Administrator

Administrator

Saturday, 19 December 2015 11:49

“የተረገመ አዙሪት”

ሰላማዊ ተቃውሞ፣ ከፖሊስ ጋር ግጭት፣ ከዚያ ረብሻና እስር፣ ቃጠሎና ግድያ... ከዚህ አሳዛኝ የጥፋት ሰንሰለት መላቀቅ ያቃተን፤ መውጫ የሌለው አዙሪት የሆነብን ለምንድነው?
እንዲህ አይነት ቀውስ በተፈጠረ ቁጥር፤ መንግስት እየደጋገመ የሚናገረው ነገር አለ። ቅሬታዎችን ማቅረብ፣ ተቃውሞን በሰላም መግለፅ፣ ተፈጥሯዊ መብት ነው ይላል - ሁልጊዜ። እና፤ መንግስት ይህንን መብት ከምር የሚያከብር ከሆነ፤ ለምን... ሰላማዊ ተቃውሞ ወደ ረብሻና ግድያ ይሸጋገራል?
በየጊዜው የሚፈጠሩ ቅሬታዎችንና ተቃውሞዎችን፣ አንድ በአንድ በቀጥታ እያስተናገደ ምላሽ ለመስጠትና ለማስተካከል ቢተጋ ኖሮ፤ ችግሮችን ለመፍታት ከማገዝ አልፎ፤ ረብሻ የማይነካካው ሰላማዊ  ተቃውሞ እንዲለመድ ይረዳ ነበር፡፡
መንግስት ይህንን ሃላፊነቱን አልተወጣም፡፡ ስልጡን የፖለቲካ ባህል እገነባለሁ እያለ ለአመታት ቢናገርም፤ ከነባሩ አዙሪት አልወጣንም፡፡
ነገር ግን፤ መንግስት፣ ሰላማዊ ተቃውሞን ለማስተናገድ ጨርሶ የማይፈልግ ቢሆንም እንኳ፣ በዚህም ሃላፊነቱን ባለመወጣት ዋና ተጠያቂ ቢሆንም እንኳ፣ እኛስ በራሳችን አቅም፣ ሰላማዊ ተቃውሞ ወደ ብጥብጥ እንዳያመራ መከላከል አንችልም?
መቼም፣ አብዛኛው ሰው፣ ጨዋ ነው። የተቃውሞ ድምፅ ለማሰማትና አቤቱታ ለማቅረብ፣ ወደ አደባባይ የሚወጡ ብዙዎቹ ሰዎችም፣ በአመዛኙ የሰውን ሕይወትና ንብረት ለመጉዳት አይፈልጉም። ታዲያ፣ ለምንድነው በየጊዜው፣ እንዲህ አይነት ቀውስ የሚፈጠረው?
እዚህ ላይ ችግር አለ። አብዛኞቹ ሰዎች  ጨዋ ቢሆኑም፣ የሰውን ሕይወትና ንብረት ለመንካት ፍላጎት ባይኖራቸውም፤ በሰላማዊ ተቃውሞ መሃል፤ ዝርፊያንና ጥቃትን ለማስቆም ይቸገራሉ። በሌላ አነጋገር፤ መዝረፍና ማቃጠል ለሚፈልግ ሰው ‘ጥሩ’ አጋጣሚ ይሆንለታል። ከዚያም አልፎ ራሱን፤ ‘ዋና የነፃነት ታጋይ፣ ዋና ተቆርቋሪ፣ ዋና ተወካይ’ አስመስሎ ስለሚሾም፣ ‘ተው የሰው ንብረት አትዝረፍ፣ አታቃጥል’ ብለን በድፍረት አንጋፈጠውም። እንዲያውም፣ አለቃ ወይም መሪ ይሆንብናል።
አንድ መጥፎ ሰው፤ ነገሩን ሁሉ የሚረብሽብን፤ አድራጊ ፈጣሪ የሚሆንብንና ወደ ጥፋት አቅጣጫ የሚመራን፣ አለምክንያት አይደለም። እሱን ለመገሰፅና ለማረም ከሞከርን፤ ‘ከሃዲ፣ ሰርጎ ገብ፣ ተብለን አጣብቂኝ ውስጥ እንዳንገባ እንሰጋለን፡፡ ‘ከሃዲ... ያዘው፣ ፈንክተው’ ብሎ ቢያነሳሳብን፣ በዚያ ግርግር መሃል፣ ምን ሊፈጠር እንደሚችልና ምን ሊደረስብን እንደሚችል ለመገመት ያስቸግራል። “ወደ ጥፋት መንገድ አንሄድም፤ ሰላማዊ ተቃውሟችንን አትረብሽብን” የሚል ትችትንም ሆነ ተግሳፅ መስማት፣ እንደ ጥቃትና እንደ ሽንፈት ይቆጥረዋል - ትችታችን ትክክለኛና ተገቢ ቢሆንም እንኳ። ግን፣ እንዲያው፣ ትችታችን ተገቢ ባይሆንስ? ትችት ስለተሰነዘረበት ብቻ... “ያዘው ፈንክተው”...?
ይሄማ፣ አምባገነን መንግስት ከሚፈፅመው አፈናና ረገጣ በምን ይለያል?
አዙሪቱ ይህንን ይመስላል።
