Administrator

Administrator

ኢንጂነር ቢጃይ ናይከር ግማሽ ሚሊዮን (500ሺህ) ብር፣
ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ 100ሺ ብር በመስጠት ጀምሯል ደጋግ ኢትዮጵያውያኖች የአቅማችሁን በማድረግ የትዕግስት ሶስት መንታ ልጆች የአይን ብርሃናቸው እንዲመለስ የበኩላችንን እናድርግ።
ሼር በማድረግ እንጀምር!
አካውንታቸው ይህው እባካችሁ
ሼር አድርጉት
* СВЕ 1000622473872
* Dashen Bank 5563671317021
* Abyssinia bank 91613069
* ኦሮሚያ ኅብረት ስራ ባንክ 1023500172828
* አዋሽ ባንክ 013471254339600
ትግስት ካሳ ቀፀላ
ስልክ
* 0911868306
* 0911137097
go fund me
ይህን ሼር ማድርግ መልካም ነገር መስራት ነውና እባካችሁ ሼር አድርጉላቸው
• ገዳሙን ለመታደግ ቅዳሜ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ይካሄዳል
ገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል የአንድነት ገዳም በ1574 የተመሰረተና የጻዲቁ አባት አቡነ ሐራ ድንግል ገድልና ገቢረ ተዓምራት የሚካሄድበት ገዳም ነው - ይላሉ የገዳሙ መነኮሳት፡፡
ከ400 ዓመት በላይ ታሪክ ያለው ይህ ትልቅ ገዳም በሰሜን ጎጃም፣ ባህርዳር ዙሪያ የሚገኝ ሲሆን፣ ጻዲቁ አቡነ ሐራ ድንግል፣ ከፈጣሪያቸው በተገባላቸው ቃልኪዳን መሠረት፣ ደዌን ሲፈውሱና ተዓምራትን ሲሰሩ የቆዩበትና አሁንም የሚሰሩበት ጥንታዊ ገዳም መሆኑን፣ የገዳሙ ገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ ያወጣው መግለጫ ይጠቁማል፡፡
ይሁን እንጂ ይህ ገቢረ ተዓምር የሚሰራበት ታሪካዊ ገዳም፣ ትልቅ ችግር እንደተጋረጠበት መነኮሳቱ ተናግረዋል፡፡
“ለፈውስና ለድህነት ከመላው አገሪቱ ወደ ገዳሙ የሚመጡ ምዕመናን ድህነትና ፈውስ ካገኙ በኋላ፣ ገዳሙን ተጠግተው ቤት በመሥራት እዚያው እየኖሩ፣ ገዳሙ ይዞታውን እየተነጠቀ ከመጣበቡም በላይ፣ የገዳሙን ቅድስና የሚያረክሱ ተግባራት እየተፈጸመበት ይገኛል፡፡” ይላል፤ የኮሚቴው መግለጫ፡፡
የገዳሙ መነኮሳት የታሪክ ዶሴና ማስረጃ ላይ ተንተርሰው እንደሚናገሩት፤ ዓጼ ዮሐንስ በነቀርሳ ተይዘው በአቡነ ሐራ ድንግል ጸበል በመዳናቸው ነበር ለገዳሙ የአንድ ሰዓት የእግር መንገድ ያህል ስፋት ያለው ቦታ ለገዳሙ የሰጡት፡፡ ደርግ ሥልጣን ሲይዝ በገዳሙ 800 የሚደርሱ መናንያን እንደነበሩ የሚያስታውሱት መነኮሳቱ፤ በወቅቱ “መሬት ላራሹ” የሚል አዋጅ በመታወጁ የገዳሙን ይዞታ አርሶ አደሮች እየተቆጣጠሩት እንደመጡና መናንያኑ ገዳሙን ጥለው መኮብለላቸውን ያስረዳሉ፡፡
በአሁኑ ወቅት በገዳሙ ይዞታ ላይ ከ250 በላይ አባወራዎች ሰፍረው እንደሚገኙ የሚገልጹት መነኮሳቱ፤ ይህን ችግር ለመቅረፍ ለመንግሥት በተደጋጋሚ አቤቱታ ካቀረቡ በኋላ፣ መንግሥት ነዋሪዎቹን አንስቶ ሌላ ቦታ ለማስፈር ፈቃደኛ ቢሆንም፣ ለነዋሪዎች ካሣ ለመክፈል በጀት እንደሌለው በመግለጽ፣ ገዳሙ ካሣውን እንዲከፍል መወሰኑን ይናገራሉ፡፡
ሆኖም የሚከፈለው ካሣ ከገዳሙ አቅም በላይ በመሆኑ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ አግኝቶታል የሚሉት የገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም የገቢ ማሰባሰቢያ ኮሚቴ አባላት፤ ዛሬ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ ስለ ገዳሙ አሁናዊ ሁኔታና ስለገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሩ ሊቃነ ጳጳሳት፣ የገዳሙ መነኮሳት፣ የቤተክህነት አባቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደተነገረው፣ የአማራ ክልል ካቢኔ ለገዳሙ ሁሉንም ይዞታውን ባይሆንም 60 ሄክታር የሚደርስ መሬት እንዲመለስለት የወሰነ ሲሆን፤ ገዳሙ በበኩሉ ለአርሶ አደሮቹ የሚገባቸውን የመሬት ካሣ መክፈል ይጠበቅበታል፡፡
ይህን የመሬት ካሣ ለመክፈልና ለገዳሙ የማስፋፊያ ልማት ለማከናወን፣ የፊታችን ቅዳሜ ሚያዝያ 19 ቀን 2016 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል፣ በቀጥታ የቴሌቪዥን ሥርጭት፣ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ እስከ ሌሊቱ 6 ሰዓት የሚቆይ ዓለማቀፍ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር እንደሚያካሂድ ኮሚቴው አስታውቋል፡፡
ለአርሶ አደሮቹ የመሬት ካሣውን ለመክፈልና የገዳሙ ይዞታ ከተለቀቀ በኋላ በሥፍራው ለሚከናወኑ ልማቶች በአጠቃላይ 100 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው የገለጸው የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴው፤ በመላው ዓለም የሚገኙ የቤተክርስትያን ልጆችና የጻድቁ አቡነ ሐራ ወዳጆች በዚህ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ላይ በንቃትና በትጋት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርቧል፡፡
በአሁኑ ወቅት በገዳሙ የሚገኙ መናንያን ቁጥር 5ሺ እንደሚደርሱና በጾም ወቅት የጸበልተኛው ቁጥር ከ50 ሺ በላይ መሆኑን የጠቆሙት የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ አባላቱ፤ እኒህን ሁሉ በአግባቡ የሚያስተናግድ በቂ መጠለያና የልማት ሥራዎች ማከናወን አስፈላጊ እንደሆነ በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡
ለገዳሙ ድጋፍ ማድረግ የሚሹ ወገኖች፡-
በንግድ ባንክ የሒሳብ ቁጥር፡- 1000610362463
በአባይ ባንክ የሒሳብ ቁጥር፡- 9221111060954312
