Administrator

Administrator

     በብሩንዲ ሶስት ወታደራዊ ጣቢያዎች ላይ በመንግስት ተቃዋሚዎች በተፈጸመ ጥቃት በርካታ ዜጎች መሞታቸውን ተከትሎ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ዛይድ ራድ አል ሁሴን አገሪቱ ዳግም ወደ አስከፊ የእርስ በርስ ጦርነት እያመራች ነው ሲሉ ማስጠንቀቃቸውን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘገበ፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በብሩንዲ የተለያዩ አካባቢዎችና በመዲናዋ ቡጁምቡራ እየተባባሰ የመጣው ግጭት እንደሚያሳስባቸው የገለጹት አል ሁሴን፣ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ፔሪ ንኩሩንዚዛ ለሶስተኛ ዙር የስልጣን ዘመን በምርጫ እንደሚወዳደሩ መግለጻቸው የቀሰቀሰው ቁጣ በተቃዋሚ ሃይሎችና በመንግስት ደጋፊዎች መካከል ለወራት የዘለቀ ግጭት መፍጠሩንና በርካታ ዜጎች መሞታቸውን አስታውሰዋል፡፡
የፖለቲካ መሪዎችና ከፍተኛ ባለስልጣናትን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ትርጉም ያለውና አካታች የሆነ ውይይት በማድረግ በብሩንዲ የተከሰተውን ግጭት ለመግታትና አገሪቱን ከከፋ ጥፋት ለመታደግ እንዲንቀሳቀሱም ጥሪ አቅርበዋል።
ባለፈው ሳምንት አርብ እጅግ የከፋ የተባለ ግጭት መከሰቱንና በመዲናዋ ቡጁምቡራ በሚገኙ ሶስት ወታደራዊ ጣቢያዎች ላይ በመንግስት ተቃዋሚዎች በተፈጸመ ጥቃት 79 ያህል የመንግስት ተቃዋሚዎችና ስምንት ወታደሮች መሞታቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡
አገሪቱ ለረጅም አመታት ከዘለቀውና ከፍተኛ እልቂት ካስከተለው በጎሳ የተከፋፈለ የእርስ በርስ ጦርነት የወጣችው ከአስር አመታት በፊት እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ ፕሬዚዳንት ንኩሩንዚዛ ስልጣናቸውን ለማራዘም ማሰባቸው የፈጠረው ተቃውሞና አመጽ፣ አገሪቱን ወደቀድሞው አስከፊ የእርስ በእርስ ጦርነት ሊያስገባት ይችላል የሚል ስጋት መፍጠሩን ገልጧል፡፡
ካለፈው ሚያዝያ ወር አንስቶ የተከሰተው ግጭት፣ በፕሬዚዳንቱ ላይ በተሞከረ ያልተሳካ መፈንቅለ መንግስት ሳያበቃ ተባብሶ መቀጠሉን የዘገበው ቢቢሲ፣ ከአመቱ መጀመሪያ አንስቶ በአገሪቱ ከ600 በላይ ሰዎች ለህልፈተ ህይወት መዳረጋቸውንና ከ220 ሺህ በላይ ዜጎችም አገራቸውን ጥለው መሰደዳቸውን አስታውሷል፡፡

- አንድ ጠርሙስ ኦክስጂን 27.99 ዶላር ይሸጣል

በቻይና የአየር ብክለት እየተባባሰ መምጣቱን ተከትሎ፣ ቪታሊቲ ኤር የተሰኘው የካናዳ ኩባንያ ከተራሮች ላይ ተወስዶ በጠርሙስ የታሸገ ንጹህ አየር ለቻይናውያን እየሸጠ እንደሚገኝ ዘ ኢንዲፔንደንት ዘገበ፡፡
በዚህ ወር መጀመሪያ የቻይና የአየር ብክለት መጠን ከፍተኛው ደረጃ ላይ መድረሱንና ለጤና ጎጂ መሆኑ ታምኖበት በመዲናዋ ቤጂንግ ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉና የግንባታ ስራዎች እንዲቋረጡ መደረጉን ያስታወሰው ዘገባው፣ ቪታሊቲ ኤር የተሰኘው የካናዳ ኩባንያም ከሰሞኑ የታሸገ አየር ለቻይና ማቅረብ መጀመሩን ገልጧል፡፡
ኩባንያው ፕሪሚየም ኦክስጂን በሚል አሽጎ የሚሸጠው ንጹህ አየር በጠርሙስ 27.99 ዶላር እየተቸበቸበ ነው ያለው ዘገባው፣ የኩባንያው ተወካይም ገበያው እንደደራላቸውና ምርቱ በቻይና ገበያ ውስጥ ከፍተኛ ተፈላጊነት ሊያገኝ መቻሉን መናገራቸውን አስታውቋል፡፡
የኩባንያው ተወካይ ሃሪሰን ዋንግ እንዳሉት፤ ኩባንያው በመጀመሪያ ዙር ለቻይና ገበያ ያቀረበው 500 ጠርሙስ የታሸገ ንጹህ አየር ተሸጦ ያለቀ ሲሆን፣ ተጨማሪ 700 ጠርሙስ የታሸገ ንጹህ አየርም በሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ቻይና ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