የመንግስት ጭፍን ፕሮፖጋንዳንና ጥፋትን፣ አፈናንና ጉልበተኝነትን ለመቃወም፤ እንከን የሌለው ትክክለኛና ጥርት ያለ ሰላማዊ ተቃውሞ ለማሰማት ብንችል እንኳ፤ እዚያው ከመሃላችን አንድ ሁለት መጥፎ ሰው አይጠፋም። ስልጣን ባይኖረውም፣ ትንሽ “አምባገነን ሊሆንብን ይሞክራል፡፡ እሱ ከሚነግረን ወሬ ውጪ፤ ለየት ያለ አንዳች መረጃ መስማት ያንጨረጭረዋል፡፡ አንዳች የተለየ የአስተያየት አማራጭ ለማየትም አይፈልግም። አለመፈለግ ብቻ አይደለም፡፡ በከሃዲነት እንድንፈረጅ ማድረግ እንደሚችል ያውቃል፡፡ እናም ጭፍን ስሜትን በማራገብና በአሉባልታ፣ በዛቻና በጉልበት፣ ዙሪያውን ‘ዝም’ በማሰኘት፣ አለቃና መሪ ሆኖ ያርፈዋል፡፡ እንደዚህ አይነት ሰው እንደሚኖር ስለምናውቅና ስለምንሰጋም ነው፤ ጭፍን ስሜቶችንና መጥፎ ድርጊቶችን ለማስቆም ብዙም ለመጣር የማንነሳሳው። እናም፤ ሰላማዊው ተቃውሞ፣ በአንድ በሁለት ሰው ተረብሾ ወደ ግርግር ይቀየርብናል። ይሄ አንደኛው ምክንያት ነው፡፡
ሁለተኛው ምክንያትስ?
የተቃውሞ ድምፃችንን ለማጉላላትና እንዳይደበዝዝ መመኘት ተገቢ ቢሆንም፤ ለዚህ በትጋት ከመጣጣር ይልቅ፣ ወደ “ቀላል” የአቋራጭ መንገድ ካዘነበልን፣ ለስህተት እንጋለጣለን፡፡ እንዴት በሉ፡፡  
አንደኛ ነገር፤ የተቃውሞ ድምፅን የሚያበርድና የሚያደበዝዝ ከመሰለን፣ እውነተኛ መረጃንና ምክንያታዊ አስተያየትንም ጭምር ችላ ብለን፣ ሰምተን እንዳልሰማን እናልፋለን። [ከድካምና ከጥረት የሚገላግል አቋረጭ መንገድ ያገኘን ይመስለናል። ግን፤ መዘዝ አለው። በዚሁ ምክንያት፣ አስተዋይ፣ ብልህና ቀና ሰዎችን እያገለልን እንደምንሄድ አናውቅም]። ይህም ብቻ አይደለም።
የተቃውሞ ድምፅን ለማማሟሟቅና ለማድመቅ የሚረዳ እስከመሰለን ድረስ፣ ተገቢ ላልሆኑ ነገሮችም ጭምር ቦታ መስጠት እንጀምራለን፡፡ ለምሳሌ፤ አንድ ሁለት ሰዎች በጭፍን የሚያስተጋቡትን የውሸት መረጃም ሆነ የጥፋት አዝማሚያ፣ ለማስተካከልና ለማረም ከመሞከር ይልቅ፣ አይተን እንዳላየን ማለፍ ይቀለናል። [ለጊዜው፣ ‘ቀላል’ ነው። ነገር ግን፣ እነዚያ በጭፍን ስሜት የተዋጡ አንድ ሁለት ሰዎች፣ ራሳቸውን አለቃና መሪ አድርገው በእኛው ላይ እንዲሾሙ፣ እድል እንከፍትላቸዋለን።] ለዚህም ነው፤ በመጀመሪያው ቀንና በማግስቱ፣ ሰላማዊ የነበረው የተቃውሞ ድምፅ፣ ቀስ በቀስ በረብሻ እየተዋጠና እየተወረሰ እንዳይሄድ ለመከላከል የምንቸገረው።
አንዴ መበላሸት ከጀመረ በኋላ ደግሞ፤ እየከበደና እየተባባሰ ይቀጥላል፡፡
ጭራሽ፣ ‘ይሄ አገር ወዴት እያመራ ነው?” የሚል ጥርጣሬ እስኪያድርብን ድረስ፣ አገር ምድሩ ይቀወጣል። “የተሻለ ነገር ያስገኝ ይሆናል” ብለን የጀመርነው ነገር፤ ከቀድሞው ወደ ባሰ ውጥንቅጥ እንዳያወርደን መስጋት ይመጣል። ያኔ፤ ለጉልበተኛ ባለስልጣን፣ መንገዱ ተመቻቸለት።
ከሰላማዊ ተቃውሞ ይልቅ፣ ረብሻ የሚመቻቸው ባለስልጣናት አሉ። ለምን? አሃ፤ ጥያቄዎችንና ትችቶችን የማስተናገድ ጣጣን ያስቀርላቸዋል፡፡ ሰላማዊ ተቃውሞ በረብሻ ከተወረሰ… በቃ፤ በማንኛውም መንገድ፣ (በፕሮፓጋንዳ፣ በዛቻና በጉልበት)... ሁሉንም ሰው ፀጥ ለማሰኘት፣ በቂ ሰበብ ይሆንላቸዋል። በሕይወት እና በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሱ ሰዎችን ብቻ በህግ ከመዳኘት ይልቅ፤ በዚህችው አጋጣሚና ሰበብ፣ አገሬውን ሁሉ ዝም ለማሰኘት፣ የትችትና የተቃውሞ ድምጽን ጨርሶ ለማጥፋት ይሞክራሉ።