እንዲሁም የዶላር ሒሳብ ቁጥር፡- 634110814 መለገስ ይችላሉ ተብሏል፡፡
እባክዎ!..አንድ የጎዳና ሰው የበዓል ምሳውን ይሸፍኑልን?
እኛ ስማችን ከዚህ በታች የተጠቀሰ ጋዜጠኞችና በጎ አድራጊዎች ሶሻል ሚድያን በመጠቀም ለመጪው የፋሲካ በዓል አስታዋሽ የለሾቹን የጎዳና ተዳዳሪ ወገኖች ምሳ በማብላት በዓሉን አብረን ለማሳለፍ አቅደናል። እርስዎም ከጎናችን ይሁኑ!..ከቻሉ አብረውን ያሳልፉ?..ቢያንስ የአንድ ሰው የምሳ ወጪ በመሸፈን አጋርነትዎን ይግለፁልን?!
መርሐግብሩን ለማዘጋጀት ያቀድነው በተለያዩ ምክንያቶች ጎዳና ለወጡ ወገኖች ቢያንስ አለኝታነታችንን ለመግለፅ እና በዓሉን ደስ ብሏቸው እንዲያሳልፉ በማሰብ ነው።
ከእርስዎ የምንፈልገው እገዛ ቢያንስ አንድ ሰው በመመገብ ዓላማችንን ደግፈው ከጎናችን እንዲቆሙ ነው።
የአንድ ሰው ምገባ ወጪ ግምት 500 ብር ነው። አቅምዎ ከፈቀደ ሁለትም ሶስትም ...ወገኖችን በመመገብ ከበረከቱ መቋደስ ይችላሉ።
የ 1 ሰው ምሳ ወጪ ለመሸፈን .................500 ብር
የ 3 ሰዎችን...ለምትሸፍኑ...1500 ብር
የ 6 ሰዎችን ...ለምትሸፍኑ.... 3000 ብር
የ 10 ሰዎችን.... ለምትሸፍኑ......5000 ብር
የ15 ሰዎችን ...ለመሸፈን...7500 ብር
የ20 ሰዎችን ....ለመሸፈን...10000 ብር
***
የምገባውን ዝርዝር መርሐግብር በቀጣይ የምናሳውቅ ይሆናል።
አሁን መላክ ጀምሩ?!...
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስላሴ ቅርንጫፍ
ሒሳብ ቁጥር
1000620235818...(ቴዎድሮስ፣ፍሬው እና አለምነሽ)
***ለተጨማሪ መረጃ አስተባባሪዎች
1.ቴዎድሮስ ካሳ(+251 98 900 0089)
2.ፍሬው አበበ (+251911617935)
3..አለምነሽ ኩምሳ (+25191 164 5458)
4.ቤቴልሄም ለገሰ (+251911335511)
5.ቆንጂት ሁሴን (+251911408541)
ሲያስገቡ ደረሰኙን መላክ አይዘንጉ!!
ማኀበራዊ ሚድያን ለበጎ ተግባር በመጠቀም ለውጥ እናመጣለን!!
እናመሰግንዎታለን!!
(በብርሃኑ በላቸው አሰፋ ፣ የ”ክቡር ልጆች” መጽሐፍ ደራሲ)
ዓለም አቀፍ የመጽሐፍ ቀን፤ የንባብ ባህልን ለማዳበር፣ ደራስያንንና አታሚዎችን ለማበረታታት ይከበራል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1995 ዓ.ም ነበር ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ የመጽሐፍ ቀን የተከበረው፡፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት ቀኑን የንባብ ልማድ እንዲዳብርና በተለይም ወጣቱን ትውልድ በማነቃቃት፣ የመረጃ ፍሰቱ በንባብ እንዲጎለብት ለማበረታታት በየዓመቱ ያስበዋል፡፡
በሀገራችንም ሀርመኒ ሂልስ ት̸ ቤት በትላንትናው ዕለት በተለያዩ ዝግጅቶች ቀኑን አክብሯል፡፡ ት̸ ቤቱ ደራሲያን መጽሐፍቶቻቸውን ለተማሪ ወላጆች እንዲያስተዋውቁ በማድረግ፣ የልጆች መጽሐፍ ደራሲያን ለተማሪዎች መጽሐፍ እንዲያነቡ በማድረግና የተማሪዎችና መምህራን መጽሐፍ የማንበብ ስነ ስርዓት በማካሄድ ዓለማቀፍ የመጽሐፍ ቀንን በድምቀት አስቦታል፡፡ በመርሃግብሩ ላይ የልጆች መጽሐፍ ደራሲ እምነቴ ድልነሳን ጨምሮ ሌሎችም ታድመዋል፡፡
የት̸ ቤቱ ዳይሬክተር ሩት መንበረ፣ ተማሪዎች የንባብ ባህላቸውን እንዲያሳድጉ ታስቦ ቀኑን አክብረነዋል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኤሌክትሮኒክስ የመጽሐፍ ንባብ ትልቁ ተግዳሮት በመሆኑ ልጆች በፍቅር እንዲያነቡ ምቹ ሁኔታን እየፈጠሩ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
ልጆች እና መጻሕፍት
በቅርቡ የተካሄደ አንድ ጥናት እንዳመለከተው፤ ምንም እንኳን 70 በመቶ ወላጆች ማታ ማታ ለልጆች ጣፋጭ ታሪኮችን ማንበብ አስፈላጊነቱን ቢያምኑም፣ ግማሽ ያህሉ ብቻ ይተገብራሉ፡፡ ከአምስት ቤተሰቦች አንዱ ደግሞ በስራ ብዛት የተነሳ ለልጆች የማንበብ ልማድ የለውም፡፡
ይሁን እና ማምሻውን የሚነበቡ ተረቶች ምን ጥቅም አላቸው ?
በወላጅና በልጅ መካከል ያለውን ግንኙነት ያጠናክራሉ
የልጆችን የማንበብ ክህሎት ያዳብራሉ
የልጆችን የፈጠራ አቅም ያጎለብታሉ
የልጆችን የቃላት ችሎታ ያሳድጋሉ
የልጆችን የስሜት ብስለት ያዳብራሉ
የልጆችን የአእምሮ ጤና ያበለፅጋሉ
ለአካላዊ ጤንነት ምግብና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ሁሉ ለአእምሮ እድገት ደግሞ ንባብ ወሳኝ ሚና አለው፡፡ ከመዋዕለ ህጻናት እስከ አራተኛ ክፍል ልጆች ለማንበብ መሰረታዊ ክህሎትን ይማራሉ፡፡ ከአራተኛ ክፍል ጀምሮ ደግሞ ለመማር ያነባሉ፡፡ የፔዳጎጂ ፅንሰ ሃሳብም ተማሪዎች በራሳቸው እንዲማሩና በቀላሉ እንዲገነዘቡ በማድረግ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ ይህ ደግሞ የማንበብ ፍላጎትና ተነሳሽነት ይጠይቃል፡፡
መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፤ የልጆች የንባብ ክሂል ብቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ ነው፡፡ የሃገራችን ተማሪዎች የመጀመሪያ እርከን ሲጨርሱ ለምን ማንበብ ያዳግታቸዋል ? የተነበበላቸውን ለምን መረዳት ይቸግራቸዋል ? የሚሉት ጥያቄዎች መልስ ያሻቸዋል፡፡
ልጆች የማንበብ ልማድን እንዲያዳብሩ
በየቀኑ ማንበብ ማለማመድ
የስነ ልቦና ባለሙያዎች እንደሚሉት፤ በየቀኑ ለ20 ደቂቃ ተረት ማታ ማታ የሚነበብላቸው ልጆች፣ የአእምሮ ጤናቸው ከመጠበቁ ባሻገር የፈጠራ አቅማቸው ከፍ ያለ ነው፡፡
ወላጆች መጽሐፍትን በማንበብ አርአያ ሊሆኑ ይገባል
ምቹ የንባብ ከባቢ መፍጠር
ከልጆች ጋር ቤተ መጽሐፍት መጎብኘት
ልጆች የሚፈልጉትን መጽሐፍ እንዲመርጡ እድል መስጠት
ልጆች ደስ የሚላቸውን መጽሐፍ ደጋግመው እንዲያነቡ ማበረታታት ይገኙበታል፡፡