     በብሩንዲ ሶስት ወታደራዊ ጣቢያዎች ላይ በመንግስት ተቃዋሚዎች በተፈጸመ ጥቃት በርካታ ዜጎች መሞታቸውን ተከትሎ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ዛይድ ራድ አል ሁሴን አገሪቱ ዳግም ወደ አስከፊ የእርስ በርስ ጦርነት እያመራች ነው ሲሉ ማስጠንቀቃቸውን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘገበ፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በብሩንዲ የተለያዩ አካባቢዎችና በመዲናዋ ቡጁምቡራ እየተባባሰ የመጣው ግጭት እንደሚያሳስባቸው የገለጹት አል ሁሴን፣ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ፔሪ ንኩሩንዚዛ ለሶስተኛ ዙር የስልጣን ዘመን በምርጫ እንደሚወዳደሩ መግለጻቸው የቀሰቀሰው ቁጣ በተቃዋሚ ሃይሎችና በመንግስት ደጋፊዎች መካከል ለወራት የዘለቀ ግጭት መፍጠሩንና በርካታ ዜጎች መሞታቸውን አስታውሰዋል፡፡
የፖለቲካ መሪዎችና ከፍተኛ ባለስልጣናትን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ትርጉም ያለውና አካታች የሆነ ውይይት በማድረግ በብሩንዲ የተከሰተውን ግጭት ለመግታትና አገሪቱን ከከፋ ጥፋት ለመታደግ እንዲንቀሳቀሱም ጥሪ አቅርበዋል።
ባለፈው ሳምንት አርብ እጅግ የከፋ የተባለ ግጭት መከሰቱንና በመዲናዋ ቡጁምቡራ በሚገኙ ሶስት ወታደራዊ ጣቢያዎች ላይ በመንግስት ተቃዋሚዎች በተፈጸመ ጥቃት 79 ያህል የመንግስት ተቃዋሚዎችና ስምንት ወታደሮች መሞታቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡
አገሪቱ ለረጅም አመታት ከዘለቀውና ከፍተኛ እልቂት ካስከተለው በጎሳ የተከፋፈለ የእርስ በርስ ጦርነት የወጣችው ከአስር አመታት በፊት እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ ፕሬዚዳንት ንኩሩንዚዛ ስልጣናቸውን ለማራዘም ማሰባቸው የፈጠረው ተቃውሞና አመጽ፣ አገሪቱን ወደቀድሞው አስከፊ የእርስ በእርስ ጦርነት ሊያስገባት ይችላል የሚል ስጋት መፍጠሩን ገልጧል፡፡
ካለፈው ሚያዝያ ወር አንስቶ የተከሰተው ግጭት፣ በፕሬዚዳንቱ ላይ በተሞከረ ያልተሳካ መፈንቅለ መንግስት ሳያበቃ ተባብሶ መቀጠሉን የዘገበው ቢቢሲ፣ ከአመቱ መጀመሪያ አንስቶ በአገሪቱ ከ600 በላይ ሰዎች ለህልፈተ ህይወት መዳረጋቸውንና ከ220 ሺህ በላይ ዜጎችም አገራቸውን ጥለው መሰደዳቸውን አስታውሷል፡፡

 በመላ አገሪቱ የተቃውሞ ሰልፎች ተደርገዋል

ባለፈው ሳምንት ሁለት የፋይናንስ ሚኒስትሮችን ከሃላፊነታቸው ያነሱት የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ፤ የአገሪቱን ኢኮኖሚ የሚያደቅ ተግባር እየፈጸሙ ነው በሚል ባለፈው ረቡዕ አደባባይ ወጥተው ተቃውሟቸውን ያሰሙ በሺህዎች የሚቆጠሩ ደቡብ አፍሪካውያን ፕሬዝዳንቱ ከስልጣን እንዲወርዱ መጠየቃቸውን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
በርካታ ደቡብ አፍሪካውያን በአገሪቱ ሙስና ተስፋፍቷል፣ በገዢው ፓርቲ የስልጣን መተካካት ላይ አግባብ ያልሆነ ተግባር ተፈጽሟል በሚል ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ መቆየታቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ በሺህዎች የሚቆጠሩ የአገሪቱ ዜጎች ረቡዕ ዕለት ጆሃንስበርግ ውስጥ ባደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ ፕሬዚዳንቱ ከስልጣን እንዲወርዱና በመንግስት የሚከናወኑ የሙስና ድርጊቶችን የሚገታ ጠንካራ ንቅናቄ እንደጀመር መጠየቃቸውን አስታውቋል፡፡
በዕለቱ ከጆሃንስበርግ በተጨማሪ በመላ አገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተቃውሞ ሰልፎች መደረጋቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ በኬፕታውን በተከናወነው ተመሳሳይ የተቃውሞ ሰልፍ የተሳተፉ በሺህዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ዙማ ከስልጣን መውረድ አለባቸው የሚል መፈክር ሲያሰሙ መዋላቸውን ጠቁሟል፡፡
ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ የቀድሞውን የአገሪቱ የፋይናንስ ሚኒስትር ናላላ ኔኔን ከሃላፊነታቸው ማንሳታቸው ከፍተኛ ትችት እንዳስከተለባቸውና ውሳኔያቸው የገበያ ቀውስ መፍጠሩንም አስታውሷል፡፡

