Administrator

Administrator

   ታዋቂው የቴክኖሎጂ ኩባንያ ማይክሮሶፍት፣ ባለፉት ሶስት ወራት ብቻ 3.1 ቢሊዮን ዶላር ትርፍ ማግኘቱን የኩባንያው ዋና ስራ አስፈጻሚ ሳትያ ናዴላ ማክሰኞ ዕለት ይፋ ማድረጋቸውን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘገበ፡፡
ኩባንያው በተጠናቀቀው ሩብ አመት 20.6 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ገቢ ማግኘቱን ያስታወቁት ናዴላ፤ባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ያገኘው ገቢ ግን 22.2 ቢሊዮን ዶላር እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
ማይክሮሶፍት ኩባንያ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ያገኘዋል ተብሎ ከተገመተው በላይ ገቢ ማግኘቱ የተገለጸ ሲሆን ገቢው ሊያድግ የቻለውም የምርታማነትና በቢዝነስ ፕሮሰስ ክፍሉ ያከናወነው ስራ ውጤታማነት እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ ማይክሮሶፍት ባለፉት ሶስት ወራት ከጌሞች ሽያጭ ያገኘው ገቢ በ9 በመቶ ቢቀንስም፣ ከማስታወቂያ ያገኘው ገቢ በአንጻሩ በ54 በመቶ እድገት ማሳየቱ ተነግሯል፡፡
ኩባንያው ባለፈው ሰኔ ወር በ26 ቢሊዮን ዶላር ሊንክዲን የተባለውን ማህበራዊ ድረገጽ መግዛቱን ያስታወሰው ዘገባው፤ ይህም በቀጣይ ገቢውን ያሳድግለታል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቋል፡፡





እስካሁን ከ50 ሺህ በላይ ሰራተኞችን አባሯል

     ባለፈው ሳምንት የተቃጣበትን መፈንቅለ መንግስት ያከሸፈው የቱርክ መንግስት፤ በድጋሚ ተመሳሳይ ሙከራ ሊደረግ ይችላል የሚል ስጋት ውስጥ እንደገባ የተጠቆመ ሲሆን በርካታ ዜጎችን ከተለያዩ የመንግስትና የግል መስሪያ ቤቶች ማባረሩን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል፡፡
የፕሬዚዳንት ኤርዶጋን መንግስት የተቃጣበትን የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ማክሸፉን ተከትሎ በበርካታ የአገሪቱ ከፍተኛ የጦር መኮንኖችና መምህራን ላይ የወሰደው የእስራትና ከስራ ገበታቸው የማባረር እርምጃ፣  በአገሪቱ ተመሳሳይ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ሊፈጸም ይችላል የሚል ስጋት መፍጠሩን ዘገባው ገልጧል፡፡
የኤርዶጋን መንግስት ባለፈው ማክሰኞ፣85 ያህል የአገሪቱን ከፍተኛ የጦር ጄኔራሎችና መኮንኖች ማሰሩን የጠቆመው ዘገባው፤ አንዳንድ ምንጮች ግን የታሳሪዎቹ ቁጥር 125 እንደሚደርስ መናገራቸውን ጠቅሶ፣ይህም መንግስት በከሸፈው መፈንቅለ መንግስት የጦር ሰራዊቱ ሃላፊዎ እጃቸው አለበት ብሎ መጠርጠሩን ያመለክታል መባሉን አውስቷል። መንግስት የጦሩን እንቅስቃሴ ለመግታት በርካታ የጦር ሰፈሮችን በከባድ የጦር መሳሪያዎች ማስከበቡ የተነገረ ሲሆን የአውሮፓ የውጭ ግንኙነት ምክር ቤት የኢስታምቡል ተወካይ አስሊ አይዲንታስባስም፤ መንግስት ይህንን እርምጃ መውሰዱ በድጋሚ የመፈንቅለ መንግስት ጥቃት ይፈጸምብኛል የሚል ስጋት ውስጥ መግባቱን ያሳያል ብለዋል፡፡ቢቢሲ በበኩሉ፤ የፕሬዚዳንት ኤርዶጋን መንግስት ከከሸፈው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ጋር በተያያዘ ከሰሞኑ እየወሰደው ያለው እርምጃ ጥብቅ እየሆነ መምጣቱን በመግለጽ፣ ከስራ ገበታቸው ያገዳቸው ወይም ያባረራቸው ሰዎች ቁጥር ከ50 ሺህ በላይ መድረሱን ዘግቧል፡፡ የአገሪቱ መንግስት እስካለፈው ረቡዕ ድረስ ከመፈንቅለ መንግስቱ ጠንሳሾች ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል የጠረጠራቸውን 15 ሺህ 200 የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና መምህራን ከስራ ገበታቸው ማባረሩንና የሌሎች ተጨማሪ 21 ሺህ መምህራንን የስራ ፈቃድ መቀማቱን የጠቆመው ዘገባው፤ 1ሺህ 577 የዩኒቨርሲቲ ዲኖችም ስራቸውን እንዲለቁ መጠየቁን ገልጧል፡፡
የፖሊስ ባልደረቦች የነበሩ 8 ሺህ ሰዎች፣ 1 ሺህ 500 የገንዘብ ሚኒስቴር ሰራተኞች፣ 2 ሺህ 745 የፍርድ ቤት ዳኞች፣ 8 ሺህ 777 የአገር ውስጥ ሚኒስቴር ሰራተኞች፣ ከ100 በላይ የብሄራዊ ደህንነት ተቋም ባልደረቦች፣ 257 የጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ ሰራተኞችና ሌሎች በርካታ የመንግስት ሰራተኞች ከስራቸው መባረራቸውንም ዘ ቴሌግራፍ ዘግቧል፡፡
የፕሬዚዳንት ኤርዶጋን ፓርቲ የተላላካቸው 300 ሺህ ያህል የኢሜይል መልእክቶች አፈትልከው መውጣታቸውን ተከትሎ፣ የአገሪቱ መንግስት ዊኪሊክስ የተባለውንና መረጃዎቹን ዘርፎ ያሰራጨውን ተቋም ድረገጽ መዝጋቱን የዘገበው ደግሞ ዘ ጋርዲያን ነው፡፡
ስካይ ኒውስ በበኩሉ፤የቱርክ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ቦርድ ባለፈው ረቡዕ ባስተላለፈው ውሳኔ፣ ማንኛውም የአገሪቱ ምሁር ወይም ተመራማሪ ላልተወሰነ ጊዜ ከአገር መውጣት እንደማይችል ማስታወቁንና በውጭ አገራት የሚገኙትም በአፋጣኝ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ጥሪ ማስተላለፉን ዘግቧል፡፡


በህንድ ጉጅራት አውራጃ የሚገኘው ሲንዱ የተባለ ሆስፒታል ሴት ልጆችን ለሚወልዱ ነፍሰጡር እናቶች ያለምንም ክፍያ የማዋለድና የህክምና አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ዘ ቴሌግራፍ ዘገበ፡፡
በአገሪቱ የሚገኙት አብዛኞቹ ነፍሰጡር እናቶች ወንድ ልጅ ለመውለድ እንደሚፈልጉና ሴት ሲወልዱ እንደሚበሳጩና እንደሚያዝኑ የጠቆመው ዘገባው፤ሆስፒታሉም ነፍሰጡሮች ሴት ልጆች ያላቸውን አመለካከት እንዲቀይሩ በማሰብ ነጻ የህክምና አገልግሎቱን እንደ ማበረታቻ መስጠት መጀመሩን አስታውቋል፡፡
በህንድ ለሴት ልጅ ያለው አመለካከት የተዛባ በመሆኑ፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የሴት ልጅ ጽንሶች በውርጃ እንደሚቋረጡ ወይም እንደተወለዱ እንደሚገደሉ የጠቆመው ዘገባው፤ የአገሪቱ መንግስት ይህን የተዛባ አመለካከት ለመቀየር እየሰራ እንደሚገኝና  የሆስፒታሉ ነጻ የህክምና አገልግሎትም የዚህ ጥረት አካል እንደሆነ ገልጧል። በሆስፒታሉ ሴት ልጆችን የሚገላገሉ ነፍሰ-ጡር እናቶች ለህክምና አግልግሎቱ መክፈል ከሚገባቸው 20 ሺህ የህንድ ሩፒ  ነጻ እንደሚደረጉ ተነግሯል፡፡
እናቶች የአገሪቱ መንግስት ከ1994 አንስቶ ተግባራዊ ባደረገው ህግ ነፍሰጡር ሴቶች ከወሊድ በፊት የጽንሱን ጾታ በምርመራ እንዳያውቁ መከልከሉን ያስታወሰው ዘገባው፤ይህም የተደረገው እናቶች ሴት ማርገዛቸውን ቀደም ብለው በማወቅ ጽንሱን ከማስወረድ ለመግታት እንደሆነ አስታውቋል፡፡ ይህም ሆኖ በህንድ ባለፉት ሶስት አስርት አመታት ብቻ 12 ሚሊዮን የሚደርሱ የሴት ጽንሶች በወላጆቻቸው የተዛባ የጾታ አመለካከት ሳቢያ በውርጃ እንዲቋረጡ መደረጋቸው በጥናት መረጋገጡን ዘገባው አመልክቷል፡፡

በአመቱ 211 ጥቃቶች ተፈጽመው፣151 ሰዎች ሞተዋል

    ያለፈው የፈረንጆች አመት 2015፣አውሮፓ በታሪኳ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሽብር ጥቃት ማስተናገዷንና በአመቱ ከፍተኛው የሽብር ጥቃት የተመዘገበው በእንግሊዝ መሆኑን ዩሮፖል የተባለው የአህጉሪቱ ተቋም ማስታወቁ ተዘገበ፡፡
ዓመቱ በአውሮፓ አህጉር በርካታ ቁጥር ያላቸው የሽብር ጥቃቶች የታቀዱበት፣የከሸፉበትና የተፈጸሙበት ነው ያለው ተቋሙ፤በተለያዩ የአውሮፓ አገራት ውስጥ 211 ያህል የሽብር ጥቃቶች መፈጸማቸውን ጠቁሞ፣ 103 ጥቃቶችን ያስተናገደቺው እንግሊዝ ከአህጉሩ ቀዳሚውን ስፍራ መያዟን አስታውቋል፡፡ በአመቱ በፈረንሳይ 72፣ በስፔን ደግሞ 25 ያህል የሽብር ጥቃቶች መፈጸማቸውን ያስታወቀው የተቋሙ የአውሮፓ ህብረት የሽብርተኝነት ሁኔታና አዝማሚያ አመላካች ሪፖርት፤ በአመቱ የጂሃዲስት የሽብር ጥቃት ፈጽመዋል የተባሉ 687 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንና ከእነዚህም ውስጥ 94 በመቶው ጥፋተኛ መሆናቸው መረጋገጡን ገልጧል፡፡
በ2015 በአውሮፓ አገራት ከሽብርተኝነት ጋር በተያያዙ ህገወጥ ድርጊቶች ተጠርጥረው የታሰሩ ግለሰቦች ከ1ሺህ በላይ እንደሆኑና ከእነዚህ መካከልም 424 የሚሆኑት በፈረንሳይ እንደታሰሩ የጠቆመው ሪፖርቱ፤151 ሰዎች በተሰነዘሩ ጥቃቶች መሞታቸውንና ከ360 በላይ መቁሰላቸውን አስታውቋል፡፡




እስካሁን ከ50 ሺህ በላይ ሰራተኞችን አባሯል

     ባለፈው ሳምንት የተቃጣበትን መፈንቅለ መንግስት ያከሸፈው የቱርክ መንግስት፤ በድጋሚ ተመሳሳይ ሙከራ ሊደረግ ይችላል የሚል ስጋት ውስጥ እንደገባ የተጠቆመ ሲሆን በርካታ ዜጎችን ከተለያዩ የመንግስትና የግል መስሪያ ቤቶች ማባረሩን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል፡፡
የፕሬዚዳንት ኤርዶጋን መንግስት የተቃጣበትን የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ማክሸፉን ተከትሎ በበርካታ የአገሪቱ ከፍተኛ የጦር መኮንኖችና መምህራን ላይ የወሰደው የእስራትና ከስራ ገበታቸው የማባረር እርምጃ፣  በአገሪቱ ተመሳሳይ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ሊፈጸም ይችላል የሚል ስጋት መፍጠሩን ዘገባው ገልጧል፡፡
የኤርዶጋን መንግስት ባለፈው ማክሰኞ፣85 ያህል የአገሪቱን ከፍተኛ የጦር ጄኔራሎችና መኮንኖች ማሰሩን የጠቆመው ዘገባው፤ አንዳንድ ምንጮች ግን የታሳሪዎቹ ቁጥር 125 እንደሚደርስ መናገራቸውን ጠቅሶ፣ይህም መንግስት በከሸፈው መፈንቅለ መንግስት የጦር ሰራዊቱ ሃላፊዎ እጃቸው አለበት ብሎ መጠርጠሩን ያመለክታል መባሉን አውስቷል። መንግስት የጦሩን እንቅስቃሴ ለመግታት በርካታ የጦር ሰፈሮችን በከባድ የጦር መሳሪያዎች ማስከበቡ የተነገረ ሲሆን የአውሮፓ የውጭ ግንኙነት ምክር ቤት የኢስታምቡል ተወካይ አስሊ አይዲንታስባስም፤ መንግስት ይህንን እርምጃ መውሰዱ በድጋሚ የመፈንቅለ መንግስት ጥቃት ይፈጸምብኛል የሚል ስጋት ውስጥ መግባቱን ያሳያል ብለዋል፡፡ቢቢሲ በበኩሉ፤ የፕሬዚዳንት ኤርዶጋን መንግስት ከከሸፈው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ጋር በተያያዘ ከሰሞኑ እየወሰደው ያለው እርምጃ ጥብቅ እየሆነ መምጣቱን በመግለጽ፣ ከስራ ገበታቸው ያገዳቸው ወይም ያባረራቸው ሰዎች ቁጥር ከ50 ሺህ በላይ መድረሱን ዘግቧል፡፡ የአገሪቱ መንግስት እስካለፈው ረቡዕ ድረስ ከመፈንቅለ መንግስቱ ጠንሳሾች ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል የጠረጠራቸውን 15 ሺህ 200 የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና መምህራን ከስራ ገበታቸው ማባረሩንና የሌሎች ተጨማሪ 21 ሺህ መምህራንን የስራ ፈቃድ መቀማቱን የጠቆመው ዘገባው፤ 1ሺህ 577 የዩኒቨርሲቲ ዲኖችም ስራቸውን እንዲለቁ መጠየቁን ገልጧል፡፡
የፖሊስ ባልደረቦች የነበሩ 8 ሺህ ሰዎች፣ 1 ሺህ 500 የገንዘብ ሚኒስቴር ሰራተኞች፣ 2 ሺህ 745 የፍርድ ቤት ዳኞች፣ 8 ሺህ 777 የአገር ውስጥ ሚኒስቴር ሰራተኞች፣ ከ100 በላይ የብሄራዊ ደህንነት ተቋም ባልደረቦች፣ 257 የጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ ሰራተኞችና ሌሎች በርካታ የመንግስት ሰራተኞች ከስራቸው መባረራቸውንም ዘ ቴሌግራፍ ዘግቧል፡፡
የፕሬዚዳንት ኤርዶጋን ፓርቲ የተላላካቸው 300 ሺህ ያህል የኢሜይል መልእክቶች አፈትልከው መውጣታቸውን ተከትሎ፣ የአገሪቱ መንግስት ዊኪሊክስ የተባለውንና መረጃዎቹን ዘርፎ ያሰራጨውን ተቋም ድረገጽ መዝጋቱን የዘገበው ደግሞ ዘ ጋርዲያን ነው፡፡
ስካይ ኒውስ በበኩሉ፤የቱርክ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ቦርድ ባለፈው ረቡዕ ባስተላለፈው ውሳኔ፣ ማንኛውም የአገሪቱ ምሁር ወይም ተመራማሪ ላልተወሰነ ጊዜ ከአገር መውጣት እንደማይችል ማስታወቁንና በውጭ አገራት የሚገኙትም በአፋጣኝ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ጥሪ ማስተላለፉን ዘግቧል፡፡