*በኤክስፖው ከ30ሺ በላይ ለሚሆኑ ጎብኚዎች  ነጻ የህክምና  ምርመራ ይሰጣል

አፍሮ-ኤዥያ ዓለማቀፍ የጤና ኤክስፖ፣ እዚህ አዲስ አበባ በኤግዚቢሽን ማዕከል፣ ከግንቦት 9-11 ቀን 2016 ዓ.ም ለሦስት ቀናት  ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ፡፡

በኤክስፖው ላይ ከ400 በላይ የአገር ውስጥና የውጭ ድርጅቶች፣ ከ30ሺ በላይ ጎብኚዎችና  ከ2ሺ በላይ የጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች  ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡

የጤና ኤክስፖውን አስመልክቶ አዘጋጆቹና አጋር ተቋማት  ዛሬ ከሰዓት በኋላ 8 ሰዓት ላይ በራማዳ  ሆቴል የሚዲያ ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት  ሰፊ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡



በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደተመለከተው፣ በጤና ኤክስፖው  ላይ የፓናል ውይይቶች፣ ዎርክሾፖችና ኤግዚቢሽኖችን ጨምሮ በርካታ ኹነቶች ይቀርባሉ፡፡ የጤና ባለሙያዎች የልምድ ልውውጥ የሚያደርጉበትና የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግር የሚካሄድበት እንዲሁም የትስስርና የትብብር ዕድሎች የሚፈጠርበት  መድረክ እንደሚኖርም ተጠቁሟል፡፡

ኤክስፖው በጤና አጠባበቅ ኢንዱስትሪ ውስጥ የህዝብ ጤናን፣ ፋርማሲዩቲካልስን፣ የህክምና ቴክኖሎጂንና ሌሎች በርካታ ርዕሰ ጉዳዮችንና ዘርፎችን እንደሚሸፍን የተገለጸ ሲሆን፤ ይህ ሁሉን አቀፍ አቀራረብም ተሳታፊ ድርጅቶችና ጎብኚዎች በተለያዩ መስኮች ከአዳዲስ ዕድገቶችና ፈጠራዎች ጋር እንዲተዋወቁ ዕድል ይፈጥራል ተብሏል፡፡

“ድልድዮችን እንገንባ፣ ህይወትን እናድን” በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ ዓለማቀፍ የጤና ኤክስፖ፤ ከ30ሺ በላይ ለሚሆኑ ጎብኚዎች ነጻ የጤና ምርመራ የሚከናወን ሲሆን፤ ለጤና አጠባበቅ  ባለሙያዎችም ነጻ ሥልጠና እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡

ለሦስት ቀናት በሚቆየው የአፍሮ- ኤዥያ ዓለማቀፍ የጤና ኤክስፖ ላይ ከህንድ፣ ዱባይ፣ ታይላንድ፣ ቱርክ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ማላይዥያና ሌሎችም አገራት የተውጣጡ በጤና ላይ የሚሰሩ ተቋማትና ባለሙያዎች እንደሚሳተፉበት ተጠቁሟል፡፡

ኤክስፖው ከወትሮው በተለየ በቢዝነስ ላይ ብቻ የሚያተኩር ሳይሆን፣ ተቋማት ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን ለመወጣት ልዩ ዕድል የሚያገኙበት እንደሆነም ተነግሯል፡፡

ይህን ዓለማቀፍ የጤና ኤክስፖ ኤፍዚ ማርኬቲንግና ኮምዩኒኬሽን ኃ.የተ.የግ. ማህበር ከሰላም ኸልዝ ኮንሰልታንሲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሲሆን፤ ሳልማር ኮንሰልታንሲ፣ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር፣ የኢፌዲሪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ባለሥልጣን፣ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብና መድሃኒት ባለሥልጣን እንዲሁም የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት በአጋርነት እንደሚሳተፉበት ታውቋል፡፡

For more than 3,000 years, the Jewish people have reenacted their journey to freedom during the Passover festival, as they joyously celebrate the Children of Israel's exodus from slavery in Egypt to a life of liberty and independence in the Land of Israel.

This holiday’s message can resonate with people of diverse backgrounds and beliefs, as it emphasizes the universal yearning for personal and collective freedom. Always coming just before the Ethiopian and other Eastern Christians’ celebrations of Fasika/Easter, the Passover holiday is one part of a larger holiday season which touches us all, Israelis and Ethiopians alike.

This year, however, our joy is tinged with sadness. As Israeli families gather for the traditional Seder meal, the Passover dinner will be accompanied by sorrow for our fallen soldiers and civilians, prayers for the recovery of the wounded, and expressions of solidarity with the tens of thousands of displaced Israelis who cannot return to their homes. Many families will set an empty place at their Passover table to symbolize our longing for the release of the 133 men, women and children still being held hostage in Gaza in the most horrific conditions imaginable.

Since October 7th, Israel has been confronted with brutal attacks and existential threats emanating from the Iranian regime and its many proxies, from Hamas in Gaza to Hezbollah in Lebanon, through the Houthis in Yemen to other militias and terrorists in Syria and Iraq. These self-declared enemies of the Jewish state openly threaten Israel with complete annihilation. More ominously, they have not hesitated to try and turn their malevolent aspirations into reality, as recently demonstrated by Iran's massive missile and drone attack and Hamas' massacre of 1,200 Israelis on 7 October.

Despite the resounding success in repelling Iran's attack on 14 April, realized with the extraordinary cooperation of the US and Israel’s allies in Europe and the region, as well as the exemplary military accomplishments made in the fight against Hamas in the Gaza Strip, the war is not yet over. Much remains to be done, including the restoration of deterrence against the Ayatollahs' regime and its proxies. This step is essential to preventing additional direct attacks on Israel, and also to stopping the spread of the Islamic revolution worldwide, Iran's efforts to become a nuclear power, and its ballistic missiles program.

A key element is the designation as a terrorist organization of the Iranian Revolutionary Guard Corps (IRGC) - which is a primary pillar of support of the regime and the spearhead of its repressive policies in Iran and aggressive actions abroad.
This war is not only about Israel. It is a combat waged with our allies to protect our shared values and the freedoms we hold so dear.

Jewish history is the story of prevailing, of a people that overcomes obstacles and challenges against all odds. The age-old longing to return to the Jewish homeland, as expressed every Passover with the words “Next year in Jerusalem," inspired generation after generation with the dream of becoming again a free people in the Land of Israel.
Alongside freedom, Passover bears a powerful message of resilience and optimism. This year too, despite the present situation, we will be strengthened by our heritage and will look forward towards the future with faith and hope.

Israel must fight to protect its citizens and their liberty against murderous aggressors. However, we will not abandon the struggle to live in peace and coexistence with other peoples of goodwill in our region.

May the festivals of Passover and Fasika bring Israel and Ethiopia – our countries and peoples – many blessings of health, peace and prosperity.

በባሮክ ኢቨንት ኦርጋናይዘር አ.ማ የተዘጋጀው የፋሲካ ባዛርና ኤክስፖ ቅዳሜ ሚያዝያ 12 ቀን 2016 ዓ.ም ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ባለሃብቶችና ታዋቂ ግለሰቦች በተገኙበት በሚሊኒየም አዳራሽ በይፋ ተከፈተ፡፡

የፋሲካ ባዛርና ኤክስፖው እስከ ሚያዝያ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ለጎብኚዎች ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ ታውቋል፡፡

በዚህ ባዛርና ኤክስፖ ሸማቹ የህብረተሰብ ክፍል በዓልን ምክንያት አድርጎ ከሚገጥመው የዋጋ ንረት በተመጣጣኝና በቅናሽ ዋጋ ከራሱ ከአምራችና አስመጪው የሚገበያይበት ሲሆን፤ አምራችና ሸማቹም ከፍተኛ የገበያ ሽያጭ በማግኘት ተጠቃሚ የሚሆንበት ነው ተብሏል፡፡

ከተከፈተ 17ኛ ዓመቱን ያስቆጠረውና እስካሁን ከ3ሺ800 በላይ የፋሽን ዲዛይነሮችን አሰልጥኖ ያስመረቀው ኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ ፤ አዲሱን የማስተር ክላስ ሥልጠናውን ቅዳሜ ምሽት ሚያዝያ 12 ቀን 2016 ዓ.ም ቦሌ ዩጎ ሰርች አጠገብ በሚገኘው ሪያሊቲ ፕላዛ ህንጻ ላይ በይፋ መጀመሩን አስታወቀ፡፡

የፋሽን ማስተር ክላስ ከሚሰጣቸው ሥልጠናዎች መካከል፡- ስፔሻል ፓተርን ዲዛይን፣ አርት ድሮዊንግ፣ ፋብሪክ ፔይንቲንግ፣ ፋሽን ስታይሊንግ፣ 3ዲ ዲዛይን፣ ፋሽን ማኔጅመንትና ሌሎችም ይገኙበታል ተብሏል፡፡

የኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ መሥራችና ባለቤት ወ/ሮ ሣራ መሃመድ በምሽቱ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ “ማስተሪንግ ክላስ ሰዎች እንደ መክሊታቸው (ተሰጥኦዋቸው) ሥልጠና የሚያገኙበት ፕሮግራም ነው” ብለዋል፡፡



