Administrator

Administrator

"ዕንቁ ሴት፣ ንቁ ሴት፣ ዝግጁ ሴት"

"ዕንቁ ሴት፣ ንቁ ሴት፣ ዝግጁ ሴት"የተሰኘ  ቅዳሜ መጋቢት 21 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ ሰንጋተራ በሚገኙ ፐርፐር ብላክ አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።

በዕለቱም ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ ፣ አርቲስት መቅደስ ፀጋዬ ፣ ሲሰተር ዘቢደር ዘውዴ ጭምሮ የተለያዩ እንግዶች ሀሳቦቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።

ሃያኛው የባለአክሲዮኖች አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤውን መጋቢት 14 ቀን 2014 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ ያካሄደው ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ፣ የተከፈለ ካፒታሉን ወደ 20 ቢሊዮን ብር ለማሳደግ ውሳኔ አሳለፈ፡፡    
የባንኩ አዲሱ የዲሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር አቶ ሺሰማ ሸዋነካ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ንብ ኢንተርናሽናል ባንክን ወደ ቀድሞ ከፍታው ለመመለስና ላቅ ወዳለ ደረጃ ለማድረስ በሚያስችል ጉዞ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
“ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በበርካታ ደንበኞች በተለይም በንግዱ ማኅበረሰብ ዘንድ ተወዳጅ ባንክ ነው’’ ያሉት ሊቀመንበሩ፤ ባለአክሲዮኖች ከምንጊዜውም በበለጠ ድጋፋቸውን እንዲያረጋግጡለት ጠይቀዋል።
ቀደም ሲል እንደ አገርም ሆነ በዘርፉ እንዳሉ ሌሎች ተቋማት ሁሉ ያጋጠሙ የገንዘብ አከል ችግሮች በንብ ባንክ ደረጃ በባሰ መልኩ መስተዋላቸውን በመጥቀስ፣ አሁን ግን አዲስ የተመረጠው የዲሬክተሮች ቦርድ ችግሮችን እያቃለለ መምጣቱን ጠቁመዋል፡፡
ባንኩ፣ “በአዲስ መንፈስ፣ ለላቀ ከፍታ!” በሚል መሪ ቃል ያስጀመረውን የማርኬቲንግ ንቅናቄ ተከትሎም፣ በሂደት የባንኩ ቅርንጫፎች ምንም አይነት የስንቅ ችግር እንዳያጋጥማቸው መሠራቱን ተናግረዋል፡፡ ደንበኞች ከቼክ ምንዛሪ ጋር በተገናኘም ስጋት እንዳይገባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
ባንኩ በምንጊዜም ባለውለታነት ሊጠቀሱ የሚችሉ የረጅም አመታት ባለአክሲዮኖችና ደንበኞች ያሉት መሆኑን የጠቀሱት ሊቀመንበሩ፤ አሁን ላይ ሁሉም ገንዘባቸውን ሲያስወጡም ሆነ ሲያስገቡ በንብ ኢንተርናሽናል ባንክ እንዲሆን ጠይቀዋል፡፡
የደንበኞቹን እምነት መልሶ ለመገንባት የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ የሚገኘው ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ፤ አስቸጋሪ ባለው የሥራ ወቅት የተከፉ ደንበኞቹን በይፋ ይቅርታ በመጠየቅ በጀመረው አገራዊ የማርኬቲንግ ንቅናቄ መልካም ለውጦችን እያመጣ መሆኑን የቦርድ ሊቀመንበሩ አቶ ሺሰማ አስታውቀዋል።
በቀጣይም ወደ ትግበራ በገባው የዘጠና ቀናት ፍኖተ ካርታ ዕቅድ መሠረት በሁሉም የባንክ አገልግሎቶች ፈጣን ለውጦችን በማምጣት ንብ ባንክን ወደነበረበትና ከዚያም ላቅ ወዳለ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ ቁርጠኝነት መኖሩን በአስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤው ለተገኙ ባለአክሲዮኖች ገልጸዋል፡፡
አዲሱ ቦርድ ወደ ሥራ ከገባበት አጭር ጊዜ አኳያ ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ የሚያስችሉ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ መሆኑን መገንዘባቸውን የገለጹት የጉባኤው ተሳታፊ ባለአክሲዮኖችም፤ ቦርዱ ባንኩን ከግል ባንኮች ዘርፍ ከፊት ለማሰለፍ የሚያደርገውን ጥረት በመደገፍ ከጎኑ እንደሚቆሙ በሰጡት ቃል አረጋግጠዋል።
በጉባኤው ከተነሱ አጀንዳዎች መካከል አንዱ፣ እ.ኤ.አ በ2022 የተገኘውና ያልተወሰነበት የትርፍ ድርሻ ክፍፍል ላይ ውይይት በማድረግ ገንዘቡ ለባንኩ ካፒታል ማሳደጊያነት እንዲውል የባለአክሲዮኖች ጉባኤ በአብላጫ ድምፅ ወስኗል።
በባንኩ በ18ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተወሰነውን የካፒታል ማሳደጊያ ጊዜ እንዲሻሻል በተደረገው ውይይትም፣ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም ተጠናቅቆ እንዲከፈል መወሰኑን ከባንኩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