- ላለፉት 12 አመታት የሚገዳደራትአልተገኘም
- ለኑሮ የማትመቸዋ የአለማችን የመጨረሻዋ አገር ኒጀር ናት

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም በየአመቱ ይፋ በሚያደርገው ሂዩማን ዲቨሎፕመንት ኢንዴክስ ሪፖርት ውስጥ ለኑሮ ምቹ የሆኑ የአለማችን አገራት ዝርዝርን ላለፉት 11 አመታት በቀዳሚነትን ይዛ የዘለቀችው ኖርዌይ፣ ዘንድሮም በቀዳሚነት መቀመጧን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡
አማካይ የህይወት ዘመን፣ ትምህርት፣ ገቢ እና የኑሮ ደረጃን በመስፈርትነት በማስቀመጥ የአለማችንን አገራት እየገመገመ ደረጃ የሚሰጠው ተቋሙ፤ ኖርዌይ በሁሉም መስፈርቶች ከፍተኛውን ውጤት በማስመዝገብ ዘንድሮም ለኑሮ ምቹዋ አገር ለመሆን መብቃቷን አስታውቋል፡፡
በኖርዌይ አማካይ የህይወት ዘመን 81.6 አመት ሲሆን ጠቅላላ አመታዊ ብሄራዊ የነፍስ ወከፍ ገቢዋም 64ሺህ 992 ዶላር መድረሱንና ይህም በተቋሙ ጥናት ከተካተቱት 188 ያህል የአለማችን አገራት በቀዳሚነት እንዳስቀመጣት  ዘገባው ገልጧል፡፡ ከኖርዌይ በመቀጠል እስከ አምስተኛ ደረጃን የያዙት የአለማችን አገራት አውስትራሊያ፣ ስዊዘርላንድ፣ ዴንማርክና ኒዘርላንድስ ናቸው ተብሏል፡፡
ለኑሮ ምቹ ያልሆኑ አምስት የአለማችን አገራት የተባሉት ደግሞ ኒጀር፣ መካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ኤርትራ፣ ቻድ እና ብሩንዲ ናቸው፡፡

    በአምቦ ዩኒቨርሲቲ በጐልማሶችና ማህበረሰብ ልማት ትምህርት ክፍል መምህርና የትምህርት ክፍሉ ሃላፊ በሆኑት በአቶ ያዴሳ ቶሎሳ ወዬሳ የተዘጋጀውና በትምህርት በምርምርና በአተገባበር ሂደቶች ላይ ትኩረት አድርጐ የተሰናዳው “አጠቃላይ የትምህርት እና የስራ ላይ ምርምር ዘዴዎችና አተገባበር” የተሰኘ መጽሐፍ ገበያ ላይ ዋለ፡፡ መጽሐፉ በማንኛውም ደረጃ ለሚገኙ ተማሪዎች፣ ለመመረቂያ ጽሑፍ ዝግጅትና በማንኛውም የስራ መስክ በተግባራዊ የስራ ላይ ምርምር ለተሰማሩ እንዲሁም ሊሰማሩ ለሚሹ ባለሙያዎችና መምህራን እንደ ማጣቀሻ ማኑዋል ሆኖ እንደሚያገለግልም ተጠቅሷል፡፡ በሁለት ክፍሎች የተዘጋጀውና በርካታ ምዕራፎችን ያካተተው መጽሐፉ፤ በ204 ገጾች የተመጠነ ሲሆን በ80 ብር ለሽያጭ ቀርቧል፡፡  

የአዕምሮ ህክምና ስፔሻሊስትና በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የአዕምሮ ህክምና ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር በሆኑት ዶ/ር ሞገስ አየሁ የተፃፈውና በአዕምሮ ህመምና ህሙማን ህይወት ላይ ትኩረቱን ያደረገው “ድፍርስ” የተሰኘ መጽሐፍ ሰሞኑን ለንባብ በቅቷል፡፡
በ18 ክፍሎች የተዘጋጀው ይኸው መጽሐፍ፤ ስለ አንጐል መታወክና መንስኤዎቹ፣ ስለ አዕምሮ ህመም ምንነት፣ አዋቂና ህፃናት ላይ ስለሚከሰት የአዕምሮ ህመም፣ ስለ ኦቲዝምና ሌሎች ከአዕምሮ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ጥልቅ ትንታኔን ይዟል፡፡ በመጽሐፉ ሽፋን ላይ አስተያየቱን ያሰፈረው ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ፤ “ዶክተሩ የፃፉት ይህ መጽሐፍ የሚጠቅመው ለአዕምሮ ህሙማንና ለአሳታሚዎች ብቻ ሳይሆን በዘርፉ ኪናዊ ስራ ለሚሰሩ ገጣሚያን፣ ልቦለድ ደራሲያንና ፊልምና ቴአትር ለሚሰሩም የጥበብ ሰዎች ግብአት የሚሆን ነው” ብሏል፡፡ በ184 ገጾች የተሰናዳው መጽሐፉ፤ ለአገር ውስጥ በ75 ብር፣ ለውጭ አገራት በ20 ዶላር ይሸጣል። 

