Administrator

Administrator

ዛሬ ሰኞ ሚያዝያ 7 2016 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ጀምሮ በዓለም ሲኒማ ጥሪ የተደረገላቸው የጥበብ ቤተሰቦች እና እንግዶች በተገኙበት በቀይ ምንጣፍ ሥነ-ሥርዓት  ይመረቃል::

ፊልሙ በደራሲና ዳይሬክተር ፍፁም ክብረት ተዘጋጅቶ በሪች ፊልም ፕሮዳክሽን የቀረበ ሲሆን አርቲስት ሰለሞን ሙሄ ፣አርቲስት ማራማዊት አባተ አርቲስት ሙሉአለም ጌታቸው፣ አርቲስት እየሩሳሌም ገበየሁ ፣ አርቲስት ሔቨን ሀብቱ፣ አርቲስት ያሬድ ኤጎ እና ሌሎችም በተዋናይነት የተሳተፉበት ፊልም ነው።

መግቢያው በነፃ!

"አቦ ሰም" ተውኔት በነፃ ለታደሚያን ይቀርባል!

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የአምስተኛ ዓመት የቴአትር ጥበባት ተማሪዎች "አቦ ሰም" በሚል ርዕስ ተውኔት አዘጋጅተዋል። የተውኔቱ ደራሲና አዘጋጅ መቅደላዊት አሰፋ ስትሆን ይህም ተውኔት ሰኞ ሚያዚያ 7 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 12:30 ጀምሮ ስድስት ኪሎ በሚገኘው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ይቀርባል።

ከዕለታት አንድ ቀን ድመት አንድ ጫካ ውስጥ ቀበሮ ታያለች፡፡ ከዚያም ለራሷ እንዲህ ትላለች፡-
“ቀበሮ በጣም ቀልጣፋ ነው፡፡ ብዙ ልምድ ያለው ነው፡፡ በሰፊውም የተከበረ ነው፡፡ ስለዚህ መልካም ሰላምታ ላቀርብለትና ልቀርበው ይገባል”፡፡ ቀጥላም፤ “እንደምን አደርክ አያ ቀበሮ! እንዴትስ ከርመሀል? ለመሆኑ ሁሉ ነገር በጣም በተወደደበት በዚህ በአሁኑ ጊዜ ኑሮን እንዴት ተቋቋምከው?”
ይሄኔ ቀበሮ በጣም እየተኩራራ ተጎማለለ፡፡ ድመቷንም ሽቅብ ቁልቁል እያየ ገረመማት፡፡ ከኩራትና ከእብሪቱ የተነሳም ለተጠየቀው ጥያቄ መልስ መስጠት ብዙ ጊዜ ፈጀበት፡፡ በመጨረሻም እዲህ አላት፡-
“አንቺ ምስኪን ጢም-ላሽ ፍጥረት! አንቺ የቤት አሽከር! ደካማ፣ የአይጥ-አባራሪ! ማነሽና ነው እኔን የተከበርኩትን ቀበሮ ኑሮ ከበደህ ወይ የምትይኝ? ማነሽናስ ነው የኑሮ ውድነቱን ተቋቋምከው ወይ? ብለሹ የምትጠይቂኝ? ለመሆኑ እስከዛሬ ድረስ አንቺ ምን ተምረሻል? በምንስ ጥበብ ሰልጥነሻል? ምን ችሎታ አለሽ?”
ድመቲትም፤ ትህትና በተላበሰ ቃና፤
“አንድ ጥበብ ብቻ ነው ያለኝ” አለችው፡፡
አያ ቀበሮም፤
“ምን ጥበብ ትችያሽ? ተናገሪ እስቲ?” አለና ጠየቃት፡፡
ድመቲትም፤
“ውሾች ድንገት መጥተው ሲያባርሩኝ ፈጥኜ ዛፍ ላይ እወጣለሁ፡፡ ይሄ ነው ጥበቤ”
ቀበሮም በጣም በኩራት ተነፋፍቶ፤
“ይሄ ብቻ ነው እንዴ ችሎታሽ? ጥበብሽ ይሄ ብቻ ሆኖ እንዲህ በአደባባይ ስትፎክሪ መስማትሽ በጣም የሚያስገርም ነገር ነው፡፡ ጉረኛ ነሽ! እኔን ስላላየሽ ነው፡፡ እኔ ከመቶ በላይ ጥበብና ችሎት አለኝ፡፡ ከዛ በተጨማሪም አንድ ከረጢት ሙሉ ዘዴና ትሪክ አለኝ፡፡ እኔ አንቺን ከልቤ እወድሻለሁ፡፡ ነይ፡፡ ነይ አብረን እንሂድና ከውሾች የምታመልጪበትን ዘዴ አስተምርሻለሁ” አላት፡፡
በድንገት ከየት መጣ ሳይባል አንድ አዳን ይመጣል፡፡
አራት ትላልቅ አዳኝ - ውሾች ይዟል፡፡
ይሄኔ እመት ድመት በከፍተኛ ፍጥነት ተቀላጥፋ ዛፍ ላይ ትወጣለች፡፡ በቅርንፎቹም ተንጠላጥላ ሙሉ በሙሉ በቅጠሎቹ ተሸፋፍና ተደብቃ ትቀመጣለች፡፡ እቅጠላ -ቅጠሎቹ መካከል ሆና፤
“አያ ቀበሮ፤ ቦርሳህን ከፈተው፡፡ ቶሎ ብለህ ቦርሳህን ክፈትና ከዘዴዎህ አንዱን አውጥተህ ተጠቀም” እያለች ትጮህ ጀመር፡፡
ግን ምን ያደርጋ፤ አያ ቀበሮ!” አለች በጮክታ፡፡ “አሁን የገባህበትን አጣብቂኝ ተመልከት፡፡
አጠራቅሜያለሁ ካልካቸው ከመቶ በላይ ዘዴዎች አንዱን እንኳ ስራ ላይ ሳታውል ፈፅሞ ከማትወጣበት ችግር ውስጥ ገባህ፡፡ እኔ ከልቤ አምኜ የያዝኳትና በረዥም ጊዜ ልምድ የተካንኳትን ሀቀኛና ፈጣን ዘዴ ተጠቀምኩ፡፡ ዛፍ የመውጣት ዘዴ ብታውቅ እንደዚህ ሆነህ አትቀርም ነበር” ብላው የበለጠ ጥቅጥቅ ወዳለ ቅጠል - ቅጠል ውስጥ ገብታ ስታበቃ በመጨረሻ አዳኙና ውሾቹ ሲሄዱ ወረደች፡፡
***
በአንድና በሁለት ነገር ብልጥ ሆኖ ሌሎችን መብለጥ ይቻላል፡፡ በሁሉም ነገር ብልጥ መሆን ግን ዘበት ነው፡፡ ሁሉ መፎከር፣ ሁሉ እኔ እበልጣለሁ እያለ መደንፋት፤ ሁሌ የትም አይደርስም እያለ መናቅ፤ ሁሌ በጊዜያዊ ድል መኩራራት የሚሰምርና ፍሬ ያለው ውጤት ሆኖ አለመገኘቱ ብቻ ሳይሆን ለችግር የሚያጋልጥ አባዜ ነው፡፡ ሥጋት፣ ጥርጣሬና አለመረጋጋትን ያነግሳል፡፡ ጥንት እንሰማ ከነበረው “አብዮታችን ከተከላካይነት ወደ አጥቂነት ተሸጋግሯል” ከሚባልበት አይነት ሁኔታ ወጥተን በውይይት ወደምናምንበት ደረጃ መሸጋገር መቻል አለብን፡፡ አለበለዚያ ሁሌ የግጭት ሁሌ የእልቂት ሀገር መሆን አንድንችም፡፡ አንድ የሀገራችን ምሁር “ታሪክ ራሱን ይደግማል” የሚባለውን አነጋገር በእኛ አገር አንፃር ሳየው ያስገርመኛል፡፡ በእኛ አገር አንዳንዴ ታሪክ፤ ታሪክ ሆኖ ሳያልቅ ይደገማል፡፡ ሲብስበትም ከናካቴው ታሪክ ሳይሆን በፊት ራሱን ይደግማል” ብለው ነበር፡፡ የበለጠ እሚያስገርመው ደግሞ የሚገርመው ክፉ ክፉው፣ ተንኮል ተንኮሉ፣ ምሬት ምሬቱ መሆኑ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ሀገር ስታለቅስ ትኖራች፡፡ የሐዘን እንባ አይለያትም፡፡
መሰረታዊው የኢኮኖሚ ውስብስብ ችግርና ጥያቄ ሳያበቃ በፖለቲካው መስክ መልስ ያላገኙ ጥያቄዎች እየበዙ፣ እየተሸረቡ፣ እየደነደኑ፣ ሲመጡና ትላንት ያከማቸነው ጥበብና ዘዴ ሁሉ አልሰራ ሲል፣ ቆም ብሎ ማሰብ ያስፈልጋል፡፡ “መድሃኒቱን ሰውነትህ ለምዶታልና አይሰራልህም፡፡ ሌላ ለውጥ”፤ እንዲል መጽፅሀፈ-ሀኪም፡፡ የዲሞክራሲ ጥያቄ፣ የፍትህ ጥያቄ፣ የፕሬስ ነፃነት ጥያቄ፣ የብዙሃን ፓርቲ  ጥያቄ፣ የሰብአዊ መብት ጥያቄ… መልስ ካላገኙ ሰልፉ ሁሉ ቀኝኋላ ዙር ነው!
የሃያሎች አማላጅነትም ቢሆን የሀገርን ችግር በዘላቂነት ፈትቶ አያውቅም፡፡
የሃያላኖች እርዳታም ሆነ ምልጃ፤ የህመም ማስታገሻ እንጂ መፈወሻ አይደለም፡፡ እነሱም የራሳቸውን ጥቅም መሰረት ያደረገ አቅጣጫ እዳላቸው አለመዘንጋት ነው፡፡
ሥራና ሰራተኛን ለማገናኘት ዋንኛ መመዘኛው ሙያዊ ብቃት ነው፡፡ ፖለቲካዊና ወገናዊ ድልደላ ካለ ከሙስና የተለየ ትርጓሜ የለውም፡፡ ለምሁር፣ ለባለሙያ፣ ለሰለጠነ የሰው ኃይል ያለን እምነት ከፖለቲካ ታሳቢነት ነፃ ካልሆነ፣ ኖሮ ኖሮ የአገርን ጥቅም የሚሸረሽር፣ ነገ ፍሬ የማያፈራ የብልጣ ብልጥ ተግባር ከመሆን አያልፍም፡፡ ስለሆነም የኋሊት እንጂ ወደፊት አያራምድም፡፡
 በዲፕሎማሲው ረገድም ሊደርስ የሚለውን ቀውስ አለመዘንጋት ተገቢ ነው፡፡ ብቃት ያላቸው አምባሳደሮችን አለመመደብ የሚያስከትለውን ቀውስ ማስዋብ ያሻል፡፡ በዚህ በሰለጠነው ዓለም አምባሳደርነት አገርን የመወከል ታላቅ ኃላፊነት እንጂ መጦሪያም ግዞትም፤ ፖለቲካም ማስታመሚያም፣ ቁሳቁስ በሻንጣ መሸከፊም አሊያም ደግሞ ቤተሰብ ማጓጓዣም አይደለም፡፡ የሀገርን ክብር በባህል፣ በኢኮኖሚና በዲፕሎማሲ ማጎልበቻ ነው፡፡ ውሎ አድሮ ከሚከሰት ዲፕሎማሲያዊ ሽንፈትም መዳኛ ነው፡፡
“አውቀን በድፍረት ሳናውቅ በስህተት በሰራነው ሁሉ ይቅር ይበለን” የሚለው የማሳረጊያ ንሥሐ የሚያስፈልግበት ዘመን ነው፡፡ ደፍሮ ተናግሮ መፅደቅ የሚሸዳ ጠፋ እጂ!!
በሀገራችን ውስጥ በየፈርጁ የሚታየው በቂም መፈላለግ ሆነ ብሎ አለመግባባት፣ ሰበብ እየፈጠሩ ነገር መፈላለግ፣ የ”ሳታመሀኝ ብላኝ” እሮሮ፣ “የብቆጣም እመታሻለሁ፣ ብትቆጪም እመታሻለሁ” ድንፋታና ማን አለብኝ፤ “በጨለማ እየሄዱ ጅብ ነገረኛ ነው ይላሉ” አለ አያ ጅቦ፤ የሚለውን ተረት የሚያስጠቅስ ክስተት ሆኗል፡፡ በዚህ ክስተት አገር አታድግም፡፡