ፕሮፓጋንዳውን፣ አፈናውን፣ ጉልበተኝነቱን፣ ከቀድሞው የባሰ ለማድረግ የሚጠቅም ማመካኛ ይሆንላቸዋል - ረብሻው። ጥያቄዎችን፣ አቤቱታዎችንና ትችቶቸን እያስተናገዱ፣ ስህተቶችን ለማስተካከልና ጥፋቶችን ለማረም ከመትጋት ይልቅ፤ ሁሉንም ሰው ዝም ማሰኘት  ይቀላቸዋል። ለጊዜው፣ ‘ቀላል’ ይመስላል። ግን፤ መፍትሄ አይሆንም። ባለስልጣናትና መንግስታት፣ በሰበብ አስባቡ፣ ‘ገናና’ እየሆኑ መሄድ፤ “ቀላል” መስሎ ቢታያቸውም፤  ብዙም አያዛልቅም። ቢሆንም ግን፤ ሰበብ ተገኘ ተብሎ፣ ‘ገናና’ ለመሆን መሯሯጥ፤ በየአቅጣጫውና የየጊዜው፣ በተደጋጋሚ የሚታይ፣ የተለመደ የበርካታ ባለስልጣናት  ባህርይ ነው። ቀውስ በተፈጠረ ቁጥር፤ ለቀውሱ ሁነኛ መፍትሔ ከማበጀት ይልቅ፤ በዚያ ሰበብ፤ ከዜጐች ላይ ገናና ለመሆን ይገለገሉበታል፡፡
በአገራችን ብቻ ሳይሆን፤ ደረጃው ቢለያይም፣ በሁሉም አገራት፣ የዘመናችን ሦስቱ ዋነኛ አለማቀፍ የቀውስ ምንጮችን ተመልከቱ።
በመንግስት እልፍ ቁጥጥሮችና ጫናዎች ሳቢያ የሚፈጠር “የቅይጥ ኢኮኖሚ ቀውስ”፣ በአለም ዙሪያ፣ ከድሃ እስከ ሃብታም አገራት፤ ሁሉንም እያናወጠ አይደል? ግን፤ ጥፋተኞቹ መንግስታት ብቻ አይደሉም፡፡ እኛም እንተባበራቸዋለን፡፡
በአንድ በኩል፤... የግል ኢንቨስትመንትንና ቢዝነስን፣ የግል ስኬትንና ብልፅግናን፣ በአድናቆትና በአርአያነት ለማየት የሚቸገር ኋላቀር ባህል በአገራችን ሞልቷል። በሌላ በኩል ደግሞ፤... በዚህም በዚያም በአየር ባየር አልያም በሙስና፣ በድጐማም ሆነ በልዩ ድጋፍ ... (ያለ ስራ እና ያለ ጥረት) ሃብት ለማግኘትና ተጠቃሚ ለመሆን መዋከብም የተለመደ ነው፡፡ እነዚህ አዝማሚያዎች፤ በብዙ ዜጐች ዘንድ የሚታዩ ስህተቶች ናቸው፡፡ የመንግስት ምላሽስ?
መንግስት፤ ቢዝነስን የሚያናንቅን ባህል ለመግታትና የአየርባየር ወከባን ለማስተካከል ከመጣር ይልቅ ወደ ነፃ ገበያ ስርዓት ለመጓዝ ከመትጋት ይልቅ፤ በዚሁ ሰበብ፤ ከነአካቴው ቢዝነስንና ነፃ ገበያን በእንጭጩ የሚቀጭ፣ የዋጋ ቁጥጥርና የዋጋ ተመን፣ የገደብና የክልከላ፣ የታክስ ጫናና የመዋጮ ዘመቻ ማካሄድ ቀላል ይሆንለታል።
ያው፤ ቢዝነስ ሳይስፋፋ ደግሞ፣ ከስራ አጥነትና ከድህነት መላቀቅ አይቻልም። አሳዛኙ ነገር፤ በስራ አጥነትና በድህነት እየተማረርን፣ ለዚህ ችግር መፍትሄ እንዲፈለግለት ‘ድማፃችንን ለማሰማት’ አደባባይ ብንወጣ፤ ከሁሉም በላይ ጎልቶ የሚወጣው ድምፅ፣ “የሸቀጦች የዋጋ ቁጥጥር ይደረግ”... የሚል መፈክር ይሆናል።
መንግስት ይህንን አግኝቶ ነው?
በዚሁ ሰበብ፤ ቢዝነስ ላይ፣ ተጨማሪ ጫናና ቁጥጥር በማወጅ፣ ይበልጥ የመንግስትን ገናናነት ለማግዘፍ የሚመኝ ባለስልጣን፣ እንደሚኖር አትጠራጠሩ። በግል ኢንቨስትመንትና በቢዝነስ ላይ ጭፍን ጥላቻን እያራገብን፣ መንገዱን ለመንግስት አመቻቸንለት ማለት ነው። እናም፣ ቢዝነስ እየተደናቀፈ፤ ከስራ አጥነትና ከድህነት ጋር እንደተቆራኘን እንቀጥላለን።
አዙሪት ነው። ለኛ አይበጅም። ለመንግስትም አያዛልቀውም። ቢዝነስን እየገታ፣ ‘ገናና’ መሆን፣ ውሎ ሲያድር መዘዙ እየከፋ ይሄዳል። በጊዜ ካልባነነ፣ መውደቂያው ይሆናል።