ማርቲን ሉተር ኪንግ
የነጻነት ታጋይ፡ የጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ መሪ እና የሰላም ኖቤል ሽልማት አሸናፊ

‹‹ህልም አለኝ! አንድ ቀን አራቱ እምቦቃቅላ ልጆቼ በቆዳቸው ቀለም (በዘራቸው) ሳይሆን በውስጣዊ ስብእናቸው በሚመዘኑበት ማህበረሰብ ውስጥ እንደሚኖሩ፡፡ ዛሬ ላይ ሆኜ ይህን ተስፋ አደርጋለሁ፡፡››
በጣም አመሰግናለሁ ወዳጆቼ፡፡ የራልፍ አቤናዚን ቅንነት የመላበትና ልብ የሚነካ የማስተዋወቂያ ንግግር እያደመጥኩ ስለ ራሴ ሳስብ ነበር፤ ስለ ማነው እንዲህ የሚናገረው እያልኩ፡፡ መቸም ጓደኛችን በሆነ የኛ የምንለው ሰው አንደበት ስለ መልካምነታችን ሲነገር መስማት ደስ ይል አይደል፡፡ ራልፍ ማለት ለኔ በአለም ላይ በጣም የቅርብ ወዳጄ እምለው ሰው ነው፡፡
(ራልፍ፤ ከማርቲን ሉተርና ከሌሎች ጥቁሮች የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ጋር በመሆን ዘረኝነትንና ጭቆናን በሰላማዊ መንገድ የሚታገለውን ሳውዘርን ክርስቲያን ሊደርሺፕ ኮንፍረንስ  መስርቷል፡፡)
ያ ሁሉ የማስጠንቀቂያ ውርጅብኝ ሳያስበረግጋችሁ ከዚህ ስፍራ የተገኛችሁ ሁሉ፤ በዚህ ምሽት እናንተን በማየቴ ደስ ብሎኛል፡፡ እምቢ አሻፈረኝ! ማለታችሁ የሚያሳየውም እስከ ምንም ድረስ መስዋእትነት ለመክፈል ያላችሁን ቁርጠኝነት ነው፡፡ ይህ እዚህ በሜምፈስ እየሆነ ያለው በመላው አለም እኛን መሰል ሕዝቦች ውስጥ ሁሉ እየሆነ ያለ ነገር ነውና፡፡
እንበልና፤ አሁን የቆምኩት ገና በእምቅድመ ዓለም ጊዜ ላይ ቢሆንና የሰው ዘር ካለፈባቸው የታሪክ ምእራፎቹ ጋር መላው ዓለም ከአጽናፍ አጽናፍ እንደ ሰፊ ትእይንት ፊት ለፊቴ ተሰትሮ እንዳየው እድሉ ተሰጥቶኝ፤ ኃያሉ አምላክም ‹‹እነሆኝ ማርቲን ሉተር ኪንግ፤ እንኪያስ በየትኛው ዘመን ላይ ትኖር ዘንድ ትወድዳለህን@›› ቢለኝ ፤ ምናበ አክናፌን ዘርግቼ አድማሱን እያካለልኩ፤ በጥንቲቱ የግብጽ ምድር ወይም በቀይ ባህር በኩል ጠፍ በረኻውን አቋርጬ ወደ ተስፋዋ ምድር አቀናና ህልቆ መሳፍርት እጹብ ድንቅ ትእይንቶች ከሞሉባት ሀገር እደርሳለሁ። ግን እዚያም አልቆምም፡፡ እንደገና በኦሊምፐስ ተራራ አናት ለማረፍ በጥንቲቱ የግሪክ ሰማይ ላይ እከንፋለሁ፡፡ በዚያም ፕሌቶ፡ አሪስቶትል፡ ሶቅራጥስ፡ ዩሪፒደስ እና አሪስቶፋነስ ረቂቅ አርእስት ጉዳይ በሆነው በምድራዊውና ዘለዓለማዊው ህይወት ዙሪያ ለመወያየት ከሚሰየሙበት ከፓርሴኖን አምባ እታደማለሁ፡፡
(ፓርሴኖን Parthenon ከክ.ል.በ በ5ኛው ክፍለ ዘመን የተገነባና ዛሬም ድረስ በአቴና - ግሪክ ውስጥ ቆሞ የሚታይ ቤተ መቅደስ ነው፡፡ ስማቸው የተዘረዘረው አምስቱ ግሪካዊያን መምህራንና ጸሐፍት የኖሩበት ዘመን ደግሞ እስከ አሪስቶትል ሞት 322 ከክ.ል.በ ድረስ 160 አመታት የሚከነዳ ሲሆን፤ የልሂቃኑ አስተሳሰብና ፍልስፍናም ለምእራቡ አለም ዘመናዊ ስልጣኔ ታላቅ ተጽእኖ የፈጠረ ነው፡፡)
ግን እዚያም አልቆምም፡፡ ወደ ጥንታዊው ገናናው የሮማ ግዛት ዘንድ ተጉዤ በየትየለሌ ነገሥታትና ጎበዛዝት ገዢዎች የተከናወኑትን የእድገትና ስልጣኔ ፈለጎች አስተውላለሁ፡፡ ግን እዚያም አልቆምም፡፡ ደግሞ መለስ ብዬ እስከ ብርሃነ ህሊና (Renaissance) ዘመን እንሳፈፍና የሬኔይሳንስ ዘመንን ዳና፡ ለሰው ልጆች ያበረከተውን የባህልና ሥነ ውበት ብልጽግና በረከቶች እቃኛለሁ፡፡ ግን እዚያም አልቆምም፡፡ እንደገና መጠሪያ ስሜ በስሙ ከተሰየመው ሰውና ዘርማንዘሮቹ ቀዬ ድረስ እዘልቅና ማርቲን ሉተር በዊተንበርግ ቤተ ክርስቲያን መግቢያ በር ላይ የለጠፈውን ዘጠና ዘጠኝ  ፍሬ ነገሮች ዝርዝር ልቅም አድርጌ አነብባቸዋለሁ፡፡
(ማርቲን ሉተር Martin Luther ከ1483 - 1546 የኖረ ጀርመናዊ የሥነ መለኮት ሊቅ theologian ሲሆን ፤ የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያንን አንዳንድ አስተምህሮዎች የሞገተባቸው መከራከሪያ ሀሳቦቹ ለፕሮቴስታንት ጅማሮ ፈር ቀዳጅ ሆነዋል፡፡)
ግን እዚያም አልቆምም፡፡ ወዲህም እስከ 1863 መጥቼ፣ ይይዝ ይጨብጠው አጥቶ ቆይቶ በመጨረሻው የጥቁር ሕዝቦችን ነጻነትና ከመላው ዜጎች እኩልነት የሚያረጋግጠውን ሰነድ Emancipation Proclamation ግድ ለመፈረም የበቃውን አብርሀም ሊንከን ተብዬውን ‹እንግጭግጩ›ን vacilating president ፕሬዚዳንት አየዋለሁ፡፡ ግን እዚያም አልቆምም፡፡ ወደ ቅርቡ የአስራ ዘጠኝ ሰላሣዎቹ አመታት ጠጋ ብዬም ሌላውንና የሀገሩን ዜጎች የከፋ የኑሮ ማሽቆልቆል Bankruptcy ለመታደግ ከጊዜው ጋር ጉሮሮ ለጉሮሮ የተናነቀውን ሰው እያየሁ፡ አንደበተ ርቱእ ድምጹ ሲያስተጋባ እሰማዋለሁ፡... ‹‹የምንፈራው አንዳችም ነገር የለም፤ ራሱን ፍርሀትን ብቻ እንጂ!››
(ማርቲን ለማስታወስ የፈለገው በ1930ዎቹ የአሜሪካዊያኑ የመከራ አመታት “The Great Depression” ወቅት የሀገሪቱ መሪ የነበሩትን ፕሬዚዳንት ፍራንክሊን ሩዝቬልትን ነው፡፡)
አሁንም ግን እዚያም አልቆምም፡፡ ባልተጠበቀ ሁኔታ እጥፍ ዘርጋ ብዬ በርሬ፣ ኃያሉ አምላክ እግር ስር እገኝና እማጸነዋለሁ... ‹‹በሃያኛው ክፍለ ዘመን ሁለተኛው አጋማሽ ጥቂት አመታትን እኖር ዘንድ ምኞቴ ነው፤ ብትፈቅድልኝ ደስታዬ ወደር አይኖረውም!›› በማለት፡፡ እርግጥ ነው ይኼ ያልተለመደ ጥያቄ (‹የከፍታ በረራ›) ስለመሆኑ አያጠራጥርም፡፡ ምክንያቱም አለም ቅጣምባሩ ጠፍቶባታልና፡፡ ሕዝቡ በደዌ ተቀስፏል፡፡ መከራ በምድሪቱ  ዙሪያ ተንሰራፍቷል፡፡ ግራ መጋባት ነግሷል፡፡ ለዚህም ነው እንዲህ ያለውን ምኞት ያልተለመደ የሚያደርገው፡፡ ሆኖም ግን አንድ ነገር እረዳለሁ፤ ይኸውም፡- ምንም ያህል አይን ይያዝ እንጂ። ድቅድቅ ጨለማው በወጉ ሲሰፍር ብቻ ነው ክዋክብቱን ጥርት አድርጎ ማየት የሚቻለው፡፡ የማስተውለውም ይህንኑ ነው፤ እግዚአብሔር በዚህ በሃያኛው ክፍለ ዘመን ለየነገሩ ምላሽ በሚሆን መልኩ ስራውን እየሰራ መሆኑን፡፡ የዚህም ማሳያው ሰዎች ለጥያቄዎች ተገቢ ያልሆነ የግርምቢጥ ምላሽ በሰጡ ቁጥር አጸፋውም የዚያኑ ያህል ሲከሰት በአለማችን ላይ ፍንትው ብሎ እየታየ ነው፡፡ ሳር ቅጠሉ ሕዝቡ ሁሉ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ተነስቷል፡፡ እናም ባሁኑ ጊዜ ሕዝቦች የትም ይሰብሰቡ ጆሀንስበርግ-ደቡብ አፍሪካም፡ ናይሮቢ-ኬንያ፡ አክራ-ጋና፡ ኒው ዮርክ ሲቲ፡ አትላንታ-ጆርጂያ፡ ጃክሰን-ሚሲሲፒ፡ ወይም እዚህ ሜምፈስ - ቴኔሲ የሁላችንም ጩኸት መቼም ቢሆን ያው አንድ ነው - ‹‹ነጻ መሆን እንሻለን›› የሚል። “ We want to be free.”
ሌላው በዚህ ዘመን በመኖሬ የምደሰትበት ነገር ቢኖር፤ እኛ ዛሬ ተገድደን ትግል የገጠምነውና ወደ መፍትኄው ጫፍ እየገፋነው ያለው ጉዳይ፡ የሰው ልጆች ባሳለፉዋቸው ዘመናት ሁሉ ሲላተሙት የኖሩት ችግርን በመሆኑ ነው፡፡ ያም ሆኖ ያለፉቱ ትውልድ የኛን ያህል እንዲጋፈጡት የሚያስችል አስገዳጅ ሁኔታ እና ለውጤት የሚያበቃ እድልና አቅምም አልገጠማቸውም ነበር፡፡ እንግዲህ ከእነርሱ የወረስናቸው ችግሮች አድገው ነው እኛ ዛሬ የተፋጠጥናቸው፡፡ የሰው ልጆች ለዘመናት ዛሬም ድረስ ስለ ጦርነትና ሰላም ያወራሉ፡፡ ከእንግዲህ ግን መወራቱ ማብቃት አለበት፡፡ ምክንያቱም አሁን የደረስንበት ጊዜ እንደስከዛሬው መብትን ለማስከበር ከሰላማዊ ትግል እና ከረብሻና የብጥብጥ ትግል የትኛውን እንምረጥ የምንልበት አይደለም፤ አማራጩ አንድና አንድ ሆኗልና፤ እርሱም ያው ሰላማዊ ትግሉን መቀጠል ወይም ደግሞ በቃ ከናካቴው ጨርሶ በህይወት አለመኖርን መምረጥ ብቻ ፡፡
ያለንበት ጊዜ ይኼ ነው፡፡ ታዲያ ግን በዚህ የሰው ልጆችን ሰብአዊ መብቶች የማስከበር አብዮት ሂደት፡ ጥቁር ህዝቦችን ለረዥም ዘመናት ከተዘፈቁበት አስከፊ ረሀብና ጉስቁልና፡ ማብቂያ ያጣ መከራና እንግልት አላቅቆ ለእፎይታ እሚያበቃቸው አንድ የሆነ መፍትኄ ያውም ባስቸኳይ ማድረግ እስካልተቻለ፤ ምድርና ሞላዋ ሁሉ በአጉል የጥፋት አዘቅት መዋጣቸው አይቀሬ ነው፡፡ ለዚህም ነው እግዚአብሔር በዚህ ዘመን እንድኖር ስለፈቀደልኝ የምደሰተው፤ ቀጣዩን ውጤት ለማየት ስለታደልኩ። ዛሬም በዚህ በሜምፈስ እገኝ ዘንድ ስለተፈቀደልኝ የምደሰተውም ለዚህ ነው፡፡
አስታውሳለሁ እኔም፡ አዎን በደንብ አስታውሰዋለሁ፡ ቅድም ራልፍ እንዳለው፤ ኔግሮዎች ያለ እረፍት ከወዲያ ወዲህ በከንቱ እየባዘኑ፡ ያልበላቸውን እያከኩ፡ ሳይኮረኮሩ እየገለፈጡ የኖሩትን ህይወት፡፡ እነሆ ያ ዘመን አክትሟል፡፡ አሁን መብታችን መከበር አለበት፡፡ ለዚህም ደግሞ እኛም እግዚአብሔር በሰጠን ምድር ላይ ተገቢ ስፍራችንን እናገኝ ዘንድ ቆርጠን ተነስተናል፡፡
እዚህ ያሰባሰበንም ጉዳይ ይኸው ነው። ከየትኛውም አካል ጋር በምንም አይነት የጥፋት ‹አዝማሚያ› ወይም አሉታዊ ንትርክ አልተጠመድንም፡፡ የምንለው ነገር ቢኖር ‹ሰው ለመሆን ቆርጠን ተነስተናል፤ ሕዝብ ለመሆን ወስነናል፤ እኛም የእግዚአብሔር ፍጡሮች/ልጆች ነን፤ ስለዚህም ሌሎች እንድንኖር በሚቀይዱልን መንገድ ብቻ ተገድደን መኖር የለብንም፡፡› ነው፡፡  
እናም እንግዲህ ይህ ዘመን በታሪክ ውስጥ አይነተኛ ጊዜ ሆኖ የሚገኘው በምንድነው@ እኛ ሁላችንም አብረን በመሆናችን ነው፡፡ አብረን ሆነንም በጋራ አንድነታችንን በማስጠበቃችን፡፡ ሁላችሁም እንደምታውቁት፤ ፈርኦን በግብጽ ምድር የነበረውን የባርነት ዘመን ለማራዘም ይጠቀምበት የነበረው አንድ የተለመደ፣ በጣም የተለመደ ቀመር formula ነበረው፡፡ ያም ፎርሙላው ምንድን ነበር@ ባሮቹን እርስ በርሳቸው ማጋጨትና እንዳይግባቡ ማድረግ፡፡ ካልሆነማ መቼም ቢሆን ባሮች ባንድነት ከቆሙ በፈርኦኑ ህልውና ላይ አንድ የሆነ ነገር መከሰቱ አይቀሬ ይሆናል፡፡ እንዲያ ከሆነ ደግሞ ፈርኦኑ ባሮቹን በባርነት ቀንበሩ ስር ኮድኩዶ ለማቆየት አይቻለውም፡፡ ባሮች ባንድነት ሲቆሙ ከባርነት ነጻ የመውጣት ጅማሮ ይሆናል፡፡ ስለዬህ (ውድ የፈርኦን ባሮች አምሳያ ወገኖቼ ሆይ!) አሁን፤ በቅድሚያ ሳንከፋፈል አንድነታችንን በጽናት እንጠብቅና እንቁም!!!
(ማርቲን ሉተር ኪንግ ከመጽሐፍ ቅዱስ ገጾች መኻከል ለምሳሌነት ያዋለው፤ እስራኤላዊያንን በባርነት ይገዛ የነበረውን ፈርኦን ነው፤ ነቢዩ ሙሴ ሕዝቡን ከግብጽ ወደ ‹የተስፋዋ ምድር› እስኪመራቸው - ማርና ወተት ወደምታፈልቀወ ከነዓን ... Canaan.)
ቀጣዩ ሁለተኛ ደረጃ ደግሞ . . .
(ውድ አንባብን፡- ዘመኖቹ በሙሉ እ.ኤ.አ ናቸው)
 ምንጭ - GLENCOE
I have seen the Promised land
              by - Martin Luther King Jr.


