንድነው? በህገ ደንቡ መሠረት መባረር ነው፡፡ ግን ፍቅረኞች ነበርን እንጂ ወሲብ አልፈፀምንም፡፡ ስለ ኃይማኖት አቋምህ ስትጠየቅ የተሰማህ ስሜት ምን ነበር? ኃይማኖት ከሌለኝ ኮምኒስት አይደለህም የምባል ወይም የሚመልሱኝ መስሎኝ ስጋት ገብቶኝ ነበር ግን እውነቱን ነግሬያቸዋለሁ፡፡ እስቲ ስለ በረሀ ምግቦች ንገረኝ? ምን ነበር የምትበሉት? ቁርስ የሚባል ነገር የለም፡፡ ለምሳ ለእራትም የሚባል ራሸን የለም፡፡ ያገኘነውን ነው የምንበላው።

ዳቦም ይሁን ቂጣ ወይም እንጀራ ህዝብ የሰጠሽን ትበያለሽ፤ ህዝብ ካልሰጠሽ ደግሞ የተገኘውን ነው የምትበይው፡፡ በለስም ቢሆን … ካልተገኘ ደግሞ ውሀ ጠጥተሽ ታድሪያለሽ፡፡ ውሀም የማይገኝበት ጊዜ አለ። ያንንም መቻል ነው፡፡ አንድ ጊዜ ወደ አርባያ በለሳ ስንሄድ ውሀ በጣም ጠማን፡፡ አንድ ወንዝ አገኘን፤ ውሀው በጣም ቆሻሻ ነበር፤ ግን ትንሽ መጐንጨት ነበረብን፡፡ በነጠላ ትሎቹን እያጠለልን ትንሽ ተንሽ ቀምሰን ሄደናል፡፡ ሽንት የሚጠጡም ነበሩ፡፡ በመፅሃፍህ ውስጥ ፀጋዬ ገብረመድህን (ደብተራው) “ቅማል መቅመል ይወዳል” ብለሀል፡፡ እስቲ ስለሱ ንገረኝ…. በየጊዜው ገላ መታጠብ እና ልብስ ማጠብ አይቻልም፡፡ አኗኗራችን የትግል ነው፤ ከቦታ ቦታ ነው የምንሄደው፡፡ ጊዜ ስናገኝ እንቀማመል ነበር። በተለይ ደብተራው መቅመል ይወዳል፡፡ ልጆች ስለነበርን በቅማል ስንሰቃይ በጣም ይጨንቀው ነበር፡፡ ቅማላችንን አራግፎ ሲሰደን በጣም ነበር የሚደሰተው። እኛ ደግሞ እሱን እንቀምለው ነበር። አንድ ጊዜ በኤርትራ በኩል የመጣ መድሃኒት ነበር፤ ዱቄት ነው፡፡ በውሀ በጥብጠን ልብሳችንን እንነክረዋለን፤ ከዛ እናሰጣዋለን፤ ቅማሎች ይራገፋሉ። አንዳንዴ ለፀጉራችንም እንጠቀምበት ነበር፡፡

ግን በጣም አደገኛ ነው፤ አንዳንዶች ራሳቸውን ይስቱ ነበር፡፡ ምክንያቱም መጠኑን አናውቀውም ነበር፡፡ ሰራዊቱ የሴቶች አያያዝ ላይ እንዴት ነበር? በእኩልነት ላይ የተመሰረተ ነበር፡፡ የሴቶች ጭቆና ድርብርብ መሆኑን ያምን ነበር፡፡ የመደብ እና የፆታ ችግር እንዳለ ያምናል፡፡ ከመጀመሪያ ፍቅረኛህ ከድላይ ጋር እቃ እንድታመጣ አብራችሁ ሄዳችሁ ነበር፡፡ እስቲ ስለሱ ደግሞ … ጓዶች ሱሪህን አውልቀህ ስጣት አሉኝ፡፡ ያኔ የሚቀልዱ ነበር የመሰለኝ፡፡ “ቶሎ በል ጊዜ ስለሌለ ቶሎ አውልቀህ ስጣት” ስባል ነው ያመንኩት፡፡ ትንሽ ዞር ብዬ ነጠላዬን አገለደምኩና ሱሪዬን አውልቄ ሰጠኋት፡፡ ያኔ ሱሪዋ ቆሽሾ ይሆናል ብዬ ነበር ያሰብኩት፡፡ ወደ ማታ ደግሞ “ይዘሀት ወደ ነበለት ትገባለህ፤ የምትፈልገውን እቃ ይዛ ትመለሳለች” ሲሉኝ ለድርጅቱ ስራ አብሪያት እንደምሄድ ነበር የጠረጠርኩት፡፡ እሷን ስጠይቃት ግን ሞዴስ ላመጣ ነው አለችኝ፡፡ ምን እንደሆነ ስጠይቃት ብትነግረኝም አልገባኝም፡፡

በመንገድ ላይ ስኮረኩራት ስኮረኩራት ነው ምን እንደሆነ የነገረችኝ፡፡ ፍቅረኛህ ድላይ በተደጋጋሚ ውሳኔህን እንድታሳውቃት ታስጠነቅቅህ ነበር፡፡ ሰራዊቱን ትተህ ወደ ሱዳን ለመውጣት ስታስብ ለመንገር ባትችል እንኳን ለምን መልዕክት አልላክባትም? ሱዳን ሆኜ ተስፋይ ኢዲዩ ደብዳቤ ላድርስልህ ቢለኝም የምልከው በነሱ ከሆነ ያነቡታል፤ ስለዚህ የግል ሚስጥር የሚባል ነገር የለም፤ ለዚህ ነው ደብዳቤውን ያልላኩት፡፡ አሲምባ የሠራዊቱ ፍርድ ቤት ነበር፡፡ አንተም ተከሰህ ለፍርድ ቀርበህ እንደነበር በመፅሃፉ ገልፀሃል። የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ፍትሀዊ ነው የሚል አዝማሚያ በፅሁፍህ ላይ ይንፀባረቃል፡፡ እውነት ፍትሀዊ ነበር ትላለህ? ለኔ በጣም ፍትሃዊ ነው፡፡ እኔ ከስሼም ተከስሼም ስለማላውቅ አማካሪ ያስፈልገዋል ተባልኩ፡፡ በዚህ ምክንያት ነው ሰላማዊት ጠበቃዬ የሆነችው፡፡ መከሰሴን ተገቢ ነው ባልልም ውሳኔው ግን ጥሩ ነበር። ፀሎተ ህዝቅያስ በፍርድ ቤት ውሳኔ ነው የተገደለው? መፅሐፍህ ላይ “ፀሎተን ደጀኔ ገደለው፣ ደጀኔን ዳዊት ገደለው፣ ደብተራው ወደ ላይ እየተኮሰ መጣ” ብለህ ነው የገለፅከው፡፡ ምንድን ነበር የሆነው? ያየሁትን ብቻ ነው የምናገረው፡፡ ፀሎተ ገና ሳይሞት ነው የደረስኩት፤ ደጀኔ ሞቶ ነበር፡፡ ይሄ የፍርድ ቤት ውሳኔ አይደለም፡፡

በዛን ጊዜ ማንኛውም የአመራር አባል ለደህንነቱ ሲባል የሚሄድበትን ይነግረናል፡፡ ጠዋት ደብተራው መጣና “ደጀኔና ፀሎተ ወደ ወንዝ ለመታጠብ ሄደዋል፤ ጥበቃ እንዲደረግላቸው” ሲለኝ የተባለው ተደረገ፡፡ በተለይ ፀሎተ የአመራር አባል ስለሆነ ጥበቃው ጠንከር ይላል፡፡ ከዛ ደብተራው ትንሽ ቆይቶ ተመለሰና “እኔና ዳዊት ይህ ቦታ ስለጠበበን ፊትለፊት ካለው ጋራ ቤት እናያለን፤ ስለዚህ ጥበቃ ይደረግ” አለ፤ ያንን አደረግን። ወድያው የሁለት አውቶማቲክ መሳሪያ ተኩስ ሰማን፡፡ መጀመሪያ እኔ ወደ ወንዙ ስደርስ ደብተራው ወጥቶ ሽጉጥ ወደሰማይ ይተኩሳል፡፡ እርዳታ ፈልጐ ይመስለኛል፡፡ እኔ ከደብተራው በስተቀር ሁሉም የተገደሉ ነበር የመሰለኝ ፡፡ ደብተራውን ምን ተፈጠረ ብዬ ስጠይቀው “ደጀኔ ፀሎተን ገደለው፤ እኛ ደግሞ ደጀኔን ገደልነው” አለኝ፡፡ ደጀኔ ሞቷል፤ ፀሎተ አልሞተም ነበር፡፡ ዳዊት ጭንቅላቱን ይዞ ሲያለቅስ ነበር፡፡ ፀሎተን ወደ ጥላ ወሰድነው፤ ከዛም ብዙ ሳይቆይ ሞተ፡፡ የዕበዮ፤ የኢህአሰ ሰራዊት ውቅሮ ላይ ባደረገው ውጊያ ነው የተገደለው፡፡ ከሱ ጋር ያለውን ተያያዥ ታሪክ ንገረኝ… የዕበዮ የውቅሮ ልጅ ነው፡፡

ስለዚህ ውቅሮ በሚደረገው ውጊያ እንዳይገባ ተወስኖ አይሆንም ብሎ ተከራክሮ ነበር ወደ ውጊያው የገባው፡፡ በውጊያው ከተሰዋ በኋላ በህይወት የተረፍነው እሱን ስንቀብር ሌሎቹ ጓዶች “አንገቱ ይቆረጥና ይቀበር፤ ምክንያቱም ደርግ የእሱ አስከሬን መሆኑን ከለየ መንገድ ላይ ያወጣዋል” ሲሉኝ “አይኔ እያየ አንገቱን አይቆረጥም” ብዬ ሳይቆረጥ ተቀበረ፡፡ እኔ ሠራዊቱን ትቼ ሱዳን ከገባሁ በኋላ ደርግ በማግስቱ አስከሬኑን ስለለየው ውቅሮ ከተማ መንገድ ላይ አስከሬኑን በመዘርጋቱ፣ እናቱም ያንን አይታ የአዕምሮ ህመምተኛ እንደሆነች ሰማሁ፡፡ ዛሬ ላይ ሳስበው ተቆርጦ ቢሆን ኖሮ እናቱ ትድን ነበር እላለሁ፡፡ ያን ጊዜ ግን የምወደውን ሰው አንገት ቆርጦ ለመውሰድ ህሊናዬ አልፈቀደልኝም፡፡ በበጌ ምድር፣ በባሕር ዳር በየከተማው የነበረውን የኢህአፓ እንቅስቃሴ በቅርበት ታውቁ ነበር? በረሃ በወጡት የፓርቲው ተወካዮች በኩል የምንሰማው መረጃ እንጂ ሌላ እውቀት የለም፡፡ ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ጋር ስትገናኙ እንዴት ነበር? የተገናኘው በ1968 ዓ.ም ነው፡፡ ከራዛ ጦርነት በኋላ የተገኘውን መሳሪያ ለመውሰድ ኤርትራ ውስጥ መነኩሲቶ የምትባል ቦታ ሄድን፡፡ አቶ መለስን አይተነው፤ ስለሱ ሰምተንም አናውቅም ነበር፡፡ እሱ የሆነ መልዕክት ይዞ የመጣ ይመስለኛል፡፡ ለሊቱን በመደዳ ተኝተን አሳለፍን፡፡ በቆይታችን ስለነበረን ልዩነቶች ተነጋግረናል፡፡ የሀሳብ ልዩነት ላይ መስማማት ስላልቻልን “ብሬይን ወሽድ ስለሆናችሁ እናንተን ማሳመን አይቻልም” አለን፡፡

ቃሉን ለመጀመሪያ ጊዜ ስለሰማሁት ፃፍኩትና ወደ ቦታችን ስንመለስ፣ መለስ ያለንን ነገርኳቸውና ምን ማለት እንደሆነ አስረዱኝ፡፡ ከህወሓት እና ከኢህአፓ ህዝቡ የቱን እንደሚመርጥ ሪፈረንደም አድርጋችሁ ነበር፡፡ እስቲ ምንድነው የሆነው? በወቅቱ የአንድ መንደር ህዝብ አስተዳዳሪው የቱ እንደሚሆን ይመርጥ ነበር፡፡ ከሁለቱ ድርጅቶች በየቱ መተዳደር ትፈልጋላችሁ ይባልና ውሳኔው ተግባራዊ ይደረጋል፡፡ ወያኔ ካለ እኛ እንለቃለን፤ ኢህአፓ ካሉ እነሱ ይለቃሉ፡፡ ህዝቡ ተወካዩን እንዲመርጥ እናደርጋለን፡፡ ታድያ ሁኔታዎች ለምን ተበላሹ? በሁለቱ ድርጅቶች መካከል የተፈጠረው ነገር በኔ ደረጃ የሚገለፅ አይደለም፤ እኔ ተራ ታጋይ ነበርኩ፡፡ ከበለሳው ቡድን በኋላ ኢህዴን/ብአዴን ከሆኑት ማንን ታውቃለህ? ያኔ አብረውን ከነበሩ ሰዎች እንደሰማሁት አርባፀጓር ላይ አቶ በረከት ስምኦን አጠገቤ እንደነበሩ ነግረውኛል፡፡ ግን አንተዋወቅም፡፡ አቶ በረከትም ከቤጌምድር ጋንታ መጥቶ ነበር፡፡ ከደብተራው ጋር ከነበራችሁ ፍቅር የተነሳ ስትለያዩ ማስታወሻ ስጠኝ ብለኸው ለማስታወሻነት መሳሪያችሁን ተለዋውጣችኋል፡፡ የደብተራው ማስታወሻ መሳሪያ የት ገባች? ከደብተራው ጋር ለየት ያለ ፍቅር ነበረን፡፡ በኔ ላይ ጥሩ እምነት ነበረው፡፡

