Administrator

Administrator

ለ35 አመታት የዘለቀው የ1 ልጅ ብቻ ፖሊሲ፣
ከ400 ሚ. በላይ ወሊዶችን አስቀርቷ
    ቻይና ዜጎቿ አንድ ልጅ ብቻ እንዲወልዱ የጣለችውንና ከ35 አመታት በላይ የዘለቀውን አስገዳጅ የስነህዝብ ፖሊሲ በማሻሻል፣ ሁለት ልጆችን መውለድ እንደሚችሉ የሚፈቅድ አዲስ ህግ ልታወጣ መወሰኗን ከትናንት በስቲያ ማስታወቋን ቢቢሲ ዘገበ፡፡የአገሪቱን የወሊድ መጠን ለመቀነስና የህዝብ ቁጥር ዕድገቱን ለመግታት ታስቦ የተቀረጸው “የአንድ
ልጅ ብቻ” ውለዱ ብሄራዊ ማዕቀብ ተግባራዊ መደረግ ከጀመረበት እ.ኤ.አ ከ1979 ጀምሮ ባሉት
አመታት፣ በአገሪቱ ሊከሰቱ ይችሉ የነበሩ 400 ሚሊዮን ያህል ወሊዶች  መምከናቸውን ዘገባው
ጠቁሟል፡፡በአገሪቱ በእድሜ የገፉ ሰዎች ቁጥር እየተበራከተ መምጣቱ፣ ቻይና ተተኪ ትውልድ እንዳታጣ
ስጋት መፍጠሩን ተከትሎ፣ መንግስት የወሊድ ገደቡን እንዲያሻሽልና ዜጎች ተጨማሪ አንድ ልጅ
መውለድ እንደሚችሉ ለመፍቀድ እንዳነሳሳው ተገልጧል፡፡አንድ ልጅ ብቻ ውለዱ የሚለውን ህግ ጥሰው ሌላ ልጅ ጸንሰው የተገኙ ቻይናውያን ሴቶች፤ ጽንሱን እንዲያጨናግፉ ይገደዱ እንደነበር እንዲሁም ከስራቸው ይፈናቀሉና የተለያዩ ቅጣቶች ይጣሉባቸው እንደነበርም ዘገባው አስታውሷል፡፡

   ታዋቂው የኮምፒውተርና ስማርት ፎን አምራች ኩባንያ አፕል፣ ባለፉት 12 ወራት የሸጣቸው አይፎን ስልኮች ቁጥር ክብረ ወሰን ማስመዝገቡንና ይህን ተከትሎም በታሪኩ ከፍተኛ የሆነውን የ53.4 ቢሊዮን ዶላር ትርፍ እንዳገኘ ማስታወቁን ዘ ቴሌግራፍ ዘገበ፡፡አፕል ባለፉት 12 ወራት ያገኘው አጠቃላይ ገቢ 233.7 ቢሊዮን ዶላር መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፤ ይህም ኩባንያው በሳምንት ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ወይም በእያንዳንዷ ሰከንድ ከ1ሺህ 693 ዶላር በላይ ትርፍ ማግኘቱን ያሳያል ብሏል፡፡ኩባንያው እስካለፈው መስከረም ወር በነበሩት ሶስት ወራት ገቢው በ22 በመቶ በማደግ 51.5 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን ያስታወቀው አፕል ኩባንያ፤ በያዝነው ሩብ አመት ከ75.5 እስከ 77.5 ቢሊዮን ዶላር ሽያጭ አስመዘግባለሁ ብሎ
እንደሚጠብቅም ገልጿል፡፡ባለፉት ሶስት ወራት 48 ሚሊዮን አይፎን ስልኮችን እንደሸጠ የጠቆመው ኩባንያው፣ በተጠቀሰው ጊዜም ሽያጩ የ22 በመቶ እድገት ማሳየቱን አስታውቋል፡፡

     ለኔፓል ሴቶች መብቶች መከበር ለረጅም አመታት በጽናት መታገላቸው የሚነገርላቸው የኔፓል ዩኒፋይድ ማርክሲስት ሌኒኒስት ኮሙኒስት ፓርቲ ምክትል ሊቀ መንበር  ቢደሃያ ዴቪ ባንዳሪ፤ በአገሪቱ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘገበ፡፡የአገሪቱን ፕሬዚዳንት ለመምረጥ ባለፈው ረቡዕ በኔፓል ፓርላማ በተከናወነው የድምጽ አሰጣጥ ውጤት መሰረት፤ የኔፓል ኮሙኒስት ፓርቲ ምክትል ሊቀ መንበር የሆኑት ዴቪ ባንዳሪ 327 ድምጽ በማግኘት በፕሬዚዳንትነት ሲመረጡ፤ ተፎካካሪያቸው 214 ድምጽ ማግኘታቸውን ዘገባው ገልጿል፡፡
ዴቪ ባንዳሪ በአገሪቱ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዚዳንት ሆነው ቢመረጡም ሆኖ፣ በአገሪቱ ህግ መሰረት የመሪነቱን ሚና የሚጫወተው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመሆኑ ሴትዮዋ እንግዳ ከመቀበል ያለፈ ተጽዕኖ መፍጠር የሚችሉበት ስልጣን እንደማይኖራቸው ዘገባው አስረድቷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ካድጋ ፕራሳድ ኦሊ፤ በዚህ ወር መጀመሪያ የተቋቋመውን የአገሪቱ ጥምር መንግስት እንዲመሩ መመረጣቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ ባለፈው ወር የጸደቀው የኔፓል ህገ መንግስት አዲስ ፕሬዚዳንት መመረጥ እንዳለበት በደነገገው መሰረት፣ ረቡዕ ዕለት በተካሄደው ምርጫ የ54 አመቷ ቢደሃያ ዴቪ ባንዳሪ መመረጣቸውን ገልጿል፡፡
አዲሱ የኔፓል ህገ መንግስት ከፓርላማ አባላት አንድ ሶስተኛ ያህሉ ሴቶች መሆን እንዳለባቸው እንዲሁም ፕሬዚዳንት ወይም ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው የሚመረጡት የፓርላማ አባል፣ ሴት መሆን እንዳለባቸው የሚያስገድድ አንቀጽ እንዳካተተም ዘገባው አስታውሷል

የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር በድሬደዋ ከተማ ካሉ የግል የህክምና

ተቋማት ጋር በመተባበር ኤችአይቪ ከእናት ወደልጅ እንዳይተላለፍ ለሚያደርገው ፕሮግራም ቴክኒካል ድጋፍ ይሰጣል፡፡ ስራው ከሚሰራባቸው የግል የህክምና ተቋማት በተወሰኑት ተገኝተን በአሁኑ ወቅት ስላለው የእናቶች እና ሕጻናቱ በቫይረስ የመያዝ ወይንም ነጻ ስለመሆን ጉዳይ የሚደረገውን ክትትል ተመልክተናል፡፡ የህክምና ባለሙያዎቹ የሰጡትን ምስክርነት ለንባብ ብለናል፡፡
ስተር እመቤት እሸቴ በሙያዋ ሚድዋይፍ ነርስ ናት፡፡ በእናቶች እና ህፃናት የህክምና ክፍል ውስጥ
ሀላፊ ሆና እየሰራች ነው፡፡ የሚከተለውን ብላለች፡፡ “...ሚድዋይፍ እንደመሆኔ አብዛኛው ስራዬ በማዋለዱ ላይ የሚያተኩር ቢሆንም ግን የእርግዝና ክትትል፣ የእናቶች እና ህፃናት አጠቃላይ ጤና እና ክትባት እነዚህን የመሳሰሉት ላይም እሰራለሁ፡፡ ከሁለት አመት ወዲህ የትኛዋም እናት ኤችአይቪ ቫይረስ በደሟ ከተገኘ መድሀኒቱን ወዲያውኑ እንድትጀምር እየሰራን ነው ያለነው፡፡ ስለዚህ ማንም እናት ወደ ተቋማችን ከመጣች በማዋለጃ ክፍልም ይሁን በእናቶች እና ህፃናት ክፍል እና በክትባትም ግዜ የሚመጡ እናቶች ከዚህ በፊት ሌላ ቦታ ተመረመሩም አልተመረመሩም እኛ ጋር የምክር አገልግሎት ተሰጥቷቸው እንዲመረመሩ ይደረጋል፡፡ ከተመረመሩ በኋላ ውጤቱ ይነገራቸዋል ውጤቱ ታይቶ ደግሞ ማድረግ ያለብን ነገር ካለ ቀጣዩን እርምጃ እንወስዳለን፡፡ ቀደም ሲል ሁሉም እናቶች ሊባል በሚችል ደረጃ የኤችአይቪ
ምርመራ ለማድረግ እሺ አይሉም ነበር፡፡ አሁን ግን መቶ በመቶ ማለት በሚያስችል ሁኔታ ለመመርመር ፈቃደኛ ናቸው፡፡ በወር ውስጥ 20 /እናቶችን ብናዋልድ ሀያዎቹም እናቶች ምርመራ ያደርጋሉ፡፡ ምርመራ በግዳጅ የሚደረግ ሳይሆን በሚገባ ግንዛቤ እንዲያገኙ አድርገን ጥቅሙ ገብቷቸው እና አምነውበት የሚደረግ ነው፡፡ አንዲት እናት የኤችአይቪ ምርመራ ማድረጓ የሚጠቅመው እራሷን ብቻ ሳይሆን ለልጇም እንደሆነ አብዛኛው የህብረተሰቡ ክፍል ተረድቶታል፡፡ ስለዚህ ምርመራውን የማታደርግ እናት የለችም ከብዛት አንድ ሊያጋጥም ይችላል እንጂ ሁሉም እናት ይመረመራል፡፡ የእርግዝና ክትትል ለማድረግ ወደ እኛ ሲመጡ እና ምርመራ ስናደርግላቸው ቫይረሱ በደማቸው የምናገኝው እናቶች ቁጥር በወር ውስጥ ሁለት ወይም ከዛ በላይ ነበሩ፡፡ አሁን ግን ያን አይነት ቁጥር የለንም፡፡ እና በጣም ትልቅ የሚባል መሻሻል ታይቷል፡፡” በድሬደዋ የግል የህክምና ተቋም ካገኘናቸው የህክምና ባለሙያዎች መካከል ሲስተር ቤተል አሸናፊ አንዱዋ ነች፡፡ ሲስተር ቤተል አሸናፊ የማዋለጃ ክፍል ኃላፊ ሆና ነው የምትሰራው፡፡ ስለአገልግሎቱ የሚከተለውን ገልጻለች፡፡                            
     “...ለእርግዝና ክትትልም ሆነ ለወሊድ አገልግሎት በወር በግምት 30-35 ክትትል የሚያደርጉ እናቶች ይኖሩናል፡፡ የሚወልዱትም በየወሩ ቢለያየም ግን በአማካይ ከ20-25 ይሆናሉ፡፡ ክትትል የሚያደርጉት ሁሉ እዚህ አይወልዱም፡፡ አንዳንዴ እዚህ ከአቅማችን በላይ የሆነ ነገር ሲፈጠር ወይም በሌላ ምክንያት በብዛት ወደ ድል ጮራ ሆስታፒታል እንልካቸዋለን፡፡ ከሌላ ቦታ ለመውለድ ብቻ እዚህ የሚመጡም አሉ፡፡ ምርመራውን እዚህ እኛ ጋር አድርገው ቫይረሱ በደማቸው ከተገኘ ወዲያው መድሀኒቱን እንድትጀምር እና አስፈላጊው ክትትል ሁሉ እንዲደረግላት እናደርጋለን፡፡ ልጁ ከተወለደ በኋላም አመት እስኪያልፈው ድረስ ምርመራም መድሀኒትም በበቂ ሁኔታ እንዲያገኝ እናደርጋለን፡፡ በቫይረሱ የሚያዙ አዲስ እናቶችን በሚመለከት ብዙም አይደለም እንጂ ይኖራሉ፡፡ አሁን ባለፈው ሀምሌ ላይ አንዲት እናት አግኝተናል፡፡ እኔ ይህንን ስራ ስሰራ ወደ ስድስት አመት ሆኖኛል፡፡ ከሁለት አመት በፊት የነበረውን እና አሁን ያለንበት ሁኔታ ሳነጻጽረው አሁን በጣም ብዙ ነገር ተቀያይሯል፡፡ ለምሳሌ አሁን ከቫይረሱ ነፃ የሆነ ልጅ እያዋለድን ነው፡፡ በፊት ይህ አይነቱ ነገር አልነበረም፡፡ አሁን ግን ሁሉም ሊባል በሚችል ደረጃ ነፃ ሆነው ነው
የሚወለዱት፡፡ ህብረተሰቡ በአሁኑ ሰአት ያለው ግንዛቤም በጣም ስለተቀየረ በዚህ ላይ ብዙ መሻሻሎች አሉ፡፡ አሁን ትንሽ ችግር አለ ብለን የምንለው እርጉዝ ሴቶች ለምርመራ ሲመጡ ባሎቻቸው አብረው ለመመርመር ፈቃደኛ አለመሆናቸው ነው፡፡ በእርግጥ አንዳንዶች ፈቃደኛ ቢሆኑም ብዙዎች ግን በስራ እና በተለያየ ምክንያት ሽፋን እየተሰጣቸው ለምርመራ እሺ ብለው አይመጡም፡፡ በእኛ በኩል ግን አስቀድሞውኑም እሺ ያሉትን ምርመራ እንሰራላቸዋለን፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ሚስቶቻቸው ሲወልዱ ስለሚመጡ በዚያን ጊዜ ምርመራ እንዲያደርግ እናግባባለን፡፡ ምክንያቱም እሱም ተመርምሮ እራሱን ማወቁ በቀጣይ ለሚኖራቸው ህይወት በጣም ጥሩ ስለሚሆን ነው፡፡ በጠቅላላው ግን በአሁኑ ሰአት ከቫይረሱ ነፃ የሆኑ ብዙ ህፃናትን እያገኘን ነው ለማለት እንችላለን፡፡    ዶ/ር ሰናይት ገ/የሱስ በኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር የኤችአይቪ ቫይረስ ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍ ለማድረግ በሚሰራው ፕሮጀክት ሙያዊ ድጋፍ የሚሰጡ ሲሆኑ ይህንን ድጋፍ ከሚያደርጉ ቡድን አባላትም ለተወሰኑት አስተባባሪ ናቸው፡፡ በድሬደዋ ከተማ ቡድኑ እየተዘዋወረ ስራውን ሲከታተል ያለውን ሁኔታ እንዲገልጹ የዚህ አምድ አዘጋጅ አነጋግራቸዋለች፡፡ “...ወደ ምስራቁ የሀገራችን ክፍል የመጣንበት ምክንያት ከኢሶግ ጋር በትብብር የሚሰሩትን የግል የህክምና ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ እና መረጃ አሰባሰብን ለመመልት ነው፡፡  ፕግራሙ በትክክለኛው መንገድ እየተሰራበት ነው ወይ?፣ አንዲት እናት ስትመጣ የኤችአይቪ ምርመራ ይደረግላታል ወይ? ምርመራውን አድርጋ ቫይረሱ በደሟ ውስጥ ከተገኘም መድሀኒቱን ወዲያው
እንድትጀምር ይደረጋል ወይ?፣ ከቫይረሱ ነፃ ከሆነችም ይህንን ውጤት ጠብቃ እንድትቆይ የሚያደርግ የምክር አገልግሎት ታገኛለች ወይ? እና ባጠቃላይ ፕሮግራሙ በትክክል እየተሰራበት መሆኑን እናረጋግጣለን፡፡ በተጨማሪም ይህንን በተመለከተ ስልጠና ያልወሰዱ ባለሙያዎች ካሉም እዛው ቦታ ላይ የተወሰኑ ነገሮችን እንዲያገኙ እናደርጋለን ማለት ነው፡፡ በጅግጅጋ እና በሐረርም ቆይታ ያደረግን ሲሆን በአብዛኛው አሰራሩ በቆንጆ ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ለምሳሌ ሀረር ላይ ያሉ ሁለት ሆስፒታሎች ፕሮግራሙን የእራሳቸው አድርገው በጥሩ ሁኔታ እየሰሩ ነው፡፡ ብዙ ቦታ ላይ ችግር እየፈጠረ ያለው ይህ ፕሮግራም የእኛ ስራ አይደለም ተቀጥላ ፕሮግራም ነው የሚለው አስተሳሰብ ነው፡፡ ነገርግን አሁን እዚህ ድሬዳዋም ሀረርም ያየነው ነገር በጣም ጥሩ የሚባል ነው፡፡ በርግጥ ጅግጅጋ ላይ ከቫይረሱ ነፃ የሆኑ ሰዎች ብዙ አላየንም ግን ሁሉም እናቶች ምርመራውን ያደርጋሉ፡ ይሄም በጣም ቆንጆ ነገር ነው፡፡ አንዲት እናት ለመውለድ ወደ ህክምና ተቋም ስትመጣ ማዋለድ ግዴታ እንደሆነ ሁሉ ምርመራ ማድረግም የዛኑ ያህል ግዴታ መሆኑን የጤና ባለሙያዎች መረዳት እና ፕግራሙን እንደ አንድ የእራሳቸው ፕሮግራም ይዘውት መስራት ይኖርባቸዋል፡፡ እዚህም የተመለከትነው ይሄንኑ ነው፡፡