ሁለተኛና ሦስተኛ የቀውስ ምንጮች፤ የሃይማኖት አክራሪነትና የዘረኝነት አባዜዎች ናቸው፡፡ በአንድ በኩል፣ መንግስታት፣ የአክራሪነት ሽብርንና የዘረኝነት ግጭትን በቀጥታ ከመከላከል ይልቅ፤ በዚሁ ሰበብ፣ የዜጎችን ቅሬታ፣ ትችትንና ሰላማዊ ተቃውሞን አፍነው ዝም ለማሰኘት፣ ይጠቀሙበታል። በአገሬው ላይ ‘ገናና’ ለመሆን፣ አስተማማኝ ማመካኛ ይሆንላቸዋል። “አገርን ከሽብር ለመታደግ፤ ሕዝብን ከዘረኝነት እልቂት ለማዳን”...እያሉ፤ ያሻቸውን ነገር ለማድረግ ይሞክራሉ።
አሳዛኙ ነገር፤ እኛም፣ እንመቻችላቸዋለን። የተቃውሞ ድምፅን ለማድመቅ የሚጠቅም እየመሰለን፣ ወይም ደግሞ የተቃውሞ ድምፅ እንዳይደበዝዝ በመስጋት፣... በፅናትና በትጋት ትክክለኛ መላ ከማበጀት ይልቅ፤ ሃይማኖትንና ተወላጅነትን ከፖለቲካ ጋር የማደበላለቅ አዝማሚያ፣ አቋራጭ መፍትሄ ሆኖ ይታየናል፡፡ ወይም “ጊዜያዊ ችግር ነው” ብለን በቸልታ እንቀበለዋለን።
በዚሁ አዝማሚያ ለመንሸራተት፣ አእምሯችን ፈቃደኛ ባይሆን እንኳ፤ ፈቃደኛ የሆኑ ሰዎችን... አክራሪነትንና ዘረኝነትን የሚያስተጋቡ መጥፎ ሰዎችን በዝምታ ለማለፍ፣ ወይም እንደ ጊዜያዊ ችግር አይተን ቸል ለማለት ይዳዳናል። ነገር ግን፣ አንድ ሁለት ሰው የሚያስተጋባው የዘረኝነት ወይም የአክራሪነት መርዝ፣ ከጎናችን ተሰልፎ በዝምታ ስናልፈው፤... ለአፍታ በአዳማቂነት አገልግሎ፣ በራሱ ጊዜ የሚከስም፣ ተራ ችግር አይሆንልንም።
በተገላቢጦሽ፣ ዋና ጉዳያችንን ሁሉ ጠቅልሎ እየዋጠና እየቀበረ፣ ከመክሰም ይልቅ እየተግለበለበና እየተቀጣጠለ ለመስፋፋት እድል ያገኛል፡፡ ብዙም ሳይቆዩ፤ በሃይማኖት ተከታይነት ወይም በዘር ወደ ማቧደን ይሸጋገራሉ፤ ከዚያም በየፊናቸው የየቡዱኑ አለቃ፣... አድራጊ ፈጣሪ ይሆኑብናል።
እንዲህ፣ ነገር እየተበላሸ፣ አገሬው ወደ መናወጥ እያመራ፤ ብዙዎቻችን ‘የባሰ መጣ’ ብለን መስጋት ስንጀምር፤ መንግስት ምን ያደርጋል?
የአክራሪነትን ሽብር፣ የዘረኝነትን ግጭት እየተከላከለ፤ የዜጎችን ቅሬታና ሰላማዊ ተቃውሞ ለማስተናገድ፤ እንዲሁም... የዜጎችን ነፃነትና መብት ለማስከበር መትጋትና መጣር ይችላል። ግን፤ ይሄ አድካሚ ነው። ከዚያ ይልቅ፤ አክራሪነትንና ሽብርን፤ ዘረኝነትንና ግጭትን በመዋጋት ሰበብ፤ ቅሬታዎችንና ተቃውሞዎችን በሙሉ እያፈነ ‘አይነኬ ገናና መንግስት’ ለመሆን መሞከር ይቀላል።
በእርግጥ፤ ‘ቀላልነቱ’ ለአጭር ጊዜ ብቻ ነው። አፈናው ሲደራረብና የዜጎች እሮሮ ሲባባስ፤ ውሎ አድሮ፣ የተቃውሞ ድምፅ ግንፍል ብሎ መውጣቱ አይቀርም። ግን፤ ምን ዋጋ አለው? ያቺ ታፍና የነበረች የተቃውሞ ድምፅ፣ እንድትጎላ በመጓጓትና እንዳትደበዝዝ በመስጋት፤ መንግስትን የሚቃወም ማንኛውንም ነገር (አክራሪነትንና ዘረኝነትንም ጭምር...) የማስተናገድ አዝማሚያ ይሰፋል። የአቋራጭ መፍትሔ ምርኮኞች እንሆናለን፡፡
ያው፤ በበርካታ አገራት እንደታየው፤ የዜጎች የተቃውሞ ድምፅ፣ በአክራሪዎች ወይም በዘረኞች ድምፅ እየተዋጠ፣ ነገሩ ሁሉ ይቃወሳል። ብዙ ሰዎች በስጋት ይጨነቃሉ።
ያኔ፣ የመንግስት ስራ፣ አክራሪነትንና ዘረኝነትን መከላከል ሳይሆን፣ እግረመንገዱን አገሬውን በአፈናና በጉልበት ዝም ለማሰኘት መሯሯጥ ይሆናል። ኡደቱ ይቀጥላል። የታሪክ ጉዞ ሳይሆን፣ የታሪክ አዙሪት ውስጥ እየተሽከረከሩ፤ መከራን እየደጋገሙ ማየት!