በአማራ ክልልና በትግራይጊዜያዊ አስተዳደር መካከል የተከሰተው ውዝግብ ተባብሶ ቀጥሏል። ሁለቱም ወገኖች በየፊናቸው ማስጠንቀቂያና መግለጫ እያወጡ ነው፡፡
የአማራ ክልል  ትናንት ባወጣው መግለጫ፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ሀገሪቱን ና ሁለቱን ክልሎች ወደ ቀውስ ከሚያስገቡ ተግባራቱ  እንዲቆጠብ አስጠንቅቋል። የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር  ያወጣው መግለጫ ጠብ አጫሪ  እንደሆነም ገልጿል። ክልሉ ባወጣው በዚሁ መግለጫው፤  “የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር  መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ.ም የራያ አላማጣ ወረዳ ቀበሌዎችን በመያዝ  የአካባቢው ነዋሪዎችን በመግደልና በማሰቃየት ላይ ይገኛል” ሲል ከስሷል።
የአማራ ክልል በመግለጫው፤ “የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከመማሪያ መጽሐፍ ካርታ ጋር በተያያዘ በአማራ ክልል ላይ ጥቃት ከመፈጸም የማይመለስ መሆኑን የሚገልጽ የጠብ አጫሪ መግለጫ ማውጣቱ ካለፉት ድርብርብ ውድቀቶች ትምህርት አለመውሰድን ከማሳየት የዘለለ ፋይዳ አይኖረውም” ብሏል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ለሀገሪቱ ቋሚ ቀውስ ምንጭ ከሚያደርጉት ተግባራት እንዲታቀብና ሀገሪቱንና ሁለቱን ክልሎች ወደ ቀውስ ከሚያስገቡ ተግባራት እንዲቆጠብም የአማራ ክልል መንግስትአስጠንቅቋል።  በተጨማሪም ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከለመደው አጓጉል የካርታ ፖለቲካ ጨዋታ እንዲወጣና የህዝብን ፍላጎት ማዕከል ባደረጉ ውይይቶች ላይ እንዲያተኩር ክልሉ  መክሯል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ በበኩሉ ሰሞኑን ባወጣው መግለጫው፤ “የአማራ ክልል መንግሥት የትግራይ መሬቶችን የግዛቱ አካል በማድረግ፣ በክልሉ ካርታ ላይ አስፍሯል፤ የትግራይ ክልል መሬቶች የሰፈሩበትን ካርታ በትምህርት ካሪኩለሙ በማካተት እያስተማረበት እንደሚገኝ ተረድቻለሁ” ብሏል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ፣ የአማራ ክልል በመማሪያ መጽሐፍት ላይ ያወጣውን የተሳሳተ ካርታ በአስቸኳይ ማስተካከያ እንዲያደርግ በመግለጫው  ያስጠነቀቀ ሲሆን፤ ይህ የማይሆን ከሆነ ግን “ይህን ተከትሎ ለሚመጣው ነገር ሁሉ ሃላፊነቱን የሚወስደው የአማራ ክልል መሆኑን ልናሳውቅ እንወዳለን” ብሏል።


ከተለያዩ ክልሎች የተውጣጡ 500 ተሳታፊዎች ይወዳደራሉ  

የአዲስ አበባ ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ከሳኦል ኩነቶች አዘጋጅ ጋር በትብብር  ለሚያዘጋጁት የአዲስ አበባ ወርልድ ቴኳንዶ ኦፕን ቶርናመንት የመግባቢያ ሰነድ የተፈራረሙ ሲሆን፤ ውድድሩ ከሚያዚያ 19  እስከ ሚያዚያ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ይካሄዳል ተብሏል፡፡

ለውድድሩ አሸናፊ የ1 ሚሊዮን ብር ሽልማት  መዘጋጀቱ ተነግሯል፡፡

አዘጋጆቹ ትላንት አርብ መጋቢት 20 ቀን 2016 ዓ.ም በአራት ኪሎ ስፖርት ትምህርት ስልጠና ማዕከል የስብሰባ አዳራሽ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ የአዲስ አበባ ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ከሳኦል ኩነቶች አዘጋጅ ጋር በትብብር የሚያዘጋጁት የአዲስ አበባ ወርልድ ቴኳንዶ ኦፕን ቶርናመንት በተለያየ የእድሜ እርከን እንደሚካሄድ ተናግረዋል፡፡

ለውድድሩ አሸናፊዎች  የአንድ ሚሊዮን ብር ሽልማት መዘጋጀቱ የተገለጸ ሲሆን፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሁሉም ክልሎች እንዲሳተፉ እንደሚደረግና ከክልል ለሚመጡ ተወዳዳሪዎች የማረፊያ ቦታ ለማዘጋጀት ጥረት እየተደረገ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸል፡፡

 በዚህ ቶርናመንት እስከ 500 ተወዳዳሪዎች ይሳተፉበታል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ተወዳዳሪዎች እንድ የእድሜ  እርከናቸው ለመመዝገቢያ ከ300 ብር እስከ 1000 ብር  እንዲከፍሉ ይጠበቃል ተብሏል፡፡



የሳኦል ኩነቶች አዘጋጅ መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት ደረጄ በመግለጫው ላይ እንደተናገሩት፤ ውድድሩን ለማዘጋጀት የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በማጠናቀቅ ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ለዝግጅቱ ማስኬጃ እስከ 700ሺ  ብር እንደመደቡ ገልፀዋል።

በእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ፣ የወተት ላሞች እርባታና የወተት ማቀነባበሪያ ሥራ ላይ የተሰማራው ርሆቦት ኃ.የተ.የግል ማህበር፤የፊልም ተዋናይዋን አርቲስት ራሄል እንግዳን የእናት ወተት ብራንድ አምባሳደር አድርጎ ሾማት፡፡

በዛሬው ዕለት ከሰዓት በኋላ በሸራተን አዲስ በተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ርሆቦት ኃ.የተ.የግል ማህበርና አርቲስት ራሄል እንግዳ በጋራ ለመሥራት ተፈራርመዋል፡፡   

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደተጠቆመው፣ አርቲስቷ  በርሆቦት ኃ.የተ.የግል ማህበር ሥር ከሚተዳደሩት አንዱ የሆነው  የእናት ወተት  የብራንድ አምባሳደር ሆና ምርቱን ታስተዋውቃለች ተብሏል፡፡

በመጋቢት 2010 ዓ.ም የተመሰረተው ድርጅቱ ዓላማው፣ ኢትዮጵያን የወተት ማማ ማድረግና የወተት እጥረትን መቅረፍ መሆኑን ይገልጻል፡፡  

ድርጅቱ፤ ትኩስ (ፍሬሽ) ወተት፣ፕሌን ዮገርት፣ የተለያዩ ጣዕም ያላቸው ፍሌቨሮች፣ ሁሉም ዓይነት የቺዝ ምርቶች እንዲሁም  የምግብና የገበታ ቅቤ የሚያመርት ሲሆን፤ ምርቶቹን በአዲስ አበባ ሁሉም ክፍለ ከተሞች ፣በኦሮሚያ ቡራዩ፣ ገላን፣ ዱከም፣ ቢሾፍቱ፣ ሞጆና አዳማ  እንደሚያከፋፍል አስታውቋል፡፡

አርቲስት ራሄል እንግዳ ከፊልም ተዋናይነቷ ባሻገር ለዓላማዋ የጸናች ትልቅ የጥበብ ባለቤት መሆኗን የገለጸው ድርጅቱ፤ የእናት ወተት  አምባሳደር ሆና  ብራንዱን በማስተዋወቅ ረገድ ጉልህ ሚና እንደምትጫወት እምነቱን ገልጧል፡፡