ስለ አማኑኤል ጥሩ እንጂ መጥፎ ነገር አትንገሩኝ ይል እንደነበር አሁን በህይወት ያሉ አመራሮች ይነግሩኛል፡፡ ስንለያይ ብረት ተለዋወጥን፡፡ ወደ ሱዳን ስሄድ በኤርትራ በኩል ስለሆነ ለኤርትራ ድርጅት አስረከብኳት፡፡ ሳስረክባት እውነቴን ነው እሱንም ያስረከብኩት ነው የመሰለኝ፡፡ ኢህአፓ እና ኢህአሠ የተቆራኙ ወይም የሚናበቡ አይመስሉም፡፡ ወታደራዊ ግዳጆቹ የተበጣጠሱ ናቸው፡፡ ስለዚህ ጉዳይ ምን ትላለህ? እኔ በማውቀው ደረጃ ያንቺን ጥያቄ መመለስ ይከብደኛል፡፡ እኛ ዛሬ እዚህ ትሄዳላችሁ ስንባል እንሄዳለን፤ ውጊያ ታካሂዳላችሁ ሲባል እንፈፅማለን። ፓርቲው ሠራዊቱን ያዛል፤ ሠራዊቱ ይፈፅማል፤ በየክፍሉ የፓርቲ ወኪሎች አሉ፡፡ በሠራዊቱ ውስጥ የነበረው የተማሩና ያልተማሩ አባላትን ልዩነት ንገረኝ? እኛ የታዘዝነውን እንፈፅማለን፡፡

አንዳንድ የተማሩት እኛን “የአመራር ቡችሎች” እና “ክሊኮች” ይሉናል፡፡ እኛ ስለፓርቲው ጠልቀን አናውቅም፤ እነሱ ስለፓርቲው ድክመትና መፈረካከስ ያውቃሉ፤ በዚህ መሀል መናበብ የለም፡፡ ያኔ እነሱ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ ናቸው፤ እኛ ደግሞ ለምን የታዘዙትን አይፈፅሙም እንላለን፡፡ እኛ ስላልተማርን ንቀውን ሳይሆን ውስጣችን የተለያየ ነገር ስለነበር ነው፤ በአቅምም እንድናድግ ጥረት ይደረግ ነበር፡፡ ለምሳሌ ጓድ ሽፈራው “The military Tactic of the Vietnamese Revolution” የሚል መፅሐፍ አስነብቦናል፡፡ ኢህአፓ/ኢህአሠ ለምን ፈረሰ? ብዙ ብቃት ያላቸው ለመስዋእትነት ዝግጁ የሆነ ሠራዊት ነበረው፡፡ ድርጅቱ ለምን ፈረሰ በኔ አቅም አይመለስም፡፡ ልዩነቶች እንደነበሩ እንሰማ ነበር፡፡ እኛ በይፋ የተነገረን በ1970 ቢሆንም ችግሩ ከ1968 ጀምሮ የነበረ ነው፡፡ ብርሃነመስቀል ከድርጅቱ ወጥቷል ይባል ነበር፡፡ ያንን የፓርቲ አባሎች ያውቃሉ፡፡

እኛ ግን በሀሜት ደረጃ እንጂ በይፋ አልተነገረንም፡፡ ድርጅቱ እየተከፋፈለ አንጃ ተብለው ታስረው የተገደሉ አሉ። በጣም የምንወዳቸውና የምናከብራቸው መዝሙር፣ በሽር፣ ታሪኩ የተባሉ እና ሌሎችም ተገደሉ፡፡ ብዙ ጓዶች በዚህ ላይ ቅሬታ ነበራቸው፡፡ ከኤርትራና ከወያኔ ጋር የነበረን ግንኙነት መሻከር ተደማምረው ይመስለኛል ለመፍረስ የበቃው፡፡ “የአሲምባ ፍቅር” … ይቅርታ ጠይቀን አስቆምናቸውና “እዚህ አካባቢ የሚኖር ሰው ብጠይቃችሁ ታውቃላችሁ?” አልናቸው፡፡ አንደኛው ሰውዬ “መሃመድ እባላለሁ፤ እዚሁ አካባቢ ነው ሀገሬ ፣እዚህ ወጣ ብሎ ይሄንን ጋራ ተሻግራችሁ ነው፡፡ ማንን ፈልጋችሁ ነው? ስሙን ታውቃላችሁ?” አሉን፡፡ “ይመር ንጉሴ የሚባል ሰው” አልኳቸው “ይመር ንጉሴ? ወይ ወንድሜን!” ብለው ጭንቅላታቸውን ይዘው ማልቀስ ጀመሩ፡፡ ልቤ ስንጥቅ አለ፡፡

የሆነውን መጠየቅ አስፈላጊ አልነበረም፤ አውቄዋለሁ፡፡ እውነቱን መቀበል ግን አልፈለግኩም፡፡ ለመናገር መዘጋጀቴን ሳላውቀው ከአፌ ምነው? የሚል ቃል ሲወጣ በጆሮዎቼ ተሰማኝ። “ይመር ንጉሴ እኮ ሞቷል!” አሉ፡፡ “እንዴት ሆኖ?” “በቃ እንዴት እንደሆነ አላወቅንም፤” የወያኔ ታጋዳዮችና በርካታ መሪዎች አውቅ ነበር፤ ብዙዎቹን በአካል ሌሎቹን ደግሞ በዝናና በወሬ ደረጃ ስማቸውን ሰምቻለሁ፣መለስን ግን ያየሁትም ሆነ ስሙን የሰማሁት ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡ መለስ የለበሰው የዘማቾች ካኪ ዩኒፎርም ሲሆን አንድ ቦርሳ ሙሉ መፅሃፍ ይዟል፡፡ ሰውነቱ ጠንካራ፣ ከመካከለኛ ሰው ትንሽ አጠር ያለ ቁመት ያለው፣ ክብ ፊትና ንቁ ዓይኖች ያለው ሰው ነው፡፡ መለስ ጨዋታና ቀልድ የሚያውቅ፣ ሃለኛ ተከራካሪ፣ በውይይት ጊዜ ፊቱን ቅጭም የሚያደርግና የሚመሰጥ እንደሆነ በዛን ቀን ቆይታችን አስተውያለሁ፡፡…የምንከራከረው እኔና አስመሮም ከአንድ ወገን፣ መለስ ደግሞ ብቻውን ስለነበር ውይታችን አድካሚ ሳይሆንበት አልቀረም። እርሱ ግን እንዲህ በቀላሉ ደክሞት የሚተው ሰው አልነበረምና እኛን ለማሳመን ብዙ ደከመ።

በመጨረሻም ከሀሳቡ መደጋገም በቀር አዲስ ነገር እያለቀብን ሲመጣ፣ “ብሬይን ወሸድ(brain washed) ስለሆናችሁ፣ እናንተን ማሳመን አይቻልም” አለ፡፡ ጸጋዬ ደብተራውን በጣም ስለምወደው “አሁን ጎንደር ከሄድኩ ላንገናኝ እንችላለንና አንተን ማስታወሻ የሚሆነኝ አንድ ነገር ስጠኝ” አልኩት፡፡ እሱም ሳቅ አለና ትንሽ ካሰበ በኋላ “እንካ ጠመንጃዬን ልቀይርህና ማስታወሻ ይሆንልሃል” ብሎ ሰጠኝ፡፡ የእርሱን ወስጄ የእኔን ሰጠሁትና ተቃቅፈን ተሳሳምን፡፡ ሁለቱም የክላሽን ኮቭ ጠመንጃዎች ነበሩ፤ምንም ልዩነት የላቸውም፡፡ ቢያንስ አንዳንዴ ጠመንጃዬን ሳይ ግን እሱን ያስታውሰኛል ብዬ በጣም ደስ አለኝ፡፡

… በጣም ግራ ገባኝ “ከሴት አስተማሪዎች የምትቀበይው ወይም ደግሞ የምታመጪው ምን እቃ ነው?” ብዬ እንደገና ስጠይቃት ሳቀች፡፡ “አንተ አታውቀውም፣ የሴት እቃ ነው፣ አማኑኤል” አለችና እንደገና አከታትላ “አማኑኤል እኔ እኮ አሞኛል፡፡ ቀኑን በሙሉ ያንተን ልብስ ለብሼ እንደዋልኩ ታውቅ የለ፡፡ የእኔ ሱሪ ተበላሽቶ ስለነበር ለማጠብ ነበር የአንተን ለብሼ ወደ ወንዝ የወረድኩት” ብትለኝም ችግሯን በትክክል አልተረዳሁትም፡፡ “ታዲያ ምንድን ነው የምናመጣው?” “እቃው ሞዴስ ይባላል” አለችኝ፡፡ “ሞዴስ ምንድነው?” “ሞዴስ ሴቶች ብቻ የሚጠቀሙበት የሴት እቃ ነው፡፡ ወንዶች ብዙም አታውቁትም” አለችና ለአፍታ ያህል ስታስብ ቆየች፡፡ “ወንዶች እኮ እንደዚህ ዓይነት ነገር ስለማታውቁ ታድላችኋል” በድምጿ ውስጥ ሐዘን ተሰማኝ፤ ችግሩ ወይም ሕመሟ ቀላል እንደሆነ ተረዳሁ፡፡ ግን ምን እንዳመማት በትክክል አልተረዳሁም፡፡ “ሞዴስ” የሚለውን ቃል ስሰማ ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር፡፡ አሁን ግን የሴት እቃ ከመሆኑ ሌላ ያሽልሻል ማለት ነው?” አልኳት፡፡ (በካህሳይ አብርሃ ብስራት ተፅፎ ባለፈው ቅዳሜ ከተመረቀው “የአሲምባ ፍቅር” መፅሃፍ የተቀነጨበ)

(1. የእንግሊዝኛ ቋንቋ 2. ኮምፒዩተር 3. ኢንተርኔት … ናቸው ስጦታዎቹ። መፃህፍት እንደልብ ለማንበብና ስኬትን ለመቀዳጀት) እውቀት የዶ/ር ቤን ካርሰን ታሪክ ምስክር ነው። በህፃንነቱ “ደደብ ነኝ” ይል ነበር - ትምህርት ጨርሶ የማይገባው። ከድህነት ጋር በምትታገል እናቱ ግፊት መፅሃፍ ማንበብ ጀመረ። በአንጎል ቀዶ ህክምና በቀዳሚነት የሚጠቀስ ሃኪም ለመሆን በቃ። በ2016 ለአሜሪካ ፕሬዚዳንትነት ይወዳደራል ተብሎ ይጠበቃል። “ተአምር” መስራት የሚቻልበት ዘመን ላይ ደርሰናል። ከሃያ አመታት በፊት በፍፁም የማይሞከሩ ነገሮች፣ ዛሬ በቀላሉ በመዳፋችን ውስጥ ልናስገባቸው እንችላለን። እስቲ አስቡት። በዚህ ሳምንት ብቻ፣ ከሁለት ሺ በላይ በእንግሊዝኛ የተፃፉ አዳዲስ የልብወለድ ድርሰቶች በኢንተርኔት አግኝቼ ኮምፒዩተሬ ውስጥ አስቀምጫለሁ - በ2012 እና በ2013 የታተሙ ተወዳጅ (bestseller) መፃህፍት ናቸው። በመቶ እና በሺ የሚቆጠሩ አዳዲስ መፃህፍት ማግኘት ይቅርና፣ ሦስት አራት አዳዲስ መፃህፍት ማግኘት ምን ያህል ብርቅ እንደነበር አታስታውሱም? ለነገሩ፣ ለብዙ ሰዎች ዛሬም ድረስ ብርቅ ነው።

የልብወለድ ድርሰቶችን ለጊዜው እንርሳቸው። ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ እስከ ሃይስኩል፣ የሂሳብም ሆነ የተፈጥሮ ሳይንስ መማሪያ መፃህፍት፣ ከዩኒቨርስቲ የ‘ፍሬሽማን’ ትምህርት እስከ ማስተርስ ዲግሪ ድረስ፣ ከኤሌክትሪክ ምህንድስና እስከ ሕክምና፣ ከቢዝነስ ማኔጅመንት እስከ አለማቀፍ ዲፕሎማሲ… በመላው አለም እጅግ የሚፈለግ ውድ መፅሃፍ በየአይነቱ “በገፍ” ቢቀርብልን ብላችሁ አስቡ። ባለፉት ምዕተ አመታት የተፃፉ ዘመን የማይሽራቸው የሳይንስ መፃህፍትን ከፈለጋችሁ… ሞልቷል። አዳዲስ የዘመናችን ምርጥ የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂና የመማሪያ መፃህፍትም እንደልብ ነው። እድሜ ለኢንተርኔት! በሺ ከሚቆጠሩት የትምህርት መፃህፍት መካከል፣ ለሙከራ ያህል ሁለት መቶ የሚሆኑትን ሰሞኑን ኮምፒዩተሬ ላይ ጭኛቸዋለሁ። አንዳንዶቹን ገለጥ ገለጥ አድርጌ አይቻቸዋለሁ። ባለፈው አመት ወይም ባለፉት ስድስት ወራት የታተሙ አዳዲስ የትምህርት መፃህፍትን እንዲህ እንደልብ ማግኘት “ተአምር” አይደለም? በቢዝነስ ጉዳዮች ዙሪያ እንደ ፎርብስ እና ዘ ኢኮኖሚስት የመሳሰሉ መፅሄቶች ሞልተዋል። የቴክኖሎጂና የሳይንስ ዘገባዎችን ወይም የጥናት ውጤቶችን ለመከታተልም፣ እንደ ፖፑላር ሜካኒክስ፣ ኔቸር፣ ዋየርድ፣ ናሽናል ጂኦግራፊ የመሳሰሉ መፅሄቶች አሉ። አዳዲስ የሰሞኑ እትሞቻቸውን በኢንተርኔት ወደ ኮምፒዩተሬ ገልብጬ አየት አየት እያደረግኳቸው ነው።