                                  ***
በስተመጨረሻም በድሬዳዋ ጤና ቢሮ ውስጥ እናቶች እና ሕጻናት ጤና ላይ አስተባባሪ ሆነው
የሚሰሩትን ሲ/ር መሰሉ አጥናፌ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡        “...የኤችአይቪ ቫይረስ ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍ የሚያስችለው ህክምና እዚህ የተጀመረው በፈረንጆቹ 2001 ነበር፡፡ በድሬዳዋ ከተማ ከመንግስት የህክምና ተቋማት ውጪ በእናቶች እና ህፃናት  ጤና ላይ የሚሰሩ የግል የሕክምና ተቋማትም አሉ፡፡ በፊት ላይ መንግስታዊ ያልሆኑ የህክምና ተቋማት የእራሳቸው አሰራር ነበራቸው፡፡ አሁን ግን በእናቶች እና ህፃናት ጤና ላይ የሚሰሩት ተቋማት ከእኛ ጋር በትብብር ነው የሚሰሩት፡፡ ስለዚህ ድሬዳዋ ላይ የመንግስትም ሆነ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በአንድላይ ነው የምንሰራው፡፡ የመንግስትን ብቻ ተይዞ የሚኬድ ከሆነ ውጤትም አይኖረውም፡፡ ምክንያቱም በአብዛኛው በተለይም ደግሞ በግል የህክምና ተቋማት የሚገለገሉ እናቶች ቁጥር በጣም ከፍተኛ መሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ ሰዎች አቅሙም ፍላጎቱም
ሲኖራቸው ወደ ግል ተቋማት ይሄዳሉ በመንግስት ተቋማትም ይጠቀማሉ፡፡ ያለን ግንኙነት ምንይመስላል የሚለውን ስንመለከት በየጊዜው ኤችአይቪን ወይም የቤተሰብ ምጣኔን የተመለከተ ስልጠና ሲኖር የመንግስት እና ህብረተሰቡን በአግባቡ እያገለገሉ የሚገኙ የግል ተቋማትን ለምሳሌ እንደ ማሪያምወርቅ፣ አርት የመሳሰሉት በአጠቃላይ በግል የሚገኙትን ባለሙያዎች አንድ ላይ አድርገን እናሰለጥናለን፡፡ ስለዚህ እኛ ስናሰለጥን የመንግስት ብቻ ብለን ለይተን አናሰለጥንም ለሱፐርቪዥን ስንወጣም በሁለቱም በኩል ያለውን ነገር እናያለን፡፡ እነሱ ሲመጡም ከአጋሮቻችን አንድ ላይ ሆነን ሁሉም ተቋማት ጋር ያለውን ሁኔታ እናያለን ስለዚህ አሁን ቆንጆ ሁኔታ ነው ያለው በግል ተቋማት ላይ እራሱ በሚገርም ሁኔታ ኤችአይቪም እንበለው የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎትም እንበለው ብዙ ግል ገበያ ያሚያስገባ ጉዳይ ቢሆንም እንኩዋን እነርሱ ግን ነፃ አገልግሎት ነው የሚሰጡት፡፡ የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎትም  የኤችአይቪ መድሀኒቶችም በነፃ ነው የሚሰጡት ከእኛ በላይ ትኩረት ሰጥተው ነው የሚሰሩት፡፡ ስልጠና ላይ የሚሰጡ ግብአቶችንም እንዴት ያገኛሉ ቢባል በድሬዳዋ ውስጥ 17 የህክምና ተቋማት ነው ያሉን ፡፡2 የመንግስት
ሆስፒታል፣ 15 ጤና ጣቢያዎች አሉን የእኛ አንዱ ሳቢያን የሚባል ጤና ጣቢያ የመጀመሪያ ደረጃ
ሆስፒታል ሆኗል፡፡ ስለዚህ ምንድነው የሚሆነው ምርመራ የሚያደርጉበት ግብአት ወይም
መድሀኒቶች ሲፈልጉ በስራቸው ያሉ ጤና ጣቢያዎች ከእነሱ ጋር ነው የሚወስዱት፡፡ ሪፖርታቸውም በእነሱ በኩል ነው የሚደርሰን፡፡ ስለዚህ እነዚህ ተቋማት ሃላፊነት አለባቸው ማለት
ነው፡፡ እያንዳንዱ የመንግስት የሕክምና ተቋማት በአካባቢያቸው ከሚገኙ የግል ተቋማት ጋር አንድ
ላይ ሆነው ነው የሚሰሩት ማለት ነው፡፡ በአሁኑ ሰአት የሚያስፈልገው ግብአት ሁሉ በአግባቡ
እየቀረበ ነው ያለው፡፡  በዚህ ስራ ላይ ለድሬዳዋ ጤና ቢሮ ድጋፍ እየሰጡን ያሉ አካላት እንደ ESOG እና CDC ያሉ ድርጅቶች አሉ እነሱን ስለሚሰጡን ድጋፍ ሁሉ ማመስገን እፈልጋለሁ፡፡ ከፌደራል ጤና ጥበቃ
ሚኒስቴር ጋርም በጣም የጠበቀ ግንኙነት አለን፡፡ እነሱም በስራ ላይ ክፍተቶች እንዳይፈጠሩ
አስፈላጊውን ግብአት በማቅረብ ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ነው፡፡ ስለዚህ አገልግሎቱ ዛሬ ያለበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የብዙ አካላትን እርብርብ ጠይቋል፡፡ ሁሉም ምስጋና ይገባቸዋል፡፡”  ስለዚህ በፊት ላይ የነበረው የኤችአይቪ የምክር አገልግሎት አንድ ሰው ብቻ ይዘሽ ከሁለታችን ውጪ ይህን የሚያውቅ የለም እያልሽ ማማከር ነው፡፡ ይህ አይነቱ የምክር አሰጣጥ በአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ላይ ከፍተኛ ጭንቀት ይፈጥራል መድሀኒቱም ሊቨራፒን የሚባል በምጥ ሰአት ብቻ የሚሰጥ ነበር፡፡ ቀስ እያለ ግን የምክር አገልግሎት አሰጣጡ መጀመሪያ ተጠቃሚዎችን በቡድን አድርጎ ስለ ኤች አይቪ ማስተማር ሆነ፡፡ ከዛም ለእርግዝና ክትትል የምትመጣ እናት ደግሞ ሌሎች ምርመራዎች እንደሚደረግላት ሁሉ የኤች አይቪ ምርመራ ማድረግ እንዳለባት እና አገልግሎቱም በነፃ የሚሰጥ እንደሆነ በሚገባ ይነገራታል፡፡ በዚህ መንገድ ተጠቃሚዎችን ሳታጨናንቂ በፈቃደኝነት እንዲመረመሩ ታደርጊያለሽ ማለት ነው፡፡ አሁን እንደበፊቱ አይደለም በፊት በቀን