     በብሩንዲ ሶስት ወታደራዊ ጣቢያዎች ላይ በመንግስት ተቃዋሚዎች በተፈጸመ ጥቃት በርካታ ዜጎች መሞታቸውን ተከትሎ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ዛይድ ራድ አል ሁሴን አገሪቱ ዳግም ወደ አስከፊ የእርስ በርስ ጦርነት እያመራች ነው ሲሉ ማስጠንቀቃቸውን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘገበ፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በብሩንዲ የተለያዩ አካባቢዎችና በመዲናዋ ቡጁምቡራ እየተባባሰ የመጣው ግጭት እንደሚያሳስባቸው የገለጹት አል ሁሴን፣ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ፔሪ ንኩሩንዚዛ ለሶስተኛ ዙር የስልጣን ዘመን በምርጫ እንደሚወዳደሩ መግለጻቸው የቀሰቀሰው ቁጣ በተቃዋሚ ሃይሎችና በመንግስት ደጋፊዎች መካከል ለወራት የዘለቀ ግጭት መፍጠሩንና በርካታ ዜጎች መሞታቸውን አስታውሰዋል፡፡
የፖለቲካ መሪዎችና ከፍተኛ ባለስልጣናትን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ትርጉም ያለውና አካታች የሆነ ውይይት በማድረግ በብሩንዲ የተከሰተውን ግጭት ለመግታትና አገሪቱን ከከፋ ጥፋት ለመታደግ እንዲንቀሳቀሱም ጥሪ አቅርበዋል።
ባለፈው ሳምንት አርብ እጅግ የከፋ የተባለ ግጭት መከሰቱንና በመዲናዋ ቡጁምቡራ በሚገኙ ሶስት ወታደራዊ ጣቢያዎች ላይ በመንግስት ተቃዋሚዎች በተፈጸመ ጥቃት 79 ያህል የመንግስት ተቃዋሚዎችና ስምንት ወታደሮች መሞታቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡
አገሪቱ ለረጅም አመታት ከዘለቀውና ከፍተኛ እልቂት ካስከተለው በጎሳ የተከፋፈለ የእርስ በርስ ጦርነት የወጣችው ከአስር አመታት በፊት እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ ፕሬዚዳንት ንኩሩንዚዛ ስልጣናቸውን ለማራዘም ማሰባቸው የፈጠረው ተቃውሞና አመጽ፣ አገሪቱን ወደቀድሞው አስከፊ የእርስ በእርስ ጦርነት ሊያስገባት ይችላል የሚል ስጋት መፍጠሩን ገልጧል፡፡
ካለፈው ሚያዝያ ወር አንስቶ የተከሰተው ግጭት፣ በፕሬዚዳንቱ ላይ በተሞከረ ያልተሳካ መፈንቅለ መንግስት ሳያበቃ ተባብሶ መቀጠሉን የዘገበው ቢቢሲ፣ ከአመቱ መጀመሪያ አንስቶ በአገሪቱ ከ600 በላይ ሰዎች ለህልፈተ ህይወት መዳረጋቸውንና ከ220 ሺህ በላይ ዜጎችም አገራቸውን ጥለው መሰደዳቸውን አስታውሷል፡፡