    ከዕለታት አንድ ቀን አንዲት መነኩሲት ጎኅ ሲቀድ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሊሄዱ ይነሳሉ፡፡ አንድ ዛፍ አጠገብ ሲደርሱ ተንበረከኩና ሁለት እጃቸውን በልመና መልክ ዘርግተው፤ ፀለዩ፡-
“አምላኬ ሆይ! መቼም አንተ የነገሩህን የማትረሳ፣ የለመኑህን የማትነሳ፣ ሰማይን ያለ ካስማ ያቆምክ፣ የማይዘሩ የማያጭዱትን ወፎች የእለት ምግባቸውን የምትሰጥ ነህ! አሁን እኔ የምለምንህ እጅግ ትንሽ ነገር ናት፡- አምላኬ ሆይ! አደራህን ዕድሜዬን ጨምርልኝ?” አሉት
ወደ ቤተ ክርስቲያን መንገድ ቀጠሉ፡፡ ወደ ቤት ተመልሰውም፣ ይሄንኑ ሲያብሰለስሉ አመሹ፡፡
በሚቀጥለው ቀን ማለዳ ጎኅ ሲቀድ፤ ተነስተው ወደዚያው ዛፍ ስር ሄደው፤ ምናልባት ፀሎቴን አሳንሼው ይሆናል በሚል፤
“አምላኬ ሆይ! ድንገት ከወትሮው ፀሎቴ አሳንሼብህ ይሆናል፡፡ የከዋክብት ብዛቱን፣ የውቂያኖስ ስፋቱን፣ የሙሴ በትሩን፣ የገብርኤል ተዓምሩን፣ የእመቤታችን አማላጅነቷን የምታውቅ፣ የምትሰጥ፤ የነገሩህን የማትረሳ፣ የለመኑህን የማትነሳ፣ ሰማይን ያለ ካስማ ያቆምክ፣ የማያርሱ የማይዘሩ ወፎችን የእለት ጉሮሮ የምትዘጋ፣ ምንም የማይሳንህ አምላክ ሆይ! ካንተ ልግስና አንፃር እጅግ ትንሽ ነገር ነው የምለምንህ፡- እባክህ ዕድሜዬን ጨምርልኝ?”
ለካ ይህን ፀሎታቸውን ሲያደርሱ፣ ሁሌ ቁጥቋጦ ውስጥ ተደብቆ የሚያዳምጣቸው አንድ ተንኮለኛ የቆሎ ተማሪ ኖሯል፡፡
በሚቀጥለው ማለዳ ጎኅ በቀደደ ሰዓት ያ የቆሎ ተማሪ፣ ቀደም ብሎ ዛፉ ላይ ወጥቶ ይጠብቃቸዋል። እሳቸው እንደልማዳቸው መጥተው ፀሎትና ልመናቸውን አሰሙ፡፡ በመጨረሻም፤ “ዕድሜዬን ጨምርልኝ፣አደራ!” አሉ፡፡
ይሄኔ፤ ያ የቆሎ ተማሪ፤
“አንቺ መነኩሲት! ምን ያህል ዕድሜ ልጨምርልሽ?” አለ ድምፁን ጎላ አድርጎ፡፡ መነኩሲቷ ደነገጡ። ፀሎታቸው ተሰማ! ሲያስቡት ሃያም ትንሽ ነው፡፡ አርባም ትንሽ ነው፡፡ መቶም ትንሽ ዕድሜ ነው። በመጨረሻ እንዲህ ሲሉ መለሱ፤ “አምላኬ ሆይ! አንድ ድሃህን ከነጭራሹስ እዚሁ ብትተወኝ፣ ምን እጎዳሃለሁ?!” አሉ፡፡
*             *           *
የዓለም ኢኮኖሚ ጉዳይ አንጋፋ ባለሙያ የሚባለው አዳም ስሚዝ፤ “የሰው ልጅ ፍላጎት ወሰን የለውም” ያለንን ከላየ ያየነው ተረት በአበሽኛ ሳይገለጥልን አልቀረም - Human wants are unlimited ማለት ይሄው ነው፡፡ ዛሬ መጠለያ ጠየቅን፡፡ ነገ ምግብ እንጠይቃለን፡፡ ከነገ ወዲያ መንቀሳቀሻ መኪና እንፈልጋለን። ከዚያ ወዲያ ሰፋ ያለ ግቢ እንዲኖረን እንጠይቃለን፤ ወዘተረፈ ችግሩ የሚመጣውና የሚስፋፋው መሰረታዊ ፍላቶታችን ከተሟላ በኋላ ነው፡፡ ወለሉ ግን መሰረታዊ ፍላጎት ነው፡፡ ኢኮኖሚያችን ከዚህ ወለል በታች ከሆነስ? “እዚሁ ላይ ነው ችግሩ” እንዳለው ነው ሼክስፒር፡፡ “መሆን ወይስ አለመሆን?” የሚባለው ጥያቄ፣ ማናቸውም ጉዳይ ለውሳኔ አሳሳቢ ደረጃ ሲደርስ የሚመጣ ነው፡፡ ውስጥን መፈተሽ አለመፈተሽ፣ እርምጃ መውሰድ አለመውሰድ? ነው ጉዱ! ምኞት ከአቅም በላይ መሆን እንደሌለበት ማንም ጅል አይስተውም። የፍላጎት አቅማችን እየኮሰሰ፣ ምኞታችንን ሲያጫጨው፤ የተስፋ መቁረጥ ጉድባ ውስጥ እንገባለን፡፡ ዜግነታችን ራሱ ያስጠላናል፡፡ የሀገር ፍቅራችን ይሟሽሻል፡፡ ሁሉን ነገር አሉታዊ እሳቤ ውስጥ እንከተዋለን። መንገድ ተሰራ ስንባል የሚሄዱበት እነሱ እንላለን፡፡ ፎቅ ተሰራ፤ ‹የማን ነውና!› ዘር ከዘር ታጋጨ፤ ‹ማን አመጣውና› ዕውነትም ውሸትም አለው ነገሩ፡፡ ህይወታችን የምንግዴ ህይወት ይሆናል፡፡
ሰብዓዊም ሆነ ቁሳዊ ዕሴት ያለን አይመስለንም፡፡ ይሄ የተስፋ ቆራጭነት ሁኔታ (desperado state) ለሀገርም፣ ለህዝብም አደገኛ ነው! አይበጅም! የኢኮኖሚ ችግር፣ የፖለቲካ ድንግዝግዝነትን (obscurantism) ብሎም ጠርዘኝነትንና ዕንፋዊ ጥላቻን ሲፈጥር፤ ‹የመጣው ይምጣ› አስተሳሰብ ይከሰታል፡፡ ማህበራዊ ቀውስ፣ ሥርዓተ-አልበኝነት፣ ምን ዳኝነት፣ ዘራፌነት፣ እኔ ምንተዳዬነት ወዘተ … ይነግሳሉ፡፡ አጠቃላይ ድቀት ይከተላል፡፡ ማንም ስለ ማንም መጨነቁን ይተዋል፡፡ ከዚህ ይሰውረን!!
ዛሬ በሀገራችን የአሳሳች መረጃዎችና ሰነዶች መብዛት ከአቅም በላይ የደረሰ ይመስላል፡፡ የወንጀለኛ መቅጫ ህጉ አለ፡፡ የተጭበረበሩ ሰነዶች ግን ከመፈጠር አላባሩም፡፡ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ፣ በሀሰት የተፈበረከ (Forged) ፈቃድ… ለምሳሌ የህንፃ ፈቃድ፣ የቀበሌ መታወቂያ፣ የግንባታ ፈቃድ፣ የመንጃ ፈቃድ፣ የንግድ ፈቃድ፣ አልፎ ተርፎም የጋብቻ ሰርተፍኬት ሳይቀር በሙስና አዋላጅነት፣ በሽበሽ ሆነዋል! የቀረው የአመፅ ፈቃድ “በፎርጅድ” ማሰራት ብቻ ነው ተብሏል! እጅ ላይ ያለው ችግር በአግባቡ መፍትሄ ባለማግኘቱ፤ ከድጡ ወደ ማጡ መሄዳችን ግድ ሆኗል፡፡ ብዙ ነገር ካንሰር - አከል በሽታ ሆኖብናል። አሰቃቂው ነገር፤ የጉዳዩ ተወናዮች- አለቃውም ምንዝሩም፣ ህግ አውጪውም፣ አስፈፃሚውም፣ መሆናቸው ነው! እርምጃ ማን ይውሰድ? አሰኝቶናል፡፡ ህገ-መንግሥቱንም፣ ህዝቡንም የረሱ አያሌ ሹማምንት ለመኖራቸው ዛሬ ብዙ አያጠራጥርም! ህገ ወጥነት ጣራውጋ ሲደርስ ማጣፊው ያጥራል! “የንጉሡን ፊት አይተህ ፈገግ በል›› የሚለውን ተረት፤ በየደረጃው እንደመሪ መፈክር የያዙ በርካታ ናቸው። ሁኔታዎች ከቁጥጥር ውጪ የሆኑ ለታ ግን ሁሉን ጥፋት በክልል ከማላከክ አልፈን የራስ ተጠያቂነት አፍጦ ይመጣል፡ ‹‹ባሪያ ላግዝሽ ሲሏት መጇን ትደብቃለች›› የሚለው ተረትም በመንግስትና በባለሙያ መካከል ይታያል፡፡
እያደር ዕውን የሆነና የሚሆን ግጭት፣ ፍጭት፣ ወደ ዘረኝነት አቅጣጫ ለመሄድ እርሾው የሚታይና አብሲቱ የተጣለ የሚመስልበት ሁኔታ፣ ብዙው የፖለቲካ ጨዋታ ሲሟጠጥ እንደሚሆነው ሁሉ ወደ ጡንቻ የሚሄድ፣ የደም መፋሰስ ትርዒት ማየት፣ ስለ ብዙ ሰላም ለምታወራ አገር የሚያምር ቁም ነገር አይደለም፡፡ ያለመረጋጋት አስረጅ ይሆናልና ከወዲሁ መገደብና ሰላማዊ መፍትሔ መሻት አስፈላጊ ነው። ቁጣን በቁጣ መመለስ አባዜው ብዙ ነው! የተኙት ብዙዎች፣ የተናደዱትና የነቁት ጥቂቶች ሲሆን፤ የበሠለ አመራር በስሜታዊነት ይዋጣል፡፡ ቁጣ ቦታ የሚያገኘው ይሄኔ ነው፡፡ መጠንቀቅ ይገባል፡፡ ሆድ ሰፊ መንግሥት an eye for an eye (ዐይን ያወጣ ዐይኑ ይውጣ) ከሚል ጥንታዊ ‹ህግ› የተላቀቀ ሊሆን ይገባዋል፡፡ የሠለጠነ ህግ አለውና፡፡ ህግ እንዳለ ከረሳን ግን የአልዛይመር ምርመራ ማረግ ነው፡፡
አሁንም የውስጥ ምርመራ ያስፈልጋል- የከአንገት በላይ ምርመራው ብቻ በቂ አይሆንምና፡፡ ትንሽ ቁስል ሰፍታ ሰፍታ የአገር ህመም የምትሆን ከሆነ ጠቅላላ ምርመራ የግድ ነው፡፡ ክፍሎቻችን ሁሉ በቅጡ ይመርመሩ!!
የሚጠራቀሙ ጥቃቅን ብሶቶች፤ ልክ ጠብ ጠብ እንደሚሉ የውሃ ጠብታዎች ናቸው፡፡ ሲጠራቀሙና አቅም ሲያገኙ ጎርፍ ይሆናሉ፤ ይላሉ የጥንቱ የጠዋቱ የቻይናው ማዖ ዜዱንግ፤ ትግላቸውን ነብሱን ይማረውና፡፡ ጫማ ልክ አልሆን ሲል እግር የመቁረጥ ፖለቲካም አይሠራም ይላሉ፡፡ ጥቃቅንና አነስተኛ ችግሮች፤ ያለ አራሚ እንደሚያድጉ አረሞች ናቸው፡፡ እያደር ዙሪያ ገባውን ዳዋ እንዲውጠው ያደርጋሉና። ከዚያ ‹‹አይጥ በበላ ዳዋ ተመታ›› ነው ተከታዩ፡፡ ሀገራችን ከዚህ ‹‹ውጣ እምቢ፣ ግባ እምቢ›› አጣብቂኝ የሚያወጣት መላ መምታት አለባት፡፡ ቅርቃር ውስጥ ናት - በሰላምና በሰላም ማጣት ራስ-ምታት መካከል። ቅርቃሩ ጊዜያዊ ነው ወይስ አይደለም? መመርመር ነው!! አሁንም ጠብታዎች ጎርፍ፣ ጎርፎች ዥረቶች፣ ዥረቶች ወንዞች እንዳይሆኑ፤ ቅድመ ማስጠንቀቂያዎችን ማየት ደግ ነው፡፡ ላቲኖች፤ ‹‹ጎርፍም ያለ እርከን፤ ምራቅም ያለ ከንፈር አይቆምም›› ያሉት ልብ ማለት ይጠቅመናል፡፡