ሁለት ፖዘቲቭ ሰዎች ይገኙ ነበር አሁን ግን ይህን አይነት ቁጥር የምታገኚው በሳምንት ውስጥ

ሊሆን ይችላል፡፡ ስለዚህ አሁን ፖዘቲቭ ለሆነች እናት ነው ጊዜ የምንሰጠው በፊት ላይ ግን

ፖዘቲቭም ሆነች ኔጌቲቭ ጊዜ ትወስጃለሽ ብዙ ተጠቃሚም ካውንስል አታደርጊም እንደገና ደግሞ

የምክር አሰጣጡ በተጠቃሚዎች ላይ ጭንቀት የሚፈጥር አይነት ነበር፡፡ መድሀኒቱም ደግሞ

እየተሻሻለ መጣ በፊት አንዲት እርጉዝ ሴት 28 ሳምንት ሲሆናት ነበር መድሀኒቱ የሚሰጣት አሁን

ግን Test and treat option B የሚባል መጥቷል ይህ እንግዲህ አንዲት እናት የኤችአይቪ

ምርመራ አድርጋ ፖዘቲቭ ከሆነች ወዲያው መድሀኒት እንድትጀምር የምናደርግበት መንገድ ነው፡፡
ቅድም እንዳልኩት የምክር አገልግሎት አሰጣጡም ተሸሽሏል እናቲቱን ከትዳር አጋሯ ጋር በአንድ ላይ አድርጎ መስጠት ያቻላል ብቻዋንም ብትመጣ አገልግሎቱን ታገኛለች፡፡ ስለዚህ አሁን
በሀገራችን እዚህ ደረጃ ላይ ደርሰናል በፊት ግን ምርመራውን ለማድረግ ብቻ ከድሬዳዋ አዲስ አበባ
ድረስ እንልክ ነበር፡፡
መ፡ አሁን ቆኝጆ ሁኔታ ነውያለው እንደ በፊቱ እድሎ እና መገለል የለም፡፡ መሰረት የጣለ ትልቅ
የማስተዋወቅ ስራ ነው የተሰራው፡፡ ህብረተሰቡም ግንዛቤ አግኝቷል እሱም ተጨማሪ ሆኖ ኤችአይቪ ፖዘቲቭ የሆኑ እናቶች ደግሞ በየህክምና ተቋማቱ እራሳቸውን አውቀው አስፈላጊውን ትምህርት ወስደው መድሀኒቱን ይጀምራሉ፡፡ ይህንን የሚያስተባብሩ በየተቋማቱ አራት አራት ባለሙያዎች ይኖራሉ፡፡ ስለዚህ ትልቅ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ ተሰርቷል በህብረተሰቡም ዘንድ ግንዛቤ መኖሩ እንዲጠነቀቁ አድጓል፡፡ ህብረተሰቡ ምርመራ አድርጎ እራሱን ያውቃል ከተመረመሩም በኋላ ደግሞ   የሚሰጠውን አገልግሎት እዛው ስለሚያገኙ አልፎ ተርፎ የቤተሰባቸውንም ጤንነት ይጠብቃሉ፡፡ እና የቫይረሱ ስርጭት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መጥቷል አዳዲስ የሚያዙ ሰዎችም ቁጥር ከበፊቱ በጣም ቀንሷል፡፡ ወደፊት ከኤችአይቪ ቫይረስ ነፃ የሆነ ትውልድ በማፍራት እረገድ ደግሞ አሁን ቫይረሱ በደማቸው ለሚገኝ እርጉዝ የሚሰጠው መድሀኒት ትልቅ አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡ እና ባጠቃላይ ይህ ቫይረሱ ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍ
የሚሰጠው የህክምና አገልግሎት እኔ በግሌ ምጣም የረካሁበት ነው፡፡ በፊት ሆስፒታል በምሰራበት ወቅት ኤችአይቪ ፖዘቲቭ ሆነው የሚወለዱ ህፃናትን ቁጥር የማየት እድሉ ነበረኝ እና አሁን ላይ ሆኜ ሳየው ከቫይረሱ ነፃ ሆኖ የመወለድ እድሉ በጣም ከፍተኛ ነው፡፡ እንግዲህ አስቢው እነዛ ሁሉ በቫይረሱ ቢያዙ ነገ ሀገርን የሚረከብ ትውልድ አይኖረንም ማለት
ነው፡፡ ከአራስነት ጊዜ ጀምሮ እስከ እድሜ ልክ መድሀኒቱን መውሰድ ማለትም በጣም ከባድ ነገር
ነው፡፡ ስለዚህ አሁን እየተሰጠ ያለው ህክምና ይህንን ሁሉ ስጋት በእጅጉ የቀነሰ ነው እኛም በጣም በጥሩ ሁኔታ እየሰራን ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ ጥ፡ በመጨረሻ በዚህ ላይ የምትጨምሪው ነገር ካለ እድሉን ልስጥሽ
መ፡ በመጀመሪያ እናንተም እዚህ ድረስ መጥታችው እየተሰራ ያለውን ስራ መመልከታችሁ በጣም ጥሩ ነገር ነው፡፡ ህብረተሰቡ በቂ ግንዛቤ ኖሮት እራሱን እንዲጠብቅ አዲስ የሚያዙ ሰዎችም ቁጥር እንዲቀንስ የማድረጉ ስራ ለህክምና ባለሙያዎች ብቻ የተተወ ሳይሆን ሌሎችም አካላት ተሳትፎ ሊያደርጉበት የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ የመገናኛ ብዙሃን ድርሻ በጣም ትልቅ የሚባል ነው፡፡ እኛ መርዳት ወይም ማሳወቅ የምንችለው ወደ ተቋማችን የሚመጡትን ብቻ ነው፡፡ ነገርግን የመገናኛ ብዙን ተደራሽነታቸው በጣም ሰፊ በመሆኑ ብዙውን የህብረተሰብ ክፍል ማስተማር እና ማሳወቅ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ እዚህ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ቢሰራበት ጥሩ ነው እላለሁ፡፡
   

ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ሹም ባለሥልጣን እሥር ቤት ይገባል፡፡
እንደገባ ወደተመደበለት ክፍል ሲደርስ፣ እሥረኛው ሁሉ በሱ ላይ መጠቋቆም   ጀመረ፡፡
አንደኛው - እንዴ ይሄንን‘ኮ አውቀዋለሁ፤ የናጠጠ ሀብታም ነው!
ሁለተኛው - እኔ ደግሞ አንቱ የተባለ ሹም መሆኑን ነው የማውቀው!
ሶስተኛው - ጐበዝ አትጃጃሉ! የናጠጠ ሀብታምም፣ አንቱ የተባለ  ሹምም  እንዳይሆን ምን ያግደዋል? እንዲያውም በዛሬ ጊዜ የሚበዙት    ሹሞች ሀብታሞች   ናቸው፡፡
አራተኛው - ቀስ እያለች ቢሮክራቲክ ካፒታሊዝም መጣች በለኛ!
አንደኛው - እንዴታ!
ስድስተኛው - እኔ እምለው ወንድሞቼ፣ ከዚህ ሁሉ ፍልስፍና ለምን ራሱን   አንጠይቀውም?
ሁሉም - ውነቱን ነው፣ ውነቱን ነው!
አንደኛው - ጋሼ
እንግዳው እሥረኛ - አቤት የኔ ልጅ
አንደኛው - ምን አድርገዋል ብለው ነው ወደዚህ ያመጡዎት?
እንግዳው እሥረኛ - ኮርቻ ሰርቀሃል ነው የሚሉኝ
አንደኛው - ለኮርቻ? እዚህ ከባድ እሥር ቤት ለኮርቻ ብለው አመጡዎት?
እንግዳው እሥረኛ - ምን እባክህ አንድ የማትረባ በቅሎ ከሥሩ አለች!
***
በሀገራችን ሌባው በጣም በዝቷል፡፡ ሁሉም ስለኮርቻው እንጂ ስለ በቅሎዋ አያወራም! የሚታሠረው እንጂ ስለ በቅሎዋ አያወራም! የሚታሠረው በርካታ የሀገር ገንዘብ ሰርቆ ይሁን እንጂ ምንም እንዳልነካ አድርጐ ደረቱን የሚነፋ መዓት ነው፡፡ የሀብት ዘረፋው ሳያንስ በሥልጣን የሚባልገው ሥፍር ቁጥር የለውም፡፡ ሥልጣን ወደ ኃላፊነት ሳይሆን ወደ ሀብት፣ ወደ መሬት መከፋፈል፣ ወደ ዘመድ መጠቃቀሚያ፣ ወደ ፍትሕ ማዛቢያ፣ ወደ ምዝበራ መረብ ማስፋፊያ፣ ወደ ህገ ወጥ ፎቅ መገንቢያ ካመራ፤ ወደ ልማት ሳይሆን ወደ ጥፋት እየሄድን ነው ማለት ነው፡፡ ውሎ አድሮ ሁሉም የበታች እንደ ቁንጩዎቹ የድርሻዬን ልውሰድ ማለቱ አይቀሬ ነው፡፡
ከባለሥልጣን የሚመሳጠረው አቀባባይም እኔም የድርሻዬን ማለቱም አይቀሬ ነው፡፡ በኮሚሽን የሚተዳደረው ሰው፤ ከዋናዎቹ ገዢና ሻጮች የተሻለ የሚያገኝበትን መንገድ ስለሚያሰላ ህገ-ወጥ ንግዱ እንዲፋፋም፣ የተለያዩ ወገኖች ገብተውበት የዘረፋ መረቡ እንዲሰፋ፣ ማድረጉን ይያያዘዋል፡፡ አንዱ ህገ ወጥ ተብሎ ሲታሰር ግን መረቡ አይነካም፡፡ ሀገራችን እስከወሲብ ድረስ የተወሳሰበ ሙስና እያስተናገደች መሆኑ ይነገራል፡፡
ይህንኑ ሙስና ምሁሩም መሀይሙም፣ ህገ አስፈፃሚውም አላዋቂውም አድናቆቱን እየገለፀና ወሬውን በመንዛት እየተባበረ ሀገራችን ወደ አሳዛኝ ፈተና እየገባች ነው!
የብዝበዛው መረብ ክሩ እየበዛ ሲሄድ ፖለቲካው ላይ ተፅዕኖ ማሳደሩ አይቀሬ ነው! ምነው ቢሉ ሌብነቱን እንዳይከላከሉ፣ በእጅ በአፍ የሚባሉ ፖለቲከኞች ይኖራሉና! ከንቲባዎች፣ የወረዳ ሊቃነ መናብርት፣ የማህበራት መሪዎች፣ ህግ አስፈፃሚዎች፣ ትላልቅ የክልል ሹማምንት ከትንሽ እስከ ትልቅ የቅሌት መዝገብ ላይ ሠፍረው ወደ ወህኒ ሲጋዙ፣ ወደ ዘብጥያ ሲወርዱ አይተናል፡፡
ገናም እናያለን፡፡ የብዝበዛው መረብ እስካልተበጣጠሰ ድረስ! በመሬት ስፋት የማይለካ፣ በፎቅ ርዝመት የማይወሰን፣ በቀረጥ ነፃ ብቻ የማይቆም የህሊና መቆሸሽና ተዛማች የሌብነት በሽታ እንደ ዘር - ደዌ መናኘቱ፤ የዲሞክራሲ፣ የመልካም አስተዳደር፣ የፍትሕ - ርትዕ፣ የዕድገት ሀገር ትሆናለች የምትባለውን ሀገራችንን፤ ህልውናዋን ጭምር የሚፈታተኑ ከተላላኪ እስከ መመሪያ አስፈፃሚ የሌብነት ባለድርሻ አካላት የሆኑባት የዘረፋ መናኸሪያ እንዳትሆን፣ ከባድ እንቅስቃሴ ትሻለች፡፡
ራሱ እየሰረቀ ሌላውን ማማት ፋሺን እየሆነ ነው፡፡ እራሱ እየገረፈ እንደ ጅራፉ የሚጮኸው እየባሰ ነው፡፡
ከሥጋ ቤት እስከ ኦፊስ ባር ሲመካከርና ሲመርብ (Weaving corruptive networks) የሚያመሸው ቁጥሩ ቀላል አይደለም፡፡
ሌብነት “ቢዝነስ” የሚል የማዕረግ ስም ከወጣላት በጣም ቆየ! አንዴ በሥልጣኑ፣ አንዴ በንግድ ውስጥ እጃቸውን እየነከሩ ያሉ በርካታ ናቸው - “የሌሊት ወፍ ገብሪ- አይጥ ነኝ፤ አይጥ ገብሪ የሌሊት ወፍ ነኝ” ማለት ይሄው ነው!   

Saturday, 24 October 2015 10:13

“ዝክረ አርቲስት አልጋነሽ

አንጋፋዋ የጥበብ ባለሙያ አልጋነሽ ታሪኩ ለ50 ዓመታት የሰራቻቸው ዘመን ተሻጋሪ ስራዎቿ የተዘከሩበት የኪነጥበብ ፕሮግራም ከትላንት በስቲያ ጠዋት በኢትዮጵያ ብሔራዊ የባህል ማዕከል ተከናወነ፡፡
 በእለቱ የአርቲስቷ ስራዎች፣ የጥበብ አጀማመሯ፣ በኪነጥበቡ ያሳለፈቻቸው ፈተናዎችና ስኬቶቿ የተወሱ ሲሆን የተለያዩ የኪነ - ጥበብ ዝግጅቶችም ቀርበዋል፡፡
 በዚህ ፕሮግራም  ላይ የአርቲስቷ የሙያ ጓደኞች፣ ወዳጅ ዘመዶች፣ የኪነጥበብ አፍቃሪያን፣ የባህልና ቱሪዝም ተወካዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመው ነበር፡፡  

• ተልዕኮዬ የጃንሆይን ትምህርት ለዓለም ማሰራጨት ነው
• Ethiopia is calling - የሚለውን እንዴት አቀነቀነው?

    ጃማይካውያን ለኢትዮጵያና ለቀድሞው ንጉስ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ያላቸው ከአምልኮ ያልተናነሰ ፍቅርና ክብር በእጅጉ የሚያስደንቅ ነው፡፡
የሬጌ አቀንቃኙ ሲዲኒ ዊን ሳልማንም፤ በኢትዮጵያና በህዝቦቿ እንዲሁም በጃንሆይ ፍቅር በእጅጉ መማረኩን ይገልፃል፡፡ ተልዕኮዬ የአባባ ጃንሆይን
መልእክት ለዓለም ማሰራጨት ነው ይላል፡፡ ከፍቅሩ ብዛት እምነቱን ሳይቀር ወደ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ቀይሯል፡፡ በቋሚነት የሚኖረውም እንደ
ሁለተኛዋ ቅድስት አገር ኢየሩሳሌም፣ በሚቆጥራት ኢትዮጵያ ውስጥ ነው፡፡ በዚያ ላይ ኢትዮጵያዊት ሚስት አግብቶ ልጆች አፍርቷል፡፡
እ.ኤ.አ በ2001 የኒውዮርክ መንትያ ህንፃዎች በአልቃይዳ በተመቱ ጊዜ “Babilon is falling Ethiopia is calling” (ባቢሎን እየፈረሰች ነው፤
ኢትዮጵያ እየተጣራች ነው እንደማለት) የሚል ዘፈን ማቀንቀኑን ይናገራል፡፡ የዛሬ 14 ዓመት ገደማ ወደ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲመጣ፣ የእረፍት
ስሜት እንደተሰማው ይገልፃል፡፡ እንዴት? ምን ዓይነት እረፍት? ለመሆኑ የዚህ ሁሉ ፍቅርና ቁርኝት ምስጢሩ ምንድነው? አርቲስት ሲዲኒ ሳልማን
ለአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ፤ ሁሉንም በስፋት አውግቷታል፡፡ በ20 ዓመቱ ከጃማይካ ወደ አሜሪካ የተሻገረበትን ምክንያት በመግለፅ
የሚጀምረው አቀንቃኙ፤ ስለህይወቱና ሙያው በተለይም አዲስ ስለሚያወጣው የሙዚቃ አልበሙ ይነግረናል፡፡