                  • ኢትዮጵያዊ መሆኑን ያወቀው ከ30 ዓመቱ በኋላ ነው
                  • የልዑል አለማየሁ አስከሬን በእንግሊዝ የለም ብሏል
                  • ልዑሉ በ18 ዓመቱ በለጋ ዕድሜው አልተቀጨም ባይ ነው





         ባለፈው ረቡዕ ወዳጄ ዘነበ ወላ ስልክ ደውሎ፣ የአጼ ቴዎድሮስ የልጅ፣ ልጅ ልጅ እዚህ እንደሚገኝና መጽሐፉን ማሳተምእንደሚፈልግና የሚዲያ ሰው ማነጋገር እንደሚሻ ነግሮኝ ስሙንና ስልኩን በቴሌግራም ላከልኝ፡፡ ”ስሜ ሲሰን አለማየሁ ቴዎድሮስይባላል፡፡ በአሜሪካን አገር ያደግሁኝ
ኢትዮጵያዊ ነኝ፡፡ ደራሲና የፊልም ፕሮዱዩሰር ስሆን፤ መጻሕፍቶቼ በኢትዮጵያ ገበያ ላይእንዲወጡልኝ እፈልጋለሁ” ይላል በቴሌግራም የደረሰኝ መልዕክት፡፡ ይህን ስም የሰማሁት ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡ አላውቀውም፡፡ ጉግል አደረግሁ፡፡ ጉግል ግን በደንብ ያውቀዋል፡፡ማንነቱን፣ ሥራዎቹን ወዘተ ዘረገፈልኝ፡፡ ጥቂት መረጃዎች ከሰበሰብኩ በኋላ ሰውየው ዘንድ ደወልኩለት፡፡ ለቃለ መጠይቅ ፈቃደኛ መሆኑንጠየቅሁት፡፡ አላቅማማም፡፡ ሲሰን አለማየሁ ቴዎድሮስ፤ የልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስና የዳግማዊ አጼ ቴዎድሮስን ጨምሮ ከ7 ያላነሱመጻኅፍትን ለንባብ ያበቃ ታታሪ ብዕረኛ በመሆኑ ደራሲ ነው ብንል አልተሳሳትንም፡፡ ደራሲ ብቻ ግን አይደለም፡፡ ደራሲና ሁለገብ ብንለው ሳይቀል አይቀርም፡፡ ምክንያቱምየፊልም ፕሮዱዩሰር ነው፣ የታሪክ ልሂቅም ነው፡፡ በተጨማሪም ቪዲዮግራፈርና ግራፊክ ዲዛይነርም ነው፡፡ ይህ ሁሉ ታዲያ ቆፍጣናየአሜሪካ ወታደር መሆኑን ሳንረሳ ነው - አሁን ጡረታ ቢወጣም፡፡ የኢራቅ ግዳጁን ፈጽሞ ሲመለስ አባቱ አንድሪውቻርልስ ሊንዚ የነገሩትምስጢር የህይወቱን ዕጣ ፈንታ እንደቀየረው ይናገራል፡፡

 

አባቴ ለመጀመሪያም ለመጨረሻም ጊዜ የነገረኝ ይህ የቤተሰብ ምስጢር፤ አስቤውም አልሜውም የማላውቀው ነውይላል፡፡ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ታዲያ የተነገረውን ምስጢር ገላልጦ እውነቱን ለማወቅ ያልፈነቀለው ድንጋይ፣ ያልረገጠው የዓለም ዳርቻ የለም፤ ኢትዮጵያን ጨምሮ፡፡ እውነቱን
አወቀ ማለት ደግሞ ራሱን ማንነቱን አወቀ ማለት ነው፡፡ በዚህ ከአዲስ አድማስ ጋር ባደረገው ልዩ ቃለ ምልልስ፣ ሲሰን አለማየሁ፣ስለ ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ ደረስኩበት ያለውን አዲስ እውነት ወይም ምስጢር ያጋራናል፡፡ የቤተሰቡን የዘር ሃረግ ለማግኘት የተጓዘበትን ርቀትናየደረሰበትንምያወጋናል፡፡
አሁን በቀጥታ ወደ ቃለ ምልልሱ፡-