ሃያኛው የባለአክሲዮኖች አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤውን መጋቢት 14 ቀን 2014 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ ያካሄደው ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ፣ የተከፈለ ካፒታሉን ወደ 20 ቢሊዮን ብር ለማሳደግ ውሳኔ አሳለፈ፡፡    
የባንኩ አዲሱ የዲሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር አቶ ሺሰማ ሸዋነካ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ንብ ኢንተርናሽናል ባንክን ወደ ቀድሞ ከፍታው ለመመለስና ላቅ ወዳለ ደረጃ ለማድረስ በሚያስችል ጉዞ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
“ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በበርካታ ደንበኞች በተለይም በንግዱ ማኅበረሰብ ዘንድ ተወዳጅ ባንክ ነው’’ ያሉት ሊቀመንበሩ፤ ባለአክሲዮኖች ከምንጊዜውም በበለጠ ድጋፋቸውን እንዲያረጋግጡለት ጠይቀዋል።
ቀደም ሲል እንደ አገርም ሆነ በዘርፉ እንዳሉ ሌሎች ተቋማት ሁሉ ያጋጠሙ የገንዘብ አከል ችግሮች በንብ ባንክ ደረጃ በባሰ መልኩ መስተዋላቸውን በመጥቀስ፣ አሁን ግን አዲስ የተመረጠው የዲሬክተሮች ቦርድ ችግሮችን እያቃለለ መምጣቱን ጠቁመዋል፡፡
ባንኩ፣ “በአዲስ መንፈስ፣ ለላቀ ከፍታ!” በሚል መሪ ቃል ያስጀመረውን የማርኬቲንግ ንቅናቄ ተከትሎም፣ በሂደት የባንኩ ቅርንጫፎች ምንም አይነት የስንቅ ችግር እንዳያጋጥማቸው መሠራቱን ተናግረዋል፡፡ ደንበኞች ከቼክ ምንዛሪ ጋር በተገናኘም ስጋት እንዳይገባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
ባንኩ በምንጊዜም ባለውለታነት ሊጠቀሱ የሚችሉ የረጅም አመታት ባለአክሲዮኖችና ደንበኞች ያሉት መሆኑን የጠቀሱት ሊቀመንበሩ፤ አሁን ላይ ሁሉም ገንዘባቸውን ሲያስወጡም ሆነ ሲያስገቡ በንብ ኢንተርናሽናል ባንክ እንዲሆን ጠይቀዋል፡፡
የደንበኞቹን እምነት መልሶ ለመገንባት የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ የሚገኘው ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ፤ አስቸጋሪ ባለው የሥራ ወቅት የተከፉ ደንበኞቹን በይፋ ይቅርታ በመጠየቅ በጀመረው አገራዊ የማርኬቲንግ ንቅናቄ መልካም ለውጦችን እያመጣ መሆኑን የቦርድ ሊቀመንበሩ አቶ ሺሰማ አስታውቀዋል።
በቀጣይም ወደ ትግበራ በገባው የዘጠና ቀናት ፍኖተ ካርታ ዕቅድ መሠረት በሁሉም የባንክ አገልግሎቶች ፈጣን ለውጦችን በማምጣት ንብ ባንክን ወደነበረበትና ከዚያም ላቅ ወዳለ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ ቁርጠኝነት መኖሩን በአስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤው ለተገኙ ባለአክሲዮኖች ገልጸዋል፡፡
አዲሱ ቦርድ ወደ ሥራ ከገባበት አጭር ጊዜ አኳያ ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ የሚያስችሉ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ መሆኑን መገንዘባቸውን የገለጹት የጉባኤው ተሳታፊ ባለአክሲዮኖችም፤ ቦርዱ ባንኩን ከግል ባንኮች ዘርፍ ከፊት ለማሰለፍ የሚያደርገውን ጥረት በመደገፍ ከጎኑ እንደሚቆሙ በሰጡት ቃል አረጋግጠዋል።
በጉባኤው ከተነሱ አጀንዳዎች መካከል አንዱ፣ እ.ኤ.አ በ2022 የተገኘውና ያልተወሰነበት የትርፍ ድርሻ ክፍፍል ላይ ውይይት በማድረግ ገንዘቡ ለባንኩ ካፒታል ማሳደጊያነት እንዲውል የባለአክሲዮኖች ጉባኤ በአብላጫ ድምፅ ወስኗል።
በባንኩ በ18ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተወሰነውን የካፒታል ማሳደጊያ ጊዜ እንዲሻሻል በተደረገው ውይይትም፣ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም ተጠናቅቆ እንዲከፈል መወሰኑን ከባንኩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