• ሁሉም የኢትዮጵያ ብሔር፣ የአንድ አባትና እናት ልጆች ነው
• አዳም የተፈጠረው ጎጃም፤ ኖህ መርከቡን ያሳረፈው አራራት ተራራ ላይ ነው
• ስለ ኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አጥንቼ አለሁ ይላሉ …


ኑሮአቸውን በአሜሪካ ያደረጉት ታዋቂው የሥነፅሁፍ ምሁር ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሣ፤ የፃፉት‹‹የኦሮሞና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ›› የተሰኘ አዲስ አነጋጋሪ የታሪክ መፅሐፍ ዛሬ ለገበያ ይቀርባል፡፡ የኦሮሞና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ ማን እንደሆነ በጥናት ደርሼበታለሁ
የሚሉት ፕሮፌሰሩ፤ እስከ ዛሬ የተለያዩ የታሪክ ምሁራን ከተናገሩት ፍፁም የተለየና አዲስ የጥናት
ውጤት ማግኘታቸውን ይናገራሉ፡፡ የሁለቱ ቋንቋዎች አመጣጥም በጥናቱ ተካቷል ብለዋል፡
፡ በሊንከን ዩኒቨርሲቲ በሂዩማኒቲስ የትምህርት ዘርፍ የሚያስተምሩት ፍቅሬ ቶሎሳ ፤ከዚህ ቀደም
‹‹Heaven to Eden›› እና ‹‹The Hidden and untold History of the Jewish People and
Ethiopians›› የሚሉ መጽሐፍትን በእንግሊዝኛ ቋንቋ ያሳተሙ ሲሆን ሁለቱም በኢንተርኔት
“አማዞን” በተባለ የመፅሃፍ ሽያጭ ድረገፅ ላይ ከተፈላጊ መፃህፍት ተርታ ተሰልፈዋል፡፡ በሙያቸው
ፀሃፌ-ተውኔትና የሥነ ፅሁፍ ምሁር ሲሆኑ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ጥልቅ ጥናትና ምርምሮችን
በማድረግም ይታወቃሉ፡፡ አንጋፋው ምሁር ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም በቅርቡ ለንባብ ባበቁት
“አዳፍኔ” የተሰኘ መፅሃፋቸው ላይ፤“የኦሮሞን ታሪክ ሙሉ አደርጎ ሊፅፍ የሚችለው ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ ብቻ ነው” ሲሉ ለብቃታቸው ምስክርነትና ዕውቅና መስጠታቸው አይዘነጋም፡፡ ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሣ በርካታ ቲያትሮችን ለደረክ ያበቁ ሲሆን ከእነዚህም መካከል “ጓደኛሞቹ”፣ “ፍቅር በአሜሪካ” እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡ በቅርቡም ‹‹ላሟ›› የተሰኘ ባለ ሁለት ገቢር ቲያትር ፅፈው ማጠናቀቃቸውንም ተናግረዋል፡፡ ፕሮፌሠሩ ለአጭር ጊዜ ዕረፍት ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበረ ሲሆን ወደ አሜሪካ ከመመለሳቸው በፊት ከአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ ጋር በታሪክ ጥናቶቻቸው ዙሪያ ቃለ ምልልስ አድርገዋል፡