በደራሲ ዘውዱ አበጋዝ ተተርጉሞ በተሻለ አሰፋ የተዘጋጀው “ቆንጆዎቹ” የተሰኘ ቲያትር ከ15 አመታት በኋላ ወደ መድረክ የተመለሰ ሲሆን ዛሬ በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ትያትርና ባህል አዳራሽ ለተመልካች ይቀርባል፡፡
በስደት ህይወት ላይ የሚያጠነጥነውና የታችኛውን የህብረተሰብ ክፍል ይዳስሳል የተባለው ይኸው ቲያትር፤ የ2፡15 ርዝማኔ እንዳለው ታውቋል፡፡ በቲያትሩ ላይ ወለላ አሰፋ፣ ትእግስት ግርማ፣ ሰለሞን ሐጐስ፣ ይገረም ደጀኔና ሕሊና ሲሳይን ጨምሮ ሌሎች አንጋፋ ተዋንያን ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡

Saturday, 19 December 2015 10:42

አሴዋ ሁሌም በልባችን ነህ!!

አይረሴ ራዕይ
እኛማ እንቆጥራለን
ዛሬም ሙሉ ሳቅክን
ያልተሸራረፈ ሙሉ ፈገግታህን
እንዳቀፍን አለን በየምላዳችን የነገ ሰብልህን
አሴ ኩራ ኩራ፣ ባለህበት ኩራ
ብርሃኑ ያዘምራል፣ ያሳብህ ተራራ
ዓመቱማ ያልፋል ወደፊት ገፍትሮን
ዘመኑ ቢሸብት፣
አይረሴ ራዕይ፤ ነጭ ፀጉር የለው
ከቶ መች ይረሳል
ህልምህ የወይን ጠጅ ሲነጋ ይበስላል፡፡
የነበረህና የነበረን ሀሳብ፣ እያደር ይጠራል፡፡
ስምህ ማዘርዘሩ፣ መንፈስህ መብቀሉ
ዕምነት ፍልስፍና ውልና ፈትሉ
ዕውቀትና ትጋት ብርሃን ፊደሉ
ሩቅ እንዳሰብነው ሩቅ ነው ገድሉ
ዛሬም አለ ቃሉ፣
ያውም በርቶ ፈክቶ፣ እስከማዕዘኑ፡፡
አውቃለሁ ታውቃለህ
የመከረኛ አገር መከሯ እስኪገባ
መከራ መብዛቱ
ዕውን ቢሆን እንኳ
ራዕይህ አለ ምስክር ይቆማል፤ ቀኑ ለመንጋቱ፡፡
አይቆምም ጉዟችን ባይቆምም ሥጋቱ
አይደለም ራዕይ ብሳና ዛፍ ግንድ
ሽበት አይወርሰውም፤ የዕድሜ ዘመን ግርድ
አይረሴ ራዕይ የቸገንክበትን
የፍል ዕውቀት እርሻ፣ የዓለም አሂዶህን
ታያለህ ማሳውን፡፡
አሴ ኩራ ኩራ
ብርሃን ያዘምራል ያሳብህ ተራራ
የራዕይ ተራራ !!
(ለአቶ አሰፋ ጎሳዬ ሙት አመት መታሰቢያ)
ነ.መ