        እስቲ ከትውልድህና አስተዳደግህ እንጀምር---የት ተወለድክ? የትስ አደግህ?
የተወለድኩት ሻን አንድሪው ሊንዚ ነው፤ ያደግሁት በከተማ ማህበረሰብ ውስጥ እንደ አፍሪካ-አሜሪካዊ፣ በሻምፓኝ፣ ኢሊኖይ ነው።የምኖርበት ሰፈር በዓመፅ፣ በአደንዛዥ ዕፅና በጠመንጃ የተሞላ ነበር። ፖሊስ የችግር ቦታ ሲል የፈረጀው ነው- አካባቢውን፡፡ ባለፉትዓመታት፣ ቤተሰቤንና የልጅነት ዘመን አብሮ አደጎቼን አጥቻለሁ፡፡ ኢትዮጵያዊ መሆኔን እስከ 30 ዓመት ዕድሜዬ ድረስ አላውቅም ነበር።በ1999 ዓ.ም የአሜሪካንን ጦርሰራዊትተቀላቀልኩ፡ በ2007 ዓ.ም የኢራቅ ግዳጄን ተወጥቼ ወደ አገር ቤት ተመለስኩ። በወቅቱ የአባቴ አንድሪው ቻርልስ ሊንዚ የጤና ሁኔታእያሽቆለቆለ ነበር፡፡ ያኔ ነው የቤተሰባችንን ምስጢሮች ለመጀመሪያ ጊዜ ገልጦ የነገረኝ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሣ ከሚባል የንጉሥቤተሰብ እንደመጣን ገለጸልኝ፡፡ መጀመሪያ ላይ
ነገሩን አምኖ ለመቀበል አዳጋች ሆኖብኝ ነበር፤ ምክንያቱም ከዚያ በፊት ስለዚህ ጉዳይ ጨርሶአንስቶ አያውቅም፡፡ ከአንድ ወር በኋላ አባቴከዚህ አለም በሞት ተለየ።
አንተስ ይህን አዲስ መረጃ ከአባትህ ካገኘህበኋላ ምን አደረግህ?
አባቴ የመጨረሻዎቹ ቀናት ላይ ማንበብ የማልችለውን የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ መያዜን አውቆ ነበር፡፡ እናም ወደ ኢትዮጵያሄጄ ቤተሰባችንን ፈልጌ እንዳገኝ ትዕዛዝ ሰጠኝ፡፡ በ2012 ዓ.ም ከአሜሪካ ጦር ሠራዊት ጡረታ ወጣሁና ወደ ኢትዮጵያ ተጓዝኩ፡፡ ወደ ባህርዳርና ጎንደርም ተሻግሬ፣ አባቴ የጠቀሰውን ሃውልት ለማየት ቻልኩ፡፡ ያኔ ነው ካሣ የሚለው ስም ለካሳ ሀይሉ ጊዮርጊስ፤ ለባለ ዘውዱ ንጉስዳግማዊ አጼ ቴዎድሮስ መሆኑንየተረዳሁት፡፡
በ2017 ዓ.ም አንዲት ሴት በአማራ ቲቪቃለ መጠይቅ ተደረገላት። አበበች ካሳ መሸሻ ቴዎድሮስ ትባላለች። እቺን ሴት ከሁለት ወራትበኋላ አገኘኋት፡፡ እዚህ ኢትዮጵያ ያለ የቅርብ ወዳጄ አዲስ አበባ ሠርጉ ላይ እንድገኝ ጋብዞኝነበር፡፡ በዚያ አጋጣሚ እኔና እሷ የዲኤንኤምርመራ አደረግን፤ ውጤቱም ዘመዳሞችመሆናችንን አረጋገጠ፡፡ አባቴ የተወለደው አሜሪካ ነው፣ አባቱ ቻርለስ ሊንዚ ግን አሜሪካ አይደለምየተወለዱት፡፡ ቻርለስ ሊንዚ ተብለው የሚጠሩት አባታቸው ደግሞ ከንጉሥ ቴዎድሮስልጆች አንዱ ነበሩ።


ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስን የተመለከተመጽሐፍ በአማርኛና በእንግሊዝኛ አሳትመሃል፡፡ አማዞን ላይ ለሽያጭ ቀርቦ ተመልክቼዋለሁ---
ትክክል ነው፡፡ በ2018 ዓ.ም በአንዱ ቀን፣ ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስን ለማክበር ወደእንግሊዝ ተጉዤ ነበር፡፡ ያኔ ነው ሚስጥሮቹንያገኘሁት፡፡ ለልዑል ዓለማየሁ በቦታው ላይ ምልክት ብቻ እንጂ የሬሳ ሳጥን መቃብር የለም።ሆኖም ሰ ዎች የ እኔንና የ ልዑል አ ለማየሁንበእጅጉ መመሳሰል ታል፡፡ እኔም ቅድመ- አያቴ የእውነትም ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ እንደነበሩ ተረዳሁ፡፡ ልዑል አለማየሁ፤ እስከ 113ዓመት ዕድሜያቸው ድረስ በህይወት ኖረው፣
በ1974 ዓ.ም ሻምፓኝ፣ ኢሊኖይ ነው የሞቱት፡፡
አንተ ልዑል አለማየሁ ቅድመ አያቴ ነበሩ ስትል ማረጋገጫህ ምንድን ነው?
መጀመሪያ ላይ ልኡል አለማየሁ ቅድመ አያቴ መ ሆኑን አ ላውቅም ነ በር። ነ ገር ግ ን ከልኡል አለማየሁ ጋር እንደምንመሳሰልበየፎቶው ላይ አስተውያለሁ። ከአበበች ካሣ መሸሻ ቴዎድሮስ ጋር የተደረገ የDNA ምርመራማስረጃ አለኝ፤ ከ50% በላይ የዲኤንኤ መዛመድ እንዳለን ያሳያል። በቅርቡ የካፒቴን ትሪሻም ቻርልስ ስፒዲ ቤተሰብ ከኒውዚላንድ የልዑል አለማየሁን ናሙና ከመቃብር ቦታ ሳይሆንከቤተሰቡ አምጥቶልኝ ነበር። የፀጉር ናሙናዎች ዲኤንኤ ነው፡፡ እኔም ከቅድመ አያቴ ቻርልስ ፎቶና ልዑል አለማየሁ ጋር የፎቶ ልየታ ሰርቼ፣85% የተዛማችነት ውጤት ታይቷል፡፡ቅድመ አ ያቴ በ 1879 ዓ.ም ወደ ፍ ልስጤም መሄዱን ተረድቻለሁ፡፡ ስምየን አንበሳ ዘዮን የሚለውን ስሙን ለውጦታል። አንበሳ ዘዮንበእንግሊዝኛ የጽዮን አንበሳ ማለት ሲሆን፤ ሊንዚ ደግሞ የጽዮን አንበሳ ነው። እስከ 1919 ዓ.ምድረስ ቤተ ሺአን እና እየሩሳሌም ውስጥ ነበርየቆየው፡፡ ቻርልስ ከካፒቴን ትሪሻም ቻርልስስፒዲ ይባላል። ኢትዮጵያ እያለ ከወንድሙ መሸሻ ቴዎድሮስ ጋር ተገናኘ። ሚስት እንዲሁምሴት ልጅና ወንድ ልጅ ነበረው። ሚስቱ
በ1925 ዓ.ም ልጃቸው ቻርልስ የ2 ወር ልጅእያለ፣ኢትዮጵያ ውስጥ ህይወቷ አለፈ፡፡ እሱከልጁ ጋር ወደ አሜሪካ ሲመጣ ሴት ልጁ ግን ቀረች።
ከሰባት በላይ መጻሕፍትን አሳትመሃል፡፡ ወደ ጸሃፊነትና ፊልም ሙያ እንዴት ገባህ? ወታደር ቤትን ከመቀላቀሌ በፊት የሙዚቃ ኮንትራት (ውል) ለማግኘት የሚሻ የሂፕ ሆፕ ሪከርዲንግ አርቲስት ነበርኩ። መጀመሪያ ዘፈኖችን መጻፍ ጀመርኩ፤ በኋላ ወደ መጻሕፍትገባሁ፡፡ የበኩር መጽሐፌ በ2006 የታተመሲሆን፤ ከዚያ በኋላ ሰባት ተጨማሪ መጻሕፍትን መፃፍ ቀጠልኩ። ስለ ቤተሰቤ የዘር ሐረግምጽፌአለሁ፡፡ እናም ጉዞዬን በፊልም መ ቅረጽ
ጀመርኩ፡፡ ስለ ቤተሰቤ ታሪክ ለማወቅ ያደረግኋቸውን ጉዞዎች ለማድመቅ ዘጋቢ ፊልም ሰርቻለሁ። የጉዞዬ አካል፣ ኢትዮጵያበመላው አለም በአሜሪካ፣ በእስራኤል፣ በአውሮፓና በጥንቷ ባቢሎን ታላቅ ታሪክ እንዳላት መማር ነው።
የኢትዮጵያን ባህልና ታሪክ በሥራዎችህ ስታጋራ ያጋጠሙህ ተግዳሮቶች ወይም የተሳሳቱአመለካከቶች የሉም? እንዴት አስተናገድካቸው?
ልዑል አለማየሁ በ18 ዓመቱ ሞቷል ተብሎ ዓለም ሁሉ ስለተነገረው ብዙ ተግዳሮቶች ገጥመውኛል፡፡ የንጉሣዊው ቤተሰብ የልዑልአለማየሁን አስክሬን ለመላክ ፈቃደኛ ያልሆነው፣ ንግሥት ቪክቶሪያ ልኡሉ ሳይሞት የሞተ አስመስላ በመናገሯ ነበር፡፡ ለዚህ ደግሞምክንያቱ ንጉሥ ዮሐንስ ልዑል ዓለማየሁ
ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለስ የሚጠይቅ ሁለት ደብዳቤዎች ለንግሥት ቪክቶሪያ በመጻፋቸው የተነሳ ነው፡፡
አሁን ወደ ኢትዮጵያ የመጣህበት የተለየ ዓላማ ወይም ተልዕኮ ይኖርህ ይሆን?
ወደ ኢትዮጵያ ስመጣ ለዘጠነኛ ጊዜ ነው፡፡ ግቤ የኢትዮጵያ መታወቂያ አግኝቼ እዚህ አገር መኖርና መማር ነው፤ ምክንያቱም ወደ ኢትዮጵያ
መምጣት የቤት ዓይነት ስሜት ይፈጥርብኛል፡፡ ህዝቤን እወዳለሁ፤ ከኢትዮጵያውያን ጋር በመሆኔ የሰማዩን አባት አመሰግነዋለሁ፡፡ሌላው ግቤ ደግሞ በአማርኛም ሆነ በሌሎች የኢትዮጵያ ቋንቋዎች መናገር፣ ማንበብና መጻፍ መማር ነው። ወደ ቤት የሚመለስበትን መንገድለማግኘት የሚሞክር የጠፋ ልጅ ዓይነት ስሜት ይሰማኛል።
በመጨረሻ፣ በሥራዎችህ ምን አሻራ ትተህ ማለፍ ትፈልጋለህ?
የኢትዮጵያ ታሪክ አካል መሆን እፈልጋለሁ። ሁሉንም ሰው የሚጠቅም ታላቅ ነገር ማድረግ እንደምችል ተስፋ አደርጋለሁ። መጽሐፎቼኢትዮጵያ ውስጥ ቢታተሙ መታደል ነው፡፡ ታሪክን በፊልም ቀርጾ መስራትና ኢትዮጵያ በአለም ላይ ያሳደረችውን ተፅእኖ ማሳየትእፈልጋለሁ።