በቀድሞው ዘመን አንድ የወረዳ ገዢ ነበሩ፡፡ መቶ አለቃ ናቸው፡፡ ዛሬ እንደ ተረት ሊወሱ አንድ ሐሙስ ነው የቀራቸው፡፡
አንድ ቀን የወረዳውን ህዝብ በሙሉ ጠርተው “ንቃት ልንሰጣችሁ ነውና አንድ ሰው እንዳይቀር፤ የቀረ ወዮለት” የሚል ማስፈራሪያ - አዘል ማሳሰቢያ ሰጡ፡፡ ህዝቡ በነቂስ ወጣ፡፡ ባይወጣ ምን እንደሚከተለው አሳምሮ ያውቃል፡፡
ለተሰበሰበው ህዝብ እንዲህ ሲሉ ንግግር አደረጉ፡-
“አብዮታችን በደረሰበት ደረጃ ይህ የዛሬው የንቃተ-ህሊና ማዳበሪያ ስብሰባ ቁልፍ ሚና  እንደሚጫወት ጠላቶችን ባይገባቸውም፣ በወገኖቻችን ዘንድ አንዳችም የጥርጣሬ መንፈስ የማይፈጥር ለመሆኑ አንድና ሁለት የለውም፡፡ ዛሬ የተሰበሰብነው ስለማንኛውም የሀገራችን ጉዳይ ያለንን አስተያየት፣ ጥያቄ ወይም ሌላ ማንኛውም ግንዛቤ የማስጨበጫ ሀሳብ እንድትሰጡና በእኔና በጓዶቼ በኩል ማናችንም ጥያቄ ለመመለስ የሚቻለንን ሁሉ እንድናደርግ በማሰብ ነው። የጓድ ሊቀመንበር አመራር የተመሰገነ ይሁንና፣ ንቃተ - ህሊናችሁ ከፍ እንደሚል ጠንካራ ዕምነት አለን፡፡ በዚህ መሰረት አሁን የምናድለውን ወረቀት ትወስዱና ስለ አብዮታችን ለመጠየቅ የምትፈልጉትን ማንኛውንም ጥያቄ ትጽፉልናላችሁ፡፡”
በተነገረው መሰረት ወረቀት ታደለ፡፡ ጥያቄ መጠየቅ የፈለገ ሁሉ ስሙን ሳይጽፍ አቀረበ፡፡
መቶ አለቃው የመጡትን በርካታ ጥያቄዎች እየተመለከቱ ለየሚመለከተው የፖለቲካ ኃላፊዎች መደቡ፡፡ ከሳቸው አጠገብ የወጣቶች ተጠሪ፣ የሴቶች ጉዳይ ኃላፊ፣ የሠራተኛ ማህበር ተወካይ ወዘተ ተቀምጠዋል፡፡ ስለዚህ መቶ አለቃ ለእነዚህ የፖለቲካ አጋሮቻቸው ጥያቄዎቹን አከፋፈሉ። ስለወጣቶቹ ከተጠየቀ ለወጣቱ ተጠሪ፣ ስለሴቶች ከሆነ ለሴቶች ጉዳይ ኃላፊዋ - በየዘርፋቸው አከፋፈሉ ማለት ነው፡፡ ኃላፊዎቹም በበኩላቸው የፖለቲካ ገለጻ አደረጉ፡፡ ከየአንዳንዱ ገለጻ በኋላም ተገቢው ጭብጨባ ተበረከተላቸው፡፡
በመጨረሻ የራሳቸው የመቶ አለቃ ተራ ደረሰ፡፡ “በዕውነቱ ሁሉም ጓዶች ተገቢውን ዕውቀትና ንቃት እንዳስጨበጡዋችሁ ከፍተኛ ዕምነት ነው ያለኝ፡፡ አሁን ደግሞ በእኔ በኩል ለደረሰኝ ጥያቄ እንደሌሎቹ ጓዶች መልስና ማብራሪያ እሰጣችኋለሁ” አሉና ተደላድለው ተቀመጡ፡፡ ከዚያ ቃለ-ምልልስ በሚያደርግ ሰው ቅላፄ ቀጠሉ፡-
“ለእኔ የመጣው ጥያቄ ከዋና ዋና የፖለቲካ ጥያቄዎች ሊመደብ የሚችል ነው፡፡ ይኸውም “የፓሪስ ኮሚዩን ለምን ፈረሰ?” የሚል ነው፡፡ እኔ ለዚህ ያለኝ መልስ”… አሉና ድምፃቸው በድንገት ወደ ቁጣ ተለወጠ፤
“የፓሪስ ኮሚዩን፤ ፈረሰ ፈረሰ! በቃ ምን መጨቃጨቅ ያስፈልጋል? ጨርሻለሁ” አሉና ተቀመጡ፡፡
***
“ፈረሰ ፈረሰ!” የሚል መሪ ወይ አለቃ ካጋጠመን ዕድለኞች አይደለንም ማለት ነው፡፡ የፈረሰው “ለምን ፈረሰ?”፣ “በፈረሰው ቦታ ምን ይተካ?”፣ “እንዴትስ ይህን ጥያቄ የህዝቡ ጥያቄ መሆኑን ማስገንዘብ ይቻላል?” መባል አለበት፡፡ ይህን የሚጠይቅ ሀላፊ ያስፈልገናል፡፡ ነገ የተሻለ ህይወት ይኖር ዘንድ የወደቀው እንዲነሳ፣ የፈረሰው እንዲገነባ፣ አወዳደቁንና አፈራረሱን ማወቅና ማሳወቅ ያስፈልጋል፡፡
“ታማኝ ነው ያሉት የስለት ዕቃ ይሰርቃል” ይባላልና የሚተማመኑበት መሪ ቀን አይቶ ይከዳል የሚል ጥርጣሬ ከህዝብ አዕምሮ አይጠፋም፡፡ ይህን ጥርጣሬ በጊዜ ካላስወገዱ ደግሞ ጥርጣሬ አድጎ ወደ ተቃውሞ፣ አድሮም ወደ ጠንካራ ፍጭት እንዳይለወጥ መጠንቀቅ የግድ ይሆናል። የሥልጣን  ሁሉ ጥልቅ ተዓምር ተለዋዋጭነቱ፣ ተሸርሻሪነቱ ከርሞም ጠዋት ያሉትን ማታ ለመካድ መመቸቱ ነው፡፡ ሥልጣን ለዚህ ኃይል ያጎናጽፋል፡፡ ስለዚህም ህዝብ ሁሌ መጠራጠሩና ለጥርጣሬው ተጨባጭ መፍቻ ካላገኘ አገር ችግር ላይ መውደቅ ጀመረች ማለት ነው፡፡ እንደ ድርቅ ሙስናና አስተዳደራዊ ኢ-ፍትሃዊነት ያለ ጎጂ ባህል ሲታከልበት፣ በችግሩ እሳት ላይ ቤንዚን ማርከፍከፍ ይሆናል፡፡ ዛሬ የኢትዮጵያን ውስብስብ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግር ለመፍታት የበርካታ ድርጅቶችን፣ ፓርቲዎችን፣ ታዋቂ ግለሰቦችን ርብርብ ይጠይቃል። በዓላማና በጠባይ ባይመሳሰሉም፣ የደም የአጥንት ቂም ቢኖራቸውም፣ ዕድሜ ልካቸውን የሚታረቁ ባይመስላቸውም፣ የችግሩ ጥልቀት ያግባባቸዋል - የግዳቸውን! የዛሬው ዕውነታ ወደድንም ጠላንም ይሄው ነው!
ሁሌ እሥር ቤት የሚያስታርቃቸውን የፖለቲካ ድርጅቶች ማየት አገራችን ሳትታክት አልቀረችም፡፡ “የመቀመጥ ብዛት የደረቀ ቁስል ያስፍቃል” እንዲሉ ብዙ ተቀምጠው የቆዩ ፖለቲከኞች ዋና ችግር የተረሳ ጉዳይን እየቀሰቀሱ መናቆር ነው፡፡ ይሄ ሊያበቃ ግድ ነው፡፡ ጊዜ ሳያልፍ፣ ሌላ ዕድል ሳያመልጥ፣ ጀንበር ሳትጠልቅ የአገራችንን ችግር በጥሞና ማስተዋል እጅግ ተገቢ ነው፡፡ አለበለዚያ ውጤቱ፡-
“ውሎ ይደር ያሉት ነገር ዕዳ ይሆናል፤ እባብ እቤት ገብቶ ዘንዶ ይሆናል” የሚለው ተረት ነው።
መከራውን ወደ መከር ለመለወጥ ጨክኖ መታገስን ይጠይቃል፡፡ ጨክኖ መከባበርን ይጠይቃል፡፡ ጨክኖ መቻቻልን ይጠይቃል፡፡ ከማንኛውም ጉዳይ፣ ከማንኛውም ወገን፣ ከማንኛውም ሰው በላይ አገርን ለማየት የሚችል የፖለቲካ ፓርቲ ማግኘት ዛሬ እንደመለኮታዊ ፀጋ የሚቆጠር ሆኗል፡፡ ከችግሮቻችን ማለትም ከአስተዳደራዊ አሽክላችን፣ ከሙስናዊ ምዝበራችን፣ ከሀሳዊ-ዲሞክራሲያችን፣ ከየአሥር ዓመት የድርቅ ልደታችን፣ ከእርስ በርስ ግጭቶቻችን፣ ከየማን-አለብኝ ዕብሪታችን ሁሉ ለመገላገል ቢቆረቁረንም፣ ቢያጎሰቋቁለንም፣ በእልህ ቢያቃጥለንም---ከሁሉ ባሻገር ያለውን ተስፋ ለመጨበጥ ሁሉን በትዕግስት ተቀብሎ አገርን ማዳን ዛሬ ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡
 በአሁኑ ሰዓት፤
“ከሸኘኸኝ አይቀር መቃብሩን አሳልፈኝ” የሚለው የሁላችንም ጥሪ የሚሆነውም ለዚህ ነው፡፡ መቃብሩን በሰላም ለመሻገር ያብቃን! አሜን!