በእንግሊዝኛ ቋንቋ ያሳተሟቸው “Heaven to Eden” እና “The Hidden and untold History of the Jewish People and Ethiopians›› የሚሉት መፃህፍት በአለማቀፍ ደረጃ ሰፊ ተቀባይነት ያገኙበት ሚስጥር ምንድነው? በምን ርዕሰ ጉዳይ ላይ ነው የሚያተኩሩት?
የመፅሐፍቱ ይዘት ነው ወሳኙ፡፡ ተቀባይነት ያገኙት በቋንቋ አጠቃቀም ለአንባቢያን ምቹ ስለሆኑ ይመስለኛል፡፡
በአይሁዶች ታሪክ ላይ የሚያተኩረው መፅሐፍ፤በጉዳዩ ላይ ከተጻፉ ሌሎች መጻህፍትና በተለምዶ ስለ አይሁዶች ከሚታወቀው ምን የተለየ ነገር ይዟል?
ብዙ ጊዜ ስለ አይሁዳውያን ሲወራ፣ቀዳማዊ ሚኒልክ የዛሬ 3ሺህ ዓመት፣ 40ሺህ አይሁዳውያንን ይዞ መጣ የሚለውን ነው የምናውቀው፡፡ ከመጡት መካከል 12ሺህ ያህሉ ንፁህ እስራኤላውያን ናቸው። 28ሺህ ያህሉ እነሱን በሥራ ያገለግሉ የነበሩ ኢያቡሳውያን የሚባሉ ነገዶች ናቸው፡፡ ቀዳማዊ ሚኒልክ ለ12 ሺህዎቹ ልዩ ቦታ ሰጥቷቸው፣ በሀገሪቷ ላይ ካህናት አድርጎ ታቦት እያስቀረፀ፣ ኢትዮጵያ ላይ በዚህ መልክ ሾሟቸው ነበር፡፡ ኢያቡሳውያን ደግሞ ንጉሱን በእጅ ስራና በውትድርና ያገለግሉት ነበር፡፡ ይሄ እንግዲህ አይሁዳውያን ወደ ኢትዮጵያ ያደረጉት ሁለተኛው ፍልሰት ነው፡፡
የመጀመሪያውና ብዙም የማይነገረው የአይሁዳውያን ፍልሰት፣ የእስራኤላውያኑ መሪ ሙሴ በህይወት እያለ አባ ብሄር የሚባል ልኡል ነበር። የሙሴ አማች ነው፡፡ አባ ብሄር የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ሊሆን ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣ፣አይሁዳውያን ተከትለውት መጥተው ነበር፡፡ ምክንያቱም አባ ብሄር ያገባት ልጅ የሙሴ እህት ነበረች፡፡ ሙሴ በወቅቱ ለአባ ብሄር ፅላት ቀርፆ እንዲሁም ቀይ ባህርን የከፈለባትን በትር ሰጥቶት፣ወደ ሳባ ከተማ መጥቶ ነግሷል፡፡ በወቅቱ ብዙ አይሁዳውያንም ተከትለውት መጥተው ነበር፡፡
ሶስተኛው ፍልሰት የምንለው፣የኢራቁ ናቡከደነፆር አሸንፏቸው በሚያሳድዳቸው ጊዜ፤ “ኢትዮጵያ ውስጥ አይሁዳውያን ወገኖች አሉን” ብለው ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል፡፡ አይሁዳውያን በነዚህ መንገዶች ነው ወደ ኢትዮጵያ የመጡት፡፡
 ትክክለኛዎቹ አይሁዳውያን በኢትዮጵያ ያሉት ናቸው የሚሉ ወገኖች አሉ…?
የሃይማኖታቸውን ስርአት፣ መፅሃፍትና ህግጋት ከመጠበቃቸው አንፃር ከሌላ ህዝብ ጋር ስላልተደባለቁ ትክክለኛው ያለው እነሱ ጋ ነው፡፡ ሌሎቹ ወደ አውሮፓ፣ እስያ፣ አሜሪካ የተሰደዱት እነዚህን ነገሮች በተለያዩ ጫናዎች የተነሳ ሙሉ ለሙሉ ጠብቀው አላቆዩትም፡፡ ወደዚህ የመጡት ግን በግድ ባህላችሁን ሃይማኖታችሁን ለውጡ ተብለው በኢትዮጵያውያን አልተረበሹም፤ነፃነት ነበራቸው፡፡ መሬትና ሁሉ ነገር የተመቻቸላቸው ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ነበር፡፡ ሌላ አገር ላይ ቦታ እንዳይኖራቸው ተደርገው በየጊዜው ይሰደዱ ነበር፡፡ እንደውም በሩሲያ ውስጥ በድንገት አይሁዳውያንን የመግደል ድርጊት ይፈፀም ነበር። ሩሲያውያኑ ተሰባስበው፤“ዛሬ አይሁዳውያንን ገድለን እንምጣ” እያሉ ይዘምቱባቸው ነበር፡፡ ወደ መንደራቸው ሄደው አውድመዋቸው ይመለሳሉ፡፡ ማንም ስለማይበቀልላቸው ደማቸው ደመ ከልብ ሆኖ ነበር የሚቀረው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ግን ከተሰጣቸው ክብር የተነሳ በትንንሽ ንጉስነት ጭምር ይሾሙ ነበር፡፡ በርካቶቹም ካህናትና ሊቀ-ካህናት ተደርገው ለአይሁድ እምነት ተሹመል፡፡ ቀጥሎ ደግሞ የሰለሞን ዘር ነን በሚሉት ውስጥም ገብተው፣ ስርወ መንግስት እስከ መመስረት የደረሱ ነበሩ፡፡ በዓለም ላይ አይሁዳውያን ደልቷቸው የኖሩት ኢትዮጵያ ላይ ብቻ ነው፡፡ በጠቅላላው በኢትዮጵያ ሀገራት ማለትም፡- በግብፅ፣ የመን፣ ኑቢያ---ኢትዮጵያ ባስተዳደረቻቸው አካባቢዎች በሙሉ በክብር ተይዘው ነው የኖሩት፡፡ ትልቁ ማስረጃ ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ፣ እናቱ ማርያምና ቅዱስ ዮሴፍ በስደቱ ዘመኑ እኛ ጋ ብቻ ነው ጥገኝነት ያገኙት። በወቅቱ ግብፅ ለሁለት ተከፍሎ ነበር፡፡ አንዱ ክፍል በሮማውያን ቁጥጥር ስር ነበር፡፡ ሁለተኛው የኢትዮጵያ ክፍል ነው፡፡ ኢየሱስ ከመወለዱ ከ880 ዓመት በፊት አማራዎች፤ አማሩላ ደልታ ወደሚባል ቦታ ሄደው፣ አክሱማይት የተባለውን ህፃን ልጅ ዙፋን በመጠበቅ ያገለግሉ ነበር፡፡ በኋላ በ800 ዓመታት ውስጥ አማሩላ ደልታ የሚባል መንደር መስርተው ነበር፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ጋርና ከቅዱስ ዮሴፍ ጋር ሲሸሹ፣ እዚያ ነው ማረፊያ ያገኙት፡፡ ይሄ መፅሃፍ ቅዱስ ውስጥ የለም፤እኛ ግን ከተለያዩ መዛግብት እናገኘዋለን፡፡ በወቅቱ የአካባቢው ንጉስ አማናቱ ተትናይ ይባላሉ፡፡ ከጎጃም ከጣና አካባቢ ነው ወደዚያ የሄደው፡፡ ሌላው አይሁዳውያኑ መፅሐፍ ቅዱሳቸው ሲጠፋባቸው ከኛ ነው የወሰዱት፡፡ አፄ ደንቀዝ የተባለው ንጉሰ ነገስት ነው ከግዕዝ ወደ እብራይስጥ አስተርጉሞ የሰጣቸው፡፡
ትክክለኛውን የአይሁድ ባህልና እምነት በመጠበቅ በኢትዮጵያ ያሉት አይሁዳውያን ብቸኞቹ ናቸው ማለት ይቻላል?
አዎ! ኦሪትን ይዘዋል፡፡ ግን በደማቸው ከኛ ተደባልቀዋል፡፡ በዚህ ምክንያት ነው ሃበሻ የተባሉት። ሃበሻ ማለት የተደባለቀ ነው፡፡ “አበሳ” ያለበት ወይም እንከን ያለበት ማለት ነው፤ ሃበሻ ማለት፡፡ በቀዳማዊ ሚኒልክ ጊዜ የመጡት ከኛ ጋር ተደባልቀው 560 ዓመት ከቆዩ በኋላ በባቢሎን ስደት ጊዜ ሶስተኛዎቹ ሲመጡ፣ነባሮችን ሲያዩአቸው በመልካቸው አይሁዳውያንን አልመስል አሏቸው። ስለዚህ፤“እናንተማ ክልስ ናችሁ፤አበሳ አለባችሁ” ብለው ይሰድቧቸዋል፡፡  ነባሮቹ አይሁዶች ደግሞ፤ “እናንተ ፈላሾች፤እኛ ሀገር አለን” እያሉ ይሰድቧቸው ነበር፡፡ በዚህም “አበሻ” እና “ፈላሻ” የሚለው መጠሪያቸው ሆነ፡፡ “ሀበሻ” የሚለው ቃል እኛን አይወክለንም የምለው ለዚህ ነው፤ሀበሻ አይሁዳውያኑን ነው የሚወክለው፡፡ እኛ የኢትዮጰያ ልጆች ነን፤ ኢትዮጵያውያን ነን፡፡
“በሃበሻነቴ እኮራለሁ” ስንል የከረምነውስ-----ቀለጠ ማለት ነው?
አዎ! እኔ ኢትዮጵያዊ እንጂ ሀበሻ አይደለሁም። ሀበሻ የሚለው ቃል የስድብ ቃል ነው፡፡ እኛን አይወክለንም፡፡ አይሁዳዊ ካልሆነ በስተቀር አንድ ሰው ራሱን “ሀበሻ ነኝ” ብሎ ሊጠራ አይገባውም። ስድብ አያኮራም፡፡ ብዙ ሰው ስለማያውቅ ነው በሀበሻነቴ እኮራለሁ የሚለው፡፡ በአረብኛም ብናየው “የተደባለቀ”፤ “ንፁህ ያልሆነ” ማለት ነው። ይሄ መልካም ቃል አይደለም፡፡ ግን ሀበሻ የሚለው “አበሳ” ከሚለው እንጂ ከአረብኛ የመጣ አይደለም። ሁለቱ አይሁዳውያን መሃል ያለ የመሰዳደቢያ ቃል ነው እንጂ እኛ ኢትዮጵያውያንን አይመለከተንም፡፡
‹‹ኢትዮጵያ›› የሚለውስ ከየት የመጣ ነው?
ኢትዮጵያ የሚለው ‹‹ኢትዮጵ›› ከተባለው ሰው የመጣ ነው፡፡ ኢትዮጵ ማን ነው ካልን፣ በመፅሐፍ ቅዱስ ላይ የተጠቀሰው መልከፀዴቅ የሚባል የሳሌም ንጉሰ ነገስትና ሊቀካህን ነበር፡፡ ይህ ሰው ሃገር ያስተዳድራልም፤ሃይማኖትም ይመራል፡፡ እሱም የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነበር፡፡ ይሄ እንዴት ይሆናል ከተባለ፣ኢየሱስ በምፅአት ቀን ሲመጣ፣ የንጉስ ንጉስ፣ የካህን  ካህን ሆኖ ነው፤መልከፀዴቅም የዚህ ምሳሌ ነው፡፡ ኢትዮጵያን ከዚሁ ጋር ምን ያገናኛታል ሊባል ይችላል፡፡ በጣም የሚያኮራ ግንኙነት አለው፡፡ የመልከፀድቅ ልጅ ኢትኤል ይባል ነበር፡፡ እግዚአብሔር ኢትኤልን ካለህበት የሳሌም ምድር ለቀህ ጣና ላይ ስፈር አለው፡፡ ‹‹ከዚያም ያንተ የልጅ ልጆች፣ እኔ ከ2000 አመታት በኋላ በምወለድበት ጊዜ በኢትዮጵያ  ግዛት ላይ ስለ መወለዴ ኮከብ አሳይሃለሁ” ይለዋል (እንደኔ ምርምር፤ይሄ ኮከብ የተባለው መልአኩ ገብርኤል ነው) በዚህ ሁኔታ ኢትኤል አሁን ወዳለችው ኢትዮጵያ ሲደርስ እግዚአብሔር፤‹‹ኢትዮጵ›› ተብለህ ተጠራ አለው፡፡ ‹‹ኢት›› - ስጦታ ማለት ነው፡፡ ‹‹ዮጵ” - ማለት ደግሞ ቢጫ ወርቅ ነው፡፡ ስለዚህ “ቢጫ ወርቅ ስጦታ” ተባለ፡፡ በኋላ ሃገሪቷን ኢትዮጵያ አሠኛት፡፡
በመፅሐፍ ቅዱስ በተደጋጋሚ ኢትዮጵያ ተብሎ የሚጠቀሰው ስም የትኛዋን ኢትዮጵያ ነው የሚወክለው?
እሱ አሁን ያለችውን ኢትዮጵያን ነው የሚወክለው፡፡ ግን ኢትዮጵያ የሚለው መጠሪያ እስከ 13ኛው ክ/ዘመን ድረስ ለመላዋ አፍሪካ መጠሪያ ሆኖ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ በኋላም የመጣው አፍሪካ የሚለው ስም ከዚሁ ከኢትዮጵያ የተገኘ ነው፡፡ ከአፋሮች ነው አፍሪካ መጠሪያዋን ያገኘችው፡፡ በመፅሃፈ እዝራ ምዕራፍ ስድስት ላይ፤‹‹አፍሪካንሳውያን›› ይላል፡፡ ይሄ አፋሮችን ነው የሚወክለው፡፡ በመርከብ ስራ በቀይ ባህር ላይ የተራቀቁ ሰዎች ነበሩ፡፡ የዛሬ 3ሺህ አመት ንጉስ ሰለሞን ቤተመቅደሱን ሲሰራ፤ልዩ እንጨት፣ እጣን፣ ወርቅ (ኦፊር የተባለ ታዋቂ ወርቅ- በነሱ የተሰየመ) ጭምር ይነግዱና ለንጉሡ ያቀርቡ ስለነበር፣ስማቸው የገነነ ሆኖ አፍሪካንሳውያን የተባሉት፡፡ በሳይንሱም አፋር የሰው ዘር መገኛ እያልን ነው፡፡ ኢስያውያንም ስያሜያቸውን ያገኙት ከሣባ ቀድሞ ከነገሰው ‹‹ኢስአኤል›› ከተባለው ንጉስ ነው፡፡ ምድሪቱን ያስተዳድር ስለነበር ኢስያ ተባለች፡፡ ‹‹አፄ” የሚለውም ከዚህ የመጣ ነው፡፡
ኢትዮጵያ የሚለው ከግሪክ ቃል የመጣ ነው የሚለውስ ---?
ኢትዮጵያ የሚለው ከግሪክ ቃል  የመጣ ነው የሚለው ውሸት ነው፡፡ ይሄን አጣርቻለሁ፡፡ በነሱ መዝገበ ቃላት ውስጥ ይሄ ቃል የለም፡፡ ‹‹ፊቱ የተቃጠለ›› የሚለው ቃል በግሪክ ቋንቋ ኢትዮጵያ የሚለውን ሳይሆን ሌላ ትርጉም ነው የሚኖረው፡፡ ግሪኮቹ ከኛው ሰምተው ነው መልሠው ኢትዮጵያ ያሉን፡፡ እኛ ከነሱ በፊት ነበርን እንጂ እነሱ ከኛ በፊት አልነበሩም፤ ስማችንን ሊያወጡልን አይችሉም፡፡
በምርምርዎ አዳምና ሄዋን የተፈጠሩበት ቦታ የት ሆኖ አገኙት?
ኢትዮጵያ ውስጥ ነው፡፡ ጎጃም፤ ዳሞትና ጣና አካባቢ ያለ ቦታ ነው፡፡
 ለዚህ ድምዳሜ ማስረጃዎ ምንድን ነው?
አንደኛ ኤደንን ከሚያጠጡ አራት ወንዞች ውስጥ አባይ የምንለው ነው ኤፌሶን የሚባለው። በኦፌር ወርቅ ዙሪያ የሚዞር መሆኑ ተፅፏል፡፡ በኔ ድምዳሜ፣የኤፌሶን ወንዝ የአሁኑ ዋቢ ሸበሌ ነው። ጤግሮስና ኤፈራጥስ ደግሞ ጊዮን ራሱ ጥንት ሜዲትራኒያን ባህር ይገባ ነበር፡፡ ድሮ ሜድትራኒያን “ኪቲ” ይባል ነበር፡፡ ጥንት ጊዮን ወንዝ ሜድትራኒያን ሲደርስ ተራራ ስለነበር ተጋጭቶ ይመለስ ነበር፡፡ ከዚያ ነው መሬት ተነቃንቆ፣ቦታው ተቆራርጦ አሁን ወዳለበት ኢራቅ የሄደው እንጂ አካባቢው እዚሁ ነበር፡፡