 

 

የቴሌግራም ቻናልችንን  በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

 

አሚጎስ የገንዘብ ቁጠባና ብድር የኅብረት ሥራ ማህበር፣ ከበላይአብ ሞተር ኃ.የተ.የግ.ማ ጋር በሀገር ውስጥ የሚገጣጠሙ መኪኖችን ለአባላት በብድር ለመስጠት የሚያስችል የስራ ስምምነት ዛሬ  ጠዋት ረፋዱ ላይ በጎልደን ቱሊፕ ሆቴል ፈጽመዋል፡፡

አሚጎስ ከበላይ አብ ሞተርስ ጋር  ባደረገው በዚህ  ስምምነት መሰረት፣ መስፈርቱን ለሚያሟሉ የማህበሩ አባላት በሀገር ውስጥ የሚገጣጠሙ መኪኖችን  በብድር ያቀርባል፡፡

በአገራችን የሚገጣጠሙ ተሽከርካሪዎች ፍላጎት ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረ መምጣቱ የሚነገር ሲሆን፤ የዜጎችን ኑሮ ባማከለ መልኩ በብድር አማራጭ እየቀረቡ የሚገኙት ሀገር ውስጥ የሚገጣጠሙ መኪኖች የፋብሪካ ዋስትና ያላቸው መሆናቸው ተመራጭ ያደርጋቸዋል ተብሏል፡፡

አሚጎስ  ላለፉት አስራ አንድ አመታት ከ7 ሺ 500 በላይ አባላትን በማቀፍ እንዲሁም ለ4000 ያህል አባላቱ የብድር አገልግሎትን በመስጠት በርካቶች ሥራቸውን እንዲያስፋፉና  የራሳቸውን ሥራ እንዲፈጥሩ ማድረጉ ተገልጿል።

ከአስር ዓመት በፊት በዘጠኝ ሺ ብር ካፒታል የተመሰረተው  የገንዘብ ቁጠባና ብድር የኅብረት ሥራ  ማህበሩ፤አሁን  ላይ ካፒታሉን ከአንድ ነጥብ አምስት ቢሊየን ብር በላይ ማድረሱን  ለማወቅ ተችሏል፡፡


•  በእሁዱ መርሃ ግብር እስከ 5ሺ የሚደርሱ ደጋግ ሰዎች ይሳተፋሉ

•  ለማዕከሉ እስከ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ  ገቢ ለማሰባሰብ ታቅዷል

 ነሕምያ ኦቲዝም ማዕከል፣ ከኢትዮ ዳንስ ፊትነስ ጂምና ሰፖ ጋር በመተባበር ከነገ ወዲያ እሁድ ሚያዝያ 6 ቀን 2016 ዓ.ም  ከጠዋቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ ጦርሀይሎች በሚገኘው ጎልፍ ክለብ የዳንስ ፊትነስ  መዘጋጀቱ የተገለጸ ሲሆን ዓለማውም ለማዕከሉ የገንዘብ ድጋፍ ማሰባሰብ ነው ተብሏል፡፡

በእዚህ ዝግጅት ላይ እስከ 5 ሺ  የሚደርሱ ደጋግ ኢትዮጵያውያን እንደሚሳተፉ የሚጠበቅ ሲሆን፤ በዕለቱ ከ5 ሚሊየን ብር ለማሠባሠብ መታቀዱን የሚገልጸው የኢትዮ ዳንስ ፊትነስ መስራችና ባለቤት ቶማስ ኃይሉ (ቶም ኘላስ)፤ ሁላችንም በመተባበር በነሕምያ የሚገኙ ህጻናትን እንድናግዝ ጥሪውን  አስተላልፏል።

ከ10 ዓመት በፊት የተመሠረተው ነሕምያ ኦቲዝም ማዕከል፤ በኦቲዝምና ተዛማጅ ችግሮች የአዕምሮ ዕድገት እከልየገጠማቸውን ህጻናትና ወጣቶችን እንዲሁም ቤተሰቦቻቸውን ከተጋረጠባቸው ዘርፈ ብዙ ማህበራዊ፣ ስነልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶች ለመታደግ አልሞ የሚሰራ መሆኑን የማዕከሉ መስራች ወይዘሮ ራሄል አባይነህ ገልጸዋል።

በመላው ኢትዮጵያ  እየተከበረ የሚገኘው  የዘንድሮውን የዓለም ኦቲዝም ግንዛቤ ማስጨበጫ ቀን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው የዳንስ ፊትነስ ኘሮግራም ላይ ለመታደም የመግቢያ ዋጋው አምስት መቶ ብር ሲሆን፤ ቲኬቶቹ ቦሌ  ኢትዮ ዳንስ ፊትነስ ጂም እና ሰፖ ፣ ቄራ አልማዝዬ ሜዳ አካባቢ በሚገኘው ነሕምያ ኦቲዝም ማዕከል እንዲሁም በእለቱ ጎልፍ ክለብ መግቢያ በር ላይ እንደሚሸጡ ተገልጿል።

በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ፣ ፖሊስ የፋኖ አባላት ናቸው ካላቸው ግለሰቦች ጋር የተኩስ ልውውጥ አድርጎ ሁለቱን መግደሉንና አንዱን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በሰጠው መረጃ መሠረት፤ ዛሬ አርብ ሚያዝያ 4 ቀን 2016 ዓ.ም. ፖሊስ ክትትል ሲያደርግባቸው በነበሩ የቡድኑ አባላት ላይ እርምጃ ወስዶ አመራር ነው የተባለ ግለሰብ ተገድሏል ብሏል።  ፖሊስ  “የፋኖ አመራሮች” ናቸው ካላቸው  ታጣቂዎች ጋር ባደረገው  የተኩስ ልውውጥ፤ ሁለቱ ሲገደሉ አንዱ ጉዳት ሳይደርስበት መያዙን ገልጿል። በተኩስ ልውውጡ ወቅት ሁለት የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላትን ጨምሮ አራት ሰዎች መቁሰላቸውን ኮሚሽኑ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ፖሊስ  የፋኖ አባላት ናቸው ባላቸው ናሁሰናይ አንድአርጌ ታረቀኝ፣ አቤኔዜር ጋሻው አባተ እና ሀብታሙ አንድአርጌ ተሰማ ላይ  ክትትል ሲያደርግ  መቆየቱን ገልጾ፤ ዛሬ  ሚያዚያ 4 ቀን 2016 ዓ.ም. በቁጥጥር ስር ለማዋል ሲሞክር  ተጠርጣሪዎቹ ዲዛዬር መኪና በመጠቀም በፖሊስ አባላት ላይ ተኩስ በመክፈት ሊያመልጡ መሞከራቸውንም ገልጿል። በዚህ የተኩስ ልውውጥ ፖሊስ የፋኖ መሪ ነው ያለው ናሁሰናይ አንዳርጌ ታረቀኝ ከቆሰለ በኋላ ወደ ህክምና ተወስዶ ሕይወቱ አልፏል ብሏል።