ስልጡን የፖለቲካ ባህል በቀጥታ ለማየት የሚፈልግ ካለም ምንም አይቸገርም። የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ወይም ቃል አቀባያቸው ለጋዜጠኞች የሚሰጡትን መግለጫ በቀጥታ መከታተል ይችላል። በአሜሪካ፣ የኮንግረስና የሴኔት ምክር ቤት ውስጥ የሚካሄዱ ክርክሮችን፣ በዚያው ሴኮንድ በቀጥታ ሲሰራጩ መመልከትስ? ከአራቱ የሲ-ስፓን ቻናሎች መካከል እያማረጡ መመልከት ነው። የምክር ቤት አባላት፣ የአክብሮት ስነምግባርን ሳይጥሱ፣ የመንግስት ሚኒስትሮችንና ከፍተኛ ባለስልጣናትን ወጥረው ሲያፋጥጡ ይታያሉ። የሳይንስና የቴክኖሎጂ ሰዎች እድሜ ይስጣቸውና፣ እንደየዝንባሌያችን እያማረጥን ያሻንን ያህል ማንበብና መከታተል የምንችልበት ዘመን ላይ ደርሰናል። ሙሉ ትኩረታችንን የሚጠይቅ ትምህርታዊ መፅሃፍ ማንበብ፣… ምን ያህል እንደሚመስጥና እንደሚያስደስት ታውቁት ይሆናል። ግን በየመሃሉ አረፍ ብሎ መንፈስን ማደስ ያስፈልግ የለ? ለምሳሌ፣ ቀለል ያለ፣ ልብ አንጠልጣይ የልብወለድ ድርሰት ማንበብ፣ ጥሩ የመዝናኛ ዘዴ ነው። ምን ጠፍቶ! አምናና ዘንድሮ በአሜሪካ የታተሙ አዳዲስ የልብወለድ መፃህፍት ሰሞኑን “በገፍ” አግኝቻለሁ።

ግን፣ በ20ኛው ክፍለዘመን፣ በልብ አንጠልጣይ የልብወለድ ድርሰት ገንነው ከሚጠቀሱ ደራሲዎች መካከል አንዱ የሆነው ሚኪ ስፕሌን ትዝ አለኝ። የስፕሌን ድርሰት ባገኝ… ብዬ በኢንተርኔት ፈለግሁ። 13 ድርሰቶቹን አገኘሁና፣ በ5 ደቂቃ ውስጥ ሁሉንም ወደ ኮምፒዩተሬ ገለበጥኳቸው። አንዱን መርጬ አነበብኩታ። በእርግጥም ዘና አደረገኝ። በዚያው አጋጣሚ ግን፣ በቪዲዮ፣ በድምፅ እና በፅሁፍ የተዘጋጁ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያዎችን አይቻለሁ - ብዛታቸውና አይነታቸው እንዲህ ቀላል አይደለም። ከነባሮቹና ከአዳዲሶቹ የቋንቋ መማሪያዎች መካከል እየመረጥኩ ወደ ኮምፒዩተሬ መገልበጥ ነው የሚቀረኝ። በመላው አለም በጣም የሚፈለጉ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማስተማሪያ መፃህፍትን ብቻ ሳይሆን፣ በድምፅና በቪዲዮ የተዘጋጁ አጋዥ መማሪያዎችን እንደ ልብ ማግኘት! “ምናለ፣ ይሄ ሁሉ እድል፣ ከአስር አመት ከሃያ አመት በፊትም በኖረ” ብዬ መቆጨቴ አልቀረም። ግን፣ አሁን መገኘቱም “ተአምር” ነው። ይልቅ፣ ይህን እድል ለመጠቀም መትጋት ነው የሚሻለው። ቀለል ባለ ልብወለድ መፅሃፍ ዘና ካልኩ በኋላ ወዲያውኑ ለሥራዬ በቀጥታ የሚጠቅመኝን መፅሃፍ ላነብ አልኩና… እንደአጋጣሚ ሃሳቤን ቀየርኩ። አልነገርኳችሁም እንጂ፤… በዚህ ሳምንት፣ ከልብወለድ ድርሰቶች በተጨማሪ፣ አንድ ሺ የሚሆኑ አዳዲስ “የሕይወት ታሪክ” መፃህፍትንም በኢንተርኔት ወደ ኮምፒዩተሬ ገልብጫለሁ።

ታዋቂው ሥራ ፈጣሪና ቢሊዮነር ሪቻርድ ብሮንሰን በ2011 ያሳተመው የግል የህይወት ታሪክ፣ የአሜሪካዊቷ ፖለቲከኛ ሳራ ፓይሊን፣ የበርማዊቷ የፖለቲካ መሪ አንሷን ሱኪ የህይወት ታሪኮች … በኢራቅ ጦርነት ብዙ አሸባሪዎችን በመግደል ሪከርድ የሰበረው ክሪስ ካይል ያሳተመው መፅሃፍ ሳይቀር… ብቻ ምን አለፋችሁ? በያዝነው የሰኔ ወር “ቤስትሴለር” ሰንጠረዥ ውስጥ ቁንጮውን ቦታ የተቆጣጠሩ መፃህፍት ሁሉ ቁጭ ብለው ለመነበብ ይጠብቃሉ። አንድ በአንድ አየኋቸው… የቀድሞው የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ቶኒ ብሌር ያዘጋጁት መፅሐፍ፣ የጆርጅ ቡሽ መፅሃፍ… እነዚህ ቆየት ያሉ ናቸው። ሌላ ጊዜ አነባቸዋለሁ። አዳዲሶቹንም አየሁ - ታዋቂው የአንጎል ቀዶ ህክምና ባለሙያ ዶ/ር ቤን ካርሰን ያሳተሙት መፅሃፍ ላይ ደረስኩ። በቅርቡ ከፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ጋር በትልቅ አመታዊ ጉባኤ ላይ ንግግር እንዲያቀርቡ ተጋብዘው የነበሩት ጥቁሩ አሜሪካዊ ቤን ካርሰን፣ ኦባማን በመተቸት ባቀረቡት የግማሽ ሰዓት ንግግር “አጃኢብ” ሲባልላቸው እንደሰነበቱ አውቃለሁ። ከኦባማ ጋር የሚያለያያቸውን ሃሳብ ዶ/ር ካርሰን ሲገልፁ፣ ድሆችን እንደግፋቸው በሚል ሰበብ የአገሪቱ ዜጎች የመንግስት ጥገኛ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው በማለት ተናግረዋል።

አሜሪካ የተመሰረተችው ግን፣ ዜጎች ምንም ድሃ ቢሆኑ እንደየጥረታቸው ራሳቸውን ችለው የሚበለፅጉባት የነፃነት አገር እንድትሆን ነው ይላሉ - ዶ/ር ካርሰን። ይህን ሃሳባቸው ለማስረዳትም ነው አዲስ መፅሐፍ ያሳተሙት። ሃብታሞችንና ድሆችን የሚለያቸው ምንድነው? ዶ/ር ካርሰን ስለ ድህነትም ሆነ ስለ ሃብታምነት ቢናገሩ ያምርባቸዋል። ያለፉበት ሕይወት ነው። ከችጋር ወደ ብልፅግና እንዴት እንደተሸጋገሩ መነሻና መድረሻውን ያውቁታል። መፅሃፋቸውን አግኝቼ ላነበው ከተዘጋጀሁ በኋላ ነው፣ ካሁን በፊት ያሳተሟቸውን የመፃህፍት ዝርዝር ያየሁት። የመጀመሪያው መፅሃፍ “ጊፍትድ ሃንድስ” በሚል ርዕስ የታተመ ነው። ርዕሱን አስታወስኩት። መፅሃፉን ባላነበውም፣ ፊልሙን አይቼዋለሁ። ለካ፣ ኩባ ጉዲን የተወነበት ያ ምርጥ ፊልም፣ በዶ/ር ቤን ካርሰን የህይወት ታሪክ ላይ የተመሰረተ ነው። ከልጅነት እስከ እውቀት፣ የሕይወት ታሪካቸውን ባሰፈሩበት መፅሃፍ ውስጥም፣ ወደ ኋላ መለስ ብለው በድህነትና በ“ደደብነት” ያሳለፉትን የልጅነት ጊዜ ይተርካሉ። ስኬታማ ሰው ለምልክት ያህል በማይታይበት የድሆች ሰፈር ውስጥ ነው፣ ሕፃኑ ቤን ካርሰን ያለ አባት ያደገው። “እንደ እገሌ ስኬታማ እሆናለሁ” የሚያስብልና በአርአያነት የሚጠቀስ ሰው አልነበረውም - በቤተሰቡም ሆነ በሰፈሩ ውስጥ። ያልተማረችና ማንበብ የማትችል የካርሰን እናት፣ ሁለት ልጆቿን ለማሳደግ ያላየችው መከራ የለም። የሃብታሞችን ሰፈር ስታካልል ነው የምትውለው።

የሃብታሞችን ቤት በማፅዳት በምታገኛት አነስተኛ ገቢ ካርሰንና ወንድሙ ፆም እንዳያድሩ ብቻ ሳይሆን፣ ከትምህርት እንዳይርቁም ከንጋት እስከ ምሽት ትሰራለች። የእለት ተእለት ልፋቷ ትዕግስትን የሚፈታተን ቢሆንም፣ እጅግ የሚከነክናትና የሚያንገበግባት ግን፣ የድካሟን ያህል ውጤት አለማየቷ ነው። ልጆቿ፣ በየእለቱ ወደ ትምህርት ቤት መሄዳቸው ባይቀርም፣ ጠብ የሚል እውቀት አልቀሰሙም። ካርሰን እንደ ወንድሙ ክፍል ውስጥ “ሲማር” ይውላል፤ አስተማሪ አንዳች ጥያቄ ሲሰነዝር፣ ሌሎቹ ተማሪዎች መልስ ለመስጠት ይሻማሉ - እውቀታቸውን ለማሳየት። ግን፣ ካርሰን ሲጠየቅ ማየትም ያጓጓቸዋል - መመለስ ሲያቅተው ወይም ከጥያቄው ጋር የማይገናኝ ነገር ሲዘባርቅ መሳቅ ለምደዋል። ፈተና ሲመጣ፣ ካርሰን ከሌሎቹ ተማሪዎች ጋር አብሮ ይፈተናል። ተማሪዎች የፈተና ውጤታቸውን በኩራት ይናገራሉ፤ 25 ከ25 የሚደፍን ይኖራል፣ አነሰ ቢባል 20 የሚያመጣም ይኖራል። ካርሰን ድምፁን ዝቅ አድርጎ የራሱን ውጤት ይናገራል። አስተማሪዋ በደንብ አልሰማቸውም… “Nine?” በጣም ጥሩ ነው፤ 9 ከ 25? በጣም ተሻሽለሃልሳ! አለችው... ደስ ብሏታል። ካርሰን አስተማሪዋን ሊያርማት ይሞክራል - “Nine” ሳይሆን፣ “None” በማለት። ከፈተናው ጥያቄዎች ውስጥ አንዱንም በትክክል አልመለሰም፤ ዜሮ ነው ያመጣው። እንደተለመደው ተማሪዎቹ ይስቁበታል። ሲስቁበት አይከፋውም።

ራሱም ቢሆን፣ “ትምህርት አይገባኝም፣ ደደብ ነኝ” ብሎ በግልፅ ይናገራል። እናቱ ግን በዝምታ አታልፈውም። “ደደብ አይደለህም፤ አንጎል አለህ አይደለም?” ትለዋለች። “አዎ” ይላል እያመነታ። “ስለዚህ፤ አንጎልህን ተጠቀምበት። አለም ሁሉ በእጅህ ናት” ትለዋለች። ባትማርም፣ በጣም አስተዋይና ብልህ እናት ናት። የካርሰን እናት፣ ልጆቿ ስኬታማ መሆን እንደሚችሉ ከምር ታምናለች። እንዴት ስኬታማ እንደሚሆኑ ነው ያላወቀችው። ማሰብ ማሰላሰሏን ግን አላቋረጠችም። የሰፈሯን የድህነት አኗኗር በደንብ ታውቀዋለች። የሃብታሞች ሰፈር ሄዳ ቤት ስታፀዳም አኗኗራቸውን ትመለከታለች። ድሆቹንና ሃብታሞቹን የሚያለያቸው ምንድነው? አስተዋይ መሆኗ ጠቀማት። አንድ ቀን፣ በሃብታም ቤተሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ ሰፊውን ክፍል እያፀዳችና ቴሌቪዥን የተቀመጠበትን አካባቢ እየጠራረገች ሳለ… ተገለጠላት። ተደራርበው የተቀመጡት መፃህፍት ቴሌቪዥኑን በከፊል ከልለውታል። አንዳንዶቹ መፃህፍት ገለጥ ገለጥ ተደርገው ተቀምጠዋል። ቀና ስትል… ያን የሚያክል ሰፊ ክፍል፣ ከወለል እስከ ጣራ ድረስ… መደርደሪያው ሁሉ በመፃህፍት ተጠቅጥቋል። በቃ! ገባት። ያን እለት በየቦታው ለሥራ ስትደክም ውላ ማታ ወደ ቤት ስትመለስ፣ ካርሰንና ወንድሙ አሮጌ ቴሌቪዥን ላይ አፍጥጠው አገኘቻቸው። ቴሌቪዥኑን አጠፋችው። “ከዛሬ ጀምሮ፣ ቴሌቪዥን የምታዩት በሳምንት ሁለት ቀን ብቻ ነው” አለቻቸው።

ለምሳሌ፤ የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ማየት ይችላሉ። “ሁለት ቀን ብቻ? ሌላውንስ ጊዜ ምን እንሰራበታለን?” ብለው ጠየቁ። “ይህንን ጥያቄ ነበር ከናንተ የምጠብቀው። ምን እንደምታደርጉ እነግራችኋለሁ። ቤተመፃህፍት ትሄዳላችሁ። በሳምንት ሁለት መፅሃፍ ታነባላችሁ” ስትላቸው፣ የምሯን አልመሰላቸውም። መፅሃፍ ማንበብ የሚባል ነገር በእውናቸውም በህልማቸውም መጥቶላቸው አያውቅም። እንግዲህ ምን ይደረጋል? ከቤተመፃህፍት በውሰት መፅሃፍ ማምጣት የግድ ቢሆንም፣ የውሸት “አንብቤዋለሁ” ብሎ መመለስ እንደሚቻል ማሰባቸው አልቀረም። ሃሳባቸውን ያወቀች ይመስል፣ ሌላ ትዕዛዝ ጨመረችላቸው። “ያነበባችሁትን ቁምነገር፣ በየራሳችሁ አገላለፅ አሳጥራችሁ ትፅፉና ለኔ ትሰጡኛላችሁ” አለቻቸው። መፅሃፍ ማንበብ፣ ለካርሰንና ለወንድሙ ቀላል አልሆነላቸውም። ትግል ነው። ግን ደግሞ፣ መፃህፍቱ ውስጥ በሚያገኟቸው አስደናቂ ታሪኮችና እውቀቶች… ተገርመዋል። እስካሁን የማያውቁትና ጨርሶ ያልጠበቁት አይነት ልዩ ደስታ አግኝተውበታል። ብዙም ሳይቆይ፣ መፅሃፍ ማንበብ፣ “ግዴታ” መሆኑ ቀረ።