አዳም የት ተፈጠረ ለሚለው በመፅሃፈ ሄኖክ ላይ “ኤልዳ” በሚባል ቦታ ተፈጠረ ይላል፡፡ ኤልዳ ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ያለው፡፡ ምክንያቱም አስሌዳውያን ወይም ኤልዳውያን የሚባሉ አሁንም ድረስ ጎጃም ውስጥ አሉ፡፡ ሄኖክ በመፅሃፉ ኤልዳ ነው የተፈጠረው ይላል፡፡ ከዚያ ወስዶ ነው እግዚአብሄር በ40 ቀኑ ወደ ኤደን ገነት የከተተው ይላል፡፡ ሄዋንን ደግሞ ከአዳም ጎን አውጥቷት ነው በ80 ቀኗ ወደ ኤደን ገነት የከተታት፡፡ ከዚህ ተነስቶ ነው ወንድ በ40፣ ሴት በ80 ቀን ክርስትና የሚነሱት። ይሄ አይነቱ ስርአት በዓለም ላይ የትም የለም፤እና ይሄ በሄኖክ መፅሃፍ የተፃፈውና አሁን ያለው እውነታ ይገኛል፡፡
ሌላው ኮሬብ የሚባል ዋሻ ውስጥ አዳም ተቀበረ ይላል፡፡ በእርግጥ በሲናይ በረሃ አካባቢ ኮሬብ የሚባል ቦታ አለ፤ ግን በተመሳሳይ ይህ ቦታ ኢትዮጵያ ውስጥም አለ፡፡ ሌላው ኖህ መርከቡን ያሳረፈው አራራት ተራራ ላይ ነው ይላል፡፡ አራራት ተራራን ለመፈለግ ወደ ቦታው ሄጄ ነበር፤ በታንኳ ጣናን አቋርጬ፡፡ አራራት ተራራ የሚባለውን ሳገኘውና አቀማመጡን ሳጠናው፣ ለመርከብ ማሳረፊያነት በአናቱ ላይ ምቹ ሜዳ አለው፡፡ ኖህ ወይን ጠጅ ጠጥቶ ሰክሮ ነበር ይላል፤መፅሃፍ ቅዱስ፡፡ በእርግጥም ቦታው የወይን ጠጅ ፍሬ ለማብቀል ተስማሚ ነው፡፡ አሁንም አትክልቶችና ጌሾ ይበቅልበታል፡፡ ከዚሁ ማስረጃ ሳልወጣ፣አዲስ አመትን አበቦች አብበው አከበረ፤የእንጨት መስዋዕትም አደረገ ይላል፡፡ ይሄ እንግዲህ ዛሬ በመላ ኢትዮጵያ ያለው የአዲስ ዓመት መቀበያ ስርአት፣ ከየት መጣነትን ሊያስረዳ ይችላል። በኋላ ወደ ክርስትናው የመስቀል በዓል ደመራነት ተለወጠ እንጂ በፊት ደመራ የሚነደው በአዲስ ዓመት መጀመሪያ ላይ ነው፡፡ ለዚህ ማስረጃው አሁንም ድረስ ክርስቲያን ያልሆኑ የሀገራችን ሰዎች የደመራ ስርአት አላቸው። ይሄ የአባታቸው የኖህ ትዝታ (ማስታወሻ) ነው ሲወረስ ሲዋረስ የመጣው፡፡ በዚህና በኖህ ጉዳይ ሰፊ ጥናት እያደረግሁ ነው፤ወደፊት ይፋ ይሆናል፡፡ አንድ እዚህ ላይ ልጠቅሰው የምፈልገው፣ሌላ አራራት የሚባል ተራራ አርመን ውስጥ አለ፡፡ ተራራው ግን በረዶ ያለበት፣ ገደላገደል፣ እንኳን መርከብ ሊያሳርፍ ለሰው ልጅ የማይመችና የማያብብ ቦታ ነው፤ ስለዚህ ያ ሊሆን አይችልም፡፡
በሰንደቅ አላማው ላይም የተለየ መከራከሪያ ያቀርባሉ፡፡ ለኢትዮጵያ የተሰጠ ስጦታ ነው ሲሉ ምን ማለትዎ ነው?
 ሰንደቅ አላማው ለኖህ ከተሰጠው ምልክት የመጣ ነው፡፡ አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ የጎሉበት ቀለማት ሰማይ ላይ ታይተዋል፡፡ እነዚያ ቀለማት ናቸው ዛሬ ያሉት፡፡ ከንግስት ሳባ በፊት የነገሰው አፄ ኢሲአኤል ነው ሰንደቅ አላማ እንዲውለበለብ ያደረገው፡፡ ሰንደቅ አላማ የሚለው የመጣው የኢስአኤል መንግስት “ሰንደቅ አለማ” ከሚለው ነው፡፡ ከዚያ የመጣ ነው። እሱ በወቅቱ የመረጠው፡- አረንጓዴ ቢጫ፣ቀይና ሰማያዊ ቀለማት ነበር፡፡ ለሰንደቅ አላማው ያልተገዛና ያላውለበለበ ይቀጣል ብሎ ለመጀመሪያ ጊዜ አስገዳጅ ህግ ያወጣውም እሱ ነበር፡፡ በሰንደቋ አናት ላይ ኮከብ ነበር የሚቀመጠው፡፡ ኢየሱስ ሲወለድ የሚጠቁመውን ኮከብ ለማስታወስ ይጠቀም ነበር፡፡ በዓለም ላይ ሰንደቅ አላማን የፈለሰፈ የመጀመሪያው ሰውም ሊሆን ይችላል፡፡
የኢትዮጵ የልጅ ልጅ የሆነው ኢስአኤል ከፈለሰፈው ሰንደቅ አላማ ነው፣ዛሬ ያሉት የሰንደቅ አላማ ቀለማት የመጡት፡፡ ስለዚህ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሰንደቅ አላማው ላይ ከዚህ ተነስቶ አንድ አይነት አቋም ቢይዝ መልካም ነው፡፡ ኢስአኤል ለኦሮሞውም፣ ለአማራውም፣ ለትግሬውም፣ለአፋሩም ለሌላውም ብሄረሰብ ሁሉ አባት ነው፡፡ ከአባቶቻችን የወረደ ሰንደቅ አላማ እንጂ ከባዕድ የመጣ አይደለም፡፡
ሰውየው እጅግ ጠቢብ ነበር፤ልእለ ሰብዕ (superman) ነበር፡፡ 150 አንበሳ መግደሉን ለማስታወስ ጭምር አፄ ኢስአኤል የሰብዕ እና የአውሬዎች ንጉሰ ነገስት ብሎ ነበር ራሱን የሚጠራው፡፡ ሰውየው እጅግ ጠቢብ ከመሆኑ የተነሳ የጀነቲክ ኢንጅነሪንግን የፈለሰፈውም እሱ ነው፡፡ እንስሳን ከእንስሳ፣ ዘርን ከዘር እየቀላቀለ የፈለሰፈ የመጀመሪያው የጀነቲክ ኢንጅነር ነበር። በቅሎን የፈጠረውም እሱ ነው፡፡ አህያንና ፈረስን አዳቅሎ፡፡ ይህ ሰው የሁሉም ኢትዮጵያውን አባት ነው፡፡ የኢትዮጵ ልጅ ነው፡፡ የኢትዮጵ 10 ወንዶች ልጆች ናቸው፤ አሁን የምናያቸውን የኢትዮጵያውያን ጎሳዎች ሁሉ የፈጠሩት፡፡    
ሰሞኑን ለአንባቢያን የሚቀርብ መፅሃፍ እንዳዘጋጁም ሰምቼአለሁ፡፡ የመፅሐፉን ይዘት በአጭሩ ሊነግሩኝ ይችላሉ?
መፅሐፉ፤“የኦሮሞና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ” የሚል ነው፡፡ አሁን ያሉት ኢትዮጵያውያን በሞላ የኢትዮጵ ልጆች መሆናቸውን ከላይ አስረድቻለሁ፡፡
አሁን እንደምናው በሁላችንም ላይ የማንነት ቀውስ አለ፡፡ የማንነት ቀውሱ የመጣውም እኛ ማን እንደሆንን በትክክል ባለማወቃችን ነው፡፡ ስለዚህ ይህ መፅሐፍ እኛ ማን እንደሆንን፣በርካታ ታሪካዊ ማስረጃዎችና ሰነዶችን አስደግፎ፣ግልጥልጥ አድርጎ  ያስረዳናል፡፡ ይህ የማንነት ቀውሳችን ከተስተካከለና ራሳችንን ካወቅን፣ በመካከላችን ግጭቶች ሊኖሩ አይችሉም፡፡ መፅሐፉ፤ፍቅር፣ ሰላምና ህብር ሊፈጥር ይችላል የሚል እምነት አለኝ፡፡ እኛ የትልቅ ሰው ዘር ነን የሚለውን በማስረጃ የሚያሳየን ነው፡፡ የሰው ዘር ምንጭ ናሙናዎች መሆናችን ይተነትናል፡፡ ማንነታችንን በትክክል ተረድተን፣ አንድ ላይ ለመጓዝ ያስችለናል ብዬ አስባለሁ - ይህ ብዙ የተደከመበት የምርምር ውጤት፡፡
የኦሮሞና የአማራ የዘር ሀረግ አንድ ነው የሚለውን ነው መፅሃፉ የሚያስረዳው?
አማራና ኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ሁሉም በኢትዮጵያ ግዛት ያለው ብሄር፣ ጎሳ ከ10ሩ የኢትዮጵ ልጆች ነው የመጣው፡፡ ዝቅ ሲል ደግሞ የኢትዮጵ የልጅ ልጅ የሆነ፣ ጎጃም ላይ አዳምና ሄዋን ተፈጥረዋል ብዬ ባልኩት አካባቢ አንድ ጠቢብ ሰው ነበር፡፡ “ደሴት” ወይም “ደሸት” ይባላል፡፡ እሱ ነው የኦሮሞና የአማራ አባት፡፡ የዛሬ 3600 ዓመት 4 ወንዶች ልጆች ወለደ፡- መንዲ፣ መደባይ፣ ማጂ፣ ጅማ የሚባሉ፡፡ እነዚህ 4ቱም አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ የሀገር መጠሪያ ሆነዋል። ማጂ ደግሞ ማራ እና ጀማን ይወልዳል። ዛሬ አማራ የምንለው ማራ ነው፡፡ “ማራ” ማለት “እውነተኛ ብርሃን” ማለት ነው፡፡ አማራ ያሉት አጋዚያን ወይም የግዕዝ ቋንቋ ተናጋሪዎች ናቸው፡፡ ማጂ ማራን ወለደ ካልን፤ ጀማ እና ማራ ወንድማማቾ ናቸው፡፡ ሁለቱ ወንድማማቾች በአካባቢው ካሉት ጋፋቶች ጋር መዋጋት ሰልችቷቸው፣ ሃገር ለቀው ወደ ሸዋ ሲመጡ አንድ ወንዝ ያገኛሉ፡፡ ወንዙን ጀማ አሉት። አሁን የጀማ ወይም የ“ዠማ” ወንዝ ማለት ነው። ከአካባቢው እየራቁ ሲሄዱ የጥንት አባቶቻቸውን ቋንቋ “ሱባ”ን ትተዉ አማርኛን መፈልሰፍ ጀመሩ፡፡ መደባይ፣ ጅማና መንዲ ደግሞ ግማሾቹ ጎጃም ላይ ቀሩ፤ ግማሾቹ ወለጋ ሄዱ፤ሌሎቹም እየራቁ በምስራቅ አፍሪካ ተሰራጩ፡፡ ኦሮሚኛ ቋንቋ የሚባለውንም ፈጠሩ፡፡ በዚህ ሁኔታ ነው ዛሬ ያሉት ኦሮሞና አማራ የመጡት፡፡ ዘረ ደሸት ይባላሉ፡፡ የደሸት ልጆች ናቸው። የዘር ሀረጋቸው አንድ ነው፡፡ ቋንቋቸው የተለያየ የሆነው በሂደት ነው፡፡
ኦሮሞው የኩሽቲክ፣ አማራው የሰሜቲክ ዘር ናቸው፤ የመጡትም ከውጭ ነው የሚለው ለዘመናት የዘለቀ ታሪክስ …?
እሱ ፈፅሞ ውሸት ነው፡፡ ሁለቱም ከውጭ አልመጡም፡፡ እንዳስረዳሁት እዚሁ የበቀሉ ናቸው። የአማራም የኦሮሞም አባት ደሸትም ሆነ ታላቁ አባት ኢትዮጵ ኩሽ ነው፡፡ መልከፀዴቅም ኩሽ ነው። ኦሮሞና አማራ ሁለቱም ኩሽ ናቸው፡፡ አማራ ሴም አይደለም፤ ኩሽ ነው፡፡
እስከ ዛሬ ሲነገር የነበረው ውሸት ነው። ምናልባት የአማርኛ ቋንቋ ከሌሎች ጋር ሲደበላለቅ ሴሜቲክ ቤተሰብ ውስጥ ተገኝቶ ሊሆን ይችላል። ሁሉም ኢትዮጵያውያን የኩሽ ዘሮች ናቸው። በዚሁ መፅሐፌ ላይ ስለ ቋንቋም አስረድቻለሁ፡፡ በእብራይስጥም ሆነ በአረቢክ የሌሉ እንደ ጨ፣ቀ፣ፀ ያሉ ድምጾች በአማርኛና በኦሮሚኛ ቋንቋ ውስጥ አሉ። ይሄን በዝርዝር በመፅሐፉ አስቀምጫለሁ፡፡
ኦሮሞና አማራ አንድ ነው የሚለው አመለካከት በተለይ በኦሮሞ ምሁራን ዘንድ እምብዛም ተቀባይነት ያገኘ አይመስልም፡፡ በግድ ኦሮሞን አማራ ለማድረግ ነው በሚል ወቀሳ የሚሰነዝሩ አሉ …
እንዲህ የሚሉት ሁሉም ከኢትዮጵ ዘር የመጣው የደሸት ልጆች መሆናቸውን ባለማወቃቸው ነው። ይሄ መረጃ ስለሌላቸው ራሳቸውን እንደ ባዕድ አግልለው ስለሚያዩ ነው እንጂ አሁን ይሄ እኔ ያቀረብኩትን ማስረጃ በቅን ልቦና አገናዝበው ለመረዳት ከሞከሩ፣ የትልቁ ሰው የኢትዮጵ፣ የጠቢቡና የሊቀካህናቱ የደሸት ልጅ እንደሆኑ በሚያውቁ ጊዜ፣ እነሱ እንደተሳሳቱ ተገንዝበው ወደ ማንነታቸው ላይ አተኩረው ይኮሩበታል ብዬ አስባለሁ፡፡ የመጣነው ከትልቅ ዘር ነው፡፡ ኦሮሞውም አማራውም የመጣው ከዚህ ትልቅ ሰው ነው፡፡ በዚህ ሁላችንም ልንኮራ ይገባናል፡፡
የአሁኗ እና የቀድሞዋ ኢትዮጵያ ልዩነታቸውና አንድነታቸው ምንድን ነው?
በግዛት ከሄድን ጥንት መላው አፍሪካ ኢትዮጵያ ነው የሚባለው፡፡ ከየመን አልፎ ሁሉ ይሄዳል፡፡ ግብፅ ውስጥ ፈርኦኖች የሚባሉት ኢትዮጵያውያን ነበሩ፡፡ ኢትዮጵያውያን ከአባይ ላይ ከመርከብ ወርደው ሜዳ አግኝተው የሰፈሩበት ቦታ ነው፤ ግብፅ፡፡ የአፍሪካ ሁሉ ነገር ከኛ አይወጣም፡፡
የኢትዮጵያ ታሪክ የ3ሺህ ዘመን ነው ይባላል፡፡ እርሶ የደረሱበት የጥናት ውጤት ምን ይላል?-
አዎ፤ በተለምዶ 3ሺህ አመት ይባላል እንጂ ከ7ሺ በላይ ነው፤ የኢትዮጵያ ታሪክ፡፡ ኖህ ኢትዮጵያ ላይ ነግሷል፤ ከዚያ ጀምሮ 7ሺህ አመት ነው፡፡
እስካሁን በነገሩን ታሪክ ውስጥ መፅሐፍ ቅዱስ ብቻ ነው በማስረጃነት የሚጠቅሱት፡፡ መፅሐፍ ቅዱስን ብቻ የታሪክ ምንጭ ማድረግ ይቻላል?
መፅሐፍ ቅዱስ ብቻ አይደለም፡፡ 42 ሰነዶችን አሁን በሚወጣው መፅሐፌ ላይ በግልፅ አስቀምጫለሁ። እነዚህ ሰነዶች በተለያዩ ሰዎች በጥንት ጊዜ የተፃፉ ናቸው፡፡ ኑቢያ ውስጥ ጀበል ኑባ በተባለ ቦታ ተቀብረው የቀሩ፣በጥንት ፍርስራሽ የኢትዮጵያ ቤተ-ክርስቲያን (ከእስልምና በፊት የነበረ) ድንጋይ ሳጥን ውስጥ ተቀብረው የነበሩ የብራና ሰነዶች አግኝቻለሁ፡፡  በዚያ ላይም የተመሰረተ ነው። ከመፅሐፍ ቅዱስ ውጪ 42 ተጨማሪ የታሪክ ሰነዶችን ተጠቅሜያለሁ፤ይሄን መፅሐፍ ሳዘጋጅ፡፡
ቀጣይዋ ኢትዮጵያ ምን መምሰል አለባት ይላሉ?
አሁን ማንነታችንን አውቀን፣ የማንነት ቀውሳችንን ፈትተን፣ሁላችንም የኢትዮጵያ ዘር፣ የአንድ አባትና እናት ልጆች-----መሆናችንን ተገንዝበን፤ በፍቅር፣ በሰላም፣ በመከባበር፣ በእኩልነት መኖር አለብን ብዬ አስባለሁ፡፡ ሁላችንንም ኢትዮጵ ያገናኘናል፡፡    