ፖሊስ፤ “ናሁሰናይ አንዳርጌ የሚባለው ተጠርጣሪን  በፖሊስ ቁጥጥር ስር ለማዋል በሚደረገው እንቅስቃሴ እጅ ላለመስጠት ከፍተኛ የሆነ ትግል ማድረጉን ገልጾ፤ በዚያ አካባቢ የሚሄድ አንድ ግለሰብ ሕይወት ማለፉንና  ሳጅን አራርሳ ተሾመና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ የተባሉ የፖሊስ አባላት ላይ  ከባድ ጉዳት መድረሱን ጠቁሟል።

ሀብታሙ አንዳርጌ ተሰማ በተኩስ ልውውጡ መሃል መገደሉን የገለፀው ፖሊስ፤ አቤኔዘር ጋሻው አባተ የተባለው ሦስተኛው ተጠርጣሪ ምንም ጉዳት ሳይደርስበት በቁጥጥር ስር መዋሉን  አስታውቋል።

አንዳንድ ጥቅስ ከእግረሙቅ ይከፋል፤ ጠፍሮ ሲይዝ፣ ሳምንት እራሴ ጠቅሼ ተወስውሼ ሳልወድ በግድ አብሬው የከረምኩት የKarl marx ንግግር ነው፤ እንዲህ ይላል፡-
“Man’s Most Preeious treasure, his greatest wealth; is man himself” (የሰው ልጅ የከበረ ሀብቱ ሆነ ታላቅ ንብረቱ እራሱ ሰው ነው)
ይሄን ጥቅስ ይዘን በሃሳብ ስንነጉድ ይሄን ዘመን፣ ይሄን ሀገርና ይሄን ሰው አገኘን…
… እንደው ለመሆኑ፤
የዚህ ዘመንና የዚህ ሀገር ሰው የሚሞትለትና የሚሟሟትለት  የህይወት ግቡ ምንድን ነው? ሀገር?.... ብሔር?… ገንዘብ?...ጥበብ?... ሥርዓት?... እምነት?… ነጻነት ?-....ዕውቀት?....ጸሎት?.... ዕውነት?--ወይስ ምን?...
    Karl Marx እንዳለው ነው? የዚህ ዘመንና ሀገር ነዋሪ የከበረ ሀብቱ ሆነ ታላቅ ንብረቱ፣ እራሱ ሰው ነው?...እዚህ ላይ ሳንቆርጥ ወደ ተናጋሪው Marx እንዙር…
… የMarx የህወይት ግብ፣ እዚህ ጥቅስ ውስጥ ተጠቅልላ ትገኛለች። የተራበው፣ የተጎሳቆለው፣ ቤተሰቡን ችግር ላይ የጣለው፣ ልጁ ስትሞት ምንም ማድረግ ሳይችል የቀረው፣ የተሰደደው… ለዚች የህወት ግቡ ነው። ርዕዮተ ዓለም እስከመሆን የደረሰው  ፍልስፍናው፤ የዚች ህይወት ግቡ ማስፈጸሚያ አቋሙ ብቻ ነው። ሰውን ሁሉ የሰው ብቸኛ ሀብት አድርጎ በመመልከቱ የዓለም አድሏዊነት ላይ ነው የዘመተው። ጨቋኝ፣ ተጨቋኝ ስለምን ይኖራል? ነው ያለው። ዓለም የሁሉም ሰው ከሆነች፣ ሁሉም ሰው ለመኖር ከተፈጠረ፣ እንዴት በዝባዥና ተበዝባዥ ይሆናል? አንዲት እናት ልጆቿን እንደከበረ ሀብቷ እንደ ታላቅ ንብረቷ የምትመለከት ከሆነ፣ በመካከላቸው ጨቋኝና ተጨቋኝ፤ በዝባዥና  ተበዛባዥ እንዲኖር ትፈቅዳለች? የማርክስ ፍልስፍና ለልጆች የወረደ የእናት ማኒፌስቶ ነው። የተገኘውን ሥራ ሆነ ያፈሩትን ሀብት በእኩልነት የሚከፋፈሉበት የእናት መተዳደሪያ ደንብ ነው።
እሺ!
    … የዚህ ዘመንና የዚህ ሀገር ሰዎች፤ በፍልስፍና የምንደግፈው፣ በሥቃይና በሞትም ቢሆን የምንጸናው ለየትኛው የህይወት ግብ ነው? ፍቅር? ህብር? ጥበብ? ወይስ ገንዘብ?...
… ገንዘብ ሳይሆን አይቀርም። ይሁን!! የህይወታቸውን ግብ እንደገመሬ ዝንጀሮ ገንዘብ ክምር ላይ ፊጥ ማለት አድርገው የተለሙ አሜሪካኖች ብዙ አስተምህሮቶች አሏቸው። አንዱ የገንዘብ ነብይ ነበረው Napoleon Hill ገንዘብ ለማግኘት እራስን መሸጥ እንደሚገባ ያስተምራል። እራስን የሚሸጠው “የሽያጭ ሠራተኛ” በመሆን ነው ይላል። ከምናምንቴ ጋር የተነካካውን የህይወት ግብ፣ የተቀደሰ ለማድረግ የታሪክ ጠገግ ሲፈልግለት እንዲህ ይላል…
“….ቄሳር፣ ታላቁ አሌክሳንደር፣ ናፖሊዮን እና መሰሎቻቸው የተዋጣላቸው የሽያጭ ሰራተኞች መሆናቸው ይታወቃል።… ጦርነትን ሸጠዋል፣ አቅርበዋል። ጦርነቱ ደግሞ የሰዎችን ደም እንባና መከራ ያስከፈለ ነበር። “ ይልሃል።”
“እ…ሺ” ስትለው፤ ይሄን ሃሳብ ጉያህ ውስጥ ይሸጉጠዋል።
“ይህን አስታውስ! በሽያጭ የተካንኩ ነኝ የምትል ሁሉ ድንጋይም፣ ጦርም ሰውም ይሁን እባብ ሽጥ!” አለ የገንዘብ ነብይ የሆነው Napoleon፡-
“ሰው ማለት፣ ሰው የሚሆን ሰው የጠፋ ዕለት” የምትለው የነተበች መፈክር፣ በ”ዘመኑ” ሰው ወርዳ በሌላ ተተክታለች።
“ሰው ማለት ሸቀጥ የሚሆን ሸቀጥ የጠፋ ዕለት” ተብሏል። ሰው፣ ሰውን ሸቀጥ አድርጎ መዳረሻው የት ነው? ግቡስ? ሰው ተሸጦ የተከማቸ ሀብት፣ለየትኛው ህይወት? ዘመኑ እዚህ ላይ ይተጋል። ህሊና የሌለው የሽያጭ ሠራተኛ ማብዛት፣ ሻጭን እራሱን ለገበያ ከማቅረብ የሚጀምር፣ የማያማርጥ መሸጥ በመልመዱ እናቱን፣ ልጁን፣ ሀገሩን የሚያስማማ…
… የዚህ ዘመን ሳይሆን “የዚያ ሰው” የነበሩት ልዑል ራስ ካሣ ኃይሉ፤ ስለ ሽያጭ ሠራተኛ (ነጋዴ) እንዲህ በማለት እራሳቸውን ይጠይቃሉ።
    “ነጋዴስ ደክሞ የሚያመጣው ወረት፣ ቀማኝነት የሌለበት እውነተኛ ገንዘብ አይደለምን?” እራሳቸው ሲመልሱ…
“ነጋዴም ቢሆን ምንም የመንገድ ድካም ቢኖርበት ወይም ሲገዛ፣ ወይም ሲሸጥ ማታለል የግድ የስራው ስለሆነ ከሚያታልለው ሰው ላይ የማይገባውን ሳይወስድ አይቀርምና ከንግድ ገንዘብ ውስጥ እንደ ቅሚያ ያለ ገንዘብ በግድ መቀላቀሉ የማይቀር ነው።”