የቴሌግራም ቻናልችንን  በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

በተፈጥሮ አካል ጉዳተኛ የሆነው ዮሴፍ በቀለ በሙያው  ሠዓሊ ሲሆን፤ የሚስለው ደግሞ  በአፉና በእግሩ ነው፡፡ ስዕል  የጀመረውም በልጅነቱ ለእንቁጣጣሽ አበባ በመሣል እንደሆነ ያስታውሳል፡፡ አካል ጉዳተኝነት አለመቻል አይደለም ሠርቶ መብላት ይቻላል የሚለው ሠዓሊው፤ ሆኖም ሥዕሎቹ እየተሸጡለት አለመሆኑን  ይናገራል፡፡  የአዲስ አድማስ ልዩ ዘጋቢ መልካሙ ተክሌ ከሠዓሊ ዮሴፍ በቀለ ጋር ካዛንቺስ በሚገኘው ስቱዲዮው ተከታዩን አጭር ቆይታ አድርጓል፡፡
**
ሥዕል የምትሰራው በእጅህ አይደለም ---?
አዎ፤ እኔ ሥዕል የምሥለው ለየት ባለ ሁኔታ ነው፡፡ በእጄ መሥራት ስለማችል በአፌ ነው የምሥለው፡፡ እጅ የሚያስፈልገውን መመገብንና መልበስን ጨምሮ ሌላ ነገር ሁሉ በሌላ ሰው እገዛ ነው የማከናውነው፡፡ እግዚአብሔር በኪነጥበቡ ስላደለኝ በእግሬም በአፌም እሥላለሁ፡፡ በአፌ ሥዬ ስዕሎቼን ሸጬ እስከመጠቀምም ደርሻለሁ፡፡
መቼ ነው ሥዕል የጀመርከው?
ሥዕል የጀመርኩት በልጅነቴ  ነው፡፡ ቀደም ሲል እንደነገርኩህ በእግሬ ነው ፊደል መጻፍ የጀመርኩት፡፡ ያየሁትን ነገር በእርሳስ እስል ነበር፡፡ እንደዚያ እያደረግሁ ነው የተለማመድኩት፡፡ ሥዕል በጣም ጠቃሚነት እንዳለው ያወቅኩት ደግሞ ለእንቁጣጣሽ ለልጆች ሥሥል ነው፡፡ ራሴ ለበዓሉ እያዞርኩ የምሠጠውን እንዲሁም ለሰፈር ልጆችም እሥል ነበር፡፡ በእግሬ እየሣልኩላቸው በአጋጣሚ ደግሞ በአፌ መሣል ጀመርኩኝ፡፡ በእግሬ እንደምሠራው በአፌ እችላለሁ እንዴ ብዬ? ብሩሼን በአፌ አንሥቼ ሥሞክር ሠራሁ፡፡ ከዚያ በኋላ ነው ሥዕል ትምህርት ቤት እንኳ እንዳለ ያወቅሁት፡፡ በአሜሪካ ሀገር እንደኔ በተፈጥሮ  ሳይሆን  ከጊዜ በኋላ አካል ጉዳተኛ  የሆነች ሴት በአፏ ሥላ፣ ራሷንና አሜሪካን እንዳስጠራች ሰማሁ፡፡ የአካል ጉዳተኞች ፌደሬሽን በኢትዮጵያ ሬዲዮ የሚያስተላልፈው “ብሩህ ተስፋ” የሚባል የሬዲዮ ዝግጅት ነበረ፡፡ እዛ ላይ ነው የሰማሁት፡፡  እሱን ሰምቼ የሥዕል ትምህርት ቤት አለ እንዴ ብዬ ስጠይቅ፣ እንዳለ ነገሩኝ፡፡ አቢሲኒያ የሥነጥበብ ትምህርት ቤት ገባሁኝ፡፡ የቀለም ትምህርትም በእግሬ እየጻፍኩ ተምሬአለሁ፡፡ በቅድስት ማርያም የቋንቋ ትምህርት ቤት ደግሞ እንግሊዝኛ ተምሬአለሁ፡፡
አሁን እንደ ስቱዲዮ የምትጠቀምበትን ቤት እንዴት አገኘህ?
እዚህ ሥዕል የምሥልበት ጋለሪ በአካል ጉዳተኝነቴ ሥም የሰጠኝ ወረዳው ነው (ቂርቆስ ወረዳ 8)፡፡ ሆኖም የቤት ኪራይ፣ የጥበቃ ወዘተ እከፍላለሁ፡፡ ግብርም እገብራለሁ፡፡ ሥራ ግን ብዙ የለም፡፡ በፊት የተሰጠን ባሕላዊ ልብስ ለመነገድ ነበር፡፡ ሦስት አራት ዓመት ያህል ያንን ብቻ ካልሠራችሁ ተብለን ተቸግረን ነበር፡፡ ሌሎቹ አስረክበው ወጥተዋል፡፡ እኔ መሔጃ ስለሌለኝ፣ የምሰራውም ስለሌለ እንደምታየው በአቧራ በተሸፈነ በማያመች ቦታ ነው እየሠራሁ ያለሁት፡፡ ልብሶቼን እንኳ ሰው ስለሚያለብስ ስለሚያወልቅልኝ፣ ከሥራዬ ጋር አይመቸኝም ብዬ ማመልከቻ አስገባሁ፡፡ አመልክቼ ሥዕል መሣሉን ቀጠልኩበት፡፡  ሥዕል ብዙ የሚገዛ ስለሌለ ግን በሥዕል መተዳደር አልቻልኩም፡፡ ባለቤቴ እዚህ ወረዳ 8 (ቂርቆስ ክፍለከተማ) ነው የምትሠራው፡፡ በሷ እየተደጎምኩ ነው - ሥዕሎቹ ቢሸጡ ግን እንኳን ለባለቤቴና ሦስት ልጆቼ ለሌላም እተርፋለሁ፡፡
ዐውደ ርእይስ አሳይተሃል?
ከሌሎች ጋር ሆኜ አሳይቼአለሁ፡፡ እዚያም ተመልካቾች ያዩና አይዞህ በርታ ይሉሃል፡፡ ነገር ግን ብዙ ሲገዙ አይታይም፡፡ ቆንጆ ናቸው በርታ ይሉህና፣ ከሌላ ሰው ይገዛሉ፡፡ የሥዕል ገዢዎች አሉ፡፡ ሆኖም ሽያጩ የሚከናወነው በደጋፊ ብዛት (በቲፎዞ) ስለሆነ ብዙም ገዢ አላገኘሁም፡፡
የሠዓሊያን ማኅበር አባል ነህ?