Saturday, 19 December 2015 10:32

ቁጣ ማለስለስ

አጨሳለሁ!...ማለቴ የሠርጌ እለት ማጨስ እፈልጋለሁ፡፡
አንሙት ጓደኛዬ ሰሞኑን ከመካኒክነት ስራው ጋር ተያያዥነት ያለው ቁጣ ማለስለስ የሚል ስልጠና ወስዷል፡፡ በዚህ ስልጠና መሰረት ቁጣዬ እንዳይነድ ልተገብር ስለሚገባኝ የተለያዩ የቁጣ ማለስለሻ ዘዴዎች ነግሮኛል፡፡ ከዘዴዎቹ መሃከል ማጨስ ይገኝበታል፡፡
የሠርጌ እለት ለትዳር ጠይቄያቸው “እምቢ” ያሉኝ አስራ አንድ ሴቶች ድንገት በአይኔ ላይ ድቅን ቢሉ ቁጣዬ መንደዱ አይቀርም፤ በጣም ነው ያረዘሙብኝ ይሄን ጐዳና፡፡ ንግስት እልፍኝ እስኪደርስ የሚደረደሩ አሳላፊዎች መሆናቸው በገባኝና “እለፍ!” ከማለታቸው በፊት አሳልፉኝ ብዬ በጠየቅኩ፡፡
ብቻ እነርሱ ድንገት ትውስ ካሉኝ ቁጣዬ ሊነድ ስለሚችል ለስለስ ለማድረግ የአንሙቴን ምክር ተግባራዊ ማድረግ ይኖርብኛል፡፡ በክብር ከሚጠራው ታዳሚ ፊት ቁጣዬን ለማለስለስ ብዬ ማስቲካ አላኝክም፡፡ ረዘም ያለ የእግር ጉዞ ማድረግ በጭራሽ አይታሰብም፤ ያለኝ አማራጭ ማጨስ ነው፡፡ ምን? ሲጃራ…አላደርገውም! እሺ ሊነድ የሚችለው ቁጣዬን እንዴት ላለስልሰው?
ምን አስጨነቀኝ ከዚህ ሁሉ ሙሽራይቱን ባጨሳትስ!? ቁጣ የእሳት አመድ ስለሆነ ታምቆ ይቆያል፡፡ ጠንካራ ሲሆን ሃይለኛ ችግር ይፈጥራል፡፡ በስራ፣ በፍቅርና በእለተ ተእለት ግንኙነት መሃከል ጣልቃ እየገባ ይበጠብጣል፡፡ በተጨማሪም ቁጣ የእሳት ፍም ስለሆነ አልፎ ወደ ትዳሬ ከዘለለ ጥሩ አይመጣም፡፡ ለትዳር ጠይቄያቸው እንቢ ባሉኝ አስራ አንዱ ሴቶች የተፋፋመው ቁጣዬ፣ ወደ ትዳሬ ተላልፎ ቤቴ ሲነድ ማየት አልሻም፡፡
***
“ዢያኛ…ኩኛ” ቁጣ ምንድነው? ቁጣ ምን ያመጣል?
ቁጣ ውስጣችሁ ሲኖር፤ እንዲሁ ይታወቃችኋል፡፡ ምቾት አይሰማችሁም፤ በሆነ ባልሆነው ትረበሻላችሁ። ደረታችሁ ጥብቅ፣ ልባችሁ ምትት…ምትት፣ ጡንቻዎቻችሁ ውጥርጥር፣ እግሮቻችሁ ድክም፣ ላብና ራስ ምታት ይፈራረቅባችኋል፡፡ ጩሁ ጩሁ፣ እቃ ስበሩ ስበሩ፣ ሰው ተማቱ ተማቱ፣ ተሳደቡ ተሳደቡ፣ አልቅሱ አልቅሱ፣ ተጋፉ ተጋፉ ይላችኋል፡፡ ለራስ በቂ የሆነ ጊዜ አለመስጠት ለቁጣችሁ መንደድ መነሻ ይሆናል፡፡ መዳረሻው ደግሞ ይከብዳል፡፡ ሃይለኛ ቁጣ ሲነድ “ምን ይሻለኛል…ልፈንዳ ይሆን? ልብረር ይሆን?” ያሰኛል፡፡
በተለይ እናትና አባት ሲጣሉ ተወርውሮ ከግድግዳ እየተጋጨ የሚሰባበረውን የቤት እቃ ሲለቃቅም ያደገ ልጅ ቁጣን መቆጣጠር ይከብደዋል፡፡ ንዴት ሁኔታዎችን ሲያባብስ እንጂ የማንንም ችግር ሲፈታ ታይቶም ተሰምቶም አይታወቅም፡፡ “ማሂቲያ” ይሄን መረዳታችሁን ቁጣን ለማለስለስ ያግዛችኋል፡፡
“ምን አይነት ቆሻሻው ነህ?”
“ልታሞኘኝ ትፈልጋለህ እንዴ?”
“ግድ የለሽ!”
“እረፊ!...ልጐዳሽ እችላለሁ”
“ይሄ አካባቢ በጣም አስጠልቶኛል”
ተቃራኒ የሆኑ አስተሳሰቦችን እንድንከተል ጫና ስለሚያሳድሩብን እንዲህ አይነት ንግግሮችን ልናስወግድ ይገባናል፡፡ “የሚወራው መጥፎ ነገር ሁሉ እኔን በማስመልከት ነው” ብለን ልናስብ አይገባም፡፡ አለበለዚያ በተወራው ሁሉ መታመማችን ነው፡፡ ስለ እኛ በጐ በጐውን ከሚናገሩ ሰዎች ልንርቅ አይገባም፡፡