ሁለተኛው ጥያቄ ከራሳቸው ከልዑል መብሰልሰል ውስጥ ይወጣል፡-
“የንግድ ገንዘብ ቅሚያ ያልተቀላቀለበት ጥሩ እንዲሆን ምን መስራት ይሻላል?”
መልሱ…
“… ከንግዱ ጎዳና አስቀድሞ መንፈሳዊነትና የዕውቀታችን  ጎዳና ይዞ ደከመውን ጉልበቱን በቅን የሚገዛ ባለምንዳ ልክ እያሰላ ዐርፎ ተድላ ደስታ ያደረባቸውን ቀኖች እየተወ ለመግዣና ለመንገድ ያወጣውን ገንዘቡን ዋና አድርጎ በጉልበቱ ልክ ትርፍን እየገመተ የሚሸጥ፣ በጉልበቱ ዋጋ ላይ ያልዋሸ እንደሆነ ሌብነት ያልተቀላቀለበት ገንዘብ ይንለታልና ቢያስቀምጠው ንፉግ ብቻ እንጂ ቀሚ አያሰኘውም።”
የዚህ ዘመንና የዚህ ሀገር ሰው ውጤቱ Napoleon Hill እንጂ የዚያ ዘመን ሰው፤ ልዑል ራስ ካሳ ኃይሉ አይደሉም። ከምክራቸው የለም። በብዛ የሚደመጠው ሰውን ስለገንዘብ ለውጡ የሚለው የዘመኑ ዋሾ ነብይ ነው።
እንደው ለመሆኑ…
… የዚህ ዘመንና የዚህ ሀገር ሰው ለልጆቹ እንዲሞቱለት ወይም እንዲሟሟቱለት የሚነግራቸው የህይወት ግብ አለ? ምንድነው? ሀገር?...ብሄር?... ህዝብ?… ጥበብ?...ወይስ ምን??
    “የዚህ ዘመን ሰው” ማለቴ “የዚያ ዘመን ሰው” የህይወት ግቡን መሳት እና ለህይወት ግቡ ሞቶ ስላለፈ ነው። የዚያ ዘመን ሰው ሀገሩን አስቀድሞ፣ ትግሉን በድል ደምድሞ፣ ለሀገሩ እምነት፣ ለእምነቱ እውነትን አስከትሎ፣ የመወጣውን ሁሉ በመቀበል አልፏል።
    ብላታ ወልደጊዮርጊስ ይሄን ምሳሌ አኑረውልና። ምሳሌው አራት መከራ የደረሰባቸው ሰዎች የተወያዩት ነው። የመጀመሪያው ሰው የደረሰበት መከራ ጠላው በድንገት ተነስቶ ጦርነት ያደረሰበት ሰው ነው አልሞት ባይ ተጋዳይ ሆኖ ነፍሱን ቢከላከልም ተዘፍፏል፤ ተገፍፏል፣ ከብቱ ተነድቷል ይሁንና በሀገር እርዳታ አንሰራርቷል፡፡
ሁለተኛው መከ
ረቃልሎ ይጀምራል “ወንድ ልጅ እጁ ካልተጨበጠ፣ የሚበላው ካጣ፣ በዋሻ በጥሻ፣ በገደል በቅጠል፣ በዱር በፈረፈር… እያለ ተከላክሎ አንድ እድል ሳይገጥመው አይቀርም፡፡” ይላል በእሱ ላይ የደረሰውን መከራ የሚያሰፋው በዱር በገደል ቢሉ ማምለጥ የማይቻው ‘ክፉ ባላጋራ ማለት ረሃብ ነው’ ብሎ ይደመድማል፡፡
ሶስተኛው ሰው የሁለቱን መከራ አጣጥሎ ጦርነትም ረሃብም ከባድ ቢሆኑም፣ መከላከያ ላይሆንለት አይቀርም በማለት የራሱን ጭንቅ ከፍ፣ ከፍ ያደርጋል፡፡ በዚህ ሰው ላይ የደረሰው በሙያ ቢስነት የሚመጣ መከራ ነው፡፡ ጭንቁ መከላከያ አልቦ እንደሆነ ያስረዳል፡፡
ሦስቱን በፀጥታ ሲያዳምጥ የቆየው ሰው እንዲህ ይላል፡፡ “መጠቃት ማለት አጥቂ ይመጣና ተከላክሎ ለመዳን ሳይቻል ቀርቶ ያገር ሰንደቅ አላማ ሲረገጥ፣ አርማዎች ሲገፈፋ፣ የንጉስ ትንፋሾች ሲጠፋ፣ አባቶች ሲሰደቡ፣ ትውልዶች ሲደበደቡ፣ ሥም ሲ ረክስ፣ ታሪክ ሲደመሰስ፣ ለመሳቂያ ሲምታቱ፣ የተቀደሱ ልማዶች ሲረክሱ፣ እርስቶች ሲወረሱ፣ የሰው ጀርባና ደረት፣ ግንባርና፣ አንገት የጥይት ጌጤዎች ሲሆኑ፣ አቤት ቢሉ ዳኛ፣ ቢሸሹ መደኛ ሲታጣ፣መሣሪያዎች ከእጅ ተፈልቅቀው ሲወሰዱ፣ የነፃነት ዘፈኖች በለቅሶ ሲለወጡ፣ ዓይኖች በዕንባ ሲሞጨመጩ፣ ጆሮዎች በጥፍ ሲደነቁሩ፣ አካላቶች በጫማ ሲረገጡ፣ እሬሳዎች መቃብር ሲነፈጉ፣ አምሮቶችና ናፍቆቶች ፍቅሮችና ትዝታዎች ጥቅጥቅ ባለ ሀዘናዊ ጉም ውስጥ ሲዘጉ፣ የአምላክ ስፍራዎና የሀይማኖት አባቶች ሲጎሳቆሉ፣ ጥርሶች ስጋቸው ያለቀ አስከሬኖች ሲመለሱ ይህንና ይህን የመሰለው የግፍ ግፍ በነፃነትና በነፃ ህዝብ ላይ ሲደረግ ከጭንቀቶ ሁሉ የበለጠ ጭንቅ ከዚህ በቀር ምንም የለም፡፡”
 በዚህ አራቱም ይስማማሉ፡፡
            አየህ!!
የዚህ ዘመንና የዚህ ሀገር ሰው ግራ የሚገባህ እዚህ ላይ ነው፡፡ ጠላት በወረራ የሚያደርገውን ሁሉ በራሱ ላይ አድርጓል፡፡ የራሱን ሰንደቅ አላማ እራሱ ረግጧል፣ የራሱን አርማዎች እራሱ ገፍፏል፣ የራሱን አባቶ እራሱ ሰድቧል፣ የራሱን ትውልዶች እራሱ ደብድቧል፣ የራሱን ሥም እራሱ አርክሷል፤ የራሱን ታሪክ እራሱ ደምስሷል፣ የራሱን መታሰቢያ እራሱ አፍርሷል የራሱን የምራቅ ጢቅታዎች በራሱ ፊቶ ላይ ተፍቷል ፤የራሱ ፉጨት ለራሱ መሳቂያ አምጥቷል፣ የራሱን የተቀደሰ ልማድ እራሱ አርክሷል፣ ከራሱ እርስት እራሱን ነቅሏል…ራሱን እራሱ አሳዷል፣ አቤት ቢል ዳኛ፣ ቢሽሽ መዳኛ አጥቷል፡፡ የራሱን ሬሳዎች እራሱ መቃብር ነፍጓል፣ የራሱን የአምላክ ስፍራዎን የራሱን የኃይማኖት አባቶች እራሱ አጎሳቁሏል፡፡
አየህ የዚህ ዘመንና የዚህ ሀገር ሰው የህይወት ግቡ ምንድነው? ተብሎ የሚጠየቀው፤ ይሄ ድርጊቱ ግራ ስለሚያጋባ ነው፡፡ ለመሆኑ የሚሞትለት ሳይሆን የሚሟሟትለት አላማስ አለው?
***
ከአዘጋጁ፡-
ጋዜጠኛ ደራሲና ሃያሲ አለማየሁ ገላጋይ ከአሥር በላይ መጻህፍትን ለህትመት ያበቃ የብዕር ሰው ሲሆን፤ የሚበዙት የህትመት ውጤቶቹ የፈጠራ ሥራዎች ናቸው - ልብወለዶች፡፡ የጋዜጠኝነት ልምድና ተሞክሮ ያካበተው አለማየሁ ገላጋይ፤በሥነጽሁፍ ሃያሲነቱም በእጅጉ ይታወቃል፡፡ ማህበራዊ ሃያሲም ነው፡፡