  በደርግ ስርዓት የኢህአፓ ታጋይ ሆነው ለእስርና ለእንግልት ስለተዳረጉ ወጣቶች የሚተርከው ‹‹ከኒያ ልጆች ጋር›› የተሰኘ መፅሐፍ ሰሞኑን ገበያ ላይ ዋለ፡፡ ከአባላቱ አንዱ በነበረው ትንሳኤ የተባለ የኢህአፓ ታጋይ ጋር በተደረገ ቃለ ምልልስ፣ በፋሲካ መለሰ የተዘጋጀው መጽሐፉ፤ባለታሪኩ በእስርና በስደት ባሳለፈው ህይወት ላይ ተመስርቶ ስለ ሌሎች ተመሳሳይ ህይወት ያሳለፉ ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች የሚተርክ ሲሆን ወጣቶቹ ምን አይነት ገድል እንደፈፀሙ፤እንዴት እንደታሰሩና እንዴት እንደተፈቱ በስፋት ይተነትናል ተብሏል፡፡ በ17 ምዕራፎች  የተከፋፈለው መፅሐፉ፤ በፋርኢስት ማተሚያ ቤት ታትሞ በክብሩ መፅሐፍ መደብር እየተከፋፈለ ሲሆን በ90 ብር ከ99 ሳንቲም ለአገር ውስጥና በ20 ዶላር በውጭ አገራት ለገበያ መቅረቡ ታውቋል፡፡

• ጃንሆይ አምላክ መባላቸውን በመቃወም፣ጃማይካ ውስጥ የቤተ-ክርስቲያን ማሰሪያ ገንዘብ ሰጥተዋል
• በሻሸመኔ መጀመሪያ መሬት የተሰጣቸው ጥቁር አሜሪካውያን እንጂ ራስ ተፈሪያን አይደሉም
• መስፍን አበበ “በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጊታር ተጫዋች ነኝ” ማለቱ ውሸት ነው

የፎቶግራፍ ባለሙያው ንጉሴ ተሾመ ደጀኔ የተወለዱት በአዲስ አበባ ልደታ አካባቢ ነው፡፡ በልጅነታቸው ከቤተሰቦቻቸው ጋር በኤርትራ ደቀመሀሪ ለተወሰኑ ዓመታት ተቀምጠው ወደ አዲስ አበባ የተመለሱ ሲሆን ለአንድ ዓመት በሊሴ ገ/ማርያም ት/ቤት ተምረው እንደገና ከቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ ሻሸመኔ በማቅናት፣ በአፄ ናኦድ ት/ቤት እስከ 8ኛ ክፍል መማራቸውን ይናገራሉ፡፡ ላለፉት 50 ዓመታት በፎቶግራፍ ባለሙያነት የሰሩት አቶ ንጉሴ፤ ፎቶግራፍ የተጻፈ ታሪክን ተጨባጭና ተዓማኒ ያደርገዋል ይላሉ፡፡ በተለይ እውነቱን የማውቀው ታሪክ ተጣሞና ተዛብቶ ሲቀርብ በጣም እናደዳለሁ የሚሉት ባለሙያው፤ በፎቶግራፎች ማስረጃነት የተዛቡ ታሪኮች እንዲታረሙ ተደጋጋሚ ጥረት ማድረጋቸውን ይናገራሉ፡፡ “ራስ ተፈሪና የራስ ተፈሪያን ማንነት” በሚል ርዕስ የጻፉት መጽሃፍም የህትመት ብርሃን እየተጠባበቀ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ ለመሆኑ ወደ ፎቶግራፍ ባለሙያነት እንዴት ገቡ? ፎቶግራፍና ታሪክን እንዴት አስተሳሰሩት? እስካሁን ምን ያህል የተዛቡ ታሪኮችን በፎቶግራፎች ማስረጃነት ለማረም ሞከሩ? ሥራና ኑሮአቸውስ ምን ይመስላል? የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ለስራ አዳማ በሄደችበት ወቅት፣ የፎቶግራፍ ባለሙያውን አቶ ንጉሴ ተሾመን አግኝታ በሙያቸው ዙሪያ አነጋግራቸዋለች፡፡ እንዲህ ተጠናቅሯል፡-