የማኅበሩ አባል አይደለሁም፡፡ ለዚያም አንደኛው ምክንያት የአባልነት ክፍያው ከፍተኛነት ነው፡፡ ሌላው የቲፎዞ ጉዳይ ነው፡፡ ለወደፊት ምን አልባት አባል እሆን ይሆናል፡፡ የማኅበር አባል ስትሆን ሙያህ እንዲጎለብት፣ ልምድ እንድትለዋወጥ፣ ሥራዎችህ እንዲጎበኙና እንዲሸጡ መታገዝ አለብህ፡፡
ቀደም ሲል የጠቀስካት አሜሪካዊት ሰዓሊ እንዳነቃቃችህ ተረድቻለሁ፡፡ አርአያዬ የምትለው ሠዓሊስ አለ?
አዎ፤ በትክክል አለ፡፡ አንጋፋው ሰዓሊ ወርቁ ማሞ በአቢሲኒያ አስተማሪዬ ነበሩ፡፡ እርሳቸው አርአያ ሆነውኛል፡፡ በራስ ሆቴል ሥንመረቅ የተገኙት ደግሞ ሠዓሊ ለማ ጉያ ነበሩ፡፡ ስለዚህ ከአንጋፋዎቹ ብዙ ተምሬአለሁ ማለት ይቻላል፡፡
አካል ጉዳተኝነት አለመቻል አለመሆኑን ከራስህ ሕይወት ተሞክሮ ተነስተህ ልታስረዳኝ ትችላለህ?
በሚገባ፡፡ ሰው ወዶ አይለምንም፡፡ የሚለምን ሁሉ ግን መለመን ነበረበት ብዬ አላምንም፡፡ በተፈጥሮም ሆነ በአደጋ ለአካል ጉዳተኝነት እንጋለጣለን፡፡ በተቻለን መጠን ግን ከአካል ጉዳታችን ጋር የሚጣጣም ሥራ መሥራት አለብን፡፡ አንዳንድ ሰዎች ግን ምንም የአካል ጉዳት ወይም በጣም አናሳ የአካል ጉዳት ኖሮባቸው ሲለምኑ ማየት እየተለመደ መጥቷል፡፡ አጋጣሚው እስከፈቀደ ድረስ መሥራት እየቻሉ  መለመን ግን ትክክል ነው ብዬ አላምንም፡፡ አኔ ተጣጥሬ ነው እዚህ የደረስኩት፡፡ የአካል ጉዳቴ ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት በተፈጥሮ ስለሆነ፣ በልጅነቴ ለልመና በጣም የተጋለጥኩ ነበርኩ፡፡ ያንን ግን አልፌ እግዚአብሔር ይመስገን ከዚህ ደርሻለሁ፡፡ የወደፊቱንም እሱ ያውቃል፡፡ እኔ እየሠራሁ እቀጥላለሁ፡፡
ባለፈው የካቲት 10 ቀን 2016 ዓ.ም ለቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስትያን የንግሥት ዘውዲቱን ሥዕል አበርከተሃል፡፡ የተለየ ምክንያት አለህ?
ንግሥት ዘውዲቱ ቤተ ክርስትያኑን በዚህ መልኩ ስላሠሩ መታሰቢያ ይሆናቸው ዘንድ ነው ሥዕሉን ያበረከትኩት፡፡ እድሳቱ ሳይጀመር ሌላ ሥዕል አበርክቼ ነበር፤ ለረዥም ዓመታት ተሰቅሎ በእድሳቱ ምክንያት ወርዷል፡፡ ቤተ ክርስትያኑ ታድሶ በተጠቀሰው ቀን ስለተጠናቀቀ፣ ለክብረ በዓሉም ጭምር ነው የንግሥት ዘውዲቱን ሥዕል ያበረከትኩት፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በቅዱስ ዑራዔል ጠበል ስለተፈወስኩኝ፣ ቅዱስ ዑራኤልን ለማመስገንም ነው፡፡
ሥዕሎችህን እስካሁን በምን ያህል ዋጋ ሸጠሃል?
ዝቅተኛውን በሰባት ሺህ ብር፣ ከፍተኛውን ደግሞ በዐሥር ሺህ ብር ሸጫለሁ፡፡ ሥዕል ከገዙኝ መካከል የብሪታንያ ኤምባሲ፣ የኢሊሌ እና የጁፒተር ሆቴሎች  ባለቤቶች ይገኙበታል፡፡ የሆቴል ባለቤቶች በርካታ ሥዕሎች ገዝተውኛል፡፡ ሆኖም አሁን ሥዕል  ከሸጥኩ ዐራት ዓመት ሆኖኛል፡፡ ሥዕሎቼ እየተሸጡ አይደለም፡፡
ሠዓሊ ባትሆን ኖሮ ምን ትሆን ነበር?
ሠዓሊ ባልሆንማ ኖሮ፣ የሬዲዮ ጋዜጠኛ ነበር መሆን የምፈልገው፤ እንደ ሰፈሬ ልጅ ጌታቸው ማንጉዳይ፣ ነፍሱን ይማርና እንደ ጎርፍነህ ይመር እሆን ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ሬዲዮ የቅዳሜ መዝናኛ ዝግጅትን በጣም ነበር የማደምጠው፡፡
የት ነው ትውልድህና ዕድገትህ?
የተወለድኩት እዚሁ ካዛንቺስ ቅዱስ ዑራዔል ቤተ ክርስትያን ጀርባ ነው፡፡ ቄስ ሰፈር ይባላል፡፡ የአካል ጉዳተኝነቴ በተፈጥሮ ስለነበር በእግሬም አልሔድም ነበር፣ ከጊዜ በኋላ ነው መሄድ የጀመርኩት፡፡ ከሰባት ዓመቴ በፊት ቤተሰቦቼ እያዘሉኝ ነበር የምንቀሳቀሰው፡፡ ከፊደል እስከ ዳዊት ድረስ ቄስ ትምህርት ቤት ስማር ወንድሞቼና እህቶቼ እያዘሉኝ ነበር፡፡ ከስምንት ከዘጠኝ ዓመቴ በኋላ ነበር፣ በቅዱስ ዑራዔል ጸበል ተጠምቄ መራመድ የጀመርኩት፡፡ እናቴ ሐኪም ቤት እየወሰደችኝም የሕክምና ድጋፍ አገኝ ነበር፡፡ እንድድንላት እናቴ ብዙ ለፍታለች፡፡
***