በምሽቱ በኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ ተመራቂዎች የተዘጋጀ ለየት ያለ የፋሽን ትርኢት ለታዳሚዎች ቀርቧል፡፡

ኮሌጁ ከዓለማቀፍ ተመሳሳይ የማሰልጠኛ ተቋማት ጋር በፈጠረው መልካም የሥራ ግንኙነት 42 ዲዛይነሮች በህንድ አገር ሙሉ የነጻ ትምህርት እንዲያገኙ በማድረግ ሥልጠናቸውን ተከታትለው በመመለስ ለኢንዱስትሪውና ለአገራቸው ትልቅ አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡

ኮሌጁ ባለፉት ዓመታት  ከሥልጠናው ጎን ለጎን የተለያዩ የፋሽን ትርኢቶችን ከአገር ውስጥ ባሻገር በኒውዮርክ፣ ፈረንሳይ፣ ጣልያን፣ ጀርመን፣ ስዊዘርላንድ፣ ኡጋንዳና ሌሎች አገራትም ማቅረቡ ታውቋል፡፡
ኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ የማስተር ክላስ ስልጠናውን በይፋ ጀመረ

ከተከፈተ 17ኛ ዓመቱን ያስቆጠረውና እስካሁን ከ3ሺ800 በላይ የፋሽን ዲዛይነሮችን አሰልጥኖ ያስመረቀው ኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ ፤ አዲሱን የማስተር ክላስ ሥልጠናውን ቅዳሜ ምሽት ሚያዝያ 12 ቀን 2016 ዓ.ም ቦሌ ዩጎ ሰርች አጠገብ በሚገኘው ሪያሊቲ ፕላዛ ህንጻ ላይ በይፋ መጀመሩን አስታወቀ፡፡

የፋሽን ማስተር ክላስ ከሚሰጣቸው ሥልጠናዎች መካከል፡- ስፔሻል ፓተርን ዲዛይን፣ አርት ድሮዊንግ፣ ፋብሪክ ፔይንቲንግ፣ ፋሽን ስታይሊንግ፣ 3ዲ ዲዛይን፣ ፋሽን ማኔጅመንትና ሌሎችም ይገኙበታል ተብሏል፡፡

የኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ መሥራችና ባለቤት ወ/ሮ ሣራ መሃመድ በምሽቱ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ “ማስተሪንግ ክላስ ሰዎች እንደ መክሊታቸው (ተሰጥኦዋቸው) ሥልጠና የሚያገኙበት ፕሮግራም ነው” ብለዋል፡፡

በምሽቱ በኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ ተመራቂዎች የተዘጋጀ ለየት ያለ የፋሽን ትርኢት ለታዳሚዎች ቀርቧል፡፡

ኮሌጁ ከዓለማቀፍ ተመሳሳይ የማሰልጠኛ ተቋማት ጋር በፈጠረው መልካም የሥራ ግንኙነት 42 ዲዛይነሮች በህንድ አገር ሙሉ የነጻ ትምህርት እንዲያገኙ በማድረግ ሥልጠናቸውን ተከታትለው በመመለስ ለኢንዱስትሪውና ለአገራቸው ትልቅ አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡

ኮሌጁ ባለፉት ዓመታት  ከሥልጠናው ጎን ለጎን የተለያዩ የፋሽን ትርኢቶችን ከአገር ውስጥ ባሻገር በኒውዮርክ፣ ፈረንሳይ፣ ጣልያን፣ ጀርመን፣ ስዊዘርላንድ፣ ኡጋንዳና ሌሎች አገራትም ማቅረቡ ታውቋል፡፡

አሜሪካ በእርስ በርስ ጦርነቱ ወቅት ያጣችው የሰው ሕይወትና ሀብት የትየለሌ ነው። በዘመኑ የነበረው አብረሃም ሊንከን፣ ለአሜሪካ ዳግም ሀገር መሆን የከፈለው ዋጋና የፈሰሰው የዜጎች ደም ቀላል አይደለም።

የኋላ ኋላ ጦርነቱ አብቅቶ፣ችግር በሰማዩ ላይ ካረበበ በኋላም የመከራው ገፈት ቀማሽ ሕዝቡ ነው። ሠራተኛ ከሥራ ሲቀነስ፣ወታደር ወደቤተሰቡ ሲመለስ፣ብዙ ቤተሰብ ወላጅና ልጆቹን ሲያጣ፣የጨለማው ድባብ፣የሐዘኑ

ምሬት ሀገሪቱን ሲዖል አድርጓት ነበር።
እውነት ነው፤ በጦርነቱ የአንድነት ኀይሉ አሸንፏል። የደቡቡ ወገን የሮበርት ሊ ጦር ተሸንፏል። ዩሊሰስ ግራንት ሲማርክ፣ሮበርት ሊ ከእነ ጦሩ ተማርኳል። ከጦርነቱ በኋላ ደብዛው ጠፍቶ የቆየው ጀኔራል ሸርማን፣

ዐሳውን ለማጥመድ ባሕሩን ብሎ አትላንታን በከባድ ምት ቢመታም፤የአትላንታ ቁስልና ጠባሳ፣መልሶ የአሜሪካ ነው። የገደለው ባልሽ የሞተው ወንድምሽ፣ሐዘንሽ ቅጥ አጣ፣ከቤትሽ አልወጣ ፤ነበር ነገሩ።
እውነት ለመናገር፣ከእርስ በርስ ጦርነት ይልቅ ከሌሎች ሀገራት ጋር የሚደረጉ ጦርነቶች ቀላል ናቸው። ለዚህ ደግሞ ማሳያዋ ራሷ አሜሪካ ናት። ለምሳሌ በዐለም ላይ ካደረገቻቸው ጦርነቶች ይልቅ የበርካታ ሰዎች

ሕይወት ያለፈው በእርስ በርስ ጦርነቱ ነው። በንጽጽር እንይ ከተባለ፣
በኮሪያ ጦርነት -  54,000
በቬትናም -  58,000
በሁለተኛው የዐለም ጦርነት-  400,000
በአንደኛው የዐለም ጦርነት-  117,000
በእርስ በርሱ ጦርነት - 620,000
የዜጎች ሕይወት ጠፍቷል።
ከዚህ በተጨማሪ፣  የደረሰው የኢኮኖሚ ቀውስ ቀላል አይደለም። ይህ ቀውስ የሚለካው ለጦርነቱ በወጣው ወጭና በጦርነቱ በወደሙት ንብረቶች ብቻ ከሆነ ግምታችን የተሳሳተ ነው። በጦርነቱ የሚያልቁት ወጣቶች

ጭንቅላትና አቅም፣ በገንዘብ የማይተመን ተዐምር ሠሪ ሀብት ነው።
ቅድም ካነሳነው የአሜሪካ ጦርነት ጀርባ፣ተገኘ ከሚባለው ድል በስተኋላ፣በርካታ የአሜሪካ እናቶች አልቅሰዋል። ኁልቁ መሳፍርት የሌላቸው  የሠርግ ሳይሆን የልቅሶ ድንኳኖች በየደጁ ተጥለዋል። በዚህ በተጣሉት የልቅሶ

ድንኳኖች ሳቢያ እንባ እንደጎርፍ ያፈሰሱት ጥቂት አይደሉም።
በተለይ በአሜሪካ ታሪክ ለሊንከን አድናቆት ያጎረፈለት አንድ ያልተለመደ ነገር ነበር። ያም አምስት ልጆቿን ላጣችው እናት በራሱ እጅ የማጽናኛ ደብዳቤ መጻፉ ነው። የሚገርም ነው። የአንዲት ታላቅ ሀገር

ፕሬዚደንት እስከመኖሯም ለማትታወቅ አንዲት መናጢ ደኻ እናት፣ ደብዳቤ መጻፉ ጉድ ያስብላል። ይሁን እንጂ በምንም ሁኔታ ላይመለሱ የተቀጠፉትን የሕይወቷን ተስፋዎች አይመልስልትም። ለሊንከን ታላቅ