- አንድ ጠርሙስ ኦክስጂን 27.99 ዶላር ይሸጣል

በቻይና የአየር ብክለት እየተባባሰ መምጣቱን ተከትሎ፣ ቪታሊቲ ኤር የተሰኘው የካናዳ ኩባንያ ከተራሮች ላይ ተወስዶ በጠርሙስ የታሸገ ንጹህ አየር ለቻይናውያን እየሸጠ እንደሚገኝ ዘ ኢንዲፔንደንት ዘገበ፡፡
በዚህ ወር መጀመሪያ የቻይና የአየር ብክለት መጠን ከፍተኛው ደረጃ ላይ መድረሱንና ለጤና ጎጂ መሆኑ ታምኖበት በመዲናዋ ቤጂንግ ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉና የግንባታ ስራዎች እንዲቋረጡ መደረጉን ያስታወሰው ዘገባው፣ ቪታሊቲ ኤር የተሰኘው የካናዳ ኩባንያም ከሰሞኑ የታሸገ አየር ለቻይና ማቅረብ መጀመሩን ገልጧል፡፡
ኩባንያው ፕሪሚየም ኦክስጂን በሚል አሽጎ የሚሸጠው ንጹህ አየር በጠርሙስ 27.99 ዶላር እየተቸበቸበ ነው ያለው ዘገባው፣ የኩባንያው ተወካይም ገበያው እንደደራላቸውና ምርቱ በቻይና ገበያ ውስጥ ከፍተኛ ተፈላጊነት ሊያገኝ መቻሉን መናገራቸውን አስታውቋል፡፡
የኩባንያው ተወካይ ሃሪሰን ዋንግ እንዳሉት፤ ኩባንያው በመጀመሪያ ዙር ለቻይና ገበያ ያቀረበው 500 ጠርሙስ የታሸገ ንጹህ አየር ተሸጦ ያለቀ ሲሆን፣ ተጨማሪ 700 ጠርሙስ የታሸገ ንጹህ አየርም በሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ቻይና ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

     በብሩንዲ ሶስት ወታደራዊ ጣቢያዎች ላይ በመንግስት ተቃዋሚዎች በተፈጸመ ጥቃት በርካታ ዜጎች መሞታቸውን ተከትሎ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ዛይድ ራድ አል ሁሴን አገሪቱ ዳግም ወደ አስከፊ የእርስ በርስ ጦርነት እያመራች ነው ሲሉ ማስጠንቀቃቸውን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘገበ፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በብሩንዲ የተለያዩ አካባቢዎችና በመዲናዋ ቡጁምቡራ እየተባባሰ የመጣው ግጭት እንደሚያሳስባቸው የገለጹት አል ሁሴን፣ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ፔሪ ንኩሩንዚዛ ለሶስተኛ ዙር የስልጣን ዘመን በምርጫ እንደሚወዳደሩ መግለጻቸው የቀሰቀሰው ቁጣ በተቃዋሚ ሃይሎችና በመንግስት ደጋፊዎች መካከል ለወራት የዘለቀ ግጭት መፍጠሩንና በርካታ ዜጎች መሞታቸውን አስታውሰዋል፡፡
የፖለቲካ መሪዎችና ከፍተኛ ባለስልጣናትን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ትርጉም ያለውና አካታች የሆነ ውይይት በማድረግ በብሩንዲ የተከሰተውን ግጭት ለመግታትና አገሪቱን ከከፋ ጥፋት ለመታደግ እንዲንቀሳቀሱም ጥሪ አቅርበዋል።
ባለፈው ሳምንት አርብ እጅግ የከፋ የተባለ ግጭት መከሰቱንና በመዲናዋ ቡጁምቡራ በሚገኙ ሶስት ወታደራዊ ጣቢያዎች ላይ በመንግስት ተቃዋሚዎች በተፈጸመ ጥቃት 79 ያህል የመንግስት ተቃዋሚዎችና ስምንት ወታደሮች መሞታቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡
አገሪቱ ለረጅም አመታት ከዘለቀውና ከፍተኛ እልቂት ካስከተለው በጎሳ የተከፋፈለ የእርስ በርስ ጦርነት የወጣችው ከአስር አመታት በፊት እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ ፕሬዚዳንት ንኩሩንዚዛ ስልጣናቸውን ለማራዘም ማሰባቸው የፈጠረው ተቃውሞና አመጽ፣ አገሪቱን ወደቀድሞው አስከፊ የእርስ በእርስ ጦርነት ሊያስገባት ይችላል የሚል ስጋት መፍጠሩን ገልጧል፡፡
ካለፈው ሚያዝያ ወር አንስቶ የተከሰተው ግጭት፣ በፕሬዚዳንቱ ላይ በተሞከረ ያልተሳካ መፈንቅለ መንግስት ሳያበቃ ተባብሶ መቀጠሉን የዘገበው ቢቢሲ፣ ከአመቱ መጀመሪያ አንስቶ በአገሪቱ ከ600 በላይ ሰዎች ለህልፈተ ህይወት መዳረጋቸውንና ከ220 ሺህ በላይ ዜጎችም አገራቸውን ጥለው መሰደዳቸውን አስታውሷል፡፡