የቀድሞ ድምፃዊ ሙሉቀን መለሰ ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ70 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡
ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ በሀገረ አሜሪካ ኑሮውን ያደረገው ሙሉቀን መለሰ፤ የሙዚቃውን ዓለም በመተው በመንፈሳዊ የሙዝሙር ስራዎች ውስጥ ያሳልፍ እንደነበር ይታወሳል።
 
ሙሉቀን መለሰ በጎጃም ክፍለ ሀገር አነደድ ወረዳ ውስጥ ዳማ ኪዳነ ምሕረት በምትባል መንደር በ1946 ዓ.ም እንደተወለደ ግለታሪኩ ያወሳል። አሥር ዓመት ሲሆነው እናቱ ስለሞቱ፤ አዲስ አበባ ይኖሩ ከነበሩ አጐቱ ጋር እንዲማር ብለው ያመጡት ሙሉቀን መለሰ፤ ኮልፌ ሰፈር ጳውሎስ ትምህርት ቤት ሊገባ ችሏል።
 
ለሙዚቃ ልዩ ፍቅር የነበረው ድምፃዊው፤ እርሱ በነበረበት አካባቢ በተከፈተው የሙዚቃ ትምህርት ቤት ገብቶ በአቶ ተፈራ አቡነ ወልድ አማካይነት ለስድስት ወራት የዘለቀ የትምህርት እገዛ አግኝቷል።
ገና የ13 ዕድሜ ታዳጊ ሳለ ሙዚቃን የጀመረው ድምፃዊው፤ በ1958 ዓ.ም በፈጣን ኦርኬስትራ ውስጥ ተቀላቅሎ በመግባት ለሁለት ዓመታት ያህል መስራት ችሏል። ከእዚያ በማስከተል በ1960 ዓ.ም ወደ ፖሊስ ኦርኬስትራ ክፍል በመግባት ይበልጥ በሙዚቃ ስራው ዝናን ማትረፍ ችሎ ነበር።
በ1972 ዓ.ም ላይ ደግሞ ከዳህላክ ባንድ ጋር ተቀላቅሎ ሰርቷል፡፡ እስከ 1980ዎቹ ድረስ በነበሩት ዓመታት እጅግ ተወዳጅ የሙዚቃ ስራዎችንም መስራት ችሏል።
ድምጻዊው፤ የአንጋፋዋ ሁለገብ ከያኒት የአለምፀሐይ ወዳጆ እና የተስፋዬ ለሜሳን ግጥምና ዜማዎች አቀንቅኗል።
ሙዚቃ በቃኝ ብሎ ራሱን ከሙዚቃው ዓለም እስካገለለበት ጊዜ ድረስ በርካታ የሙዚቃ ስራዎችን ለትውልድ አበርክቷል።
ከ1980ዎቹ በኋላ ፊቱን ወደ መንፈሳዊ ስራዎች በማዞር የመዝሙር ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል።
እስከ ህልፈተ ሕይወቱ ድረስ በሀገረ አሜሪካ ኑሮውን አድርጎ በእዚያው ቆይቷል።
የዝግጅት ክፍላችን በአንጋፋው ድምጻዊ ሙሉቀን መለሰ ህልፈት የተሰማውን ሀዘን እየገለጸ፤ ለቤተሰቦቹና ለአድናቂዎቹ መጽናናትን ይመኛል።
 

“አንዱን ሥራ ከሌላው አላበላልጥም“

      አለማየሁ ገላጋይ የቃላት አመራረጡና አተራረኩ፣ ቦታዎችን የሚመርጥበትና አገላለፁ በእጅጉ ይገርመኛል፡፡ በየትኛውም የዕድሜ ክልል ያሉ ሰዎች የሚያነቧቸው መጻሕፍት  እያበረከተልን ነው፡፡ የብርሀን  ፈለጎች ወደ ፊልም ቢቀየሩ ምርጥ ድርሰት ነው፡፡ ውልብታ፤ የፖስት ካርድ አፃፃፍ ሙከራ ድንቅ ነው፡፡ በበኩሌ አንዱን መፅሐፍ ከሌላው ማበላለጥ አልችል፡፡ ምክኒያቱም ሁሉም የራሳቸው የሆነ ጣዕምና ለዛ አላቸው፡፡
(አስቴር - መምህርና አድናቂ)
***
አለማየሁ ገላጋይ - የአማርኛ ሥነጽሁፍ ጌጥ
አለማየሁ ገላጋይ ገና በማለዳው ጠለቅ ባለ ንባብ፣ በመጠቀ ምናብ፣ አድማስ-ዘለል ጭብጥና ጥልቅ ሥነ ልቡናዊ ፍተሻን በመፍተል ጀምሮ፣በየጊዜው መሰላሉን በወጉ እየረገጠ፣ ከፍ ያለ ማማ ላይ የተቀመጠ የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ጌጥ ነው። መሥዋዕትነቱ እንደ ጆርጅ በርናንድ ሾ ፣ ተቆርቋሪነቱ እንደ ፑሽኪን፣የሰው ወገናዊነቱ እንደ ቶልስቶይ፣ፍልስፍናው እንደ ኤሚሊ ዲክንሰን ሆነው በጽሑፎቹ ውስጥ ብቅ ይላሉ።
አለማየሁ ወደ ፈጠራ ሥነ ጽሑፍ እልፍኝ ሲገባ፣ዘው ብሎ ሳይሆን ትንፋሹን ቆጥቦ፣የካበተ የንባብ ሀብቱን በካዝናው አጭቆ፣ በቶጀረ አቅም ስለሆነ ደመናውን ካሳየ በኋላ የጥበብ ዝናቡ ሳያባራ አስራ ሰባተኛ ጎሉን ሊያስቆጥር ነው። ቤቱን በአሸዋ ላይ አልጀመረምና የመጣው ንፋስ ሁሉ ሳይነቀንቀው፣የንፋሱን ፉጨት ሙዚቃው አድርጎ እየታጀበ፣ የሥነ ጽሑፍ ማጀታችንን እየሞላ፣ረሀባችንን እያስታገሰ፣ከአድማስ አንደምትናፈቅ የክረምት ጀንበር ብርቅ ሆኗል። ይህንንም ሲያደርግ፣ የአዲሱን ትውልድ ቀለም ሳይንቅ ፣ለቀደመው ሳይሰግድ፤የፈረንጁን ሳይገፋ፣ሀገራዊ እርሾውን ሳይደፋ አዋህዶና አዋድዶ፣በሮማዊ ሥልጣኔ ብልሃት፣የጥበብ ሥራውን ቀጥሏል። በቋንቋ ውበት፣በገለጻ ብቃት እያሳመረ፣በጣፋጭ ኪናዊ  ትረካ እነሆ የተጠማውን ምድረበዳ እያራሰ ዛሬን ደርሷል።
(ደራሲ ደረጀ በላይነሀ)
***


“የአገር ጉዳይ የሚገደው ደራሲ“
ለከት የተበጀለት ምናባዊነት የድርሰት ማባያ ነው፤ ምናብ ከዕውን የሰማይ ያክል መራቅ አይጠበቅበትም፤ ታዲያ ዓለማየሁ ገላጋይ ለምናባዊነት ገደብ ያበጅና፣ ማሕበረ-ባሕላዊ ዕሴቶቻችንን፣ ግርንቢጦሻዊ የአኗኗር ይትባሃላችንን፣ ላይሞላ ጎጆ ጉዟችን በመናጆ፣ የሚጣምን ግብታዊነታችንን…ሌላም ሌላም በድርሰቶቹ አስጎብኝቶናል፤ ከሚጽፍለትና ከሚጽፍበት ማሕበረሰብ የተናጠበ ድርሰት ጀባ ባለማለቱ ሁሌም ምስጉን ነው፤ የማይለፋደዱና የማይነታረኩ ስልታዊ ማንቂያና ማብቂያ ናቸው ድርሰቶቹ!... …ዓለማየሁ ገላጋይ አገር ይገደዋል፤ የአለማሰብ ጣመን ይመዘምዘዋል፤ ወለፈንዴነታችን እንደሻህላ ይቧጥጠዋል፤ በግብታዊነት የምንኖረው ሁሉ እንደ ለበቅ ይፈጀዋል፤ እንደ ዕጣን ፎናኔ ላንታይ ላናይ መንከላወስ መባተላችን ይመዘምዘዋል፤ ቁምነገር ላንጽፍ እንደ ጉንዳን ኮቴ መጥተን ማለፋችን የዕንቅልፍ ለምኔው ምክንያት ነው፤ ትውልድ እንዲገደው ዕሙን ነው፤ ገጸ-ባሕሪይ እና መቼት መቅረፅ ከረቀቀባቸው ጉዳዮች መካከል ዋንኞቹ ናቸው፤ የንባብ ልምዱ ግሩም ነው፤ ያንን ማካፈል ያውቅበታል፤ ሀሳቡን የሚሸከም ቋንቋ መቀመም ልማዱ ሆኖ በአሥራ ስድስቱም ድርሰቶቹ አስተውለናል፤ በአዲሱ ሥራ አዳዲስ የአተራረክ ቴክኒኮችን ይዞ እንደሚመጣ በልበ-ሙሉነት እጠባበቃለሁ!
(ዮናስ ታምሩ - ሃያሲ)