የፖለቲካ ድል ነው፤ለእናትየው ግን የማይጠገን ስብራት ነው።
ጦርነቱ በድል ተጠናቅቆ ሲያበቃ፣በደማቁ ድል ማግስት ወደ ጎተራ የሚገባ አንድ ኩንታል እህል የለም። የሚለቀመው አጥንት ነው። የሚተርፈው ጸጸት ነው። የዚህ ዐይነት በርካታ ጦርነቶች አልፈዋል። እናቶች ልጆቻቸው

እንደ ችቦ እጅብ ብለው እየዘፈኑ ሄደው፣ላይመለሱ ነድደው ሲቀሩ፣ወገባቸውን አሥረው በእንባ ሲታጠቡ ማየት የሕዝቦች ዕጣ ነው። በነዚያ በነደዱት ወጣቶች ብርሃን ሀገር አትደምቅም፤ከአድማሱ ላይ ጨለማ

አይወገድም። እንደገና ሌላ ወጣት ይገበራል። አንዳንድ ሀገራት የዚህ ዐይነት ጦርነቶች እንዳይደገም፣ዳናቸውም ወደሚቀጥለው ትውልድ እንዳያልፍ፣ ከዚያችው ቀን ጀምረው መስመር ያበጃሉ። ለዚያ ሰቀቀን ሥዕል

ያበጁለታል፤ትዕይንቱ እንዳይደገም መሰመር ያሠምራሉ። አንዳንዶች ግን እንደ መዝሙር ያዜሙታል፤እንደ ውበት ይተርኩታል።
ቁስሉን እንደ ንቅሳት፣ሕመሙን እንደ ምቾት ያቀነቅኑታል።...የወንድ ልጅ እናት ታጠቂ በገመድ፣ልጅሽን አሞራ እንጂ አይቀብረውም ዘመድ፤ እያሉ እናት ወልዳ ለፍሬ ሳይሆን፣ወልዳ ለአሞራ መስጠት እንዳለባት

ይነገራታል። ወይም በሌላ ዜማ፣”መላኩ ተፈራ፣
የእግዜር ታናሽ ወንድም፣የዛሬን ማርልኝ
ዳግም ወንድ አልወልድም” ይባላል።
የጀግና እናት እንባ የሌላት ቋንጣ ሆና እየነደደች ትኖራለች። በአንድ ጦርነት ውስጥ እናት ብቻ ሳትሆን እናት ሀገርም ብዙ የተስፋ ቡቃያዎቿን ታጣለች። ጠመንጃ ይዘው በየፈፋው የወደቁ ልጆቿ መልክ ቢፈተሽ፣ብዙ

ሳይንቲስቶች፣ሺህ መሐንዲሶች፣ተመራማሪዎች፣ወዘተ ይኖራሉ። ይህን ለማየት በዐለማችን ላይ ከተደረጉ ጦርነቶች የተረፉና በኋላ የታላላቅ ግኝቶችና ውጤቶች ባለቤት የሆኑ ሰዎችን ማየት በቂ ነው።እንግዲህ እነዚህ

ትሩፋን ከሞት አፍ ስለወጡ ያንን ሠሩ እንጂ አብረዋቸው ወድቀው የቀሩት ምን ሊሠሩ ይችሉ እንደነበር የሚገምት የለም። ብቻ በድኑ ያምማል።
ታዲያ እነዚያ ሁሉ ወደ ተሰጥዖና ክሎታቸው ሳይደርሱ እሳት በልቶ ዐመድ ያደርጋቸዋል። ወጣቶች በጦርነት ውስጥ ሲማገዱ፣ያልተፈለፈሉ እንቁላሎች ናቸው። ገና ፍሬያቸው ሳይታይ፣ቀናየውን ሳያገኙ ከንቱ ሆነው

ይቀራሉ። ይህ በሰው ልጆች ታሪክ አሳዛኙ ትራጀዲ ነው።
ጦርነት አንዳንዴ ፈጣን ፈውስ፣ወሳኝ መፍትሔ ሊሆን ይችላል። ሰው በገዛ ሀገሩ በነፃነት እንዳይኖር፣ቀንበር ጫንቃው ላይ ሊጭኑበት “አጎንብስልኝ”ሲሉት፣ተቆጥቶ ከሺህ ቀን ባርነት የአንድ ቀን ነፃነት ሲል፣ያኔ “አንዱን

ወንድ እንደሺህ...መመረቅ ግድ ይላል። ሠፈር ተቀምጦ የሚያውደለድል፣ጦር ግንባር ሄዶ ጠላቱን አምሶ ሲያልፍ፣ የጀግና ዘፈን ይዘፈንለታል እንጂ ደረት ተጥሎ አይለቀስም። ጭካኔውም እንደ ርኅራኄ ይታያል።
በጀመርናት ኀያል ሀገር መሪ በትሩማን ገጠመኝ ሰው መግደል፣ ማረፍና ማሳረፍ የሚሆንበትን አጋጣሚ እንይ። ከዕለታት በአንዱ ቀን የ18ኛው ፕሬዚደንት የዩሊሰስ ግራንት ሴቶች ልጆች ትሩማን ቤት ይገኙና ሁሌ

የሚገርማቸውን ጥያቄ ይጠይቋቸዋል።
“ለመሆኑ ሒሮሽማና ናጋሳኪ ላይ ቦምብ ያስጣሉ ቀን እንቅልፍ ወሰደዎት?”
ሲሏቸው፣ መልሳቸው የሚያስደነግጥ ነበር።
“በጣም ኀይለኛ እንቅልፍ ነበር የወሰደኝ” አሉ።
”እንዴት በሰዎች ላይ ያንን ሁሉ እሳት አዝንበው፣ እንቅልፍ ሊወስዳቸው ቻለ?”ብለን መጠየቃችን አይቀርም። ይሁን እንጂ ጉዳዩ ሲፈተሽ፣የጦርነቱ መንሥዔና ዓላማ ሌሎችን ዕረፍት ለመንሳት ኂትለር የጠነሰሰው

ስለነበር፣ሌሎቹ የሚዋጉት ለህዝባቸው ሕልውናና ለሀገራቸው ሉዐላዊነት ስለነበር፣ጦርነቱን በድል ደምድሞ ከዚያ አንገፍጋፊ ስቃይ መውጣት ያስፈልግ ነበር።
ጦርነቱን ያለማሸነፍ ደግሞ የሚያስከትለው ፍዳ እንቅልፍ አይሰጥም። ይሁን እንጂ ጦርነትን ከሚያዝዘው በላይ ጦርነቱ ላይ በቀጥታ የተሳተፈው ወታደር የተለየ ስሜት ሊፈጠርበት ይችላል። በዚያው ጦርነት

የመጀመሪያውን ጄት ያበረረው ምክትል የመቶ አለቃ፣በሕይወቱ ላይ የተፈጠረው ቀውስ ሌላ ነበር። ያ ወጣት መኮንን ቦምቡን ሲጥል፣ የተጣለበት የከተማዋ ነዋሪዎች የጮኹት ጩኸት በእዝነ-ልቡናው

እየተሰማው፣ምስላቸው በዐይነ ሕሊናው እየታየው እንቅልፍ እምቢ አለው። ምንም ዐይነት ሱስ ያልነበረበት ሰው፣ሲጋራ ማጤስ፣መጠጥ መጠጣት ጀመረ። ጦርነት መልኩ ብቻ ሳይሆን ውጤቱም ልዩ ልዩ ነው።

ከጦርነቱ ዳር የሚያጋፍረውና ውስጥ ሆኖ የሚፋለመው የስሜት ድንበራቸው ይለያያል።
በአሜሪካው የእርስ በርስ ጦርነት ከግማሽ ሚሊየን በላይ ሕዝብ አልቆ፣ቁጥር ስፍር የሌለው ውድመት ደርሶ መጨረሻ ላይ የሁለቱ ወገን የጦር አዛዦች ሲገናኙ፣ ስለቀደመውና በሜክሲኮ ጦርነት አብረው በነበሩበት

ጊዜ ስለሠሩት የሼክስፒር ቴአትር ማውራት ጀምረው ነበር። የዚያ ሁሉ ሰው ደም መፍሰስ ከኪሳራና እልቂት ውጭ አንዳች ጥቅም የለውም። በምንም መንገድ ቢሰላ፣በየቱም አቅጣጫ ቢተነተን፣ ከኪሳራ የተለየ