 በመላ አገሪቱ የተቃውሞ ሰልፎች ተደርገዋል

ባለፈው ሳምንት ሁለት የፋይናንስ ሚኒስትሮችን ከሃላፊነታቸው ያነሱት የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ፤ የአገሪቱን ኢኮኖሚ የሚያደቅ ተግባር እየፈጸሙ ነው በሚል ባለፈው ረቡዕ አደባባይ ወጥተው ተቃውሟቸውን ያሰሙ በሺህዎች የሚቆጠሩ ደቡብ አፍሪካውያን ፕሬዝዳንቱ ከስልጣን እንዲወርዱ መጠየቃቸውን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
በርካታ ደቡብ አፍሪካውያን በአገሪቱ ሙስና ተስፋፍቷል፣ በገዢው ፓርቲ የስልጣን መተካካት ላይ አግባብ ያልሆነ ተግባር ተፈጽሟል በሚል ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ መቆየታቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ በሺህዎች የሚቆጠሩ የአገሪቱ ዜጎች ረቡዕ ዕለት ጆሃንስበርግ ውስጥ ባደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ ፕሬዚዳንቱ ከስልጣን እንዲወርዱና በመንግስት የሚከናወኑ የሙስና ድርጊቶችን የሚገታ ጠንካራ ንቅናቄ እንደጀመር መጠየቃቸውን አስታውቋል፡፡
በዕለቱ ከጆሃንስበርግ በተጨማሪ በመላ አገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተቃውሞ ሰልፎች መደረጋቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ በኬፕታውን በተከናወነው ተመሳሳይ የተቃውሞ ሰልፍ የተሳተፉ በሺህዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ዙማ ከስልጣን መውረድ አለባቸው የሚል መፈክር ሲያሰሙ መዋላቸውን ጠቁሟል፡፡
ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ የቀድሞውን የአገሪቱ የፋይናንስ ሚኒስትር ናላላ ኔኔን ከሃላፊነታቸው ማንሳታቸው ከፍተኛ ትችት እንዳስከተለባቸውና ውሳኔያቸው የገበያ ቀውስ መፍጠሩንም አስታውሷል፡፡

- ላለፉት 12 አመታት የሚገዳደራትአልተገኘም
- ለኑሮ የማትመቸዋ የአለማችን የመጨረሻዋ አገር ኒጀር ናት

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም በየአመቱ ይፋ በሚያደርገው ሂዩማን ዲቨሎፕመንት ኢንዴክስ ሪፖርት ውስጥ ለኑሮ ምቹ የሆኑ የአለማችን አገራት ዝርዝርን ላለፉት 11 አመታት በቀዳሚነትን ይዛ የዘለቀችው ኖርዌይ፣ ዘንድሮም በቀዳሚነት መቀመጧን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡
አማካይ የህይወት ዘመን፣ ትምህርት፣ ገቢ እና የኑሮ ደረጃን በመስፈርትነት በማስቀመጥ የአለማችንን አገራት እየገመገመ ደረጃ የሚሰጠው ተቋሙ፤ ኖርዌይ በሁሉም መስፈርቶች ከፍተኛውን ውጤት በማስመዝገብ ዘንድሮም ለኑሮ ምቹዋ አገር ለመሆን መብቃቷን አስታውቋል፡፡
በኖርዌይ አማካይ የህይወት ዘመን 81.6 አመት ሲሆን ጠቅላላ አመታዊ ብሄራዊ የነፍስ ወከፍ ገቢዋም 64ሺህ 992 ዶላር መድረሱንና ይህም በተቋሙ ጥናት ከተካተቱት 188 ያህል የአለማችን አገራት በቀዳሚነት እንዳስቀመጣት  ዘገባው ገልጧል፡፡ ከኖርዌይ በመቀጠል እስከ አምስተኛ ደረጃን የያዙት የአለማችን አገራት አውስትራሊያ፣ ስዊዘርላንድ፣ ዴንማርክና ኒዘርላንድስ ናቸው ተብሏል፡፡
ለኑሮ ምቹ ያልሆኑ አምስት የአለማችን አገራት የተባሉት ደግሞ ኒጀር፣ መካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ኤርትራ፣ ቻድ እና ብሩንዲ ናቸው፡፡

    በአምቦ ዩኒቨርሲቲ በጐልማሶችና ማህበረሰብ ልማት ትምህርት ክፍል መምህርና የትምህርት ክፍሉ ሃላፊ በሆኑት በአቶ ያዴሳ ቶሎሳ ወዬሳ የተዘጋጀውና በትምህርት በምርምርና በአተገባበር ሂደቶች ላይ ትኩረት አድርጐ የተሰናዳው “አጠቃላይ የትምህርት እና የስራ ላይ ምርምር ዘዴዎችና አተገባበር” የተሰኘ መጽሐፍ ገበያ ላይ ዋለ፡፡ መጽሐፉ በማንኛውም ደረጃ ለሚገኙ ተማሪዎች፣ ለመመረቂያ ጽሑፍ ዝግጅትና በማንኛውም የስራ መስክ በተግባራዊ የስራ ላይ ምርምር ለተሰማሩ እንዲሁም ሊሰማሩ ለሚሹ ባለሙያዎችና መምህራን እንደ ማጣቀሻ ማኑዋል ሆኖ እንደሚያገለግልም ተጠቅሷል፡፡ በሁለት ክፍሎች የተዘጋጀውና በርካታ ምዕራፎችን ያካተተው መጽሐፉ፤ በ204 ገጾች የተመጠነ ሲሆን በ80 ብር ለሽያጭ ቀርቧል፡፡  