ቤተሰቦችዎ ከቦታ ቦታ የሚዘዋወሩት በምን ምክንያት ነበር?
በወቅቱ አባቴ ሹፌር ስለነበሩ የተለያየ ቦታ ይጓዛሉ፡፡ በዚህ ምክንያት ቤተሰባችን ተረጋግቶ አይቀመጥም ነበር፡፡ በኋላ ላይ አባቴ ማዕከላቸውን ሻሸመኔ አደረጉና፣ እኛም ከ1949 ዓ.ም ጀምሮ እዚያ መኖር ጀመርን፡፡ አፄ ናኦድ ት/ቤት እስከ 8ኛ ክፍል ተማርኩኝ፤ አባቴም ዲላ ወላይታ እየሄዱ በሹፍርና ይሰሩ ነበር፡፡ በቃ እዚያው አደግሁኝ፡፡ ስለ ሻሸመኔ ብዙ ነገር አውቃለሁ፤ ብዙ የፎቶግራፍ ማስረጃዎችም አሉኝ፡፡
እንዴት ወደ ፎቶግራፍ አንሺነት ሙያ ሊገቡ ቻሉ? ለመጀመሪያ ጊዜ ፎቶግራፍ ያነሱትና ካሜራ የጨበጡት መቼ ነበር?
በ1963 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቴን እንዳጠናቀቅኩ በ27 ብር “ሉቢቴልቱ” የተባለች የራሺያ ካሜራ ከነማኑዋሏ ገዝቼ፣ ከዚያን ጊዜ አንስቶ ከተማ እየዞርኩ ታሪክ ማስቀረት ጀመርኩ። ፍላጎቱ ያደረብኝ በአሰብ መንገድ አንድ ተኮላ የሚባል ኢንጂነር መንገድ እያሰራ ፎቶ ያነሳና ስዕል ይሰራል፤ ስዕሉን ከፎቶው ላይ ነበር አስመስሎ በትልቁ የሚስለው፡፡ እሱ በወቅቱ ያቀረበውን የስዕል ኤግዚቢሽን በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አየሁኝ፡፡ በካሜራ ካነሳሁ በኋላ ነው የምስለው ብሎ ሲናገርም ሰማሁ፤ ለምን እኔስ በካሜራ እያነሳሁ አልስልም በሚል ካሜራውን ገዛሁ፤ከዚያ በኋላ ማንሳቱን ቀጠልኩኝ ማለት ነው፡፡
እስከ ዛሬ ከ200 ሺህ በላይ ፎቶዎችን አንስተዋል ይባላል፡፡ እውነት ነው?
አይበልጥም ብለሽ ነው፡፡ ምክንያቱም ዲጂታል ካሜራ ከመጣ ያነሳሁት እንኳን ብዙ ስለሆነ ያለኝ የፎቶ ብዛት ወደ 300 ሺህ ሳይጠጋ አይቀርም፡፡ የካሴት ከቨር የሆኑ ወደ 300 አልበም ፎቶዎች አሉኝ። የቀድሞው ቱሪዝም ኮሚሽን የሚያሳትመውን ፖስተርና ፖስት ካርድ ሰብስቤ ከ400 በላይ አለኝ፡፡ እነሱ ጋ አንድም የለም፤ሸጠው ሸጠው ጨርሰውታል፤የተሳሳተ ነገር ሲያወጡ እየፃፍኩ አርማቸዋለሁ፡፡  
በሻሸመኔ መጀመሪያ መሬት የተሰጠው ለራስ ተፈሪያን አይደለም፤የሚለውን ማስረጃ ከየት ነው ያገኙት?
 ቀደም ብዬ እንደነገርኩሽ እኛ ሻሸመኔ በቋሚነት መኖር የጀመርነው በ1949 ዓ.ም ነው፡፡ በ1942 ግን በጃንሆይ በጎ ፈቃድ መሬት የተሰጠው ለሶስት አፍሮ አሜሪካዊያን ነው፡፡ እነሱም፡- ግላድስተን ሮቢንሰን፣ ጀምስ ፓይፐር እና ባለቤታቸው ወ/ሮ ፓይፐር ብቻ ነበሩ፡፡
እነዚህ አፍሪካ አሜሪካዊያን እንዴት ከጃንሆይ መሬቱ ሊሰጣቸው ቻለ?
በጣም ጥሩ፡፡ ፋሽስት ጣሊያን ለሁለተኛ ጊዜ አገራችንን በ1928 ዓ.ም በወረረ ጊዜ ጃንሆይ ለአምስት አመታት ለንደን ነበሩ፡፡ ያኔ ጥቁር አሜሪካውያን ኒውዮርክ ሀርለም ላይ ኢትዮጵያን ለማገዝና ለመዋጋት 17 ሺህ ያህል ሆነው ተመዝግበው ነበር፡፡ ነገር ግን ፈረንሳይ፣ ጣሊያንና እንግሊዝ ዙሪያውን ከበው ስለነበር መግባት አይቻልም ነበር፡፡ ስለዚህ ሶስት ተደማጭነት ያላቸው አፍሮ አሜሪካዊያን ተመርጠውና ተወክለው ጃንሆይ የሚኖሩበት ለንደን ድረስ ሄደው አነጋገሯቸው፡፡ የጥቁር አሜሪካዊያኑንም ኢትዮጵያን የማገዝ ፍላጎት አስረዷቸው፡፡ ከህዝቡ ማለትም ከአሜሪካውያኑ የተውጣጣውን አራት ሚሊዮን ብርም ሰጧቸው፤ ምክንያቱም ኒውዮርክ ላይ “የምኒሊክ ክበብ” የሚል አቋቁመው የእርዳታ ገንዘብ ያሰባስቡ ነበር፤ ጥቁር አሜሪካውያኑ፡፡ በኋላ ጃንሆይ “ወደ ኢትዮጵያ መግባት አትችሉም፤ዙሪያውን በቅኝ ገዢዎች የተከበበ ነው፤ ለስንቅና ትጥቅም አይመቻችሁም፤ እዛው ሆናችሁ ታገሉልን” አሏቸው “እንግዲያውስ አንድ አስተባባሪ ስጡን; ብለው ጠየቁ፡፡ ከዚያ ዶክተር መላኩ አማኑኤል በያን የተባለውን የአጎታቸውን ልጅ፣ ጃንሆይ በአስተባባሪነት ሰጧቸው፡፡ ዶ/ር መላኩ በአሜሪካ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ዶ/ር ነው፡፡ ዶ/ር መላኩም አሜሪካ ሄዶ “Ethiopian World Federation” የተባለ ማህበር እ.ኤ.አ በ1937 አቋቋመ፡፡ ከዚያም እርዳታውን እያስተባበረ ለአርበኞች ትጥቅና ስንቅ፣ መድሀኒት፣ ለጃንሆይ መኖሪያ ሁሉን ማሟላት ጀመረ፡፡
 ጦርነቱ ካበቃ በኋላ ጃንሆይ ወደ አገራቸው እንደተመለሱ ለጥቁር አሜሪካዊያኑ ደብዳቤ ፃፉ፡፡ በጣሊያን ወረራ ጊዜ ላደረጉት ውለታ ለማመስገን፣ ሻሸመኔ ላይ መጥተው እንዲኖሩ የሚጋብዝ ደብዳቤ ነው፡፡ በዚህ ግብዣ መሰረት ሚስተር ጀምስ ፓይፐር፣ ባለቤታቸው ወ/ሮ ፓይፐርና ግላድስተን ሮቢንሰን በ1942 ዓ.ም ወደ ኢትዮጰያ መጥተው ሻሸመኔ መኖር ጀመሩ፡፡ የሚገርምሽ ወ/ሮ ፓይፐር ለንደን ውስጥ ለጃንሆይ ምግብ ያበስሉላቸው ነበር፡፡ እንዲያውም በወቅቱ የሻሸመኔ አካባቢ ባላባትና ሹም ፊታውራሪ ጁላ ሾቤ ይባሉ ነበር፡፡ ከዚያም ጃንሆይ ለፊታውራሪው፤“እነዚህ ባለውለታችን ስለሆኑ አምስት ጋሻ መሬት ፈልገህ ለአውራ ጎዳናው ቅርብ የሆነ ቦታ ስጣቸው” ብለው አዘዙ፡፡ ፊታውራሪውም፤ “ጃንሆይ፤ የመንግስት መሬት አውራ ጎዳናው ላይ የለም፤ መሬት ያለው ከከተማው ርቆ ወደ ኮፈሌ ገጠሩ ውስጥ ነው፤እዚያ ደግሞ አውሬዎች በብዛት ስላሉ ለመኖር አስቸጋሪ ነው፡፡ ስለዚህ ወደ ወላይታ ይሂዱና እዚያ ይኑሩ” የሚል ምላሽ ሰጡ፡፡ ጃንሆይ ደግሞ “አይ አንዴ አዝዤሀለሁ፤ከየትኛውም ሰው ላይ ቀምተህ ስጣቸውና ቤተ-መንግስት መጥተህ ሪፖርት አድርግ” የሚል ቀጭን ትዕዛዝ አስተላለፉ፡፡ በዚህ መሰረት ፊታውራሪ ጁላ፤ ከቄስ ገመኔ ላይ ሶስት ጋሻ መሬት፣ ከዋቻሞው ባላባት ላይ ሁለት ጋሻ ቀምተው አውራ ጎዳናው ላይ ያለ መሬት ሰጧቸው፡፡ ከዚያ ጀምስ ፓይፐርና ባለቤታቸው ወይዘሮ ፓይፐር እንዲሁም ግላድስተን ሮቢንሰን ከ1942 ጀምሮ መኖር ጀመሩ፡፡ ባልና ሚስቱ የአይሁድ እምነት ተከታይ ሲሆኑ ግላድስተን ሮቢንሰን የኦርቶዶክስ እምነትን ተቀብሎ ተጠምቆ በኋላ ስሙ ፍቅረ ስላሴ ይባል ነበር፡፡ ስምህ ማን ነው ሲባል እንኳን የባርነት ስሜ ግላድስተን ሮቢንሰን፣ የነፃነት ስሜ ፍቅረ ሥላሴ እያለ ይመልስ ነበር፡፡ በቅርብ ከአራት አመት በፊት ነው ፍቅረ ስላሴ የሞተው፤ እንቀራረብ ነበር፡፡
ታዲያ ጃማይካዊያን መቼ ነው ወደ ሻሸመኔ የመጡት?
ጃማይካዊያኑ በ1962 ዓ.ም ማለትም አፍሮ አሜሪካኑ ከመጡ ከ20 ዓመታት በኋላ ነው ስምንት ሆነው ወደ ሻሸመኔ የመጡት፡፡ አፍሮ አሜሪካኑ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ጃማይካዊያን በወቅቱ በእንግሊዝ ቅኝ አገዛዝ ስር ስለነበሩ ሻይቅጠልና ትምባሆ እያስተከሏቸው ነበር፡፡ ያን  ጊዜ ለራሳቸውም ነፃነት ስላልነበራቸው ኢትዮጵያን እንደ አሜሪካዊያን ሊያግዙ አልቻሉም ነበር፡፡ ከ20 ዓመታት በኋላ በ1962 ዓ.ም ስምንት ጃማይካዊያን መጡ፤በወቅቱ የግቢ ሚኒስትር በነበሩት ፀሐፌ ትዕዛዝ ተፈራወርቅ ኪዳነወልድ፣ ከቤተ መንግስት፤ “በሉ እንግዲህ ከእናንተ ጋር ይኑሩ” ብለው ወደ ሻሸመኔ ላኳቸው፡፡ አፍሮ አሜሪካኖቹ ተቃወሙ፡፡
ምን ብለው ተቃወሙ?
“እኛ አፍሮ አሜሪካዊያን ነን፤እነሱ ጃማይካዊያን ናቸው፤ በምንም አንገናኝም እንዴት አብረን እንኖራለን፤ይሄ መሬት የተሰጠው በኢትዮጵያ ወርልድ ፌደሬሽን ስም ለእኛ ነው” የሚል ነበር ተቃውሞው፡፡ ከዚያም የላኳቸው ፀሀፌ ትዕዛዝ፤“መልካችሁ አንድ አይነት ነው የአገራችሁ ርቀትም እንደዚያው፤በዚያ ላይ ለኢትዮጵያም ያላችሁ ፍቅር አንድ አይነት ነው ስለዚህ አብራችሁ ኑሩ” ሲባል “አብረን አንኖርም” ብለው አሻፈረኝ ሲሉ፣ የጃንሆይ ልጅ ልዕልት ተናኘወርቅ ጣልቃ ገብተው፤ “ለወደፊቱ እኔ ወንዶገነት ወዳለኝ መሬት እወስዳቸዋለሁ፤ አሁን አምስት አምስት ሄክታር ይሰጣቸውና ይቀመጡ; ተብሎ የዝዋይ አውራጃ ገዢ በተገኙበት (ፊታውራሪ ጁላ በወቅቱ ሞተው ስለነበር) ልጃቸው ነጌሶ ጁላ እየለካ፣ አምስት አምስት ሄክታር ሰጥቷቸው መኖር ጀመሩ፡፡ ይህ ሲደረግ የተፈረመው ደብዳቤ በእጄ ላይ ስላለ ማስረጃ ነው፡፡ ይህንን እውነታ ለምን እንደሚቆለምሙት አይገባኝም፡፡
ጃንሆይ ጃማይካን ለመጎብኘት በሄዱ ቀን ሲዘንብ ያደረ ዝናብ ቆመ እንጂ እሳቸው እዚያ ሲደርሱ ዝናብ አልዘነበም ብለው እንደሚከራከሩም ሰምቻለሁ-----
አዎ እከራከራለሁ፡፡ ለምን መሰለሽ----ጃንሆይ በጃማይካዎቹ አምላክ የተባሉት በ1923 ገና ዘውድ እንደጫኑ ነው፡፡ ጃማይካን የጎበኙት እ.ኤ.አ በ1958 ሊወርዱ ሲሉ ነው፡፡ ጉብኝቱም በጃማይካ መንግስት ግብዣ የተደረገ ነው፡፡ የዝናቡን ጉዳይ በተመለከተ ጃንሆይ እዚያ ከመድረሳቸው ከአንድ ቀን በፊት ሲዘንብ አደረና፣ ከገጠር ከአገሪቱ ጥግ ሁሉ ኪንግስተን ከተማ አምላኩን ለመቀበል የመጣውን የጃማይካ ህዝብ ሲቀጠቅጥ አድሮ፣ በነጋታው ጃንሆይ እዚያ ሲደርሱ ዝናብ አልነበረም፡፡ ፊልሙ እኔ ጋር ይገኛል፤ላሳይሽ እችላለሁ፤በዕለቱ በአቀባበሉ ላይ ጃንጥላም አልተያዘም፡፡
ጃንሆይን አምላክ ብሎ የተቀበለውም ያልተቀበለውም የጃማይካ ህዝብ እሳቸውን ለማየት ኪንግስተን ከተማ ወጥቶ ዝናብ እየቀጠቀጠው ስለነበር ጃንሆይ ከአውሮፕላን ሳይወርዱ አየር ላይ ለሶስት ሰዓት ያህል ቆይተዋል የሚባለውስ----?
ትክክለኛውን ስሚኝ፡፡ አየር ላይ አልቆዩም፤እንደውም ከአውሮፕላን ሲወርዱ ህዝቡ አጥሩን ሰብሮ ክቡር ዘበኛውን ጥሶ፣ አውሮፕላኑ ስር ይፍለከለክ ነበር፤ ይሄ ነው የሆነው፡፡
ታዲያ የታሪክ መፋለሱ የመጣው ከታሪክ ፀሐፊዎች ነው ወይስ በጃንሆይ ወገን የተወራ ነው?
እንደውም ጃንሆይ ስለ ራሳቸው አጋንነው የሚያወሩት ነገር የለም፡፡ አንድ ጊዜ ማርከስ ጋርቬይ እንግሊዝ ሊጎበኛቸው ሄዶ እንኳን አልተቀበሉትም፡፡
ማርከስ ጋርቬይ በ1890ዎቹ መጨረሻ “ከኢትዮጵያ አምላክ ይወጣል ወደ አፍሪካ ተመለሱ” እያለ የነበረና አሜሪካ የሚኖር ጃማይካዊ አይደለም እንዴ?
አዎ፤ እሱ ጃንሆይን አምላክ ነው ብሎ የሚናገር፣ በጃማይካዊያን ዘንድ እንደ ትንቢት ተናጋሪ የሚቆጠር ስለነበር፣ እኔ አምላክ ሳልሆን አምላክ እያለ ያወራል ብለው አልተቀበሉትም ነበር። በኋላ ጃንሆይ “ህዝባቸውን ለጣሊያን ትተው ወደ እንግሊዝ ሄደዋል” እያለ ሲከሰሳቸው ዶ/ር መላኩ አማኑኤል በያን ያልኩሽ የጃንሆይ የአጎት ልጅ፣ ክሱን በመቃወም መልስ ይሰጠው ነበር። ስለዚህ ጃንሆይ አምላክ መባላቸውን አጥብቀው ከመቃወማቸው የተነሳ ጃማይካ ውስጥ የቤተ ክርስቲያን ማሰሪያ የሚሆን ገንዘብ ሰጥተዋል፤ ትልልቅ የሀይማኖት መሪዎቻቸውን ሰብስበው፡፡ አባ ላዕከ ማሪያም የተባሉ የኦርቶዶክስ ቄስ በአጥማቂነት መድበው፣ “እኛ የምንከተለውን የኦርቶዶክስ ሀይማኖት ተከተሉ፤ እኛ አምላክ አይደለንም” ነው ያሉት ጃንሆይ። ጃማይካዎች “እናውቃለን ይሄ የትህትና ንግግር ነው፤ ኢየሱስ ክርስቶስም እኔ ክርስቶስ መሆኔን ለማንም እንዳትናገሩ ብሏል በመፅሀፍ ቅዱስ፤ ስለዚህ እኛ እርሶ አምላክ እንደሆኑ እናምናለን” አሉ፡፡ ኦርቶዶክስን የተቀበሉ ተጠመቁ፤ ያልተቀበሉ እርሳቸውን አምላክ ናቸው ብለው ቀጠሉ፤ ይሄው ነው፡፡ ወሬው ግን ከየት ተነስቶ የት እንደሚደርስ ተመልከቺ፡፡ ለምሳሌ የሻሸመኔ ልጆች ማህበር አለን፡፡ ከመሃላችን ትልልቅ የመንግስት ኃላፊዎችም አሉ፤የአካባቢው ተወላጆች የሆኑ----ስንሰበሰብና ራስ ተፈሪያን መጀመሪያ መሬት እንዳልተሰጣቸው፣ ለጥቁር አሜሪካውያኑ የተሰጠ የምስጋና መሬት እንደሆነ በፊት ለፊታቸው ስንናገር፣ ትንፍሽ አይሉም፤ እውነታውን ያውቁታላ፡፡
እርስዎ እንግዲህ የፎግራፍ ባለሙያ እንጂ የታሪክ ተመራማሪ አይደሉም፡፡ ይህን ሁሉ ታሪክ ያወቁት አካባቢው ላይ ስለኖሩ ብቻ ነው ወይስ ታሪክ የመሰነድ ፍላጎትም አለዎት?
በነገራችን ላይ ፎቶግራፍ ስታነሺም ታሪክ ነው የምታሰባስቢው፡፡ አንዳንድ ታሪኮች ተፅፈው በፎቶግራፍ ሲደገፉ ታሪክን የበለጠ ተጨባጭና ተዓማኒ ያደርጉታል፡፡ በዚያ ላይ ፎቶግራፍ ስታነሺ ገብቶሽ አንድን ነገር መሰረት አድርገሽ ስለምታነሺ፣በመረጃነት በአዕምሮሽም በወረቀትም ይቀመጣል፡፡ ታዲያ ታሪክ ሲዛባ ስትመለከቺ፣ ለምን የሚለውን ጥያቄ ታነሺና ፎቶዎቹን በማስረጃነት ታቀርቢያለሽ፡፡ ለምሳሌ በቅርቡ የጊታር ተጫዋቹ መስፍን አበበ በሰይፉ በኢቢኤስ ላይ ቀርቦ፣ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጊታር ተጫዋች ነኝ ብሎ ተናግሯል፡፡ ነገር ግን ውሸት ነው፤አሁን በእርግጥ በህይወት የለም እንጂ ፊት ለፊት እንነጋገር ነበር፡፡ የሆነ ሆኖ እኔ ዘንድ በርካታ መረጃ አለ፡፡ መስፍን አበበ አምስተኛ ጊታር ተጫዋች ነው፡፡ ለዚህም “የጊታር አጀማመር በኢትዮጵያ” በሚል 60 ገፅ ፅሁፍ ፅፌ፣ 120 ያህል ፎቶግራፎች አስገብቼበት ተቀምጧል፡፡ በቅርቡ ይፋ ይሆናል፡፡
የመጀመሪያዎቹን ማለትም ከመስፍን አበበ በፊት ጊታር ተጫውተዋል የሚሏቸውን በቅደም ተከተል ሊነግሩኝ ይችላሉ?
አንደኛ የክቡር ዘበኛው ተዘራ ሃይለሚካኤል በ1952 ዓ.ም ተጫውቷል፣ ሁለተኛው የጅማው ግርማ ምንተስኖት በ1962 ጊታር ይጫወት ነበር፤ በኢቲቪ ሁሉ ይታይ ነበር፡፡ ሶስተኛው በ1968 የዘፈነው ፀጋዬ መርጊያ ነው፣ ሙሉጌታ ረታ አለሙ በ1970 በጊታር ዘፍኗል፡፡ መስፍን አበበ ከአራቱ በኋላ በ1972 ነው የመጣው፡፡ ይሄ መስተካከል አለበት፤ በሚል በመረጃ አስደግፌ በቅርቡ እለቀዋለሁ ብያለሁ፡፡
ሌላው የአርሲዋ ሴት ጉደቱ ካዎ ጉዳይ ነው። ይህቺ የአርሲ ሴት የቀድሞው ቱሪዝም ኮሚሽን ፎቶዋን በፖስት ካርድነት ይጠቀመው የነበረች ሴት ናት፡፡ ስለዚህች ሴት እኔ በ1981 ዓ.ም በዛሬይቱ ኢትዮጵያ ጋዜጣ ላይ፣ “አባቴን አፈላልጉኝ” በሚል ርዕስ ከአስር በላይ መጣጥፍ ፅፌ ነበር፡፡
 ምክንያቱም ፎቶውን ያነሳሁት እኔ ነኝ በሚሉ ሰዎች መሀል ጭቅጭቅ ተነስቶ ነበር፡፡ የሆነ ሆኖ በ2000 ዓ.ም የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር የነበሩት መሀመድ ድሪር፣ የግብርና ሚኒስትር የነበሩት ሰው፣ የኦሮሚያ ባህል ቢሮ ኃላፊው እሷም አሀራ ተቀምጣ፣ ትልቅ ዝግጅት ተዘጋጅቶ አዳማ ላይ 105 ካ.ሜ ቦታ ተሸልማለች፡፡ የሀራምቤ ኮሌጅ ባለቤት ለ10 ዓመት በየወሩ 300 ብር እንድትወስድ ቃል ሲገባ በቦታው ተገኝቼ ፎቶ አንስቻለሁ፤ ስትወስድም አውቃለሁ፡፡ ቦታውን 45 ሺህ ብር መሸጧንም አውቃለሁ፤ነገር ግን በ2006 ዓ.ም በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ምንም እንዳልተደረገላት ክዳለች፡፡
ጋዜጠኛውን ስለ ራሷ የተፃፉ 10 የጋዜጣ ኮፒና 15 ፎቶግራፎች ሰጥተነው፣ 15 ቀን ስጡኝ አስተካክላለሁ ብሎ ሁለት ወር ተጠበቀ፤ አልመለሰም፡፡ ከዚያ እውነታውን በፌስቡክ “የኢቲቪ ጋዜጠኛ የቀደዳ አርበኛ” በሚል ለቀቅኩት፡፡ ይሄው እዚህ አዳራሽ ውስጥ ለጥፌዋለሁ፤ አንብቢው፡፡ እውነተኛ ማስረጃ ስላለኝ አንድም ሰው አልተቃወመም፡፡ ለምን ታሪክ ይዛባል። አቶ ሀብተስላሴ ታፈሰስ መዋሸት ነበረባቸው?
አቶ ሀብተስላሴ-----?
 አቶ ሀብተስላሴ ታፈሰ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት ናቸው፡፡ እኔ በግሌ ለቱሪዝም መበልፀግ በሰሩት ትልቅ ስራ ክብር አለኝ፤ ነገር ግን በዚች ሴት ፖስት ካርድ ላይ አሻጥር ሰርተዋል። ፎቶውን ያነሳት አንቶኒዮ ቪራኖ የተባለው ጣሊያናዊ ነው፡፡ ክሪያዚዝ ዜርፎዝ የተባለ ፎቶ ቤት የነበረው አርመን፣ አሁን ፒያሳ ክሪያዚዝ ኬክ ቤት አጠገብ የነበረ ፎቶ ቤት ባለቤት “ከለር ማተም ጀምሬያለሁና ስጠኝ ጥሩ አድርጌ ላትምልህ” ይልና ከአንቶኒዮ ይቀበላል፡፡ ኮሚሽነሩ የክሪያዚዝ ጓደኛ ስለነበሩ፣እሳቸው ጋ ወስዶ በራሱ ስም አሳተማት፡፡
 አንቶኒዮና ክሪያዚዝ አቶ ሀብተስላሴ ጋ ሄደው ይካሰሳሉ፡፡ ለክሪያዚዝ አግዘው ፍርድ ሳይሰጡ ፎቶዋን እንደያዙ ደርግ መጣና እስር ቤት ከተታቸው፡፡ ከዚያ ራሱ ደርግ ፈታና መልሶ የቱሪዝም ኮሚሽን ኮሚሽነር አደረጋቸው፡፡ ፊልሟን አገኟትና በራሳቸው ስም፤ “Girl On the Baro River Gambella” ብለው አወጥዋት፡፡ ይሄንን ታሪክ ከራሷ ከጉዳቱ ካዎ መስማት ትችያለሽ፤ አርሲ ነገሌ በህይወት ያለች ሴት ናት፤ ታገኚያታለሽ፡፡ ላገናኝሽ እችላለሁ፡፡
ይህን ሁሉ ውሸት ለማጋለጥ ነው በ1981 በዛሬይቱ ኢትዮጵያ ላይ “አባቴን አፈላልጉኝ” በሚል ርዕስ በተከታታይ 10 መጣጥፍ ያወጣሁት፡፡ ያኔ ቱሪዝም ኮሚሽን “ስህተቱን እናርማለን” በሚል የፃፈልኝ ደብዳቤ በእጄ ላይ አለ፡፡
 የኢቲቪው ጋዜጠኛ ይህን ሁሉ ማስረጃ ካሰባሰበ በኋላ ነው ያልሆነ ታሪክ ያወጣው፡፡ በጣም ያሳዝናል፡፡ በተለይ እውነታውን እያወቅሁት ተጣሞና ተዛብቶ ሲቀርብ በጣም እናደዳለሁ፡፡
ሌላው ሰው ጋ የማይገኝና እኔ ብቻ አለኝ የሚሉት ፎቶ አለዎት?
እኔ ከሌላው የምለየው በአንድ ወቅት በምንም ሁኔታ ያነሳሁትን ፎቶ አልጥልም፤ ምክኒያቱም ፎቶ ቅርስ ነው፣ማስረጃ መፅሀፍ ነው፡፡ ሌላው ያነሳና ይጥለዋል፡፡ እኔ  በማንኛውም ጉዳይ ላይ መረጃ ስፈልግ አቀርባለሁ፤ልክ አሁን ለተዛቡ ታሪኮች መረጃ እንደማቀርበው ማለት ነው፡፡ ለፎቶግራፎች ክብር ሰጥቼ በማስቀመጤ ነው ከሌላው የምለየው፡፡ ስለዚህ አንቺ ፎቶ አንስተሸ ከጣልሽ እኔ ጋ አለ፤አንቺ ጋ የለም ማለት ነው፡፡
የፎቶግራፍ ኤግዚቢሽን አቅርበው ያውቃሉ?
በጣም ብዙ ጊዜ በተለያየ ቦታ አቅርቤያለሁ። በጣሊያን ካልቸር፣ በአሊያንስ ኢትዮ-ፍራንሴዝ፣ በፑሽኪን አዳራሽ ---- በበርካታ ቦታዎች አቅርቤያለሁ፡፡
በራስ ተፈሪያን ላይ የጻፉት መጽሀፍ በምን ደረጃ ላይ ነው?
ተፅፎ ካለቀ ቆይቷል፡፡ ታሪኩን በትክክል እንዲቀመጥ ለማድረግ ነው እንጂ ብር የለኝም። አሁን ግን የኔ የፎቶ ተማሪ የነበረ፣ እንደገና እኔን ኤዲቲንግ ያስተማረኝ በኃይሉ ግርማ የተባለ ልጅ፣እንደሚያሳትምልኝ ቃል ገብቷል፤እግዚአብሔር ይርዳው እንግዲህ፡፡
እስኪ ስለ ራስዎ ይንገሩኝ---በምን ሁኔታ ነው የሚኖሩት?
አሁን በቋሚነት የምኖረው አዳማ ነው፡፡ 45 ዓመት እዚህ የኖርንበትን ቤት፣ “ለእናታችሁ ነው ያከራየነው አናቅህም” ተብዬ ሰባት ዓመት ተከራክሬ አሸንፌ፣እዚሁ ቤት ውስጥ ብቻዬን እኖራለሁ። በትዳር በኩል የመጀመሪያዋ ባለቤቴ ከመላዕክና ከሰው የተፈጠረች ነበረች፤ በጣም ትረዳኝ ነበር ፈጣሪ ወሰዳት፤ አላመሰገንኩትም መሰለኝ፡፡
ሁለተኛዋ ባለቤቴ፣ ጥሩ ጥሩ ልጆች ሰጥታኛለች፤ሶ ስት ልጆች ከሰጠችኝ በኋላ እራሴ እንደመጣሁ እራሴ እሄዳለሁ አለች፤ ሸኘሁ መቼስ ምን አደርጋለሁ፡፡ አሁን ብቻዬን ነው የምኖረው፡፡
ልጆችዎ የት ነው ያሉት?
ልጆቹን ወስዳቸዋለች፡፡ ከአባት እናት ይበልጣል በሚል ሀዋሳ ይዛቸው ትኖራለች፡፡ ከሟች ሚስቴ የወለድኳት የመጀመሪያ ልጄ ትዝታ ንጉሴ፣ ራሷን ችላ እየሰራች ነው፡፡ እኔም ራሴን ችዬ እየኖርኩ ነው።