ውጤት ሊያመጣ አይችልም።
የአሜሪካው ልዩነት ግን ያንን ጦርነት፣ “ጠባሳን ያየ በእሳት አይጫወትም” ማለታቸው ነው።
ለሀገራቸው ጥቅም ብለው እስካሁን ሲዋጉ እንኳ፣በገዛ ምድራቸው ሳይሆን በሌሎች ሀገራት ነው። እኛ ግን ዘመናችንን ሁሉ በጦርነት የፈጀን፣ጦርነት መዋጋት ብቻ ሳይሆን፣መፍጠር እንችላለን ብለን

የምንመጻደቅ፣ውርደትን እንደ ክብር የምንቆጥር ነን። ጀግና ብለን የምንዘፍንላቸውና ስማቸውን የምናነሳቸው እንኳ ጦር ሜዳ የዋሉ፣የውጭ ጠላት ብቻ ሳይሆን ወገናቸውን የገደሉትን ነው።
አሳዛኙ ነገር ብዙ ጊዜ ከፈረንጅ ብድር የምንወስደው፣ፋብሪካ ለመገንባት፣እርሻ ለማስፋፋት አይደለም፤ለመገዳደል ነው። የሥልጣን ውርርሳችንም ሁሌም በሚባል ደረጃ በጠመንጃና በኀይል ስለሆነ፣ከጥንት ጀምሮ በአንድ

እጃችን ጠመንጃ፣በሌላኛው ዳቦ ስንለምን እንኖራለን። የተፈጠርነው ለጦርነት እስኪመስል ድረስ ጭር ሲል አንወድድም፤በየትውልዱ የጦርነት እሳቶች ይነድዳሉ፤ወጣቶች እንደችቦ እሳት ውስጥ ገብተው ይነድዳሉ።

ወልዶ፣አሳድጎ ለእሳት መቀለብ ብርቃችን አይደለም። ወንድምን ገድሎ መፎከር እንደ እርም አይቆጠርም። በቀደሙት አባቶቻችን ዘመን እንደሚሰማው፣ልጃገረዷ ወፍጮ ላይ ሆና እህሉን እየሸረከተች፣ግጥም

ስትገጥም፣ዜማ ስታንቆረቁር ወንዱ ፈረሱን ጭኖ ለግድያ ይወጣል። ወይ ይገድላል፤አሊያም ይሞታል። በቅርቡ ዘመን ደግሞ ዘመናዊው ኪነት ጦር ግንባር ድረስ ሄዶ “ወደፊት በሉለት፣ይለይለት”ይላል።
ይህ በራሱ ሀገር ለማዳን ሲሆን ችግር የለበትም፤ምርጫ ሲጠፋ ሀገር መፍረስ አይገባትም። ግን ከጦርነት ሌላ ምርጫ የለም ወይ?...ችግሮችን ለመፍታት ተሞክሮ ካልተሳካ በስተቀር፣እርቅን ገፍተው ካልመጡብን

ለምን እንጋደላለን?...ለምን ገንዘባችን ይባክናል?..ሥራ አጦችን ጦር ሜዳ ወስደን ከምንማግድ፣ለምን ጠመንጃና መድፍ በምንገዛበት ብር ፋብሪካ አናቋቁምም?...እኛ ዕድገት አያስፈልገንም?...ጥሩ

ኑሮ፣ጥሩ ሕይወት አይገባንም?...በሳይንስና ቴክኖሎጂ፣በጥናትና በምርምር ከዐለም ሕዝቦች ጋር እኩል እንዳንራመድ ማን ከለከለን? ገንዘባችንስ ለልማት የሚውለው መቼ ነው?..አንጀታችንን አሥረን መልማት

ሲገባን፣አንጀታችንን አሥረን ከጠገበ ፈረንጅ መሳሪያ በመግዛት ኪሱን የምናሳብጠው እስከ መቼ ነው?
ፕሮፌሰር መስፍን፤ ስለ እኛ ጦርነት ወዳድነት እንዲህ ሲሉ ጽፈው ነበር፤
“...ጦርነትን፥ጀግንነትንና ገዳይነትን እንደ ትልቅ የክብርና የማዕረግ ምንጭ አድርጎ የሚመለከት ሕዝብ ታሪክ፤ በአጠቃላይ የጦርነት ታሪክ ቢሆን የሚያስደንቅ አይደለም። ሌላው ትልቁና አስገራሚው ነገር፣ጦርነቶቹ

በአብዛኛው በውጭ ሰዎች ቁስቆሳ የተደረጉና የተጀመሩ መሆናቸው ነው። በተለይ ቅኝ ገዢዎች በየዐውደ-ውጊያው ያጡትን ድል በተለያዩ ስልቶች በመጠቀም ሊበታትኑን ሞክረዋል።
አንዳንዶቹ እንድንገነጣጠል፣ሌሎቹ እርስ በርስ እንድንዋጋና ሰላም እንድናጣ ሌት ተቀን ሠርተዋል። እኛም ማስተዋል ስላቃቸን ጦር መዝዘን ተላልቀናል። በተለይ በቅርብ ዐመታት የብሔር ብሔረሰቦችን መብት ታክኮ

የመጣው ጥላቻ፣ ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ሀገራችንን አደጋ ላይ ጥሏታል። በደርግ ዘመን በሕወሓት የሚመራው ኀይል አምፆ በተደረገው የዐሥራ ሰባት ዐመታት ጦርነት፣ የጠፋው የሰው ሕይወትና የባከነው ሀብት

ለልማት ቢውል ኖሮ ምን ያህል መራመድ እንችል እንደነበር መገመት አያዳግትም።
በወቅቱ ጭቆናን ተቃውሜያለሁ ያለው ደርግ፣ በተራው ጨቋኝ ሆኖ፣ዐማፅያን እግሩ ሥር ሲፈለፈሉ፣ከመደራደር ይልቅ በጠመንጃ ብቻ መፍትሔ ለማምጣት አስቦ የማያቋርጥ ጦርነት ውስጥ ገብቷል።

በቀጣዩ፣ሥልጣን ላይ የወጣው ወያኔ መራሹ መንግሥትም ከደርግ ስላልተማረ፣ወዲያውኑ ኦነግን ከመንግሥት መዋቅር በመንቀል የሴራ ፖለቲካውን ጀምሮ እርሱም በተራው እያሳደደ የሚገድለው አንድ ጠላት አዘጋጀ።

...እናም ተራራና ሜዳው ባሩድ ማሸተቱን፣ደም መጠጣቱን ቀጠለ። በምሥራቅ ኢትዮጵያም በተመሳሳይ ሌላ ተቃዋሚ ተፈጥሮ የተለመደው ደም የመፋሰስ መንገድ ቀጠለ።
በምሥራቅ ኢትዮጵያም በተመሳሳይ ሌላ ተቃዋሚ ተፈጥሮ የተለመደው ደም የመፋሰስ መንገድ ቀጠለ። ከዚያም በኋላ ሀገራችን ከጦርነት አላረፈችም። ከጦርነት የሚገኝ ምንም ትርፍ ያለመኖሩን እያወቅን እንኳ

ከጦርነት አንወጣም። እንደ ኅበረተሰብ እልኸኞችና ዳተኞች ስለሆንን፣ ነገሮችን በይቅርታና በእርቅ መፍታት አይሆንልንም። ስለዚህ በቅርብ ዐመታት እንኳ በሰሜን ኢትዮጵያ ዘግናኝ የሆነ ጦርነት አካሂደናል። ይሁንና

ከጦርነቱ ማግስት የሰበሰብነው ሬሳ እንጂ ሀብት አይደለም። ያፈራነው አካል ጉዳተኝነት፣ጉሥቁልናና ረሀብ እንጂ ጥጋብና ፍስሃ አይደለም።
ወያኔም ሆነ የመንግሥት ሠራዊት ያወደሙትን  ሀብትና ንብረት፣ መልሰን የምንተካው እኛው ራሳችን ነን። ትግራይ ውስጥ ትምህርት ቤቶች መቃጠላቸው ኪሳራው ዞሮ የሚያንኳኳው የኛኑ ቤት ነው። አማራ ክልል