“ሚፊቺሚ” “እኔ ፍፁም ነኝ!” ይሄ አስተሳሰብ ፍፁም ቁጠኛ እንድትሆኑ በአያሌው ይተባበራችኋል፡፡ የሰው ፍፁም የለውም! ወይ ማግኘት አልያም መሞት የሚባል ነገር አይሰራም፡፡ ማግኘት ካላገኙም እንደገና ለማግኘት መኖር፡፡ ለምን ትቸኩላላችሁ? ሞት እንደው ሳትጠሩትም ቢሆን መምጣቱ አይቀርም፡፡
“ዩኒ ሚት” ቁጣን ለማንደድ መንገድ ጠራጊ የሆኑትን ተቃራኒ አስተሳሰቦች እንዴት ማስወገድ እንደምትችሉ ላሳያችሁ…
የሆነ ሰው አፍጥጦ ሲመለከታችሁ “ለምን እንዲህ አፍጥጦ ያየኛል? ይሄኔ በሆዱ ሲያስጠላ እያለኝ ነው” እያላችሁ ከማሰብ “አፍጥጦ እያየኝ ነው፤ነገር ግን ምን እያሰበ እንደሆነ አላውቅም” ማለት ይሻላችኋል፡፡ “ለምንድነው ጣል ጣል የሚያደርጉኝ?” ከማለት “አንድ ቀን ውድድድ…ያደርጉኛል” ብሎ ማሰብ፡፡ “ስለ እኔ ምንም ግድ አይሰጣትም፤ የሆነች ግድ የለሽ!” ከምትይ “በራሷ ጉዳይ በጣም ስለተወጣጠረች ረስታኛለች” ማለቱ አይበጅሽም ወይ?
“እኔ ቁጣ የለብኝም፤ ቁጣዬ የሚነደው ሰዎች ተልካሻ የሆነ ነገር ሲያደርጉ ሳይ ነው” የምትል ከሆነ፡፡ ከውጪ መጥቶ ይስፈርብህም ከውስጥህ ይንደድብህም ንዳድ እንደው ንዳድ፤ ቁጣም እንደው ቁጣ ነው፡፡
“ሺን ሹአ” ቁጣ ሲነድ ከማይሆን ቦታ ይጥላችኋልና ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ አለባችሁ፡፡ ቁጣዬ ሲነድ መቆጣጠር ይከብደኛል ከምትሉ ቀድሞ መንገድ ጠራጊ የሆኑትን ጉዳዮች መቀናነስ ይጠቅማል፡፡ ለራሳችሁ በቂ ጊዜ ከመስጠት አትቦዝኑ፡፡ አቅሙ ካላችሁ “ዮጋ” ብትማሩ መልካም ነው፡፡ ካልሆነም ስሜቱ ሲሰማችሁ ሙዚቃ ማዳመጥ፣ ቴሌቪዥን ማየት (ከዜና በስተቀር)፣ ማስቲካ ማኘክ፣ ማሽላ ማፈንዳት (ፈንዲሻ) ወይም የፈነዳውን መብላት፣ ፎቶ መነሳት (እየሳቃችሁ ቢሆን ይመረጣል) እና እየደጋገማችሁ ምስር ክክ! ምስር ክክ! ማለት ወዘተ…፡፡
“ሁጂን ቹኣ?!” ሚስቴ በጩኸት…”ከስራ የምትወጣው ስንት ሰአት ላይ ነው?!” ስትለኝ “ቲሞቻሚሽ” “ቆይ መጣሁ ማሬ” እላትና ከነደደው ቁጣዬ ለመለስለስ ሽንት ቤት ገብቼ ለሁለት ሰአታት ያህል በረዥሙ አየር አስባለሁኝ፡፡ ለስልሼ ስጨርስ ተመልሼ እሄድና “ሁሻቺ” “ለምን እንዲህ ብለሽ ጠየቅሽኝ? እስቲ ቁጭ በይና ባነሳሽው ሃሳብ ዙሪያ እንወያይበት” ብዬ እርሷንም አለሰልሳታለሁኝ፡፡
ቁጠኛ ብሆን ገና ጥያቄውን ከማንሳቷ “ሺን ሲሺ ፒካ ሲኦ!” “ለምን አስፈለገሽ? በመሃከላችን መተማመን ጠፋ ማለት ነው?” እያልኩ አፍ አፏን እላታለሁኝ፡፡ እሷም እየጮኸች መልስ ትሰጠኛለች፤ቤታችን በአንድ እግሩ ቆመ ማለት አይደለም? “ላሼ ላሼ” የራስን ብቻ ማዳመጥ ሳይሆን መደማመጥም ያስፈልጋል፡፡
በፈጠራችሁ “እኔ መቼም ቢሆን ተወዳጅ ሰው ልሆን አልችልም!” አትበሉ፡፡ “ሁዋል ሲኛ” ሰው አንደኛ የሚወድላችሁ ነገር ቢኖር እራሳችሁን መውደዳችሁን ነው! የማትወዱት ማንነታችሁን ማንም አይወድላችሁም!