የአዕምሮ ህክምና ስፔሻሊስትና በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የአዕምሮ ህክምና ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር በሆኑት ዶ/ር ሞገስ አየሁ የተፃፈውና በአዕምሮ ህመምና ህሙማን ህይወት ላይ ትኩረቱን ያደረገው “ድፍርስ” የተሰኘ መጽሐፍ ሰሞኑን ለንባብ በቅቷል፡፡
በ18 ክፍሎች የተዘጋጀው ይኸው መጽሐፍ፤ ስለ አንጐል መታወክና መንስኤዎቹ፣ ስለ አዕምሮ ህመም ምንነት፣ አዋቂና ህፃናት ላይ ስለሚከሰት የአዕምሮ ህመም፣ ስለ ኦቲዝምና ሌሎች ከአዕምሮ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ጥልቅ ትንታኔን ይዟል፡፡ በመጽሐፉ ሽፋን ላይ አስተያየቱን ያሰፈረው ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ፤ “ዶክተሩ የፃፉት ይህ መጽሐፍ የሚጠቅመው ለአዕምሮ ህሙማንና ለአሳታሚዎች ብቻ ሳይሆን በዘርፉ ኪናዊ ስራ ለሚሰሩ ገጣሚያን፣ ልቦለድ ደራሲያንና ፊልምና ቴአትር ለሚሰሩም የጥበብ ሰዎች ግብአት የሚሆን ነው” ብሏል፡፡ በ184 ገጾች የተሰናዳው መጽሐፉ፤ ለአገር ውስጥ በ75 ብር፣ ለውጭ አገራት በ20 ዶላር ይሸጣል። 

በደራሲ ዘውዱ አበጋዝ ተተርጉሞ በተሻለ አሰፋ የተዘጋጀው “ቆንጆዎቹ” የተሰኘ ቲያትር ከ15 አመታት በኋላ ወደ መድረክ የተመለሰ ሲሆን ዛሬ በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ትያትርና ባህል አዳራሽ ለተመልካች ይቀርባል፡፡
በስደት ህይወት ላይ የሚያጠነጥነውና የታችኛውን የህብረተሰብ ክፍል ይዳስሳል የተባለው ይኸው ቲያትር፤ የ2፡15 ርዝማኔ እንዳለው ታውቋል፡፡ በቲያትሩ ላይ ወለላ አሰፋ፣ ትእግስት ግርማ፣ ሰለሞን ሐጐስ፣ ይገረም ደጀኔና ሕሊና ሲሳይን ጨምሮ ሌሎች አንጋፋ ተዋንያን ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡

Saturday, 19 December 2015 10:42

አሴዋ ሁሌም በልባችን ነህ!!

አይረሴ ራዕይ
እኛማ እንቆጥራለን
ዛሬም ሙሉ ሳቅክን
ያልተሸራረፈ ሙሉ ፈገግታህን
እንዳቀፍን አለን በየምላዳችን የነገ ሰብልህን
አሴ ኩራ ኩራ፣ ባለህበት ኩራ
ብርሃኑ ያዘምራል፣ ያሳብህ ተራራ
ዓመቱማ ያልፋል ወደፊት ገፍትሮን
ዘመኑ ቢሸብት፣
አይረሴ ራዕይ፤ ነጭ ፀጉር የለው
ከቶ መች ይረሳል
ህልምህ የወይን ጠጅ ሲነጋ ይበስላል፡፡
የነበረህና የነበረን ሀሳብ፣ እያደር ይጠራል፡፡
ስምህ ማዘርዘሩ፣ መንፈስህ መብቀሉ
ዕምነት ፍልስፍና ውልና ፈትሉ
ዕውቀትና ትጋት ብርሃን ፊደሉ
ሩቅ እንዳሰብነው ሩቅ ነው ገድሉ
ዛሬም አለ ቃሉ፣
ያውም በርቶ ፈክቶ፣ እስከማዕዘኑ፡፡
አውቃለሁ ታውቃለህ
የመከረኛ አገር መከሯ እስኪገባ
መከራ መብዛቱ
ዕውን ቢሆን እንኳ
ራዕይህ አለ ምስክር ይቆማል፤ ቀኑ ለመንጋቱ፡፡
አይቆምም ጉዟችን ባይቆምም ሥጋቱ
አይደለም ራዕይ ብሳና ዛፍ ግንድ
ሽበት አይወርሰውም፤ የዕድሜ ዘመን ግርድ
አይረሴ ራዕይ የቸገንክበትን
የፍል ዕውቀት እርሻ፣ የዓለም አሂዶህን
ታያለህ ማሳውን፡፡
አሴ ኩራ ኩራ
ብርሃን ያዘምራል ያሳብህ ተራራ
የራዕይ ተራራ !!
(ለአቶ አሰፋ ጎሳዬ ሙት አመት መታሰቢያ)
ነ.መ