የፈራረሱት ተቋማት፣ የትግራይንም ክልል ይጎዳሉ። እኛ ያፈረስነውን የምንገነባው ራሳችን እንጂ ሌላ ማንም አጥደለም፡፡  ዳቦ ስንለምን የምንለምነው ሁላችንም ነን።
ትናንት፣ከትናንት ወዲያ፣ዛሬም ጦርነት ውስጥ ነን። እረፍት ኖሮን አያውቅም፤ብራችን ለልማት አልዋለም።ቁስላችን አልደረቀም፤እንባችን አልታበሰም፤እልሀችን አልተነፈሰም። ታዲያ ጦርነት ጥቅሙ፣ሞትና ድኽነት

ከሆነ፣ለምን ምክክርና ውይይትን፣ሰላምና ይቅርታን ለምን አንሞክርም?...ምድራችን ከደም ለምን አታርፍም?...ለመሆኑ ሰው ዐይኑ እያየ፣ለኪሳራ ይነግዳል?...ኧረ ይህን ያደፈ ታሪክ፣በቃ የሚል ጎበዝ፣ጦርነትን

የሚንቅ ጀግና እንፍጠር!
ከአዘጋጁ፡-
ደራሲና ሃያሲ ደረጀ በላይነህ፣ ላለፉት በርካታ ዓመታት በዚሁ ጋዜጣ ላይ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ አያሌ መጣጥፎችን አስነብቧል፡፡ በርካታ የሥነጽሁፍ ሥራዎች ላይ ሂሳዊ ትንተና አቅርቧል፡፡ ደረጀ በላይነህ

ገጣሚና አርታኢም ነው፡፡ 12 ያህል መጻሕፍትን አሳትሞ  ለአንባቢያን አድርሷል፡፡

የመጨረሻ አመት የኮሌጅ ተማሪ ነበርኩ፡፡ ለገና ወደ ቤተሰቦቼ ዘንድ ስሄድ ከሁለት ወንድሞቼ ጋር አስደሳች ጊዜ እንደማሳልፍ ጠብቄአለሁ፡፡ ሦስት ወንድማማቾች በመገናኘታችን ደስታችን ወደር የለሽ ነበር፡፡ አባትና

እናታችን በስራ ተወጥረው ለዓመታት ተዝናንተው አያውቁም፡፡
ስለዚህ እኛ መደብሩን ለመጠበቅ ተስማማንና ለጥቂት ጊዜ ወጣ ብለው እንዲዝናኑ ነገርናቸው፡፡ ሁለቱም አልተቃወሙም፡፡ ወደ ቦስተን ለመጓዝ ሻንጣቸውን መሸከፍ ያዙ፡፡
ከጉዟቸው አንድ ቀን በፊት አባቴ እጄን ይዞ በቀስታ ከመደብሩ ኋላ ወዳለችው ማረፍያ ክፍል ወሰደኝ፡፡ ክፍሏ ጠባብ ናት - አንድ ፒያኖና ታጣፊ አልጋ ብቻ ነው የያዘችው፡፡
በእርግጥ አልጋው ሲዘረጋ ክፍሉ ይሞላል፡፡ አልጋው ግርጌ ተቀምጦ ፒያኖ ከመጫወት በቀር አያፈናፍንም፡፡ አባቴ ከአሮጌው ፒያኖ ጀርባ እጁን ሰደደና ትንሽዬ ሳጥን ጐትቶ አወጣ፡፡
ከዚያም ሳጥኑን ከፍቶ አሳየኝ፡፡ ተከርክመው የወጡ የጋዜጣ ፅሁፎች ናቸው፡፡ በመገረም አፌን ከፍቼ ፅሁፎቹን እመለከት ጀመር፡፡ ብዙዎቹን የናንሲ ድሪው የወንጀል ምርመራ ታሪኮች አንብቤአቸዋለሁ፡፡ እዚያ ሳጥን

ውስጥ የተቀመጡበት ምክንያት ግን አልገባኝም፡፡
“ምንድናቸው?” አልኩት፤ አባቴን ቀና ብዬ እያየሁት፡፡
“እኔ የፃፍኳቸው ታሪኮች ናቸው፤ ለአዘጋጁ የፃፍኳቸውም ደብዳቤዎች አሉበት” ሲል መለሰልኝ፤ ኮስተር ብሎ፡፡
አባቴ እያፌዘ እንዳልሆነ ከድምፁ ቃና ተረድቼአለሁ፡፡ በመገረምና ግራ በመጋባት መሃል ሆኜ ጋዜጦቹን ሳገላብጥ፣ ከእያንዳንዱ ፅሁፍ ሥር “ዋልተር ቻፕማን ኢኤስ ኪው” ተብሎ የተፃፈውን አየሁት - የአባቴ

እውነተኛ ስም ነው፡፡ ሳላስበው ደሜ መሞቅ ጀምሯል፡፡ “ለምንድነው እስከ ዛሬ ያልነገርከኝ?”  ጠየቅሁት፤ ንዴቴን እንደምንም ተቆጣጥሬ፡፡
“እናትህ ስለማትፈልግ ነው”
“ምኑን?” ድምፄ መጮሁን ያወቅሁት ዘግይቼ ነው፡፡
አባቴ ድምፄን እንድቀንስ በምልክት ነገረኝና፣ አስገራሚውን ልቦለድ የሚመስል ታሪክ አወጋኝ፤ ዝግ ባለ የተረጋጋ ድምፅ፡፡
“እናትህ ጋዜጣ ላይ መፃፌን አትወደውም ነበር…”
“ለምን? ለምንድነው የማትወደው?”
አሁንም ድምፄን እንድቀንስ አሳሰበኝ፤ እናትህ ከሰማች ትገለናለች በሚል፡፡
“በቂ ትምህርት ስለሌለህ ባትሞክረው ይሻላል ብላ ደጋግማ አስጠንቅቃኛለች”
የእናቴ ነገር ገርሞኝ ጭንቅላቴን ስነቀንቅ አባቴ ቀጠለ፤
“አንድ ጊዜ በፖለቲካ ምርጫ ልወዳደር ፈልጌ ነበር… ይሄንንም ባትሞክረው ይሻልሃል አለችኝ”
“ቆይ ለምን?” አሁንም እንደ አዲስ ጠየቅሁት፡፡
“ተሸንፈህ ታዋርደናለህ.. ክብራችንን እንደጠበቅን ብንኖር ይሻላል አለችኝና ተውኩት” አለኝ፤ በቁጭት በታሸመ ቃና፡፡
እናቴን የማላውቃት ያህል ተሰማኝ፡፡ አባቴ አንጀቴን እየበላው፣ እሷ እያስጠላችኝ መጣች - በልቤ ውስጥ፡፡ ይሄን ያህል ጨካኝ እንደነበረች አላውቅም ነበር፡፡ በእጆቼ ላይ ካሉት የአባቴ መጣጥፎች አንደኛውን

ሳላውቀው ማንበብ ጀምሬ ነበር፡፡ በመሃላችን የነገሰውን ዝምታ የሰበርኩት ግን እኔው ነበርኩ፡፡ አይኖቼን ከጋዜጣው ፅሁፍ ላይ ነቅዬ አባቴን ቀና ብዬ እያየሁ ጠየቅሁት፤
“ታዲያ ይሄ ሁሉ ፅሁፍ እንዴት ታተመ?”
“እስቲ ልሞክር ብዬ እሷ ሳታውቅ መፃፍ ጀመርኩ… እያንዳንዱ ፅሁፌ ጋዜጣው ላይ ሲወጣልኝ ከርክሜ አወጣውና እዚህች ሳጥን ውስጥ እደብቀዋለሁ… አንድ ቀን ሳጥኗን ለአንድ ሰው እንደማሳየው አውቅ ነበር”
“ለማን?” ሳላስበው ከአፌ ተስፈትልኮ የወጣ ጥያቄ ነው፡፡
“ላንተ ነዋ!” አለኝ፤ በእውነተኛ የአባትነት ፍቅር ትክ ብሎ እያየኝ፡፡ ዓይኖቼን ሰብሬ የጋዜጣው ፅሁፍ ላይ ተከልኳቸው፡፡ ሁለት ፅሁፎቹን አንብቤ እስክጨርስ አባቴ ቁጭ ብሎ እየተመለከተኝ ነበር፡፡
ቀና ብዬ ሳየው ትላልቅ ሰማያዊ ዓይኖቹ በእንባ እርሰዋል፡፡ መሃረቡን ከኪሱ ውስጥ አወጣና ዓይኖቹን ከጠራረገ በኋላ፤ “ባለፈው ጊዜ ያለ አቅሜ ትልቅ ነገር ሞከርኩ መሰለኝ ይኸው ሦስት ወሩ… አልወጣም”

አለኝ፤ በፈገግታ፡፡
“ሌላ ነገር ፅፈህ ነበር?” ጠየቅሁት፤ በጉጉት፡፡
“አዎ ብሄራዊ መራጭ ኮሚቴ እንዴት ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ሊመረጥ እንደሚችል አንዳንድ ሃሳቦችን ፅፌ ለሃይማኖታዊ መፅሄታችን ልኬ ነበር፤ ግን እስካሁን አልታተመም… ትንሽ ያለ አቅሜ ሳልንጠራራ

አልቀረሁም”
ይሄ ጉዳይ እኔ የማላውቀው የአባቴ አዲስ ገፅታ ቢሆንም፣ አንድ ነገር ማለት ነበረብኝ፡፡
“አይታወቅም … ሊወጣ ይችላል” አልኩት
“ምናልባት ይወጣ ይሆናል…
ግን አይመስለኝም”
ቁራጭ ፈገግታ እያሳየኝ የጋዜጣ ቁርጥራጮቹን ሳጥኑ ውስጥ ከቶ ዘጋባቸውና፣ ከፒያኖው ጀርባ ባለው ክፍት ቦታ መልሶ ወሸቀው፡፡
በነጋታው ወላጆቻችን በአውቶብስ ተሳፍረው ወደ ሃቨርሂል ዲፖት ሄዱ፡፡ እዚያ ሲደርሱ በባቡር ተሳፍረው ነው፣ ወደ ቦስተን የሚጓዙት፡፡ እኔና ሁለት ወንድሞቼ ፣ጂምና ሮን መደብሩ ውስጥ ስንሰራ ዋልን፡፡ ቀኑን

ሙሉ ስለ አባቴ ሳስብ ነበር፡፡
የአባቴን የጋዜጣ ፅሁፎች ደብቃ ስለያዘችው ትንሽዬ ሳጥንም ማሰላሰሌ አልቀረም፡፡ አባቴ መፃፍ እንደሚወድ ፈፅሞ አላውቅም ነበር፡፡ ስለዚህ ጉዳይ ለወንድሞቼ አልነገርኳቸውም፡፡
የአባቴና የእኔ ምስጢር ነዋ! የተደበቀችው ሳጥን ምስጢር!
የዚያኑ እለት ፀሃይ መጥለቂያዋ ላይ መደብር ውስጤ ቆሜ በመስኮት ስመለከት እናቴ ከአውቶብስ ስትወርድ አየኋት - ብቻዋን፡፡ አደባባዩን ተሻገረችና ጥድፍ ጥድፍ እያለች ወደ መደብሩ ገባች፡፡
“አባባስ?” ስንል በአንድ ድምፅ ጠየቅናት፡፡
“አባታችሁ ሞቷል” አለችን፤ አይኗ እንደደረቀ፡፡
ጆሮአችን የሰማውን በመጠራጠር ተከትለናት ወጥ ቤት ገባን፡፡ መሞቱ እውነት መሆኑን በደንብ አረጋገጥን፡፡ በፓርክ ስትሪት የምድር የውስጥ ለውስጥ ባቡር ጣቢያ በኩል ሲያልፉ ነው፣ ህዝብ መሃል አባታችን

ድንገት የወደቀው፡፡
አጐንብሳ ስትመለከተው የነበረችው ነርስ ወደ እናቴ እያየች፤ “ሞቷል!” አለቻት እንደዘበት፡፡
እናታችን በድንጋጤ እምታደርገው ጠፍቷት ዝም ብላ አጠገቡ ተገትራ ነበር፡፡ መንገደኞች ወደ ባቡር ጣቢያው ለመግባት ሲጣደፉ እየረጋገጡ አስቸገሯት፡፡ ለአንድ ሰዓት ያህል እግሯን አንፈራጣ የአባባን አስከሬን

ከመንገደኞች ስትከላከል ከቆየች በኋላ አምቡላንስ ደረሰ፡፡
እናታችንንና አስከሬኑን ይዞ በአካባቢው ወዳለው ብቸኛ የመቃብር ቤት ወሰዳቸው፡፡ ኪሱን ፈታትሻ ሰዓቱን አወለቀችለትና ባቡር ተሳፍራ ብቻዋን ወደ ቤት ተመለሰች፡፡
እናታችን ይሄን አስደንጋጭ ታሪክ የነገረችን አንዲትም እንባ ጠብ ሳታደርግ ነው፡፡
ሁሌም ቢሆን ስሜታዊ አለመሆን ለሷ የስርዓትና የክብር ጉዳይ ነው፡፡ እኛም ራሳችን እንድናለቅስ አልተፈቀደልንም፡፡ የመደብሩን ደንበኞች ተራ ገብተን ማስተናገድ ያዝን፡፡ አንድ የመደብሩ የዘወትር ደንበኛ መጣና፤
“ዛሬ ሽማግሌው የት ገባ?” አለኝ
“ሞተ” አልኩት “ኦው… በጣም አሳዛኝ ነው” ብሎ ሄደ፡፡
የደንበኛው አጠያየቅ አሳብዶኝ ነበር፡፡
 አባቴን እንደ ሽማግሌ አስቤው አላውቅም፡፡ በእርግጥ እሱ 70፣ እናቴ 60 ዓመቷ ነበር፡፡ ሁልጊዜም ጤናማና ደስተኛ ሆኖ ነው የኖረው፡፡ ጤና የሌላትን እናታችንን አንዴም ሳይነጫነጭ ተንከባክቧታል፡፡  አሁን ግን

“ሽማግሌው ሞቷል፡፡”
በነጋታው ቁጭ ብዬ ለቤተሰቡ የተላኩ የሀዘን መግለጫ ካርዶችን ከፖስታ ውስጥ እየከፈትኩ ስመለከት አንድ የቤተ ክርስትያን መፅሄት አየሁኝ፡፡ ሌላ ጊዜ ቢሆን የሃይማኖት መፅሄት ትኩረቴን አይስበውም ነበር፡፡

ምናልባት የአባቴ ፅሁፍ ወጥቶ እንደሆነ ለማየት፣ መፅሄቱን ማገላበጥ ያዝኩ፡፡ የአባቴ ፅሁፍ ታትሟል፡፡ መፅሄቱን ይዤ ወደ ትንሿ ክፍል ሹልክ ብዬ ገባሁና በሩን ቆልፌ ተንሰቅስቄ አለቀስኩ፡፡ እስከዚያች ቅፅበት

ድረስ ራሴን አጀግኜ ነበር፡፡ አባቴ የሰጠው ደፋር ሃሳብና ምክር መፅሄቱ ላይ ታትሞ ስመለከት ግን ከአቅሜ በላይ ሆነብኝ፡፡ ጽሁፉን አነብና አለቅሳለሁ፤ ከዛ ደግሞ አነባለሁ፡፡
ከፒያኖው ኋላ የተወሸቀችውን ሳጥን አውጥቼ በውስጡ ያሉትን ፅሁፎች ማገላበጥ ጀመርኩ፡፡ ሳገላብጥ ከሰር ካቦት ሎጅ የተፃፈለትን ባለ ሁለት ገፅ ደብዳቤ ተመለከትኩ፡፡ አባቴ ለጻፈው  የምርጫ ዘመቻ ሃሳብ

የተላከለት የምስጋና ደብዳቤ ነበር፡፡ እስካሁን ስለዚህች ሳጥን ምስጢር  ለማንም ሰው አውርቼ አላውቅም፡፡ ምስጢሩ የእኔና የአባቴ ነው፡፡
(በኢየብ ካሣ “Chicken Soup For The Soul” መፅሐፍ ላይ የተተረጎመ)

Page 1 of 702