“ሲሞ ሺሞ ሺኝ” በትውልዳችሁ እርግማን እንዳይመጣ ሌሎችንም መውደድና መንከባከብ ተማሩ፡፡ የጥቁር ህዝቦች እናት ምድር ኢትዮጲስ፤ የበኩር ልጆቿ ሌሎችን ልክ እንደራሳቸው መውደድና መንከባከብ ሊማሩ አልቻሉም፡፡ በእነርሱ ምክንያት አምላክ ተቆጥቶ ረግሟት እስከ አሁን ድረስ ክፉኛ ተጐሳቁላለች፡፡ በቀደመው ዘመን ምድሪቱን ከገነት የሚፈሱ ወንዞች ያጠጧታል፤ከእርሷ ዘንድ የሚወለዱት ሁሉ በክርታዝ ጥቅል ነው፡፡ ከሽሉ ውስጥ የደም ጠብታ አይገኝም፤ ንፁህ ውሃ ብቻ! በአምላክ አብዝታ የተወደደች የሰው ዘር መገኛ፡፡
“ላይሙ ዣቲዬ” ታዲያ እንዲህ ሆነ፡፡ በየሜዳው ታርደው የሚጣሉት እንስሳት ደም ነፍስ ወደ ሰባተኛው ሰማይ አብዝቶ ጮኸ፡፡ በተለይ የአንዲት ላምና የበግ ግልገል ደመ-ነፍስ፡፡ አምላክም…
“ከጠይሟ መሬት ዘንድ እሪታ በረከተ፤ የአንዲት ላምና የበግ ግልገል ከደመ ነፍሳቸው “የበደል ወናፋችን ሞላ፤ ፍረድልን!” የሚል እሪታ ከሁሉም አይሎ ይሰማኛል፡፡ እስቲ ወርደህ የጠይሚቱ ልጆች የሆኑት ሀበሻትና ሙካሪብን ጠርተህልኝ ተመለስ!” አለው ለመልዐኩ፡፡
በመልዐኩ መልእክት አድራሽነት ሀበሻትና ሙካሪብ አብረው እንዲመጡ ቢጠሩም፣ ሙካሪብ አዲስ ለሚሰራው ጐጆ ማጣበቂያ እንዲሆነው በማሰብ የሰጐን እንቁላሎችን እየሰባበረ ስለነበር ሳይሄድ ቀረ፡፡ ሀበሻት ብቻውን መጥቶ ከአምላክ ፊት ቆመ…
“የኢትዮጲስ ልጆች፤ ስለምንድን ነው የላሚቱንና የበግ ግልገሉን ቆዳ ደመ - ነፍሳቸው ሳይወጣ በፊት ከላያቸው የላጣችሁት?” አምላክ ሀበሻትን ጠየቀው፡፡
“ወደ ፑንት ወረድንና ግብር አድርሰን ስናበቃ፣ በቅባት የራሱት መዳፎቻችንን ለማፅጃ የሚሆነን እንስሳ በዙሪያችን አላገኘንም፡፡ እናም ከሙካሪብ ተማክረን ከአምባው ላይ ሳር ስትግጥ ያገኘናትን ላም ቆዳዋን ላጥንላት፡፡ ከማረዳችን ቀድመን ቆዳዋን ስናነሳባት፤ ስታጠባው የነበረ እንቦሳዋ ሲጮህ በአንድ ጥፊ ፀጥ አሰኘሁት፡፡ እሜዳው ላይ ተንፈራፈረ፤ ድፍት ሳይል አልቀረም፡፡ እርሱን እርሳው፡፡ አሀሀሀሀ! ይገርምል አምላክ፤ ላሚቱን ልጠን ስናበቃ ግልጥ አላለልን መሰለህ። ለካንስ የላሚቱ ቆዳ ልስላሴው መዳፍ ለመጥረግ አይበጅም ኖሯል፤ አሀሀሀ…” እያስካካ መለሰለት፡፡
ሀበሻት ቀጠለ….”ለጥቆ ካለው ቀዬ እልፍ እንዳልን ማለፊያ ጠጉር ያለውን ግልገል በግ ስናገኝ ቆዳውን ገፈፍንለትና መዳፎቻችንን አፀዳን፡፡ ጨዋታ ይዞን ስለነበር ከነ ነፍሱ፤ በህይወት እያለ ቆዳውን መግፈፋችን ትዝም አላለን፡፡ በኋላ ላይ እንደ ላሚቱና እንደ እንቦሳዋ እርሱም ተደፋ” አለው፡፡
አምላክ “ስለምን ቆዳቸውን መላጥ አስፈለገ? እንደ ከዚህ ቀደሙ እጆቻችሁን እንስሶቹ በህይወት ሳሉ በላያቸው አትጠርጉም ነበር ወይ?” ሲል ጠየቀው፡፡
ሀበሻት “ኤዲያ፤ ኖሩ አልኖሩ ምን አባታቸው ይሰራሉ?! ሲል መለሰለት፡፡
“ሺን ሲሺ ፒካ ሲሜ ቱዪ ሾማ ኦኦ!!! ኦ!!! ኦ!! ኦ!...”
በሙካሪብና ሃበሻት ግድ የለሽነት የአምላክ ቁጣው ነደደ…
“ሳይሞቱ፤ በህይወት እያሉ ቆዳቸው ይላጥ፡፡ ሁለቱም ከጉልበታቸው የሚወጣ፤ ዘራቸው በሙላ ቆዳ ቢስ ይሁን!” ሲልም ተራገመ፡፡
ከዛን ጊዜ ጀምሮ አትችሉም፡፡ ምንም እንኳን ከገነት እየወጡ ምድሪቱን የሚያረሰርሱት ወንዞች እስከ አሁን ቢኖሯችሁም፤ የምትዋለዱት የመንፈሳችሁ ቆዳ እንደተላጠ ነውና ስትነካኩ ክፉኛ ያማችኋል፡፡ ለቻይና ሊትረፈረፍ የሚችል የተፈጥሮ ገፀ በረከት ለእናንተ ግን አልበቃችሁም! እስቲ ተዋደዱ? አትችሉም፡፡ ከተዋደዳችሁ መተቃቀፍ አይቀርም፤ መተቃቀፍ ደግሞ የመንፈሳችሁ ቆዳ ስለተነሳ ለእናንተ በሽታ ነው፤ ደዌ፡፡ ስትነካኩ ክፉኛ ያማችኋል!