በንባብ ፍቅር፣ መፅሃፍ እንደያዙ ሌሊቱ ይጋመሳል። መፅሃፍ አንብቡ እያለች ስትወተውታቸው የነበረችው እናት፣ ቶሎ አንብበው በጊዜ እንዲተኙ መምከር ጀመረች። ካርሰን፣ “ደደብ” እንዳልሆነ ገባው። የሳይንስም ሆነ የሂሳብ፣ የቋንቋም ሆነ የታሪክ ትምህርቶችን ሁሉ በቀላሉ መረዳት እንደሚችል ሲያይ፣ ለማመን ከብዶት ነበር። ግን፣ የፈተና ውጤቱም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተሻሽሏል። በሁለተኛው አመት ደግሞ፣ ከክፍሉ አንደኛ ወጣ። ከዚያም ከትምህርት ቤቱ አንደኛ በመሆን ተሸለመ። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ሲያጠናቅቅ በመላ አሜሪካ ከፍተኛ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎችን አወዳድሮ ወደሚቀበለው ሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ ገባ - በከፍተኛ ውጤት ነፃ የትምህርት እድል ተሰጥቶት። በቃ፤ የሚያቆመው አልተገኘም። ጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ ገብቶ፣ የአንጎል ቀዶ ህክምናን በማጥናት ተመረቀ። በሳይንሳዊ ጥናቶች ዙሪያ፣ ጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲን የሚስተካከል የትምህርት ተቋም በአለማችን የለም። 33 የዩኒቨርስቲው ተመራቂዎችና አስተማሪዎች የኖቤል ተሸላሚ ሆነዋል። በዚህ ዩኒቨርስቲ ተምሮ መመረቅ ራሱ፣ ለካርሰን ትልቅ ስኬት ነው።

ግን አልበቃውም። በየአመቱ ከሶስት መቶ በላይ ከባድ የቀዶ ህክምና አገልግሎት በመስጠት የብዙ ሰዎችን ህይወት አድኗል። ይህም ብቻ አይደለም። በህፃናት የአንጎል ህክምና ላይ፣ መፍትሄ ላልነበራቸው በሽታዎች አዳዲስ የህክምና ዘዴዎችን በመፍጠር በመላው አለም በቀዳሚነት የሚጠቀስ ታላቅ ሰው ለመሆን በቅቷል - ዶ/ር ቤን ካርሰን። ሰዎች በራሳቸው ጥረት፣ ከ“ደደብነት” ወደ እውቀት ማማ መምጠቅ፣ በእውቀታቸውም ከድህነት ወደ ብልፅግና መሸጋገር እንደሚችሉ ይጠረጠራል? በቤን ካርሰን የጀግንነት ታሪክ ውስጥኮ ቁልጭ ብሎ ይታያል። አርአያነቱ፣ ለሁላችንም ነው። እውቀትን እየጨበጡ ወደ ስኬት መጓዝ ይቻላል። እስካሁን በጥበበኛ ሰዎች ጥረት የተገኙ አስደናቂ እውቀቶችን በስፋት መቅሰም የምንችለው ከመፃህፍት ነው። አዳዲስ እውቀቶችን ለመጨበጥ የሚያስችሉ ሳይንሳዊ ዘዴዎችንም ከመፃህፍት ውስጥ እናገኛለን። ያኔ፣ እንደ እውቀታችን መጠን እየሰራን ስኬትን እናጣጥማለን - በቃ… የጥረት ጉዳይ ነው፤ የንባብን ፍቅር የማዳበር ጉዳይ ነው። በእርግጥ፣ ሁሉም ሰው እንደ ልብ ጥሩ ጥሩ መፃህፍት ያገኛል ማለት አይደለም። የምንፈልገው አይነት መፅሃፍ ማግኘት… ለብዙዎች ብርቅ ነበር - እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ።

ኢትዮጵያ ውስጥ ቤተመፃህፍት ያላቸው ከተሞች ስንት ቢሆኑ ነው? እነሱም ቢሆኑ፣ የያዙት የመፃህፍት አይነትና ብዛት ቢቆጠር ኢምንት ነው። ዛሬ ግን፣ ያ ሁሉ “የመፅሃፍ ችጋር” ተረት እየሆነ ነው። የ“ኮፒ ራይት” ጥያቄ አነጋጋሪ ቢሆንም፣ በየትኛውም የእውቀት መስክ፣ በየትኛውም የእውቀት ደረጃ… ማማረጥ እስኪቸግረን ድረስ እልፍ መፃህፍት ማግኘት እንችላለን - በኢንተርኔት። ዛሬ፣ በመፃህፍት እጥረት ማሳበብ አይቻልም። የእውቀትና የስኬት በር፣ እዚሁ አጠገባችን መጥቷል። አንኳኩቶ መክፈትና መግባት ነው የኛ ድርሻ። በሩ ኮምፒዩተር ነው። ኢንተርኔትን በመጠቀም እናንኳኳ። መክፈቻው፣ የ“እንግሊዝኛ” ቋንቋ ነው። አብዛኞቹ መፃህፍት በእንግሊዝኛ የተዘጋጁ ናቸውና።

በቅርቡ በአዲስ አበባ ከተማ የተጀመረውን የቤቶች ልማት ፕሮግራም ምዝገባ አስመልክቶ አስተያየታቸውን የተጠየቁ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ፕሮግራሙ የሚሳካ አይመስለንም ይላሉ፡፡ በርካታ የቤት ተመዝጋቢዎችም መንግስት ቃል የገባው የቤቶች ግንባታ ይሣካ ይሆን የሚል ጥርጣሬ አላቸው፡፡ ይሄንን መነሻ በማድረግ የቤት ፕሮግራሙን በተመለከተ የተቃዋሚ አመራሮቹ አይሳካም የሚሉበትን ምክንያት በዝርዝር እንዲያስረዱን ጠይቀናቸው የሰጡንን ምላሽ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡


“እንደ ብሄራዊ ሎተሪ በእጣ ቤት ማደል የኢኮኖሚ ስራ ነው ብዬ አላምንም”
አቶ ሙሼ ሠሙ
የባንክ ባለሙያና የኢዴፓ ሊቀመንበር
መጀመሪያ ማንም ዜጋ ቤት ማግኘት ያለበት በጥረቱ ነው ብዬ ነው የማስበው እንጂ ልክ እንደብሄራዊ ሎተሪ በእጣ ቤት ማደል የኢኮኖሚ ስራ ነው ብዬ አላምንም፡፡ መጨረሻ ላይ ማጣፊያው ያጥራል፡፡ መጀመሪያውኑ የኮንዶሚኒየም ቤቶች ሲታደሉ መንግስት እያንዳንዱ ቤት ፈላጊ የተወሠነ ገንዘብ አጠራቅሞ ባጠራቀመው ገንዘብ ላይ ድጋፍ ተደርጐለት በረጅም ጊዜ ብድር ቤት የሚያገኝበት እድል ቢያመቻች ኖሮ ዛሬ የሚሠሩት ቤቶች አጣብቂኝ ውስጥ አይገቡም ነበር፡፡ መንግስት ከዚህ አኳያ ሊገጥመው የሚችለው ችግር የገንዘብ አቅም ጉዳይ ነው፡፡ ገንዘቡ ከአሁን በኋላ ተጠራቅሞ ነው እንግዲህ ሠዎች የቤት ባለቤት የሚሆኑት። በዚህ መሀል መገንባት አለበት፡፡ ቤቱን ለመገንባት ደግሞ ወደ ብድር መግባት አለበት፡፡ የኢትዮጵያ መንግስትን አቅም እናውቀዋለን - 1.2 ሚሊዮን ቤት ለመገንባት የሚያስችል አቅም ሊፈጥር የሚችል ገንዘብ የተለየ ፈንድ ካላገኘ በቀር ከየትም ሊያመጣ አይችልም፡፡ ገንዘብ ማተም ውስጥ ካልገባ በቀር ወይም ደግሞ በጣም ከፍተኛ ገንዘብ ከቻይናና ከህንድ የሚያገኝበትን ሁኔታ ካላመቻቸ በቀር እነዚህን ቤቶች በሰባት አመት ውስጥ ሊገነባ የሚያስችለውን አቅም ሊያገኝ አይችልም፡፡ ሁለተኛው ይሄንን ቤት ለመገንባት የሠው ሃይል ጥያቄ አለ፡፡ 1.2 ሚሊዮን ቤቶች ለመገንባት በቤት ግንባታ እውቀት ያላቸው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሠዎች ያስፈልጋሉ፡፡ እነዚህ ሠዎች ከየት ነው የሚመጡት? ሶስተኛው ደግሞ የተፈጥሮ ሃብት ነው - መሬት፣ ድንጋይ፣ ብረት፣ ሲሚንቶ፣ ጠጠር የመሣሠሉት በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ከየት ነው ሊመጡ የሚችሉት? እነዚህ መሠረታዊ ጉዳዮች በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ይሟላሉ ብዬ አላምንም፡፡ የተባለው ፕሮግራምም ይሣካል ብዬ አልገምትም፡፡
“መንግስት የዜጐች ቤት ሠሪ ሊሆን አይችልም”
የተከበሩ አቶ ግርማ ሠይፉ
የፓርላማ አባል- የአንድነት ፓርቲ አመራር
እኔ በግሌ ትርጉም የሚሠጥ ነው ብዬ አስቤውም አላውቅም፡፡ የህዝቡን ስሜት ለመግዛት ምን ማድረግ እንዳለባቸው ሲያስቡ የመጣላቸው እና የታያቸው አንዱ መንገድ ነው፡፡ አሁን እየተደረገ ያለው ነገር በዋናነት የሃገር ውስጥ ቁጠባ አነስተኛ ነው ከሚለው በመነሣት የመጣ ነው፡፡ እርግጥ ነው የሃገር ውስጥ ቁጠባ አነስተኛ ነው ነገር ግን ህዝቡ ዝም ብሎ አይቆጥብም። ስለዚህ መንግስት ህዝቡ እንዲቆጥብ አንድ ነገር ራቅ አድርጐ ሠቅሎ ማሣየት ነበረበት፡፡ የቤቶች ፕሮግራሙ ዋና አላማው በሃገር ውስጥ ያለውን የቁጠባ ባህል ከፍ ማድረግ ነው፡፡
ስለዚህ ቤት በማግኘትና ባለማግኘት ቁም ነገር ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ ሣይሆን የሃገር ውስጥ ቁጠባን ለማሣደግ ተብሎ ነው፡፡ ከዚያ ውጪ ግን በመርህ ደረጃ መንግስት የዜጐች ቤት ሠሪ ሊሆን አይችልም፡፡ ለምሣሌ ባለፈው ክቡር ጠ/ሚኒስትሩ መቶ ሺህ ቤቶች ሠርተናል ብለው በኩራት ተናግረዋል፡፡ እነሱ ጉልበትና ስልጣን ስላላቸው የሠው ስራ ቀምተው በመስራታቸው ሊኩራሩ አይገባም፡፡ በ1998 ለተመዘገቡ 450 ሺህ ቤት ፈላጊዎች በስምንት አመት ጊዜ ውስጥ ቤቶች ሰርተን እናጠናቅቃለን ብለው ይኸው ስምንት አመት አልፎ እንኳ 100ሺህ ቤቶች መስራት አልቻሉም፡፡ ጅምሮቹን ጭምር ነው 100 ሺህ ቤቶች ሠርተናል ያሉት። ለእነዚህ ቤቶች አንድ ጊዜ መሠረት በመጣል፣ አንድ ጊዜ በማስመረቅ ሌላ ጊዜ ቁልፍ በመስጠት አምስት ጊዜ ይወራና 500ሺህ ያስመስሉታል። አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የተሠሩት ቤቶች 100ሺህ ናቸው - እስክስታው ዘፈኑ ግን ሚሊዮን ነው። በተቃራኒው ግን በማህበር በመሣሠሉት ከዚህ ከላይ ቤቶች ተሠርተዋል፡፡ ከዚህ አንፃር መታየት ያለበት ፕሮግራሙ አንደኛ አላማው ለዜጐች ቤት መስጠት ሣይሆን የቁጠባ ባህሉን ማበረታታት ነው፡፡ ግን በየአመቱ ትንሽ ትንሽ ነገር እየሠጡ በማሣየት ሠዎች በተስፋ እንዲቆጥቡ ይደረጋል፡፡ በዚህ ማሣያው ቁጠባውን ያቋረጠ ይሠረዛል ይላል፡፡ ቤቱን ይሠሩታል አይሠሩትም ለሚለው በእርግጠኝነት አይሠሩትም፡፡ የሆነ አስማት እንኳ ተፈጥሮ ቢሠሩት ትክክል ነው ብዬ አላምንም። ሌሎች በሪል ስቴት ውስጥ ተሣትፈው ይሄን ሊያደርጉ የሚችሉ ሠዎችን ስራ እየቀሙ ነው እንሰራለን የሚሉት፡፡ መንግስት ዜጐች በተመጣጣኝ ዋጋ ቤት ማግኘት አለባቸው የሚል አቋም ሊይዝ ይችላል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ቤትን ውድ የሚያደርገው አንደኛው መሬት ነው - ራሱ ሲሠራ በነፃ መሬት ይወስዳል፡፡ የግንባታ ግብአትም ከቀረጥ ነፃ እንዲገባ ያደርጋል፡፡ ስለዚህ በርካሽ ዋጋ የመስራት አቅምን ለራሱ ያመቻቻል፡፡ ይህን አቅም ወደ ግል ሴክተሩ አዘዋውሮ እነዚህን ማበረታቻዎች ሠጥቶ ሜዳውን ለነሡ ቢለቅ ነበር የሚሻለው፡፡ አሁን ግን ፕሮግራሙን ወደ ገጠር አካባቢዎችም ለማስፋት እቅድ ያለው ይመስላል። በየቦታው የተከፈቱ የንግድ ባንክ ቅርንጫፎችም ለዚህ የተመቻቹ ናቸው፡፡ ሠው አሁን ቆጥቦ በኋላ ባይደርሠው ገንዘቡን መውሠድ እንደሚችልም አማራጭ ተቀምጧል፡፡ ነገር ግን ቆጣቢው ኋላ ላይ የሚያገኘው ገንዘብ በዋጋ ንረት የተጐዳና የመግዛት አቅም የሌለው ነው የሚሆነው፡፡

“መንግስት የሚመረጠው ነጋዴ እንዲሆን አይደለም”
አቶ ቡልቻ ደመቅሣ
የፋይናንስ ባለሙያና የመድረክ አመራር አባል
የቤቶች ፕሮግራሙ የተዘረጋው የፖለቲካ ጥቅም ለማግኘት ነው፡፡ የእነዚህ ፕሮግራም ተሣታፊዎች የኢህአዴግ አባል እንዲሆኑ ነው የሚደረጉት፡፡ ለምሣሌ አንድ ሠው ቤት ልስራ ብሎ 40/60 የሚባለው ውስጥ ቢገባ መጀመሪያ ማረጋገጥ የሚፈልጉት የኢህአዴግ አባል መሆኑን ነው፣ ስለዚህ ይሄ ጠቃሚ ሳይሆን ጐጂ ነው። መንግስት የሚመረጠው ነጋዴ እንዲሆን አይደለም። ፍርድ እንዲሠጥ፣ የፖሊስ ስራ እንዲሠራ፣ ጉምሩክ እቃ ሲገባ ቀረጥ እንዲያስከፍል፣ መሬት በደንብ እንዲለማ፣ የኢኮኖሚ ልማት እንዲመጣ ነው እንጂ ንግድ ውስጥ ገብቶ እንደ ተራ ነጋዴ ለመቸብቸብ አይደለም፡፡ ዞሮ ዞሮ ደግሞ ይሄ ሃገራችንን ይጐዳል፡፡ የአለም ንግድ ድርጅት አባል መሆን ያልቻልነው እኮ መንግስት ከንግድ ውስጥ መውጣት ባለመቻሉ ነው፡፡ በዚህ ድርጅት ውስጥ አለመግባት ደግሞ ለዘለቄታው ጉዳት አለው፡፡ ለኢህአዴግ ንግድ ፖለቲካ ነው። በንግዱ የፖለቲካ ትርፍ ማግኘት ይችላሉ፡፡ አሁን ለህዝቡ ቃል እንደገባው ተሣክቶለት ቤቱን ቢሠራም ትክክል አይደለም፡፡ ገንዘብ ከዚህ ሁሉ ሠው መሠብሠቡ በራሱ ቀላል አይደለም። የመንግስት ዋነኛ ስራው መሆን የለበትም፡፡ የመንግስት ሠራተኛ የሚቀጠረው የመንግስት ስራ ተብለው የተለዩትን ለመስራት ብቻ ነው፡፡ ግብር መሠብሠብ እንጂ ከህዝቡ ጋር እየተጋፉ ገንዘብ ለማስገባት አይደለም፡፡ አሁንም አጥብቄ የምናገረው ይህ የመንግስት ተግባር አለመሆኑን ነው፡፡ የመንግስት ሥራ ዳር ድንበር መጠበቅ፣ ፍትህ ማስፈን፣ መንገድ መገንባት እንጂ ብር እያበደሩ ቤት መስራት አይደለም፡፡

“የቤት ፕሮግራሙ ለቀጣዩ ምርጫ የታለመ ይመስላል”
ዶ/ር መረራ ጉዲና
የፖለቲካ ሣይንስ ምሁር እና የመድረክ አመራር አባል
መንግስት ብዙ ድስቶችን ጥዶ ነው የሚንቀሣቀሰው፡፡ አንደኛው ድስት ይሄ መሆኑ ነው፡፡ ዋናው ግን ይሄ የቤት ፕሮግራም ለ2007 ምርጫ የታለመ ይመስላል፡፡ የዚያን ጊዜ እኛን ካልመረጣችሁ ቤት አታገኙም ሊሉ ይመስላል ዳር ዳር የሚሉት፡፡ አሁን እንግዲህ ወደ 2 ሚሊዮን ቤት ነው እንሰራለን ያሉት፡፡ ይሄ ደግሞ በኛ አቅም አጠያያቂ ነው፡፡ ደግሞ ሁሉን አይነት ሠው ነው የሚመዘግቡት፡፡ ውጤቱን እንግዲህ ውሎ አድሮ ማየቱ ይሻላል፡፡ የኔ ጥርጣሬ ግን የ2007 ምርጫን ታሣቢ አድርገው ነው የሚል ነው፡፡ ጨዋታው ቀላል አይደለም፡፡
ቤት መስራት ብቻ ሣይሆን ከዚያ ጋር ብዙ የተያያዙ ነገሮች አሉ፡፡ መሠረተ ልማቱ መጨመር አለበት- ውሃ፣ መብራት፣ መንገድ፣ ስልክ አለ። እኒህን ሁሉ ማሳካት ከቻሉ ጥሩ ነው፣ ግን አይመስለኝም፡፡

ከክርስቶስ ልደት በፊት በሶስተኛው ክፍለ ዘመን የነበረ ኩንግ ሲ የተባለ አንድ ንጉስ በቻይና ይኖር ነበር፡፡ ንጉስ አሳ በጣም ይወድ የነበረ መሪ ነበር ይባላል፡፡ የአገሩ ህዝብ በሞላ አሳ ይገዛና እጅ መንሻ ያቀርብለታል፡፡ ንጉሱ ኩንግ ሲዩ ግን ስጦታውን አልቀበልም፤ይላል፡፡ ይህንን ያየው ታናሽ ወንድሙ ወደ ንጉሱ ይመጣና “ያለጥርጥር አሳ በጣም እንደምትወድ አውቃለሁ፡፡

ስለምን ነው የአሳ ስጦታቸውን አልቀበልም ያልከው?” ሲል ጠየቀው፡፡ ንጉሱም፤ “ወንድሜ ሆይ ! የአሳ ስጦታ የማልቀበልበት ምክንያት፤ እያንዳንዱ ስጦታ በውለታ እንድትታሰር ያደርግሃልና ነው፡፡ በውለታ ከታሰርኩኝ የሃገራችንን ህግ እስከመጠምዘዝ ድረስ እሄዳለሁ፡፡” “ለምን ትጠመዝዛለህ?” “ውለታ የዋልክለት ህዝብ በፋንታው ይሄን አድርግ ብሎ ስለሚጠቨቅህ ነዋ!” “ለምን እምቢ አትልም ታዲያ?” “አሳ የምወድደወው ጭንቅላቴን ረቂቅ ስለሚያደርግልኝ ነው፡፡

ይሄንን እንዳረግ ያደረገኝም አሳ ነው!” “አልገባኝም” “አሳ አትበላማ! አሳ ሳትበላ እንዴት ይግባህ?” “ህጉ ቢጣመም ምን ቸገረህ? ስልጣኑ ያንተ?” “ህጉን ካጣመምኩ ራሴ ተጣምሜ ከስልጣኔ እወርዳለሁ” “ከስልጣንህ ብትወርድ ምን ቸገረህ?” “ከስልጣኔ ከወረድኩ በኋላ ራሴን አሳ ለመመገብ አልችል ይሆናል! በተቃራኒው ካየኸው ግን፤ከህዝብ የአሳ ስጦታ ባልቀበል፣ ከመንበሬ ባልወርድ፣ መቼም ቢሆን አሳ ገዝቼ መብላት አያቅተኝም!!”

                                                    * * *

ስጦታና እጅ መንሻ ስርዓትን እስከመናድ እንደሚደርስ በሀገራችን አይተናል፡፡ ከፈረንሳይ ድረስ የ70,000(ሰባ ሺ) ብር ሽቶ (ብራችን በዶላር 2.05 ብር ይመነዘር በነበረ ጊዜ) ለልደታቸው ስጦታ ይመጣላቸው የነበሩ ልዕልቶች እንደነበሩ ታዝበናል፡፡ የሀገር መሪዎች በስዊስ ባንክ አያሌ ሚሊዎን ብርና ወርቅ አስቀምጠው የነበረበት ወቅት እንደነበር አንረሳም፡፡ ይህን ዓይነቱ ነገር የዛሬ ስሙ ሙስና ነው፡፡ መታያ፣እጅ -መንሻ፣ስጦታ ፣የደስ ደስ ፣ቤት ማሞቂያ፣ህንፃ ማድመቂያ፣እጅ ማበሻ… ሁሉም የሙስና ተለዋጭ ስሞች ናቸው፡፡ “ሙሳዊ ጫና የክፉ ስራዎች ሁሉ የዓመት ከዓመት ፀደይ ነው፡፡

የስርዓቱ ብልሽት መጠንሰሻ ነው፡፡ የአገር ዕዳ ክምር - ክንብንብ ነው፡፡ ክንዳችንን ያልማል፡፡ ከሸንጎ ውስጥ የጥበብን ብልት ቆርጦ ስልጣንን ለግል ጥቅም ለማዋልና ስምና ዝናን ማትረፊያ ለማድረግ እንድናውለው ያመቻችልናል!” ይለናል በርክ የተባለው ፀሐፊ፡፡ ይህሁነት በዲሞክራሲ ማነቆነት፣ በልማት እንቅፋትነት፣ በሃይማኖት ግጭት መንስዔነት፣ በጦርነት ሰበብነት ትልቅ ተፅዕኖ ቢፈጠር ዞሮ ዞሮ ጦሱ ለሀገር ነው የሚተርፈው፡፡ ጀርመኖች ደግሞ ስለታላላቅ ጦርነቶች የሚከተለውን ይላሉ፡- ታላቅ ጦርነት ሃገሪቱን የሶሰት ዓይነት ሰራዊት ባለቤት ያደርጋታል፡- የጦር- ጉዳተኞች ሰራዊት፣ የሐዘንተኞች ሰራዊት እና የሌቦች ሰራዊት! ሃይማኖቶች የቅዱሳት፣የቀና መንፈስ፣የመልካም ስራ መመሪያ የሚሰጡ፣የበጎ ምግባር አቅጣጫ መሪ እንጂ የግጭት መንስኤና ሰበብ መሆን የለባቸውም፡፡ ለዚህ ነው:- “ሃይማኖት ታረደ ደሙን ኩቲ ላሰው እንግዲህ ሆድ ለሆድ አልተገናኘም ሰው” እያለ የሀገራችን ሰው የሚገጥመው፡፡

ሁሌ የምንሰራው ስራና የእንቅስቃሴያችን ሂደት “በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ተገለፀ”፣ “የስራ ግምገማው እንደሚያሳየው የዕድገት አቅጣጫ ጠቋሚ ነው”፤ “በይሄን ያህል ፐርሰንት ያደግን መሆኑ ተገለፀ” ወዘተ እየተባባልን ችግሮቻችንን እንዳናይ ዐይናችንን መጨፈን ትልቅ አባዜ ነው፡፡ “ሞኝ፤የሚያደንቀው ሞኝ አያጣም”፤ እንዲሉ እርስ በርስ በመደናነቅና “አበጀህ”፣ “አበጀህ!” በመባባል ብዙ የተራመድን በመሰለን ጊዜ መስጋትና መጠንቀቅ ብልህነት ነው፡፡ ፍትህ፤ ዕውነታችን በየትኛው አቅጣጫ እንዲበራ እንደምናደርግ ራሳችንን የምንፈትሽበት ድንቅ መሳሪያ ነው፡፡ “ስለ አገርህ፣ስለ አምላክህ፣ስለ ዕውነትህ፤ ይሁን እንጂ ቅን ዓላማህ፣ ፍትሐዊነት ቅን ፀጋ ነው፣ ፈፅሞ ፍርሃት አይግባህ” (ይላል ሼክስፒር) ዲሞክራሲያችንን እንፈትሽ፡፡ “ዲሞክራሲን ማፍቀር እኩልነትን ማፍቀር ነው፡፡”

ይለናል ሞንቴስኩ፡፡ ይህ የእኩልነት ፍቅር አለን ወይ? “ዲሞክራሲ ምርጥና ለመተግበር እጅግ አዳጋች የፖለቲካ አደረጃጀት ነው” ይለናል ራልፍ ባርተን፡፡ ይህንንስ ተገንዝበናል?(dynamic democracy) ተንቀሳቃሽ እና አንቀሳቃሽ ዲሞክራሲ ካልሆነ ዲሞክራሲ የለም ብንል ይሻላል፡፡ ህዝባችን መሳተፍ ሲያቆም፣ፀሀይ ውስጥ ቦታ ሲያጣ -ያኔ ሁላችንም በመበስበስ (በንትበት) ጨለማ (darkness of decadence)ውስጥ በነን እናልቃለን፡፡ ሁላችንም ዲዳ ፣ሞራለ - ቢስ እና የቀለጡ ነብሶች እንሆናለን” (ሳውል ደ-አሊንስኪ) ዲሞክራሲ ስንል እንደፕሉታርክ “ሂድ፡፡ በራስህ ቤት የራስህ ዓይነት ዲሞክራሲ ሞክር” ማለታችን ቢሆንም ይመረጣል፡፡ የሙስናን፣ የጎረቤትን የጦርነትን፣ የሃይማኖትን ነገር፣ የዲሞክራሲንና የዕድገትን ነገር፣ በወጉ ለማየት ችግራችንና መፈርትሄዎቻችንን በተያያዘ ጥምረት ማገናዘብ አለብን፡፡

የሃገራችንን ችግር ስንቃኝ አንዱን ካንዱ አስተሳስረን መሆን አለበት፡፡ አለበለዚያ የአንድ ሰሞን ግርግር ዘመቻ ብቻ ይሆናል፡፡ ተከታታይ ጥረትና ቀጣይነት አይኖረውም፡፡ አንዱን ዘመቻ ሌላው እያስረሳውና እየሻረው ስለሚሄድ ዕድገታችን ደብዛዛ ይሆናል፡፡ የተሳሰረ ጥረት የማይረሳሳ ትግል ነው ሊኖረን የሚገባው፡፡ በተበታተነ ሁኔታ ውስጥ እንዳንበታተን፤ አረሙን፣ እንቅፋቱን፣ ዳተኝነቱንና ግብዝነቱን ትተን፣ ለመጓዝ፤ ”የመጣ ሳይመጣ የውሃ ቦይ ጥረግ” የሚለውን ተረት ማሰብ አለብን!!