ከዝግጅት ክፍሉ፡- የሠዓሊውን ስዕሎች መግዛት የምትፈልጉ ወይም ሠዓሊውን መደገፍና ማበረታታት የምትሹ በ0902567909 ወይም 0913569353  ልታገኙት ትችላላችሁ፡፡

•  ”የቢጂአይ ኢትዮጵያ አመራር፣ ያሰርነውን ውልና የፍ/ቤት ትዕዛዝ  ጥሷል”
 
•  ”የበለጸጉና የተደራጁ ኤጀንቶችን በአዳዲስ መተካት የሚል አዲስ ስትራቴጂ መጥቷል“

ከተመሰረተ 14 ዓመት ገደማ ማስቆጠሩ የተነገረለት ቢጂአይ ኢትዮጵያ ኃ. የተ. የግል ወኪል
 አከፋፋይ አሰሪ ማህበር፤ በቢጂአይ ኢትዮጵያ አመራሮች ደረሱብኝ ያላቸውን በደሎች
  ለጋዜጠኞች በተሰጠው መግለጫ ላይ አብራርቷል፡፡  

ማህበሩ በፍርድ ቤት ክስ መሥርቶ ውሳኔ እየተጠባበቀም መሆኑንም አስታውቋል፡፡

የማህበሩ ፕሬዚዳንት አቶ ስንታየሁ ገ/ሥላሴ ሐሙስ መጋቢት 19 ቀን 2016 ዓ.ም  በመግለጫው ላይ እንዳብራሩት፤ በመላ አገሪቱ በወኪል አከፋፋይነት የተሰየሙ የማህበሩ አባላት ቁጥር ወደ 36 የሚደርስ ሲሆን፤እኒህ አባላት ወደ 6 ቢሊዮን ብር ኢንቨስትመንት አፍሰው፣ በቂ የሆኑ መጋዘኖች ገንብተው፣ 40 ቶን የሚሆኑ ትላልቅ መኪኖች ገዝተውና በሥራቸው ወደ 4ሺ ዜጎች ቀጥረው የሚያስተዳድሩ ናቸው ብለዋል፡፡

ማህበራቸው ከቢጂአይ ኢትዮጵያ ጋር በፈጠረው የሥራ ግንኙነት፣ መጀመሪያ ያቀረቡት ጥያቄ፣ ቀደም ሲል ለ1ዓመት ብቻ የተሰጠውን ኮንትራት በመገምገም፣ ለዚህ ትልቅ ኢንቨስትመንት ለሚጠይቅ ሰፊ ሥራ የአንድ ዓመት የኮንትራት ውል በቂ ባለመሆኑ የተሻለ የኮንትራት ውል ማሰር አለብን የሚል ነበር፡፡  

ፕሬዚዳንቱ እንደሚሉት፤ ለዚህ ጥያቄ  ከቢጂአይ ኢትዮጵያ ያገኙት ምላሽ አዎንታዊ አልነበረም፡፡ እንደውም የ2 ወር ኮንትራት በቂ ነው የሚል የፌዝ የሚመስል ምላሽ እንደተሰጣቸው ያስታውሳሉ፡፡ ደግነቱ በኋላ ላይ እነሱም ጥያቄውን አምነውበት የ2 ዓመት ኮንትራት አስረን ወደ ሥራ ገባን ብለዋል፡፡ በመሃል ብዙ መደነቃቀፎች እንደነበሩ የሚያወሱት የማህበሩ ፕሬዚዳንት፤ ቢሆንም በሚያግባቡን ጉዳዮች ላይ በጋር ለመስራት ወስነን ቀጠልንበት ይላሉ፡፡