ለምን ነበር ወደ አሜሪካ የሄድከው?
በዚያን ጊዜ እናትና አባቴ የተሻለ ህይወት ፍለጋ ወደ አሜሪካ በመሻገራቸው ነው እኔም  ከቤተሰቤ ጋር የሄድኩት፡፡ እዚያ እንደሄድኩ የኮሌጅ ትምህርት ጀመርኩኝ፡፡ በብሩክሊን ከተማ ብሩክሊን ኮሌጅ ውስጥ ቢዝነስ አድሚንስትሬሽን አጠናሁ፡፡ ድምፅና ጊታር ያጠናሁት ግን  በሞንሮው ኮሌጅና ኢሮኖቲካስ ኮሌጅ በመሳሰሉት ውስጥ ነው፡፡…
በስንት ዓመትህ ነው ማንጐራጐር የጀመርከው?
የ12 አመት ልጅ ሆኜ ጃማይካ ውስጥ በትምህርት ቤት የተሰጥኦ ውድድር ላይ ተሳተፍኩ፡፡ በማመልክበት ቤተ-ክርስቲያንም እዘምር ነበር፡፡ በዚያን ሰዓት ድምፅህ አሪፍ ነው የሚሉ አስተያየቶች ይሰጡኝ ነበር፡፡ በፕሮፌሽናል ደረጃ መዝፈን የጀመርኩት ግን ኒውዮርክ ውስጥ ነው፡፡ ከኮሌጅ ምርቃቴ በኋላ ማለት ነው፡፡ ከዚያም እምነቴን ወደ ኦርቶዶክስ ቀየርኩኝ፡፡ ሃይማኖቴን ኦርቶዶክስ ካደረግሁ በኋላ በሙሉ አቅሜና ችሎታዬ ስለ ኢትዮጵያና ፍትህ ስለተነፈጉ ድሆች ለመዝፈን ወሰንኩና መዝፈን ጀመርኩኝ፡፡
እምነትህን ለምንድነው ወደ ኦርቶዶክስ ሃየማኖት የቀየርከው?
በአባባ ጃንሆይ ምክንያት ስለ ኢትዮጵያ እንዲሁም ኢትዮጵያዊያን ለሰው ልጆች ስላላቸው ፍቅር በልጅነቴም እሰማ ነበር፡፡ ወደ አሜሪካ ከሄድኩ በኋላ ከኢትዮጵያዊያን ጋር የመገናኘት እድል ስለገጠመኝ የበለጠ ሰው ወዳድነታቸውን፣ ለሃይማኖታቸው ያላቸውን አክብሮት በተግባር ለማየት ቻልኩ፡፡ እንደምታውቂው ምዕራባዊያን ሁሌ ወከባ፣ ሁሌ ለአለማዊ ነገር ግርግር ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ኢትዮጵያ ለመኖርና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ለመሆን በቃሁ፡፡ የኢትዮጵያ ባህልና እምነት የህይወት ልምዴ አንዱ አካል እንዲሆን መረጥኩ፡፡
“Babilon is falling Ethiopia is calling” የሚለውን ዘፈን ያቀነቀንከው ለዚህ ነው?
አዎ፡፡ ግን ይሄ አልበም የተሰራው በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2001 ዓ.ም ኒውዮርክ ውስጥ የሚገኙት ሁለት መንትያ የቢዝነስ ህንፃዎች በአልቃይዳ በተመቱ ወቅት ነው፡፡ የሚገርምሽ የኔም የስራ ቦታ እነዚያ ህንፃዎች ውስጥ ነበር፡፡ በቃ እንደዛ ህንፃዎቹ ተመትተው ሲወድቁ “Babilon is falling Ethiopia is calling” የሚለው ዘፈን መጣልኝ፡፡ ብዙ ኢትዮጵያኖች ይህን ዘፈን ያውቁታል፡፡ ከዚያም አልበሙ እንደወጣ (ከ14 አመት በፊት ማለት ነው) ሰሞን ወደ ኢትዮጵያ መጣሁ፡፡
ወደ ኢትዮጵያ ስትመጣ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰማህ ስሜት ምን ነበር?
እዚህ እንደመጣሁ የተሰማኝ እረፍት ነው፡፡ ምንም እንኳን ለአገሪቱ አዲስ ብሆንም እረፍት ተሰምቶኛል፡፡ ምክንያቱም በኖርኩበት ኒውዮርክ ሁሌም ወከባ ነው፤ ያለሽን 95 በመቶ ጊዜ የምታሳልፊው በስራ ነው፡፡ ለመኖር… ለቤት ኪራይ… ለሶሻል ሴኪዩሪቲ… ለሁሉም መስራት አለብሽ፡፡ ይህን ሁሉ ለማሟላት ገንዘብ ያስፈልግሻል፡፡ አሜሪካ ውስጥ አንድ ቀን እንኳን ስራሽን አጣሽ ማለት ውው….ው በቃ ህይወትሽ ተመሳቀለ ማለት ነው፡፡ እኔም በዚህ ህይወት ውስጥ ስለኖርኩ ስልችት ብሎኝ ነበር፡፡ እዚህ ስመጣ አዲስ ህይወት… እረፍት… ልክ እንደ ኢትዮጵያዊያን በክርስቶስ ፍቅር ውስጥ ተረጋግቼ የመኖር ፍላጐት አደረብኝ፡፡ በቃ ኢትዮጵያ እንደገባሁ እረፍት ነው የተሰማኝ፡፡
ህዝቦቹም እንግዳን እንደ ህፃን ልጅ በፍቅር ነው የሚንከባከቡት፡፡ አየሩም… ሁሉም ነገር ለእኔ በጣም ተስማሚ ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ መጥቼ አማርኛ መናገር ስጀምር፣ እየሳቁ ያበረታቱኝና ሞራል ይሰጡኝ ነበር፡፡ ብቻ ኢትዮጵያ ፍቅር… የፍቅር አገር ናት፡፡ ከዚህ ፍቅር ደግሞ እኔ ብዙ ነገር ተምሬያለሁ፡፡ ኢትዮጵያን እኔ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደተወለደባት ቅዱስ አገር፣ እንደ ኢየሩሳሌም ነው የማያት፡፡ ለእኔ ሁለተኛዋ ኢየሩሳሌም ናት ማለት እችላለሁ፡፡ ነገር ግን ኢየሩሳሌም እስራኤል ውስጥ ጦርነት አለ፡፡ ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት በሰላም በኩል ከኢየሩሳሌም ትበልጣለች፡፡
ኢየሩሳሌም ኖረህ ታውቃለህ?
በፍፁም! ኢየሩሳሌምን በመፅሀፍ ቅዱስ ነው የማውቃት፡፡ ነገር ግን በፍፁም የምረሳት አገር አይደለችም፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ዋናው ስራህ ምንድን ነው? ሙዚቃ? ንግድ ወይስ?
ዋናው የእኔ ተልእኮ የመፅሃፍ ቅዱስን ትምህርት፣ የኢየሱስ ክርስቶስን ፍቅርና መልእክት መስበክና ማሰራጨት ነው፡፡ የአባባ ጃንሆይን መልእክትና ትምህርት ለዓለም ማሳወቅ ነው፡፡ አባባ ጃንሆይ የአለም ህዝቦች ፣ በዘርና በቀለም ሳንለያይ በፍቅር እንድንኖር አስተምረውናል፡፡ የእኔም ዋና ስራ እነዚህን ነገሮች ማስተማር ነው፡፡ ትምህርቱን የማስተላልፈው ደግሞ በሙዚቃ ነው፡፡ ስለዚህ ዋና ስራዬ ሙዚቃ ነው ማለት ነው፡፡
ኢትዮጵያዊት አግብተህ ሁለት ልጆች ማፍራትህን ሰምቻለሁ፡፡ እስቲ ስለትዳርህ አጫውተኝ?
ልክ ነው ሚስቴ ኢትዮጵያዊት ናት፡፡ ለይላ ትባላለች፡፡ ሁለት ቆንጆ ቆንጆ ሴት ልጆችን ከእሷ ወልጃለሁ፡፡ ምስጋናዬ ሲዲኒ እና መባፅዮን ሲዲኒ ይባላሉ፡፡ ምስጋናዬ ዘጠኝ አመቷ ሲሆን መባፅዮን የአራት አመት ልጅ ናት፡፡ በኑሮዬ፣ በልጆቼና በትዳሬ በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡
እስቲ ስለ ባለቤትህ ለይላ እና ስለተገናኛችሁበት አጋጣሚ አጫውተኝ…
ባለቤቴ ለይላ መኩሪያ ትባላለች፡፡ የተገናኘነው ናዝሬት ውስጥ ነው፡፡ እኔ ገና አዲስ አበባ እንደመጣሁ ኑሮዬን ለማመቻቸትና ስራ ለመስራት ወዲህ ወዲያ እያልኩ ሳለ ነበር ያገኘኋት፡፡ ናዝሬት አንድ ዝግጅት ነበረኝ፤ እዚያ ለስራ ስሄድ የፕሮግራሙ አደራጅ ነበረች፡፡ በዚያን ጊዜ የአዳማ ወጣቶች ልማት ላይ የመስራት ፍላጐት እንዳላት ነገረችኝ፡፡ እኔም ሻሸመኔ ውስጥ የሆነ ድርጅት አለን፤ ራስታዎች የምንሳተፍበት፡፡ አዳማና ሻሸመኔ ደግሞ ሁለቱም የኦሮሚያ ክልሎች እንደመሆናቸው ብዙ የልማት ስራዎችን አብረው ይሰራሉ፡፡ በዚህ ምክንያት አዳማና ሻሸመኔ ላይ ፌስቲቫሎች ተዘጋጀና እኔም በበጐ ፈቃደኝነት ስራዎቼን አቀረብኩኝ፡፡ ላይላ ባላት አቅም አገሯንና ህዝቧን ማገልገል የምትወድ ጐበዝ ሴት ናት፡፡ እንዲህ ተቀራርበን ነው ያገባኋት፡፡ ለይላ ለእኔ ጥሩ ሚስት ናት፡፡
የባለቤትህ ዋና ሙያ ምንድን ነው?
እሷ የተዋጣላት ማናጀር ናት፡፡ በማኔጅመንትና በእንግዳ አቀባበልና አያያዝ ዘርፍ ነው የተመረቀችው፡፡ አዳማ ትልቅ ሆቴል ውስጥ በስኬታማ ማናጀርነት ለረጅም ጊዜ ሰርታለች፡፡ አሁን ደግሞ በሙዚቃና ኢንተርቴይንመንት ዘርፍ ትልልቅ ዝግጅቶችን ታሰናዳለች፡፡
የመጀመሪያ ሚስትህ ናት ወይስ ከዚያ በፊት ትዳር ነበረህ?
አሜሪካ እያለሁ ሌላ ሚስት ነበረችኝ፤ ከእሷ ሁለት ትልልቅ ሴት ልጆች አሉኝ፡፡
“The Ultimate Challenge” (ታላቁ ፈተና) የተባለው ሁለተኛ አዲስ አልበምህ … ምን ላይ ደረሰ?
“ታላቁ ፈተና” አልበሜ አልቋል ግን አልተለቀቀም፡፡ በመጀመሪያ የአልበሙ መጠሪያ የሆነውን ነጠላ ዜማ ለቅቄያለሁ፡፡ በመቀጠል ሶስት ነጠላ ዜማዎችን እለቅና ከዚያ በኋላ ታህሳስ ወር ላይ ሙሉ አልበሙ ይለቀቃል፡፡
“ታላቁ ፈተና” የተሰኘውን ነጠላ ዜማ በለቀቅህ ጊዜ የዘፈኑ መነሻ አባባ ጃንሆይ እ.ኤ.አ በ1963 በተባበሩት መንግስታት ስብሰባ ላይ ጀኔቫ ውስጥ ያደረጉት ንግግር እንደሆነ ገልፀህ ነበር…
ልክ ነው፡፡ አባባ ጃንሆይ ዓለምን ትልቅ ፈተና እንደገጠማት፣ በፍቅር መኖር ሰላምና አብሮነት እየጠፋ፣ የሰው ልጅ ፈተና ውስጥ መውደቁን ተናግረው ነበር፡፡ መነሻው ያ ንግግር ነው፤ እሳቸው ኢትዮጵያ የራሷ ባህል፣ ፈሪሀ እግዚአብሄር፣ መዋደድና መፋቀር ያላት አገር እንደሆነች በግልፅ አስቀምጠዋል፡፡ እኔም እዚህ ላይ አፅንኦት ሰጥቻለሁ፡፡ ምክንያቱም ዋናው ስራዬ በሙያዬ ፍቅርና አንድነትን መስበክ ነው ብዬሻለሁ፡፡
በእሳቸው ንግግር መነሻነት ቦብ ማርሌይም ያቀነቀነ ይመስለኛል፡፡ ያንተ በምን ይለያል?
ትክክል ነው፤ ቦብ በዚህ ላይ መዝፈኑን አስታውሳለሁ፡፡ እሱ የቆዳ ቀለም፣ የአይን ቀለም… ልዩነት የአለምን ህዝብ መለያየት የለበትም፤ ሁሉም የአለም ህዝብ እኩል ነው… የሚለውን ነው ማስተላለፍ የፈለገው፡፡ የእኔም ከዚህ ብዙ አይለይም፡፡ አሁንም ታላቅ ፈተና የሆነው ይኸው በዘር፣ በቆዳ ቀለም መከፋፈል… የሰው ልጅ አንድነትን ያለመቀበል ሲሆን፣ ይህ ደግሞ እግዚአብሄርን በማመንና በእግዚአብሄር ፍቅር ውስጥ ሊፈታ የሚችል ነው፡፡ በመሆኑም ሁሉም ልቡን ወደ ፈጣሪ በማዞር፣ እርስ በእርስ መዋደድ እንዳለበት ነው ጃንሆይ በአፅንኦት የተናገሩት፡፡ እኔም በዚህ ላይ ነው ያተኮርኩት፡፡ ትንሽ ልዩነት ያለው እዚህ ላይ ነው፡፡ አባባ ጃንሆይ በንግግራቸው መጨረሻ፤ “ልባችሁን ክፈቱና ሌሎችን በፍቅር ተቀበሉ፤ ያን ጊዜ ታላቁ ፈተና ያበቃል” ነበር ያሉት፡፡
ባለፈው ወር የአልበምህን መምጣት ለማስተዋወቅና “ታላቁ ፈተና” የተሰኘ ነጠላ ዜማህን ለማስመረቅ በአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሴስ ኮንሰርት አዘጋጅተህ ነበር፡፡ የታዳሚው አቀባበል እንዴት ነበር?
በኮንሰርቱ ያገኘሁት ምላሽና የሰዎች አስተያየት ከጠበቅሁት በላይ አሪፍ ነበር፡፡ አልበሜ ውጤታማ እንደሚሆን አመላካች ኮንሰርት ነው፡፡
ከኢትዮጵያዊያን አርቲስቶች ጋር የመስራት እድል ገጥሞሃል?
ኦ…ው በጣም በጣም ከብዙዎች ጋር ሰርቼአለሁ፡፡
ለምሳሌ …?
ለምሳሌ ከፀሃዬ ዮሐንስ ጋር ሰርቻለሁ፤ “ሳቂልኝ ሳቂልኝ” የሚለውን ዘፈኑን ካስታወስሽ “ቆንጅዬ ደህና ነሽ” እያልኩኝ ፊቸሪንግ ሰርቻለሁ፡፡ መድረክ ላይ ከጆኒ ራጋ (ዮሐንስ በቀለ) እንዲሁም ከሃይሌ ሩት ጋር ሰርቻለሁ፡፡
ከብዙ ዓመታት በፊት ከቴዲ አፍሮ ጋር ሻሸመኔ ውስጥ አብረን ሰርተናል፡፡ በሻሸመኔ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች የሚማሩበትና እኛ የምንረዳው ት/ቤት አለ፡፡ “ጃማይካ ራስተፈሪያን ደቨሎፕመንት ኮሚዩኒቲ” የሚባል ት/ቤት ነው፤ ወደ 800 ያህል ተማሪዎች አሉት፡፡ እነዚህ ተማሪዎች በትምህርታቸው መቶ በመቶ ውጤታማ ናቸው፡፡
 በጥሩ ሁኔታ እንግሊዝኛ ይናገራሉ፤ ሻሸመኔ ብትሄጂ ብዙዎቹ ወጣቶች በትክክልና በአጥጋቢ ሁኔታ እንግሊዝኛ ይናገራሉ፡፡ ሌላው አካባቢ ይሄንን አታይም፡፡ ለማንኛውም እኔና ቴዲ አፍሮ በጋራ ኮንሰርት አዘጋጅተን፤ ለዚህ ት/ቤት አቅርበናል፡፡ ከጋሽ መሐሙድና ከሌሎችም ትልልቅ የኢትዮጵያ ሙዚቀኞች ጋር ሰርቻለሁ፡፡ በዚህ ክብርና ደስታ ይሰማኛል፡፡
እስቲ ኢምፔሪያል ማጀስቲክ ስለተባለው የሙዚቃ ባንድህ ንገረኝ…
ኢምፔሪያል ማጀስቲክ ባንድ ከተለያየ አለም በተውጣጡ ሙዚቀኖች የተዋቀረ ባንድ ነው፡፡ አብዛኞቻችን የተገናኘነው ሻሸመኔ በተደረገ የራስተፈሪያን ኮሚዩኒቲ ስብሰባ ላይ ነው፡፡ መጀመሪያ እኔ፣ ጁዳ፣ አልተን፣ ዛብሌን የተባልን ሰዎች ነን ያቋቋምነው፡፡
ዋና ዋናዎቹ የባንዱ ሰዎች እኛ ነን፡፡ ከዛ በፊት ሌሎችም ሰዎች ነበሩ፤ ግን በቋሚነት ባንዱ ውስጥ የሚሰሩ አልነበሩም፡፡
ስንት አይነት የሬጌ ስልቶች አሉ?
አር ኤንድ ቢ ሬጌ አለ፡፡ ወደ ኢትዮጵያ ስትመጪ አንቺ ሆዬ፣ ባቲ፣ ትዝታ፣ አምባሰል ስልት ሬጌዎች አሉ፡፡ “ታላቁ ፈተና” የተሰኘው አልበሜም በነዚህ አራት የሙዚቃ ስኬሎች የተሰራ ነው፡፡
በአልበሜ ትዝታ ማይነር አንቺሆዬ፣ ባቲ ማይነር ተካተውበታል፡፡ ከበሮና ዋሽንትንም በተለያዩ ሙዚቃዎች ውስጥ አስገብቻለሁ፡፡ የጃማይካ ሬጌ ላይ ደግሞ ድራምና የሬጌን ስሜት የሚፈጥሩ መሳሪያዎችን አካትቻለሁ፡፡
በአልበሙ ላይ አማርኛ ዘፈኖች የሉህም?
“Ethiopia is calling” የተባለው የመጀመሪያ አልበሜ ላይ ሁለት የአማርኛ ዘፈኖች ነበሩ፡፡  “ስላሴ የነፍስ ዋሴ” እና “ኢትዮጵያ የኔ መመኪያ” የተሰኙ እንደውም “ስሜን የማታውቁ ካላችሁ፣ ሲዲኒ ሳልማን እባላለሁ ልንገራችሁ” እያልኩ ነው የዘፈንኩት፡፡
በአሁኑ አልበሜ ላይ አማርኛና እንግሊዝኛ እየደባለቅሁ እንጂ ብቻውን አማርኛ አልዘፈንኩም፡፡ ወደፊት ሙሉ በሙሉ የአማርኛ አልበም አወጣለሁ፡፡ ምክንያቱም የአማርኛ ቋንቋ ችሎታዬ እያደገ ነው፡፡ እንቁላል ቀስ በቀስ በእግሩ ይሄዳል አይደለም የሚባለው... (በሚያስቅ አማርኛ)፡፡
ከኢትዮጵያ ባህላዊ ምግቦች በጣም የምትወደው ምንድን ነው?
ለእኔ አንደኛ ዶሮ ወጥ ነው፤ ሽሮም ነፍሴ ነው፤ አልጫና ጥብስም እወዳለሁ፡፡ ዶሮና ሽሮ ወጥ ግን ለእኔ በጣም ተወዳጅ ምግቦች ናቸው፡፡
ሻሸመኔ የሚገኘው “Twelve Tribes of Israel” የተባለው ድርጅታችሁ አሁንም አለ?
አለ፡፡ እኔ በ2001 እ..ኤ ሀምሌ ነው ወደ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የመጣሁት፡፡ የመጣሁትም ይሄ ድርጅት ጋብዞኝ ነው፡፡
ወደ ኢትዮጵያ መጥቼ ለመኖር አፈልግ ሰለነበር በድርጅቱ ግብዣ ሀምሌና ነሐሴን እዚህ ቆይቼ ሁሉንም ነገር ካጠናሁ በኋላ መስከረም ላይ የሆነ ፕሮግራም ስለነበረኝ ለንደን ሄጄ፣ ከዚያ ወደ አሜሪካ ከሄድኩ በኋላ ነው ጠቅልዬ ወደ ኢትዮጵያ የመጣሁት፡፡
 “ትዌልቭ ትራይብስ ኦፍ እስራኤል” በእየሱስ ክርስቶስ የሚያምኑ ራስ ተፈሪያን ያቋቋሙት የእምነት ድርጅት ነው፡፡ አሁንም አለ፡፡
አሁን የት ነው የምትኖረው?
እዚሁ አዲስ አበባ ሰሚት ነው የምኖረው፡፡ ሻሸመኔ መኖሪያ ቤት ሰርቻለሁ፤ አሁን በጥሩ ሁኔታ ላይ እገኛለሁ፡፡ ሻሸመኔ አለ ያልኩሽ “ጃማይካ ራስተፈሪያን ዴቭሎፕመንት ኮሙዩኒቲ” ት/ቤት ውስጥም አልፎ አልፎ አስተምራለሁ፡፡
    በገቢ በኩል ይሄም ያግዘኛል፡፡ ሚስቴ ጐበዝ ሰራተኛ ናት፤ በጣም ደስተኛ ህይወት እየኖርኩኝ ነው፡፡    