“ሙኣ ሙኣ!...ሙኣ” “ሲካ ማቼ??...ሲካ…ማቼ??”
እንዴ…ለምን? ለምን?...ለምን አትሉም? አይበቃም! አይበቃም! አይበቃችሁም ወይ? ይህ ብሶት የሚወልደው የአፍሪካውያን ጩኸት መቼ ነው የሚሰማው? በዚህች ምድር ላይ የወንድማማቾች ጥላቻ እስከ መቼ እድሜውን እያራዘመ ይኖራል?
እረኡኡኡኡ…ኡኡኡኡ “እባክህን እባክህን ስለ ፍቅር እረደን??? እረረ!! ደ!!ደ!! ንንን!!” “እረደን” በሉት። “ማኦቲኛ” …ምህረቱን አውርዶላችሁ አሳርዱትና፤ ሳትላጡ ከነመንፈሳችሁ ቆዳ ለመተቃቀፍ ምቹ እየሆናችሁ…ደጋግማችሁ ተወለዱ፤ ዳግም በፍቅር መንፈስ ተወለዱ እንጂ?!
*   *   *
ቁጣ ማለስለስ ከተባለው ትምህርት ላይ ቀንጨብ አድርጐ ይሄን ገራሚ ታሪክ ያወጋኝ አንሙቴ ሲሆን፣ ያስተማራቸው ደግሞ የባቡር ሃዲድ ዝርጋታ የከፍተኛ ትምህርቱን ያጠናቀቀ ቻይናዊ ነው፡፡
ኤዲያ፤ ቻይና ተናገረ አልተናገረ ምን አባቱ ይሰራልኛል?!
ሲጀመር የቻይናዊና የኢትዮጵያዊ ቁጣ መሃል ሰፊ ልዩነት አለ፡፡ የቻይኖቹ ቁጣ ቀሰስተኛ፤ የሚነደውም ቀስ በቀስ ነው፡፡ ድህነታቸው ላይ ቁጣቸው ነዶ ሰላሳ አመት ሙሉ ሲጐተት ከርሞ ነው ትቷቸው የሄደው፡፡ የእነርሱን አይነት ቁጣ ኑሮዬን እቆጣዋለሁ፡፡
እንደነርሱ ቁጣው ድህነት ላይ አልነደደም እንጂ ኢትዮጵያዊ ድህነቱን ቢቆጣ በአምስት አመት ችግር ድራሹ ይጠፋ ነበር፡፡ አመሉ መሬት ነው! ኮሶ ኮሶ እስከሚለው ድረስ እጅግ ካላስመረሩት፤ የአበሻ ቁጣው አይነድም፡፡
ይቅርበት ኮሶ እንዳታቀምሰው! ኢትዮጵያዊን ነካክተህ መሬት የሆነ ሸጋ አመሉን ካስጣልከው፤ እምር ብሎ ይነሳብሃል! እምር ብሎ ከተነሳ በኋላ ምኑን ልንገርህ? ከቁጣው ንዳድ ብዛት…ከቁጣው ንዳድ ብዛት፤ አህያ ብትሆን እንኳን ክንፍ አውጥተህ ትበራለህ!
ጣልያንን ያበረርነው በቁጣችን፣ ከሰው ሀገር ገብተን የኮሪያን “ኮሚውኒስት” ያበረርነው በቁጣችን፤ መንግስቱ ሃይለማርያምን ያበረርነው በቁጣችን፣ ኤርትራንም ያበረርናት በቁጣችን፡፡ የኢትዮጵያዊ ቁጣው የነደደ እለት ፈጣሪ በኮባ ቅጠል ሸብልሎ ይሰውረኝ፡፡
አወይ እዳ፤ እንግዲህ የሠርጌ እለት ቁጣዬ የሚነድ ከሆነ ሠርገኛውን ከነድንኳኑ ማብረሬ ነው፡፡ እሺ ቁጣዬ በምን ይለስልስ? “ሙሽራይቱን በጥፊ ማጨስ” የሚለው ሃሳብ አልተዋጠልኝም፤ በስንት ዳዴ አግኝቻትማ አላጨሳትም፡፡
እምምም…ወ-ተ-ት …አሹ…ወተት!
ከሙሽሪትና ከእኔ ፊት የሚደረደረው ጠላና ጠጅ አጠገብ በብርሌ ተደርጐ ወተት ቢቀመጥልኝስ? ወተት እንኳንስ ቁጣ መርዝ ያረክስ የለ፡፡ የምን ቁጣ ማለስለስ፤ ስለ ቁጣ ማለስለስ በተማረው መሰረት አንሙቴ የራሱን ቁጣ ማለስለስ ይችላል፡፡ እኔ ግን የሠርጌ እለት ልክ እንደ አያት ቅድመ አያቶቼ፤ ከወተቱ እየተጐነጨሁ ቁጣዬን አረክሰዋለሁ!
ምርጥ ሃሳብ…አሹ ዳይሊጋዳ!
(“ክብሪት” ከተሰኘው የይግረም አሸናፊ
የልብወለድና ወጎች
ስብስብ መጽሐፍ የተወሰደ ከገጽ 40-47 - 2007)