የማህበሩ መሰረታዊ ሥራ ቢጂአይ የሚያመርተውን ቢራ ለገበያውና ለሚፈለጉባቸው ሥፍራዎች ማሰራጨት ነው የሚሉት አቶ ስንታየሁ፤ የትራንስፖርት ወጪውን ኩባንያው እንደሚሸፍን ጠቁመው፣ በየጊዜው የነዳጅ ዋጋ እየጨመረ ሲመጣ ግን በነባሩ ታሪፍ መሥራት ባለመቻላችን የታሪፍ ማሻሻያ እንዲደረግ ጥያቄ አቀረብን ብለዋል፡፡

ጥያቄያችንን በተደጋጋሚ አቀረብን፤ በግንባር ሄደን አስረዳን፤ ሆኖም ሰሚ ጆሮ አላገኘንም የሚሉት ፕሬዚዳንቱ፤ ለአንድ ዓመት ያህል ከ8 ጊዜ በላይ ጥያቄ ብናቀርብም ምላሽ ሳናገኝ ቀረን ይላሉ፡፡ ”ጭራሽ ችግሩን በማህበር ሳይሆን በየግል ነው የምንፈታው የሚል ነገር አመጡ፤ እንደ ማህበር ዕውቅና ሊሰጡን አልፈለጉም” ሲሉ ሁኔታውን ያስረዳሉ፡፡

ጥያቄያቸው መልስ ባያገኝምና መፍትሄ ባይሰጣቸውም በኪሳራም ቢሆን አገልግሎት መስጠታቸውን ቀጠሉበት፡፡ ይህን ያደረግነው በኪሳራም ቢሆን ከድርጅቱ ጋር ያለን የረዥም ጊዜ የሥራ ግንኙነት መቀጠል አለበት በሚል እምነት ነው ይላሉ፤ ፕሬዚዳንቱ፡፡ ነገር ግን እስካሁን በኪሳራ የሰራንበትንም ቢሆን ክፈሉን ብለን ስንጠይቅ፣ ሰባራ ሳንቲም ሳይከፍሉን ቀሩ ሲሉ ምሬታቸውን ይገልጻሉ፡፡

 የዛሬ 3 ወር ገደማ  የታሪፍ ማሻሻያውን ጉዳይ እናጠናዋለን የሚል ምላሽ ሰጡን የሚሉት የማህበሩ ፕሬዚዳንት፤ ይሄ እኮ የሮኬት ሳይንስ አይደለም፤ መንግሥት እንኳን ቤንዚን ሲጨምር የታሪፍ ማሻሻያ ያደርጋል ሲሉ ያስረዳሉ፡፡

በዚህ ሁኔታ ነገሮች ወዳልተፈለገ አቅጣጫ እየሄዱ መምጣታቸውን የጠቆሙት አቶ ስንታየሁ፤ በመሃል ደግሞ ቢጂአይ አዲስ ስትራቴጂ ይዞ መምጣቱን ይናገራሉ፡፡ አዲሱ ስትራቴጂ የደረጁትንና የበለጸጉትን ኤጀንቶች በአዳዲስና ጀማሪ ኤጀንቶች መተካት የሚል ስልት የያዘ መሆኑንም ይገልጻሉ፡፡  ስትራቴጂው የገበያ ሽንሸናንም የሚያካትት ነው የሚሉት ፕሬዚዳንቱ፤ ይህንንም ለመተግበር ለ2 ዓመት ያሰርነውን የኮንትራት ውል ጥሰዋል ሲሉ ይከሳሉ፡፡

ኮንትራቱን በመጣስ ወደ አዲስ ገበያ ሽንሸናና ኤጀንት ምልመላ ሲገቡ፣ እኛም  ምርጫ ስላልነበረን ጉዳዩን በጠበቆች አማካኝነት ወደ ፍርድ ቤት ወሰድነው ይላሉ - በቢጂአይ ላይ ክስ መመሥረታቸውን በመግለጽ፡፡ ጉዳዩ በፍ/ቤት ሂደት ላይ እያለም ጥሰቱን ቀጠሉበት፤ ማስፈራራትና ማገድ ሁሉ ጀመሩ ያሉት አቶ ስንታየሁ፤ በጠበቆች አማካኝነት ለፍ/ቤት አቤት ብለን የህግ ሂደቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ ምንም ዓይነት የገበያ ሽንሸናና ኤጀንት ምልመላ እንዳይደረግ ብሎ ፍ/ቤቱ አገደ ይላሉ፡፡  

እንዲያም ሆኖ የድርጅቱ አመራሮች  በጥሰቱ ቀጥለውበታል ያሉት የማህበሩ ፕሬዚዳንት፤ አሁን ጠቡ ከኛ ጋር ሳይሆን ከአገሪቱ የፍትህ ሥርዓት ጋር ነው ብለዋል፤ ፍ/ቤት ያዘዘውን እየጣሱ መሆናቸውን በመግለጽ፡፡ ፍ/ቤት በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት ለመጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም መቅጠሩንም አክለው ገልጸዋል፡፡

ማህበሩ በሰጠው ጋዜጣዊ  መግለጫ ላይ ቢጂአይ ኢትዮጵያ ምላሽ ካለው፣ በማንኛውም ጊዜ መድረኩ ክፍት ነው፡፡

አማራ ባንክ ከኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን፣ አክሲዮን ለመግዛት የሚያስችለውን ስምምነት የፈጸመ ሲሆን፤  የ10% አክሲዮን ድርሻ ገዝቷል፡፡

 የአማራ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ተወያይቶ ባፀደቀው መሠረት፣ ከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ በመመደብ የአክሲዮን ድርሻ የገዛው ባንኩ፤ ሲሆን፤ ይህም በገንዘብ ሲተመን 90.6 ሚሊዮን ብር እንደሆነ ተገልጿል።

አማራ ባንክ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገትና ለህዝብ ኑሮ መሻሻል ጉልህ አስተዋጽዖ ከሚያደርጉ ተግባራት ጀርባ ሆኖ መገኘት መገለጫው እንደሆነ የተጠቆመ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መዋዕለ ነዋይ ገበያው ጠንካራ ሆኖ እንዲቋቋምና ሀገራዊ ተልዕኮውን በብቃት መወጣት እንዲችል፤ አሠራሩ ቀልጣፋና ዘመናዊ እንዲሆን ብሎም የታሰበለትን ግብና አላማ እንዲያሳካ ባንኩ አቅሙ በፈቀደው ሁሉ ተባብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑ ተገልጿል።

