Administrator

Administrator

አስከሬኑ ወደ ለንደን ተወስዶ እንዲመረመር ተጠየቀ

       በደቡብ ሱዳን ዐማፅያን ዘንድ ከፍተኛ ተሰሚነት የነበራቸው ዋኒ ቶምቤ ላኮ በአዲስ አበባ በመኖርያ አፓርትመንታቸው ውስጥ ሞተው ተገኙ፤ ቤተሰቦቻቸው አስከሬናቸው ወደ ለንደን ተወስዶ እንዲመረመር ጠይቀዋል፡፡
በለንደን በስደት ይኖሩ የነበሩት ቶምቤ፤ ባለፈው ዓመት ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት በቀድሞው የደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዝዳንት ሬክ ማቻር የሚመራውን የመንግሥት ተቃዋሚ ቡድን ተቀላቅለዋል፡፡ በተቃዋሚው ቡድን ውስጥ የተለየ የኃላፊነተ ቦታ ባይሰጣቸውም ሚያዚያ አጋማሽ ላይ በተደረገው የዐማፅያኑ የከፍተኛ ኃላፊዎች ስብሰባ ላይ ተሳታፊ ነበሩ፡፡ የተቃዋሚው መሪ ሬክ ማቻር የቶምቤን ሞት ተከትሎ በሰጡት መግለጫ፣ የእርሳቸው መሞት ለደቡብ ሱዳን፣ ለተቃዋሚ ቡድን እና ለቤተሰቦቻቸው ከፍተኛ ጉዳት እንደሆነ በመግለጽ ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡
የሞታቸውን መንስኤ በተመለከተ ከሐኪም የተሰጠ መረጃ ባይኖርም በቅርብ የሚያውቋቸው ጓደኞቻቸው በልብ ድካም ህይወታቸው አልፎ ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ የቶምቤ ቤተሰቦች በበኩላቸው፣ አስከሬናቸው ለንደን ሄዶ እንዲመረመር መጠየቃቸውን “ሱዳን ትሪቢዩን” ዘግቧል፡፡
ቶምቤ፣ በደቡብ ሱዳን የተቀሰቀሰውን የእርስ በርስ ጦርነት ተከትሎ በአሜሪካ፣ በካናዳ እና በአውስትራልያ በመዘዋወር ደቡብ ሱዳናውያን አሁን በሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት ለመጣል የትጥቅ ትግሉን እንዲቀላቀሉ ሰፊ ቅስቀሳ ማድረጋቸው ይነገርላቸዋል፡፡

  ፖሊስ የ10 ቀን የምርመራ ጊዜ ጠይቆባቸዋል

    በደቡብ ክልል የስልጤ ዞን ምሥራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ፣ የቂልጦ ጎሞሮ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤና የደብሩ ሕንፃ አሠሪ ኮሚቴ አባላት “ሃይማኖትን ከሃይማኖት ለማጋጨት ተንቀሳቅሳችኋል” በሚል በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡
የወረዳው ፖሊስ፣ ባለፈው ሳምንት ዓርብ እና በዚኽ ሳምንት ሰኞ ስድስት የሰበካ ጉባኤውንና የቤተ ክርስቲያኒቱን የሕንፃ አሠሪ ኮሚቴ አባላት በቁጥጥር ሥር በማዋል በቂልጦ ወረዳ ፍርድ ቤት አቅርቧቸዋል፡፡
ግለሰቦቹ “የድረሱልኝ ጥሪ” በሚል “ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጭ ጽሑፍ ጽፈው በፌስቡክ አሰራጭተዋል” ሲል ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ ግለሰቦቹ “የድረሱልኝ ጥሪ”  በሚል ደብዳቤ መጻፋቸውን ቢያምኑም በፌስቡክ አለመልቀቃቸውን ለፍርድ ቤቱ ገልጸዋል፡፡ ፖሊስ በቁጥጥር ሥር በዋሉት ግለሰቦች ላይ የማጣራው ነገር አለ በሚል የ21 ቀን የምርመራ ጊዜ የጠየቀባቸው ቢሆንም ፍርድ ቤቱ የ10 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ፈቅዶለታል፡፡
የወረዳው የጸጥታ ዘርፍ ሓላፊ አቶ ቶፊቅ ከድር፣ ስለ ጉዳዩ በስልክ ጠይቀናቸው፤ “በሕግ የተያዘ ጉዳይ በመሆኑ አስተያየት ለመስጠት አልችልም” ብለዋል፡፡
በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የሚገኙት የቂልጦ ቅድስት ማርያም ሰበካ ጉባኤ እና ሕንፃ አሠሪ ኮሚቴ አባላት÷ ሊቀ መንበሩ መ/ር የማርያም ወርቅ ተሻገር፣ መ/ር ሀብታሙ ተካ፣ አቶ ሙሉጌታ አራጋው፣ ወ/ሪት ንጋት ለማ፣ አቶ ማስረሻ ሰይፈ እና አቶ ማሩ ለማ ሲሆኑ በወረዳው የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ መሰናዶ ት/ቤት፣ የፖሊስ፣ የጤና እና የግብርና ጽ/ቤቶች እንዲሁም የባንክ ቅርንጫፍ ሠራተኞች ናቸው፡፡
‹‹የድረሱልኝ ጥሪ›› በሚል ርእስ የተሰራጨውና የደብሩን የሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት ማኅተም የያዘው ጽሑፍ÷ በስልጤ ዞን በምሥራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ምእመናን፣ በሃይማኖታዊ ማንነታቸው ላይ ባለሥልጣናት ይፈጽሙብናል ባሏቸው ግፎች መማረራቸውን፣ የአምልኮ ነጻነታቸው እና ሠርተው የመኖር ዋስትናቸውም አደጋ ላይ መውደቁን ያስረዳል፡፡
ኢትዮጵያ የሃይማኖት እኩልነት የተረጋገጠባት መሆኗን በፅሁፋቸው የጠቆሙት ምእመናኑ፣ ስለሚፈጸምባቸው ግፍና ሥቃይ ለወረዳው የፖሊስ እና የሕግ አካላት በየደረጃው ቢያመለክቱም የአስተዳደሩ መዋቅር እና አሠራር ያልተገባ “ሕጋዊ ሽፋን” በመስጠቱ የጥቃቱ ስልት ዐይነት እየጠነከረ መጣ እንጂ መፍትሔ አለማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡
በየመኖሪያ አካባቢያችንና በሥራ ቦታዎች እየደረሰብን ነው ያሉት እስር፣ እንግልት፣ ዛቻ፣ እንዲሁም በመ/ቤት ከደረጃ ዝቅ መደረግና መታገድ እና መባረር እየተጠናከረ መምጣቱን የገለጹት ምእምኑ፣ ድርጊቱ የተባባሰው፤ የቤተ ክርስቲያን መሥሪያ ቦታ ተረክበው የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ የመሠረት ድንጋይ ካስቀመጡበት ከጥቅምት 24 ቀን 2007 ወዲህ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
ለመንግሥት እና ለቤተ ክህነት አካላት አቤቱታቸውን ያሰሙበት “የድረሱልኝ ጥሪ” የሚለው ይኸው ጽሑፍ፣ የሀገረ ስብከቱን ፈቃድ በመጠየቅ የተዘጋጀ መሆኑን የገለፁት ምእመናኑ በአንዳንድ ባለሥልጣናት የሚደርስባቸውን ሥቃይ በመዘርዘር መፍትሔ የጠየቁበት እንደሆነ ጠቁመው፤ “ታምኑበታላችኹ ወይስ አታምኑበትም” እየተባለ ሃይማኖታዊ ግጭት እንደቀሰቀስንና የወረዳውን ስም እንዳጠፋን ተደርገን መታየታችን አሳዝኖናል ሲሉ ርምጃውን ተቃውመዋል፡፡
ቀድሞ ያስቀድሱበትና የመካነ መቃብር አገልግሎት ያገኙበት የነበረው የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ከ20 ዓመት በፊት መቃጠሉን ያስታወሱት ምእመናኑ፣ በምትኩ የሚያሠሩት የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኒቱ መቃኞ በመጪው ሰኔ 21 ቀን የሚመረቅ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
የሃዲያ እና ስልጤ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅን ጨምሮ የወረዳ ቤተ ክህነቱ ሓላፊዎች እንዲሁም የሰበካው ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ከወረዳው አስተዳደር ጋር በጉዳዩ ላይ እየተነጋገሩበት እንደሆነ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በሌላ በኩል ‹‹የድረሱልኝ ጥሪ›› በሚል በፌስቡክ ተሰራጭቷል ለተባለው ጽሑፍ የታሰሩት የሰበካ ጉባኤ አባላት ማስተባበያ እንዲሰጡና መሳሳታቸውን አምነው ይቅርታ እንዲጠይቁ በማግባባት ከእስር ለማስፈታት ጥረት እየተደረገ መኾኑንም ምንጮቹ አክለው ገልፀዋል፡፡

Saturday, 30 May 2015 12:52

የትንፋሽ ህክምና

ክብደትን ለመቀነስ

በመሬት ላይ እግርዎን አጣጥፈው ይቀመጡ፤

ወገብዎን ቀና፣ ሆድዎን ወደ ውስጥ ሳብ ያድርጉት፤

ግራ እጅዎን ጉልበትዎ ላይ ያድርጉ፣ በቀኝ እጅዎ

ሌባ ጣት የግራ አፍንጫዎን ይዝጉት፡፡ ወደ ውጪ

ይተንፍሱ፣ ይ ህንን በ መደጋገም ይ ከውኑ። በቀን

ውስጥ በተመችዎ ጊዜ የቻሉትን ያህል ለመሥራት

ይሞክሩ፡፡ በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ ክብደትዎ

መቀነሱንና የምግብ ፍላጎትዎ መቆጠቡን

ይታዘባሉ። እስቲ አሁኑኑ ይሞክሩት …

(ምንጭ፡- ታይም መፅሔት

June 2011)

Saturday, 30 May 2015 12:44

የሰውነታችን እውነታዎች

 

 

 

- ጨጓራችን የላም ወተትን ለማብላላት አንድ

ሰዓት ይፈጅበታል

- የሴቶች አይን ከወንዶች ይልቅ በእጥፉ

ይርገበገባል

- አንድ ሰው በአማካይ 2 ሚሊዮን የላብ

እጢዎች ይኖሩታል

- ህፃናት ሲወለዱ የጉልበት ሎሚ

አይኖራቸውም፤ ይህ ሰውነት ክፍል

የሚወጣው ከ2-6 ዓመት ባለው የህፃናቱ

እድሜ ውስጥ ጊዜ ነው

- በፀደይ ወራት የህፃናት እድገት ፈጣን ነው

 

 

 

 

Saturday, 30 May 2015 12:40

የግጥም ጥግ

እልፍ ከሲታዎች ቀጥነው የሞገጉ

“ሥጋችን የት ሄደ” ብለው ሲፈልጉ

በየሸንተረሩ በየጥጋጥጉ

አስሰው አስሰው በምድር በሰማይ

አገኙት ቦርጭ ሆኖ አንድ ሰው ገላ ላይ፡፡

(“ኗሪ አልባ ጎጆዎች”፤ በዕውቀቱ ስዩም)

Saturday, 30 May 2015 12:39

የፍቅር ጥግ

 

 

 

* ፍቅር በፈገግታ ይጀምራል፤በመሳሳም ያድጋል፤በእንባ ይቋጫል፡፡

            ያልታወቀ ሰው

* ፍቅር እንደ ነፋስ ነው፤አታየውም ግን ይሰማሃል፡፡

            ኒኮላስ ስፓርክስ

* ምክንያት የሌለው ፍቅር ዕድሜው ረዥም ነው፡፡

            ያልታወቀ ሰው

* ፍቅር አብሮን የተፈጠረ ሲሆን ፍርሃት እዚህ የምንማረው ነው፡፡

            ማሪያኔ ዊላምሰን

* የሚወደን ሰው ከሌለ፣ ራሳችንን መውደድ ትተናል ማለት ነው፡፡

      ማዳም ዲ ስቴል

* ራሳችሁን ማፍቀር እንዳትረሱ፡፡

      ሶረን ኪርክጋርድ-

* ሰውን መውደድ የእግዜርን ፊት ማየት ነው፡፡

      ሌስ ሚዘረብልስ

* ፍቅር ከባድ ሥራ ነው፡፡ ከባድ ሥራ ደግሞ አንዳንዴ ይጎዳል፡፡

      ያልታወቀ ሰው

* ፍቅር ሲይዘን በጣም የምናምነውን ነገር እንጠራጠራለን፡፡

      ላ ሮቼፎካልድ

* ስለፍቅር የምናውቀውን ብዙውን ነገር የምንማረው ከቤት ነው፡፡

      ያልታወቀ ሰው

* ፍቅር ከምንም በላይ የራስ ስጦታ ነው፡፡

      ጄን አኖይልህ

* በፍቅር መውደቅ ቀላል ነው፤ከባዱ የሚያነሳህ ሰው ማግኘቱ ነው፡፡

      በርትራንድ ራሴል

* ልብህን ለከፈትክላቸው ሰዎች አንደበትህን አትዝጋባቸው፡፡

      ቻርልስ ዲከንስ

* ፍቅር፤የሌላው ሰው ደስታ ለራስህ ወሳኝ የሚሆንበት ሁኔታ ነው፡፡

      ሮበርት ሄይንሊን

ሰው ሊደብቃቸው የማይችላቸው ሁለት ነገሮች፡ ስካር እና ፍቅር፡፡

አንቲፋንስ

* ሰዎችን የምትተች ከሆነ ለመውደድ ጊዜ አይኖርህም፡፡

ማዘር ቴሬዛ

 

 

 

 

 

 

 

ኢትዮጵያዊ ፊልሞችን የሚሰራው “ካም ግሎባል ፒክቸርስ” የተመሰረተበትን 20ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ባለፈው ረቡዕ ለስድስት እውቅ ተዋንያን የክብር ሽልማት ሰጠ፡፡ ተሸላሚዎቹ አርቲስት ኪሮስ ኃ/ሥላሴ፣ ሰለሞን ቦጋለ፣ ግሩም ኤርሚያስ፣ ማህደር አሰፋ፣ አማኑኤል ሀብታሙ እና የትናየት ታምራት ሲሆኑ ሁሉም ተዋናዮች ባለፉት ዓመታት ”ካም ግሎባል ፒክቸርስ” በሰራቸው ፊልሞች ላይ መተወናቸው ታውቋል፡፡ ድርጅቱ ከሰራቸው ፊልሞች መካከል “ስውሩ እስረኛ”፣ “በራሪ ልቦች”፣ “አማላዩ”፣ “ሼፉ” (ቁጥር 1 እና 2)፣ “ወደ ገደለው” እና “አማረኝ” ይገኙበታል፡፡

 

 

 

 

“እስኪ ተጠየቁ” የተሰኘው የዮሐንስ አድማሱ የግጥም መድበል ነገ በ8 ሰዓት በብሄራዊ ቤተ መፃሕፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት ይደረግበታል፡፡ለውይይቱ መነሻ ሃሳብ የሚያቀርቡት አርክቴክትና ደራሲ ሚካኤል ሽፈራው እንደሆኑ ታውቋል፡፡ውይይቱን ያዘጋጁት እናት የማስታወቂያ ድርጅት፣ ጀርመን የባህል ማዕከልና ብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ-መፃሕፍት ኤጀንሲ በጋራ ሲሆን የሥነፅሁፍ ቤተሰቦች በውይይቱ ላይ እንዲገኙ ጥሪ ቀርቦላቸዋል፡፡

 

     የገጣሚ ኃይሌ ተስፋዬ ቸኮል የግጥም ስብስቦች የተካተቱበት “የራዕይ እግሮች” የተሰኘ የግጥም መድበል ነገ ከጧቱ 3፡00 ጀምሮ በፍፁም ሲኒማ ይመረቃል፡፡ የግጥሙ ይዘት ማህበራዊ፣ መንፈሳዊና ፖለቲካዊ ትዝብት ላይ የሚያተኩር ሲሆን የግዕዝን ቋንቋ በመቀላቀል በጠንካራ አገላለፅ የታጀበ ነው ተብሏል፡፡

ገጣሚው ግጥም ወደመፃፍ የተሳበበትን ምክንያት በመድበሉ መግቢያ ላይ ሲያስረዳ፤ “ገና በ11 ዓመቴ አካባቢ ቤተክርስቲያን ስማር የእነሙሴን፣ ዳዊትን … ረዣዥም ግጥሞች ከመፅሀፍ ቅዱስ ቃል በቃል እገለብጥ ነበር፡፡ ይህ የህይወት ልምምድም እድሜዬ እየጨመረ በመጣ ጊዜ ትልቅ ዕርዳታ አድርጎልኛል” ብሏል ገጣሚው፡፡ በ110 ገፆች የተቀነበበው መድበሉ፤ 73 ግጥሞችን ያካተተ ሲሆን ለአገር ውስጥ በብር 35.50፣ ለውጭ ደግሞ በ15 ዶላር እንደሚሸጥ ታውቋል፡፡ 

 

 

 

 

በዘመናዊ ቴክኖሎጂ፣ በምቹ ወንበሮችና ከውጭ አገራት በገቡ የተለያዩ መሳሪያዎች የተደራጀው “ሶሎዳ ቪአይፒ ሲኒማ” በከተማዋ እምብርት አራት ኪሎ፣ ዴንቨር ታዎር ላይ ከትላንት በስቲያ ተመርቆ ተከፈተ፡፡በቪአይፒ ደረጃ የታነፀው ሲኒማ ቤቱ፤ በአንድ ጊዜ ውስን የተመልካች ቁጥር እንደሚያስተናግድ ተገልጿል፡፡

ሲኒማ ቤቱ የተከፈተበትን ምክንያት ለአዲስ አድማስ በላከው መግለጫ ያብራራው ድርጅቱ፤ በሃገራችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሲኒማ ኢንዱስትሪ ላይ እየታየ ያለውን መነቃቃት ከግምት ውስጥ በማስገባትና የማህበረሰባችንን አፍቅሮተ ጥበብ በመገንዘብ መሆኑን አስታውቋል፡፡