__________________




                     ”አሌክስ የሥነጽሁፍ አዝመራው ሰፊ ነው”


       አንድን ደራሲ ልናደንቀው የሚገባን በአንባቢነቱ መሆን የለበትም ብዬ አምናለሁ:: ወታደሩን ያለ ተኩስ፣ ገበሬውንም ያለ እርሻ ማሰብ ከባድ እንደሆነው ሁሉ፣ ለደራሲ ትጥቁና ስንቁ መጻሕፍት ናቸው:: ይልቁንስ ደራሲ ሊደነቅ የሚገባው ሳይታክት መናበብ ሲችል ነው::
ወዳጃችን አለማየሁ ገላጋይ ለዚህ ታድሏል:: ብዙውን ጊዜ ከራሱ፣ ከጊዜው መንፈስና ከዘመኑ የሥነፅሁፍ እንቅስቃሴ ጋር ለመናበብ ቤቱ ብቻ ሳይሆን ልቡም ክፍት ነው፡፡ ለዚህም ነው በሃሳብ የተለየህ ብትሆን እንኳን ሊያነብህና ሊያስነብብህ ዝግጁ ሆኖ የሚያስተናግድህ!
አሌክስ የሥነጽሁፍ አዝመራው ሰፊ ነው! ደግሞም በሰጠ ቁጥር የሚበዛለት አይነት ሰው:: ሲሰጥ የፊተኛውን ያልመሰለ እንዲሆንለት ይመኛል:: በተለይ ከቴክኒክ አንጻር! እንኳንስ ሌላውን ራሱንም ባይኮርጅ ጽኑ ምኞቱ ነው:: ጭብጦቹ የማህበረሰቡን ፎከሎር የሚገልፁ፣ ለተገፋው ለተከፋውና  ለተናቀው ‘ምስኪን’ ጥብቅና የሚቆሙ ናቸው:: የሚሞግቱ የሚያሟግቱ፣ ምን ሆነን ነው ከነበርንበት ዝቅ ያልነው? የሚሉ!
ዛሬ ዛሬ ‘እገሌ መጽሀፍ አወጣ!’ ሲባል፣ ‘ስለምን?’ ብለን ሳንጠይቅ፣ ተማምነን የምንገዛቸው ጥቂት ደራሲያን  መሃል አንዱ አለማየሁ ገላጋይ ሆኗል፤ መልሶ መላልሶ በመጣልን የምንለው ደራሲ ነው፤ እናም እንጓጓለን፤ በአዲሱ መፅሐፉ ምን ብሎ ያጫውተን፣ ይጎነትለን ይሆን እያልን!
(ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ)




_________________




                 ሌላው “የሥነጽሁፍ ወዛደር”


       ዓለማየሁ ገላጋይ፣ በወሪሳ አውድማ ላይ በምጸታዊ መንሽ ማኅበራዊ አዝዕርትን ንፋስ ላይ አበጥሯል። በታለ ማሰሮ ጦማራዊ ልቦለድን ንጧል። በኢህአዴግን እከስሳለሁ ሙቀጫ የጋዜጠኝነትን ዘነዘና ይዞ ምኩራብ ወጥቷል። በቅበላ ብራና የድህረ ዘመናዊ ልቦለድን ከትቧል። በመልክአ ስብሃት ሰፌድ ላይ ሰበዝም፣ አለላም፣ አክርማም ሆነ ስንደዶ ለመሆን የሚመች፥ የደቦ ከያኔ መሆኑን ተመልክተናል። በየፍልስፍና አጽናፍ ተርጓሚነቱን፣ በስብሃት ገ/እግዚአብሔር ሕይወትና ክሕሎት - ኀያሲነቱን አስመስክሯል። በየተጠላው እንዳልተጠላው አይነኬ ዕሳቤዎችን በመጠይቅ ወንፊት አንገዋሏል። በአጥቢያ የንስር ዓይናማነቱን፣ በመለያየት ሞት ነው ሊቀ-መጣጥፍነቱን፣ በፍቅር ስም ላይ ደግሞ experimental novelist-ነቱን ተመልክተናል። በኩርቢት መም ላይ የስሜት ጂምናስቲክ አሠርቶናል። በ17ኛው መጽሐፉ ደሞ 24 እንዳልሞላው ሊያስታውቀን ተከስቷል። እኔ በበኩሌ በጋሽ ወንድዬ ዓሊ ብሂል፤ “የሥነ-ጽሑፍ ወዛደር” ብዬዋለሁ።
(ደራሲ ቢንያም ቡራ)




__________________




                  “ቃላት አጠቃቀሙ ልክ እንደ ቼኾቭ ነው”


       ከጓደኞቻችን መሀል እንደሱ በንባብ የበልፀግ ሰው አላየሁም፤ የአስተሳሰብ አድማሱ ጥልቅ ነው ፤ ቃላት አጠቃቀሙ ልክ እንደ ቼኸቭ ነው፤ ገፀ ባሕርያቶቹን ደሞ የሚያብሰለስላቸው ልክ እንደ ደስታየቭስኪ ነው ፣ ያውቅበታል።
የጨፈገገ ፊት ያለው ደራሲ  አለማየው ገላጋይ፤ ተወልዶ ያደገው  የከተማ እንብርት በሆነችው አራት ኪሎ በፈካና በነቃ ማህበረሰብ ውስጥ ነው ።  በዚያ ሳቅና ፈገግታ፣ ጨዋታና ፌሽታ፣ ዝሙትና  ስካር ፣ማግኘትና ማጣት፤ ከዩኒቨርሲቲ ተማሪ እስከ ዩንቨርስቲ ምሁራን፣ ከቄስ ቆጶሳት እስከ መነኮሳት ፣እስከ ጳጳሳት፣ ሲበሉ ሲጠጡ ሲሾሙ ሲሻሩ፣ ሲነግሱ፣ ሲረክሱ፤ የከተማ መናኝ ሆኖ ዘመኑንና  ዓይኑን በንባብና በትዝብት ያሳለፈ፤ የዓይን ምስክርነቱን በፃፋቸው መጻሕፍቱ  ፍትሃነቱን ያስመሰከረ፤ ከደመና መሳይ ጭጋግማ መልኩ ፈገግታን የሚፈነጥቅ ፣ሲያሻውም በምፀት የሚያስጨንቅ ሀቀኛ ብዕረኛ ነውና፡፡       ብዙ ህይወትና ገጠመኙን በመኖር ሳይሆን በትዝብትና በማብሰልሰል የሚፈጅ፤ አጭር ጊዜውን በማብሰልሰል የቋጠረውን የሀሳብ ሽል ደበቅ ብሎ እራሱን የሚያዋልድና ፈገግታ ፣ሀዘንና ፣ቁጭቱን ፣ህልምና ተስፋውን ፣ግን በመልካም ሥነ ፅሁፍ ላደገበትና ለኖረበት ማህበረሰብ የበኩሉን ዕሳቤ ጠብ የሚያደርግ. ኢትዮጵያ ዊ ዶስቶቭስኪ ነውና
     ዓለማየሁ ገላጋይ በአተራረኩ እየተረከ ሳይኾን እያጫወተ ያወያያል፣ ገጸ ባሕርያቱ አጠገብህ ያሉ እየመሰለኽ ከንባብ ተናጥበህ ዙሪያህ  ትፈልጋቸዋለህ። የሚጽፋቸው ልቦለዶች ውስጥ ጥልቅ ንባቡንና ብያኔዎቹን ታገኛቸዋለህ። ለመጻፍ ብሎ የጻፈ ይመስልሃል እንጂ እርሱ ግን ከንባቡ ሞልቶ ሲፈስ ነው የጻፈው። አንዳንዶች አለማየሁ ያነበበውን አስታውሶ ይጽፋል ቢሉትም፣ ነገሩ ግን ሙዚቃዊ ወይም ግጥማዊ ድንገቴነት የከሰተው ይመስለኛል።
(አለማየሁ አሊ)


Page 1 of 700