አድማስ አድቨርታይዚንግ እ.ኤ.አ በ1990 የተቋቋመ የግል ድርጅት ነው፡፡ አድማስ አድቨርታይዚንግ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ሁለት ዋና ክፍሎች አሉት፡፡

የህትመቱ ክንፍ አንዱ ሲሆን ሳምንታዊው ጋዜጣ አዲስ አድማስ ያሳትማል የማስታወቂያ ክንፉ ደግሞ የፊልም መስሪያስቱዲዮ እና ግራፊክ ዲዛይን ያለው ነው፡፡ ድርጅታችን በኤሌክትሮኒክስ ሆነ በህትመት ሚዲያ ላይ የሚሰራ የማስታወቂያ ኤጀንሲ ነው፡፡ የቴሌቪዢንና ሬዲዮ ማስታወቂያዎችን በመስራት በአየር ላይ ከማዋላችንም በተጨማሪ የሚዲያ ምክርና ዕቅድ አገልግሎቶች እንሰጣለን፡፡ በሚሰጠን ቅድመ መረጃ አማካይነት ማናቸውንም የቲቪ፣ሬዲዮ እና ፕሬስ ማስታወቂያዎች እንዲሁም ግራፊክ አርትስ እንሰራለን፡፡

አገልግሎታችን በሚዲያ ምርጫ ላይ ማማከር፣ማቀድ፣መከታተል፣የማስታወቂያዎቹ ያስገኙትን የመጨረሻ ውጤት መገምገምን ያካትታል፡፡ በርፉ ያልን በቂ ልምድና በቡድን የመስራት ባህል ሚዲያውን እንዴት ደንበኞቻችን በሚያረካና ውጤታማ በሚያደርግ መልኩ መጠቀም እንዳለብን እንድናውቅ አስችሎናል፡፡ አድማስ አድቨርታይዚንግ የአዲስ አበባ ንግድ ም/ቤት አባል ሲሆን በተለያዩ ባህላዊና ማሕበራዊ እንቅስቃሴዎች ንቁ ተሳታፊ ነው፡፡

Audio visual studio

የማስታወቂያ አገልግሎት እና ኦዲዮ/ቪዥዋል ስቱዲዮበላቀ የፕሮዳክሽን ደረጃው ዪታወቀው የማስታወቂያ ክፍላችን ለንግዱ ዘርፍና ለማህበራዊ ግብይት ዋነኛ አጋርነቱን አረጋግጧል፡፡ ፕሮፌሽናል የኦዲዮ/ቪዲዮ ስቲዲዮችን፡፡ በፕሮፌሽናል ዲቪ ካሜራዎች ከአማራጭ ሌልሶች ጋር የመብራትና የድምጽ መሳሪያዎች የካሜራ ክሬን በተሟላ የኤዲቲንግ ስቱዲዮ እና በሌሎች ተፈላጊ መሳሪያዎች የተደራጀ ነው፡፡ ቴክኖሎጂ ያፈራቸውን የተደራጀ ዘመናዊ መሳሪያዎች የያዘው ስቱዲዮአችን በአገራችን ካ ጥቂት ምርጥ የፊልም ስቱዲዮዎች አንዱ ያደርገዋል፡፡

አድማስ አድቨርታይዚንግ ብቁና ተፎካካሪ በሆኑ የአስተዳደር የፋይናንስ እና በጥበብ ባለሙያዎች የተሞላ ነው በድርጅቱ የሚሰሩት ተርጓሚዎች ገጣሚዎች የአርት ዳይሬክተሮች እና ጋዜጠኞች በሙያቸው የተሞከሩ የተፈተኑና በበርካታ ፕሮጀክቶች አመርቂ ውጤት ያስመዘገቡ ናቸው፡፡ በተጨማሪው ድርጅቱ በህዝቡ ዘንድ በተቀዳጀው አክብሮት እና አስተማማኝ የሥራ ሁኔታ የተነሳ በአገሪቱ የሚገኙ ምርጥ የፈጠራ ችሎታ ያላቸው ባለሙያዎች ለመቅጠርና አብረውን እንዲሰሩ ለማድረግ አስችሎታል፡፡ ለዚህም በየጊዜው ያስመዘግባቸው የስኬት ክብረወሰኖች ከቃላት በላይ ይናገራሉ፡፡

የአድማስ አድቨርታይዚንግ ኃ/የተወሰነ የግል ማህበር ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ አሰፋ በኢትዮጵያ የማስታወቂያ ኢንዱስትሪ ጉልህ ለውጥ ማምጣታቸውም ይታወቃል፡፡

በኢትዮጵያ በተፈጠረው የዲሞክራሲ ስርዓት ሚዛናዊ ሂሳዊ ጋዜጣ በመመስረት ለህብረተሰቡ የንባብና የዕውቀት ዕድል የፈጠረ ሰው ነበር፣ያሉት በቀብር ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አቶ በረከት ስምኦን ሲሆኑ የሪፖርተር ጋዜጣ ባለቤትና ዋና አዘጋጅ አቶ አማረ አረጋዊ በበኩላቸው ‹‹ በኢትዮጵያ ፕሬስ የተግባር ሚና ከተጫወቱ ሰዎች ግንባር ቀደም ነው ›› ብለዋል፡፡የአቶ ድንገተኛ ሞት አስመልክተው ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ አስተያየታቸውን ሲሰጡዕ ‹‹ እንደ ህብረተሰብ ትልቅ ሰው ነው ያጣነው ›› ብለዋል፡፡

በብዙዎች ዘንድ አድንቶትን ያተረፈውንና በስምንት ድምፃውያን የተዜመውን ‹‹ ማውቀር ነው መሰልጠን ›› የተሰኘ የዘፈን ክሊፕ ከተለያዩ ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት አድማስ አድቨርታይዚነግ ማሰራቱ የማታወቅ ሲሆን በቅርቡ በኮራ አሸናፊ የሆነው የድምፃዊት ፀደንያ ገ/ማርቆስ የዘፈን ክሊፕ አቶ አሰፋ እራሳአው በቅርቡ ባቋቋሙት የፊልም ስቱዲዮ መሰራቱ ታውቋል፡፡

በአድማስ አድቨርታይዚንግ ስር የሚታተመውና በአገራችን በስርጭት ብዛት ከሁለት ዓመት ወዲህ በቀዳሚነት ሥፍራ የሚገኘው የአዲስ አድማስ ጋዜጣ መስራች ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ አሰፋ ከምዕራብ አገራት የፊልም ደረጃ ጋር የሚስተካከል ፊልም ለመስራት ባላቸው ራዕይ ለየት ያለ ስቲዲዮ በመገንባት ላይ ነበሩ፡፡


Saturday, 22 June 2013 12:18

የፌዴሬሽኑ ቅሌት

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫው ማጣሪያ የሁለተኛ ዙር ግጥሚያ ጋቦሮኒ ላይ ከቦትስዋና አቻው ጋር ባደረገው ጨዋታ ሁለት ቢጫ ያየውን ምንያህል ተሾመ በማሰለፉ በፊፋ የቀረበው ክስ ለመላው የእግር ኳስ ቤተሰብ ያልተጠበቀ መርዶ ነበር፡፡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ለቀረበበት ክስ በቂ መከላከያ ማቅረብ ካልቻለ ከቦትስዋና ጋር ተጫውቶ ያስመዘገበው የ2-1 ውጤት ተሰርዞ ለቦትስዋና ቡድን በፎርፌ 3 ነጥብ እንደሚመዘገብላት ተገልጿል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ኢትዮጵያ 130ሺ ብር ቅጣት መክፈል ይጠበቅባታል፡፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ወደ ዓለም ዋንጫ ለማለፍ መስከረም 6 ቀን 2006 ዓ.ም ከመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር የሚያደርገውን ጨዋታ የግድ ማሸነፍ ይኖርበታል፡፡ ለዚህ ሁሉ ተጠያቂው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ዝርክርክ አሰራር ነው፡፡

ከዋልያዎቹ የ2ለ1 ድል በፊት የደረሰው መርዶ መርዶው በይፋ የተሰማበት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ጋዜጣዊ መግለጫ ማክሰኞ እለት በጊዮን ሆቴል ሳባ አዳራሽ ሲሰጥ በደስታ መግለጫና በምስጋና ነበር የተጀመረው፡፡ ከዚያም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በደቡብ አፍሪካ ላይ 2ለ1 በሆነ ውጤት ካስመዘገበው ድል ጋር በተያያዘ በመላው ኢትዮጵያ በነበረው የደስታ አገላለጽ ለሞቱ ሁለት ወጣቶችም የ1 ደቂቃ የህሊና ፀሎት ተደርጓል፡፡ ሁለቱ የባህርዳር ወጣቶች የ16 ዓመት ተማሪ እና የ13 ዓመት ሊስትሮ ናቸው፡፡ ፌዴሬሽኑ በደስታ አገላለፁ የሞቱት ሁለት ወጣቶች መሆናቸውንም ቢገልጽም በመግለጫው ላይ የተገኙ አንዳንድ ጋዜጠኞች የሟቾች ቁጥር 4 ይሆናል የሞት አደጋ ያጋጠመው በባህርዳር ብቻ አልነበረም በሱልልታና በአዳማም ጭምር እንጅ ብለው እርማት አድርገዋል፡፡

ጋዜጣዊ መግለጫውን የመሩት የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ሳህሉ ገ/ወልድ፣ በደቡብ አፍሪካ ላይ በተመዘገበው የ2ለ1 ድል ዘግተናል ያልነውን ምዕራፍ እንደገና ለመክፈት ተገደናል በሚል የመግቢያ ንግግራቸው መግለጫውን የጀመሩት ፤ አስደንጋጩ መርዶ ፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት የደረሰው ረቡዕ ዕለት መሆኑን በመግለፅ ነበር፡፡ ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ በአዲስ አበባ ስታድዬም ከመገናኘታቸው ሶስት ቀናት ቀደም ብሎ ማለት ነው፡፡ ከፊፋ የመጣው የክስ “ኮምኒኬ” ረቡዕ 5 ሰዓት ላይ ለፌዴሬሽኑ በፋክስ ሲደርስ በጽ/ቤቱ ስለ እሁድ ጨዋታ አጠቃላይ ዝግጅት ለመነጋገር ተሰብስበው የነበሩት የፌዴሬሽኑ ኃላፊዎች፣ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ሳህሉ ገ/ወልድ ፤ተቀዳሚ ም/ፕሬዚዳንቱ አቶ ብርሃኑ ከበደ ፤ ዋና ፀሐፊው አሸናፊ እጅጉ ናቸው፡፡ ለፌዴሬሽኑ ኃላፊዎች አስደንጋጭ፣ የሚረብሽና ከፍተኛ የሃዘን ስሜት ውስጥ የከተተ መርዶ ሆኖባቸው እንደነበርም ገልፀዋል፡፡ ዋና ተቀዳሚ ም/ፕሬዚዳንት አቶ ተካ አስፋው፣ በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ስብሰባ ካይሮ ሄደው ነበርና ሐሙስ ሲመለሱ የፌዴሬሽኑ ኃላፊዎች አስቸኳይ ስብሰባ ተቀመጡ፡፡ እንዲህ በሚልም ተነጋገሩ፡፡ “እሁድ ጨዋታ አለን፡፡ ህዝቡ ጉጉት ላይ ነው፡፡ ተጨዋቾቹ ስሜታቸው የተነሳሳበት ወቅት ነው፡፡ ያለውን ድባብ ማፍረስ ስለሌለብን ጉዳዩን በከፍተኛ ምስጢር መያዝ አለብን” በማለት ተማማሉ፡፡ መማማሉ በየትኛውም መንገድ መረጃው እንዳይወጣ፣ የብሔራዊ ቡድን ተጨዋቾች እንዳይረበሹ፣ ህዝቡ ስሜቱ እንዳይጎዳ በሚል ነበር፡፡

እንደ አቶ ሳህሉ ገለፃ፣ ዋልያዎቹ የእግዚአብሔር ፈቃድ ሆኖ ከደቡብ አፍሪካ ጋር የተደረገውን ጨዋታ በድል በመወጣታቸው ለፌደሬሽኑ ሃላፊዎች ከእነጭራሹ ደብዝዞና ከስሞ የነበረው ተስፋቸውን አለመለመላቸው፡፡ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ግን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫው የመጨረሻ ማጣሪያ ምዕራፍ መግባቱን ባረጋገጠ ደስታ ተውጦ ነበር፡፡ ስለመርዶው ምንም የሚያውቀው ነገር አልነበረም፡፡ የፌዴሬሽኑ ሥ/አስፈፃሚ አባላት ሰኞ ዕለት 10 ሰዓት ላይ አስቸኳይ ስብሰባ ተቀመጡ፡፡ ስብሰባው የተፈጠረውን ሁኔታ በመገምገም እና ችግሩን ለይቶ አጠቃላይ የጋራ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ነበር፡፡ በዚህ የስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ ከ11 አባላቱ ባሻገር ዋና አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻውና የጽ/ቤት ኃላፊዎች በሙሉ ተገኝተውበታል፡፡ እንደ ፌደሬሽኑ አመራሮች ማብራርያ፣ በስብሰባው የፊፋን የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ህገ ደንብ በማጣቀስ በቀረበው ክስ ዙርያ መከራከርያ ነጥቦች ተነስተው ተመክሯል፡፡

ከቀኑ 10 ሰዓት ተጀምሮ እስከ ምሽቱ 2 ሰዓት ተኩል በዘለቀው ስብሰባ፣ የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚዎች እንደየሃላፊነታቸው እና የስራ ድርሻቸው በቡድንና በተናጠል ተገማግመዋል፡፡ ስብሰባው የመደናገጥ እና የመላቀስ ድባብ እንደነበረውና ስፖርታዊ ጨዋነትን በተላበሰ መንገድ እንደተከናወነ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የተናገሩት የፌደሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ሳህሉ፣ በመገማገም መድረኩ ስህተት መፈፀሙ እንደተረጋገጠ ፤ በቀረበው ክስ ለፊፋ ይግባኝ ለመጠየቅ እና ለመከራከር እንደማይቻል ታወቀ ብለዋል፡፡ ለደረሰው ጥፋት ተጠያቂ መኖር እንዳለበት በመተማመን በየደረጃው ተጠያቂ አካላትን በመለየት በጋራ መግባባት ውሳኔ ላይ መደረሱን ሲያብራሩም ምንም አይነት ሆን ተብሎ የተደረገ (Deliberate) የተሸረበ ሴራ (sabotage) ፣ የታቀደ ተንኮል (Intentional) እንዳልሆነ ተረድተናል ብለዋል፡፡ ዋልያዎቹን ነጥብ ያስጣለው ዝርክርክ አሰራር፤ ተጠያቂዎቹ እና ቃላቸው በፌደሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ግምገማ ላይ ለተፈፀመው ጥፋት የመጀመርያው ተጠያቂ የሆኑት ተቀዳሚ ም/ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃኑ ከበደ ናቸው፡፡ አቶ ብርሃኑ ከበደ የቡድን መሪ ሆነው የተሾሙት የዓለም ዋንጫው የምድብ ማጣርያ በደቡብ አፍሪካ እና ኢትዮጵያ ጨዋታ ሩስተንበርግ ላይ ሲጀመር እና ከዚያም በኋላ በሁለተኛ ዙር የምድብ ማጣርያ አዲስ አበባ ላይ ኢትዮጵያ እና ሴንትራል አፍሪካ ባደረጉት ግጥሚያ የቡድን መሪ ከነበሩት አቶ አፈወርቅ አየለ ሃላፊነቱን በመረከብ ነበር፡፡ ከሁሉም በላይ በእኔ ኃላፊነት ይህ ጥፋት በመድረሱ የተሰማኝን ሃዘን መግለጽ እፈልጋለሁ በማለት ቃላቸውን መስጠት የጀመሩት አቶ ብርሃኑ ከበደ፤ በዋልያዎቹ የቡድን መሪነት ስራቸውን የጀመሩት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በጋብሮኒ ከቦትስዋና አቻው ጋር በተጋጠመበት ወቅት ነበር፡፡

የፌደሬሽኑ ፅህፈት ቤት የዚሁን ጨዋታ ኮሚኒኬ አስፈርሞ እንደሰጣቸው ቢገልፅም፤ አቶ ብርሃኑ ግን በሰጡት ቃል ፈረሙበት የተባለው ደብዳቤ ኮፒ እጃቸው ላይ እንደማይገኝ፤ እንደተሰጣቸው እንደማያስታውሱ፣ ተሰጥቷቸውም ከሆነ ደብዳቤው እንዴት ከእጃቸው እንዳመለጠ እንደማይገባቸው ነው የገለፁት፡፡ በጋብሮኒ ለተካሄደው ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ልዑካን የቪዛ ጉዳዮች እና ሌሎች ጉዳዮች የማስፈፀም ድርብ ሃላፊነት እንደነበረባቸው ያስታወሱት አቶ ብርሃኑ ከበደ፣ በወቅቱ ዋና ተቀዳሚው ም/ፕሬዚዳንት አቶ ተካ አስፋውና ዋና ፀሐፊው አቶ አሸናፊ እጅጉ ሞሪሽዬስ ውስጥ በሚደረግ የካፍ ስብሰባ ላይ ለመካፈል ሄደው ስለነበር በሎጀስቲክ ስራዎች ላይ አተኩረው እንደነበር ፣ ተቀጥረው የሚሰሩበት ከፌደሬሽኑ ውጭ ያለ ስራቸውም ለተጨማሪ ውጥረት እንደዳረጋቸው፣ በዚህ ውዥንብር ውስጥ “ደብዳቤው እንዳመለጠኝ ነው የሚገባኝ” ብለዋል፡፡ ልጆቹ ወደ ሜዳ ሲመጡ እኮ እንደ ቡድን መሪነት ብቻ ሳይሆን እንደ አሰልጣኞቹ ረዳት ሆኜ ኳሶችና የመለማመጃ ቁሳቁሶችን ይዤ ነው የምጠብቃቸው፣ ዋናው ነገር ከእጅ ላይ መጥፋቱን እንዴት ላስተውል በማለት በተሰበረ ስሜት ማብራርያቸውን የቀጠሉት አቶ ብርሃኑ፤ ከጽ/ቤት በኩልም ብርሃኑ እንደዚህ አይነት ወረቀት ሰጥተንሃል ብሎ ያስታወሳቸው እንዳልነበር በመጥቀስ፣ የልጆቹን መነሳሳት በጣም እፈልገው ስለነበር ስለሚገጥሙን ውጣ ውረዶች ለማንም ሳልናገር የጉዞ እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በማስፈፀም አተኮርኩ እንጂ የቀይና ቢጫ ጉዳይ ትዝ አላለኝም ነበር በማለት አስረድተዋል፡፡ በተፈጠረው ስህተት ጥፋተኛው ራሴ እንጅ ማንም ላይ ለማላከክ አልፈልግም ያሉት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ብርሃኑ ከበደ፤ ደብዳቤው አምልጦኛል፡፡ ለምን አመለጠህ ቢባል እንኳን አላውቀውም፡፡ ከማናችንም በላይ ያዘንኩት እኔ ነኝ፡፡

ወደዚህ የመጣሁት ላገለግል ልሠራ ነው፡፡ በህይወቴ እንደዚህ አይነት ነገር እንዲያጋጥመኝ አልጠብቅም ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብን በጣም ይቅርታ እጠይቃለሁ በማለት ንግግራቸውን ቋጭተዋል፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ተጠያቂ የሆኑት ደግሞ የብሄራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝን ሰውነት ቢሻውና ሌሎች አካላት ናቸው፡፡ ያጋጠመው ጥፋት ሁላችንንም ከልብ አሳዝኖናል ያሉት አሰልጣኝ ሰውነት፤ለደረሰንበት ደረጃ ሚዲያው፣ ህብረተሰቡ፣ ስራ አስፈፃሚው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሁሉም አካላት ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸውን ከገለፁ በኋላ በቡድን ነው እየተሰራ የነበረው ችግር ቢኖር ኖሮ ከሚዲያው በኩል ይጠቆመን ነበር ብዬ ነው አስብ የነበረው ብለዋል፡፡ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው አስተያየታቸውን ሲቀጥሉ ‹‹ከፅህፈት ቤቱ ተሰጥቶታል የተባለው ኮሚኒኬ ለአቶ ብርሃኑ ደርሶ ይሆናል፣ እኔ አልወሰድኩም፡፡ እሱ ባይደርሰው እኔ ከደረሰኝ መረጃው አለ ማለት ነው፡፡ በእንግሊዝኛ ቢፃፍም አነባለሁ፡፡ እንግሊዝኛ ማንበብ ባልችል ኖሮ ተተርጉሞ ይላክልኝ ነበር፡፡ ወረቀቱ አልደረሰኝም፡፡ ያ በመሆኑ እጅግ አዝናለሁ፡፡ ለአንዳችን ቢደርሰን ምናለበት፡፡ እኛ ወረቀቱም አንጠብቅም፡፡ ቢጫ ያዩትን ልጆች እናውቃቸዋለን፡፡ ምንያህል በደቡብ አፍሪካው ጨዋታ ያየው ቢጫ ካርድ አለ፣ ከዚያ በኋላ አፍሪካ ዋንጫ ተካሂዶ ከቦትስዋና ጋር ባደረግነው ጨዋታ ሁለተኛውን ቢጫ ካርድ አየ፡፡ ያንን የሚገልጽ ወረቀት ግን አልደረሰኝም፡፡

ከዚህ ውጭ የተቀጡ ልጆችን በሚደርሰን መረጃ መሰረት እንዳይሰለፉ እናሳርፋቸዋለን፡፡ ቢጫና ቀይ ያላቸው ተጨዋቾች ጋር እንነጋገራለን፡፡ ተጨዋቾችም ያለባቸውን ቅጣት በሜዳ ላይ ከሚያደርጉት እንቅስቃሴ ጋር በማያያዝ ይነግሩናል፡፡›› በማለት አጠቃላይ ሁኔታውን ለማብራራት ሞክረዋል፡፡ ስህተቱን ሰርተን አንድ ደረጃ እንድደርስ የተፈጠረ ሁኔታ ይመስለኛል ያሉት ዋና አሰልጣኙ፤በምንሰራቸው ስራዎች ሁሉ በቂ ጥንቃቄና ትኩረት እንዲኖረን ያስተማረን ነው በማለት አሁንም ቡድናቸው የማለፍ ሰፊ ዕድል እንዳለው ለማስገንዘብ ጥረዋል፡፡ ‹‹የተሰደብንበት፣ ኢትዮጵያ የተሰደበችበት ውድድር ነው፣ በቢጫና ቀይ ጥፋት የምንተወው ነገር አይደለም፡፡ አንድ ታሪክ ሰርተን ቆመን በአደባባይ የምንናገርበት ስራ እኮ ነው፡፡ ማንም አሳልፎ የሚሰጠው ነገር የለም፡፡ በቃ 3 ነጥብ አጣን፣ ቦትስዋና ትወስደዋለች፡፡ ደቡብ አፍሪካን እንበልጣታለን፡፡ አስቀድሞ በነበረን እቅድ ከሴንትራል አፍሪካ ጋር ከምናደርገው ጨዋታ ሁለተኛውን ቡድን ለማሳለፍ ነበር፡፡ ያንን ማድረግ አንችልም፡፡ እስከመጨረሻው የማጣሪያ ጨዋታ ባለን ጊዜ ተጨዋቾችንን በሙሉ አቅም ሰብሰብ አድርገን አደራጅተን፣ በቂ ዝግጅት አድርገን መስከረም 6ቀን 2006 ዓ.ም ሴንተር አፍሪካን ገጥመን በማሸነፍ ለመጨረሻው የማጣሪያ ምዕራፍ እንገባለን፡፡

ለወደፊት የሚደገም ስህተት አይሆንም፡፡›› በማለትም ብሄራዊ ቡድኑ በውጤታማነት እንደሚቀጥልም በልበሙሉነት ተናግረዋል፡፡ ከአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ጋር በፌደሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ በሁለተኛ ደረጃ የተጠየቁት የቀድሞው የብሄራዊ ቡድን ረዳት አሰልጣኝ ስዩም ከበደ እና የስራ አስፈፃሚው አባል እና በደቡብ አፍሪካ እና ኢትዮጵያ ጨዋታ የቡድን መሪ የነበሩት አቶ አፈወርቅ አየለ ናቸው፡፡ አሰልጣኝ ስዩም ከበደ፣ ባለህ የዳበረ ልምድ እንዲሁም ከኮምፒውተርና ከኢንተርኔት ጋር በነበረህ የተሻለ ቅርበት የደቡብ አፍሪካው ጨዋታ ላይ የነበረውን የቢጫ ካርድ ጥፋት እያወቅህ በቅንነት አልተናገርክም በሚል ተገምግሟል፡፡ የቡድን መሪ የነበሩት አቶ አፈወርቅ አየለ ደግሞ በ2014 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ሲጀመር፣ የቡድን መሪ ሆነው በሰሩበት ወቅት፣ የፊፋ የውድድር ህገ ደንብ ተሰጥቷቸው ለሚመለከታቸው ባለመስጠታቸውና ለተጨዋቾች በቂ ግንዛቤ እንዲፈጠር ባለመስራታቸው እንዲሁም ለተተኪው የቡድን መሪ መረጃዎችን ባለማስተላለፋቸው በቅንነት መጓደል ጥፋተኛ ተብለዋል፡፡

የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ በ3ኛ ደረጃ ተጠያቂ ያደረገው ምንያህል ተሾመን ነው፡፡ ምንም እንኳን በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ በርካታ ጋዜጠኞች በተጨዋቹ ተጠያቂነት ላይ ፌደሬሽኑ የደረሰበት ድምዳሜ የልጁን ድካምና አስተዋፅኦ ከግምት አላስገባም በሚል ውሳኔው በድጋሚ እንዲጤን ግፊት ቢያደርጉም የፌደሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ሳህሉ ገብረወልድ ተጨዋቹ ለተፈፀመው ጥፋት የኢትዮጵያ ህዝብን በግልፅ ይቅርታ ሊጠይቅ እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት፡፡ ምንያህል ተሾመ ለስራ አስፈጻሚው ስብሰባ ተጠርቶ ሊገኝ አለመቻሉን በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የጠቆሙት የፌደሬሽኑ ፕሬዝዳንት፤ በተፈፀመው ጥፋት ተጨዋቹ በጣም ማዘኑንና መከፋቱን ከመገናኛ ብዙሃን መረዳታቸውን ገልፀው፣ ፌዴሬሽኑ ጥሪ ያደረገለት በጉዳዩ ላይ ለሚቀርብበት ጥያቄ ምላሽና ማብራሪያ እንዲሰጥ እንደነበረና እንደ ፕሮፌሽናል ተጨዋች ሙያውን አክብሮ ስህተቱ እንዳይፈፀም ባለመጠንቀቁ፣ እንዲሁም እኔ አይደለሁም ቢጫ ካርዱ የተሰጠኝ፣ አጠገቤ ለነበረው ለሌላ ተጨዋች ነው በማለት አሳማኝ ያልሆነ አስተያየት መስጠቱን ኮንነዋል፡፡ ዳኛ በቃሬዛ ለሚወጣ ተጨዋች እንኳን የካርድ ቅጣት ይሰጣል፡፡ አላወቅሁም አላስተዋልኩም ማለቱ አያሳምንም ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ማሰብ ያለበት ለብሔራዊ ቡድን፣ ለአገራዊ ኃላፊነትና ግዴታ ነበር፡፡ ያለበትን ኃላፊነት ስነምግባራዊ በሆነ መንገድ አልተወጣም፤ ስለዚህም ተጠያቂ ነው ብለዋል፡፡ የፌደሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ በ4ኛ ደረጃ ተጠያቂ ያደረገው ጽ/ቤቱ እና ዋና ፀሐፊውን አቶ አሸናፊ እጅጉ ነው፡፡

የፌዴሬሽኑ ዋና ፀሐፊ አቶ አሸናፊ እጅጉ፤ በጋዜጣዊ መግለጫ መጀመርያ ላይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የዓለም ዋንጫውን ማጣሪያ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ችግሩ እስከተፈጠረበት የቦትስዋና ጨዋታ ድረስ ያለውን የስራ ሂደት አስረድተው ነበር፡፡ “በማንኛውም ጊዜ በወንዶቹም በሴቶችም ብሔራዊ ቡድኖች የአፍሪካና የዓለም አቀፍ ውድድር በሚመጣበት ጊዜ ለፌዴሬሽኑ ጽ/ቤት ኮሚኒኬ ይደርሰናል” ያሉት ዋና ፀሃፊው አቶ አሸናፊ እጅጉ፤ ኮሙኒኬዎች ሲደርሱ በቀጥታ የሚሰጣቸው አካላት አሉ፡፡ ኮሚኒኬዎች በተለያዩ የሰነድ ወረቀቶች ተደብቀው እንዳይቀሩ በአስቸኳይ ወዲያውኑ ለሚመለከተው አካል የምንሰጥበት አሰራር አለ በማለት ዝርዝር ማብራርያ አቅርበዋል፡፡ በአጠቃላይ ዋና ፀሐፊው የአራቱ የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ግጥሚያዎች ኮሚኒኬዎች ከፊፋ ተልከው ወደ ፅህፈት ቤቱ በደረሱ ማግስት ለቡድን መሪዎች በማስፈረም፤ ኮሚኒኬው እንዲደርሳቸው መደረጉን በቀረን ማስረጃ አረጋግጠናል በማለት ለፅህፈት ቤቱ በኮፒ የቀሩ ማስረጃዎችንም አሳይተዋል፡፡

ጽ/ቤቱ ምን ማድረግ ሲገባው ምን እንዳላደረገ መግለጽ እንዳለበት የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ካሳሰቡ በኋላ፤ ዋና ፀሐፊው አሸናፊ ተጠያቂ ስለመሆናቸው በራሳቸው አንደበት እንዲናገሩ እድል በተሰጣቸው ጊዜ “ግዴታዬን በሚገባ ተወጥቻለሁ፣ ማስተዋል ነበረብህ ለሚባለው እያወቅሁ ያጠፋሁት አይደለም፡፡ ኮሙኒኬዎች ለቡድን መሪው በአስቸኳይ እንዲሰጥ አድርጌያለሁ፡፡ ተጨዋቹ ሁለት ቢጫ እንዳለበት አላየሁም፤ አለማስታወሴ ጥፋት ሊሆን ይችላል፡፡” በማለት አጠር ያለ ቃላቸውን ሲሰጡ፤ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ሳህሉ ዋና ፀሃፊው ለምን ተጠያቂ እንደሆኑ አብራርተዋል፡፡ ዋና ፀሐፊው ለፌደሬሽኑ ከፍተኛ አመራሮች እና ሃላፊዎች ትኩረት በመስጠት ደብዳቤዎችን ማድረስ ሲገባው፤ በጽሕፈት ቤት በኩል ወይም በፀሐፊው አማካኝነት ደብዳቤው ይሰጠው በሚል መስራቱ ትክክል አልነበረም ያሉት ፕሬዝዳንቱ ፤ አቶ አሸናፊ እጅጉ ተገቢውን የአሰራር ስነምግባር እና ስነስርዓት በመጠበቅ በስልክ ጠርቶ በአካል ተገናኝቶ ደብዳቤዎችን ለሚመለከታቸው መስጠት ሲገባው ይህን ባለማድረጉ ተጠያቂ ነው፡፡

ለዋና አስልጣኙም ይህን አላደረገም፡፡ ስለዚህ ጽ/ቤቱ በነፈገው ትኩረት ተጠያቂ ነው፡፡ ተገቢ የሆነ ክብርና ስነምግባር ባለመከተል ለተፈጠረው ችግር አስተዋጽኦ እንደነበረው በግምግማችን አምኖ ተቀብሏል በማለት አስረድተዋል፡፡ የፌደሬሽኑ ቀጣይ ተስፋ በጋዜጣዊ መግለጫው ከበርካታ የስፖርት ጋዜጠኞች የተነሱ ጥያቄዎች የፌደሬሽኑን ስራ አስፈፃሚዎች ያስጨነቁ ነበሩ፡፡ የፌደሬሽኑ ስራ አስፋፃሚ በጋዜጣዊ መግለጫው የደረሰውን ጥፋት በወረቀት መጥፋት ማሳበቡ፤ በጠቅላላው ስራ አስፈፃሚው ሙሉ ለሙሉ ተጠያቂ መሆን ሲገባው ግለሰቦችን በተናጠል ተጠያቂ ማድረጉ ተገቢ አለመሆኑን፤ የፌደሬሽኑ አሰራር የተበላሸ እና በአማተሪዝም የወደቀ መሆኑ ለችግሩ መንስኤ እንደሚሆን እንዲሁም ፌደሬሽኑ በሀምሌ ወር መጨረሻ ጠቅላላ ጉባኤ ያደርጋል ተብሎ ሲጠበቅ ይሄው ቀነ ቀጠሮ እንዲራዘምለት ስፖርት ኮሚሽን መጠየቁን በተመለከተ በተነሱ አንኳር ጉዳዮች እና አጀንዳዎች ላይ የፌደሬሽኑ አመራሮች ምላሾችንም ሰጥተዋል፡፡ የተሳሳትነው በርካታ ፈታኝ የውድድር ምእራፎችን በማለፋችን በተደራራቢ የእድገት እና የለውጥ ምእራፎች ስንቀሳቀስ በመቆየታችን ነው ሲሉ የተናገሩት አቶ ሳህሉ ገብረወልድ ‹‹በአጠቃላይ በውስጥ አካሎች ድክመት በፌዴሬሽኑ የተሰራው ስራ ሁሉ ጥላሸት ተቀብቷል፡፡ የኃላፊነትና ተጠያቂነት ስራ በየደረጃው ባለመፈፀሙ ለተፈጠረው ስህተት አዝነናል፡፡

በተጠያቂዎች ላይ ርምጃ ለመውሰድ ሰኞ የተደረገው የስራ አስፈፃሚ ስብሰባ በቂ ግዜ አልነበረም፡፡ ጊዜ ባለመኖሩ በተጠያቂዎች ላይ የሚተላለፈው ቅጣት አልተላለፈም፡፡ በተጠያቂዎች ላይ በየደረጃው በማድረጉ ስብሰባዎች የቅጣት ውሳኔዎችን እናስተላልፋለን›› ብለዋል፡፡ የፌደሬሽኑን አመራር በፕሮፌሽናሊዝም የአሰራር መዋቅር ለማጠናከር ስንቀሳቀስ ቆይተናል የሚሉት አቶ ሳህሉ ገብረወልድ፤ ባለፉት አራት አመታት የሰው ሃይል በማደራጀት፤ አሰራሮችን በማሻሻል የገቢ ምንጮችን በማስፋት ብዙ ተግባራት እንደተከነወኑ ገልፀው እውቀትና ችሎታ ያላቸውን ባለሙያዎች ከያሉበት አሰባስበን በእድገት እና ለውጥ ለመቀጠል በያዝነው እቅድ እንቀጥላለን ብለዋል፡፡ ፌደሬሽኑ ሃላፊነትን ወስዶ ተጠያቂነትን የሚሸሽበት ምንም ምክንያት የለም ያሉት የፌደሬሽኑ ዋና ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ተካ አስፋው ሲሆኑ የምንሰራው በጋራ አመራር ስለሆነ ሃላፊነት አለብን ሁላችንም ጥፋት ፈፅመናል እንጅ ጥፋት ፈፅመዋል አላልንም ሲሉ አስረድተው የትም አገር ላይ ስህተት ይፈፀማል፤ አምስት አገር ተሳስቷል፡ ብቸኛዎቹ እኛ ብንሆን ምን ሊፈጠር ነበር፡፡

ስህተቱን ማሳነስ አይደለም ብሄራዊ ቡድኑ 3 ነጥብ አሳጥተነዋል ለዚህ ሁላችንም ተጠያቂ ነን፡፡ በህግ አነጋገር ሆን ተብሎ ወይም በቸልተኝነት ጥፋት አለ፡፡ እኛ የሰራነው ስህተት ግን ሁለቱንም አይደለም ›› በማለት የፌደሬሽኑን ተዓማኒነት ለመከላከል ሞክረዋል፡፡ የደረሰው ጥፋት የተቋሙ ውድቀትን አያሳይም ድክመት ግን እንዳለ ቢያመለክት ነው ያሉት አቶ ተካ፤ አስቀድመው ከነበሩት ፌዴሬሽኖች የተሻለ ሰርተናል ፤ ለውጦችም አሳይተናል፡፡ ከደቡብ አፍሪካው 29ኛው አፍሪካ ዋንጫ ስንመለስ ህዝብ በደማቅ አቀባበል ነው የተቀበለን፡፡ ዋንጫ ስላሸነፍን አይደለም ጥሩ ተሳትፎ ስለነበረን ነው፡፡ ህዝብ ዳኝነት ያውቃል፡፡ አሁን በተፈጠረው ስህተት ህዝቡ ፌደሬሽኑን አይንህን ላፈር ይለዋል ብለን አንጠብቅም፡፡ 4 ዓመታትን ሰርተናል፡፡ ለ12 አምስት ጉዳይ በተፈፀመ ስህተት መኮነን የለብንም፤ የሚሰራ ነው የሚሳተተው እኛስ መጥኔ ለሚመጣው ፌደሬሽን ነው የምንለው›› በማለትም ተጨማሪ ማብራርያ ሰጥተዋል፡፡

በኢትዮጵያውያን የዲሞክራሲ እና የነፃነት ትግል ላይ ተንተርሶ የተፃፈው “የአሲምባ ፍቅር” መጽሐፍ ዛሬ እንደሚመረቅ ሜሮኢ መልቲሚዲያ አስታወቀ፡፡ 448 ገፅ ያለውን መጽሐፍ የደረሱት ካህሳይ አብርሃ ብስራት ናቸው፡፡ በኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ እና ግንባር (ኢህአፓ/ኢህአሠ) ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ላይ ተመስርቶ የተፃፈው መጽሐፍ የሚመረቀው መስቀል አደባባይ በሚገኘው የቀይ ሽብር ሰማዕታት ብሔራዊ ሙዚየም ነው፡፡ “የአሲምባ ፍቅር” በ100 ብር እየተሸጠ ነው፡፡ በሌላ በኩል “ውጥንቅጥ” የተሰኘው የግጥም መጽሐፍ ነገ እንደሚመረቅ ገጣሚው አስታወቀ፡፡ ባምቢስ አካባቢ በሚገኘው ትልቁ ዮርዳኖስ ሆቴል የሚመረቀውን የግጥም መጽሐፍ የፃፈው ዮርዳኖስ ፍቃዱ ተክለማርያም ነው፡፡

በአስራት አብርሃም የተሰናዳውና “ፍኖተ ቃየል” በሚል ርእስ “የኢትዮጵያን ፖለቲካ ሽርፍራፊ ገፆች” የሚያሳየው መጽሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ 199 ገፅ ያለው መጽሐፍ የተቃዋሚ ኃይሎችን አሰላለፍ፣ የርእዮተዓለማዊ ትግልን፣ ሕወሓትንና ሌሎችን የተመለከቱ ርእሰ ጉዳዮች አካቷል፡፡ የመጽሐፉ መሸጫ ዋጋ 45 ብር ነው፡፡ አዘጋጁ አቶ አስራት ካሁን ቀደም “መለስ እና ግብፅ”፣ “ከአገር በስተጀርባ” እና “ጎበዝ ተማሪ የመሆን ምስጢር” በተሰኙ መጻሕፍቶቻቸው ይታወቃሉ፡፡

“ኬሮ” የተሰኘው የድምፃዊት ቢጢቅ እምላዕሉ የሙዚቃ አልበም ለገበያ ቀረበ፡፡ አስራ አራት ዘፈኖች የተካተቱበት አልበም መጠርያ ወላይትኛ ሲሆን አስሩ ዘፈኖች የአማርኛ፣ አራቱ ዘፈኖች ደግሞ የእንግሊዝኛ ናቸው፡፡ ሉሽስ መልቲ ፕሮዳክሽን አሳትሞ አምባሰል ሙዚቃ ቤት እያከፋፈለ የሚገኘውን አልበም ግጥሞች ማትያስ ይልማ፣ ዲጄ ዊሽ፣ ቤቲ ሮክ፣ ዳዊት ወርቁና ሌሎችም የፃፉት ሲሆን ዜማው በማትያስ ይልማ ተዘጋጅቷል፡፡ ሙዚቃውን ያቀናበሩት ደግሞ አቤል ጳውሎስ እና ኬኒ አለን ናቸው፡፡

በአዲስ አበባ የሚገኙ ወጣቶች የሙዚቃ ምትን በመጠቀም መልእክት ማስተላለፍ በሚቻልበት መንገድ ሥልጠና ተሰጣቸው፡፡ ለሃያ ወጣቶች ለአስር ቀናት የተሰጠው ስልጠና በኢትዮጵያ ሲካሄድ የመጀመርያው መሆኑን ሥልጠናውን ያስተባበረው ኢንትራሄልዝ ኢንተርናሽናል - ኢትዮጵያ አስታውቋል፡፡ “ቢት ሜኪንግ ላብ” በተሰኘ በጀርባ ቦርሳ ሊያዝ የሚችል የሙዚቃ ስቱዲዮ በመጠቀም ስልጠናውን የሰጡት በአሜሪካ የሰሜን ካሮላይና ዩኒቨርሲቲ የሙዚቃ ፕሮፌሰሮች እና የተንቀሳቃሽ ስቱዲዮው መስራቾች ናቸው፡፡ በጤና ላይ የሚሠራው ኢንትራሄልዝ እና የዩኒቨርሲቲው የሙዚቃ ፕሮፌሰሮች ቀጣይነት ያለው ሥልጠና የወጣቶችን የሙዚቃ ክህሎት በማዳበር ወጣቱን በተዋልዶ ጤና፣ ኤችአይቪ/ኤድስ፣ በእናቶችና ሕፃናት ጤና እና በሌሎችም ማህበራዊ ዘርፎች የምት ሙዚቃ በመጠቀም ማስተማር እንደሚቻል ያሳየንበት ነው ብለዋል፡፡ ተማሪዎቹ ከትናንት ወዲያ ኮከበ ጽባሕ አካባቢ በሚገኘው የኢንትራሄልዝ ግቢ ሲመረቁ ለማስተማርያ የመጡት ተንቀሳቃሽ ስቱዲዮዎች ከወጣቶች ጋር ለሚሰሩት ለሚዩዚክ ሜይደይ ኢትዮጵያና “ሴቭ አወር ጀነሬሽን” ለተባለ ድርጅት ተለግሰዋል፡፡