Saturday, 24 October 2015 10:09

የዝነኞች ጥግ

(ስለ ኢንተርኔት)

- ኢንተርኔትን በተመለከተ አንድ ትልቅ
ችግር አለብኝ፡፡ ይኸውም በውሸታሞች
የተሞላ መሆኑ ነው፡፡
ጆን ላይዶን
- የማስታወቂያ የወደፊት እጣ ፈንታ
በኢንተርኔት ላይ የተመሰረተ ነው፡፡
ቢል ጌትስ
- ዛሬ እርሻ የተለየ መልክ ይዟል -
ገበሬዎቻችን GPS እየተጠቀሙ ነው፡
፡ የመስኖ ሥራችሁን በኢንተርኔት
መቆጣጠር ትችላላችሁ፡፡
ዴቢ ስታብናው
- ሰዎች ስለግል ህይወታቸው ለማውራት
በጣም ፈቃደኞች አይደሉም፤ ወደ
ኢንተርኔት ስትመጡ ግን የበዛ
ግልፅነታቸውን ታያላችሁ፡፡
ፓውሎ ኮልሆ
- ኢንተርኔት ለሰው ልጅ ብዙ ያልተነገሩ
ጥቅሞችን ይሰጣል፡፡ ከኢንተርኔት ብዙ
ለመጠቀም ከፈለግን እንደራሳችን ሃብት
ልንቆጥረው ይገባል፡፡
ሚሼል ቤከር
- የመጨረሻ ቃል፡- ስለ ኢንተርኔት ዕውቀት
የለኝም፡፡ ኮምፒዩተር የለኝም፡፡ በ74
ዓመት ዕድሜዮ እሱን የመማር ትዕግስት
አይኖረኝም፡፡
ዴቪድ ዊልከርሰን
- ሰዎች ኢንተርኔት ላይ በሚያጠፉት የጊዜ
መጠን እገረማለሁ፡፡
ጄ.ኤል.ፓከር
- ኢንተርኔትን እፈራ ነበር፤ ለምን? ቢሉ
መተየብ አልችልም ነበር፡፡
ጃክ ዌልሽ
- ኢንተርኔትን ልታምኑት አትችሉም፡፡
ኒኮሌቴ ሼሪዳን
- ኢንተርኔት አገራዊ ድንበር የሚባል ነገር
አያውቅም፡፡
ኢላን ዴርሾዊትዝ
- በአሁኑ ጊዜ እንግሊዝኛ መናገር የማይችልና
ኢንተርኔት መጠቀም የማይችል ሰው እንደ
ኋላቀር ተደርጎ ይቆጠራል፡፡
አል - ዋሊድ ቢን ታላል
የዝነኞች ጥግ

እኛንም የሚያሳስብ ጉዳይ ሆኗል




 

Saturday, 24 October 2015 10:05

የፀሐፍት ጥግ

• የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ሳለሁ ስለ ሳንባ
ነቀርሳ በፃፍኩት ድርሰት ተሸልሜአለሁ፡፡
ወጉን ጽፌ ሳጠናቅቅ በሽታው
እንደነበረብኝ እርግጠኛ ነበርኩ፡፡
ኮንስታንስ ቤከር ሞትሌይ
• በፅሁፌ ውስጥ ብዙ የወግ አላባውያንን
ለመጨመር እሞክራለሁ፡፡
ራይስዛርድ ካፑስቺኒስኪ
• የእኔ ጉብዝና መጽሐፍ አንብቦ ሂሳዊ
መጣጥፍ መፃፍ ላይ ነው፡፡
ሪቨርስ ኩኦም
• ወግ ነፍሴ ነው፡፡ ልሰራበት የምወደው
ዘውግም ነው፡፡
ሜግሃን ዳዩም
• በ1980 ዓ.ም የ11ኛ ዓመት ልደቴን
ከማክበሬ ጥቂት ቀደም ብሎ የመጀመሪያ
ወጌን በእንግሊዝኛ ፃፍኩኝ፡፡
ፓንካጅ ሚሽራ
• አዕምሮዬን ለማጽዳት ወግ እጽፋለሁ፡፡
ልቤን ለመክፈት ልብወለድ እጽፋለሁ፡፡
ታዪዬ ሴላሲ
• የምፅፋቸውን የግል ወጐች በተመለከተ
ማንም እንደማያነባቸው ራሴን
አሳምኘዋለሁ፡፡
ዳኒ ሻፒሮ
• አብዮት የእራት ግብዣ ወይም ወግ
መፃፍ ወይም ስዕል መሳል አሊያም ጥልፍ
መጥለፍ አይደለም፡፡
ማኦ ዜዶንግ
• ልብወለድ መፃፍ አይመቸኝም ነበር፡፡
እኔ የምወደው ከረዥም ልብወለድ ይልቅ
የግል ወጐችን ነበር፡፡
አላይን ዲቦ ቶን
• የወግ ዋናው ነገር ሁኔታዎችን መለወጥ
ነው፡፡
ኢድዋርድ ቱፍቴ
• ወጐችን ወይም ፅንሰ ሃሳብ መፃፍ
አልወድም፡፡
አድሪያን ሚሼል


Saturday, 24 October 2015 10:04

የመንግሥት ጥግ

 ሥራ ለመፍጠር የግሉ ሴክተር ያስፈልገናል፡
፡ መንግስት ሥራ መፍጠር የሚችል ቢሆን
ኖሮ ኮሙኒዝም በተሳካለት ነበር፡፡ ግን
አልሆነለትም፡፡
ቲም ስኮት
- የቅርቡን ብቻ ማሰብ የመልካም መንግስት
ትልቁ ጠላቱ ነው፡፡
አንቶኒ አልባኔዜ
- መንግሥት ማለት እኛ ነን፤ እናንተና እኔ፡፡
ቴዎዶር ሩስቬልት
- ዲሞክራሲ ለእያንዳንዱ ሰው የራሱ ጨቋኝ
የመሆን መብት ያጎናፅፈዋል፡፡
ጄምስ ረስል ሎዌል
- ሰዎች መላእክት ቢሆኑ ኖሮ መንግስት
የሚባል አያስፈልግም ነበር፡፡
ጄምስ ማዲሰን
- ገንዘብ ሊገዛው የሚችል ምርጥ መንግስት
አለን፡፡
ማርክ ትዌይን
- ዓለም ህግ በማውጣት አትድንም፡፡
ዊሊያም ሆዋርድ
- መንግስት ምርት ቢሆን ኖሮ፣ እሱን መሸጥ
ህገወጥ ይሆን ነበር፡፡
ፒ.ጄ. ኦ‘ሮዩርኬ
- እያንዳንዱ አገር የሚገባውን መንግስት
ያገኛል፡፡
ጆሴፍ ዲ ማይስትሬ
- መንግስት የሰሃራ በረሃን እንዲያስተዳድር
ኃላፊነት ቢሰጠው፣ በ5 ዓመት ውስጥ የአሸዋ
እጥረት ይፈጠር ነበር፡፡
ሚልተን ፍራይድማን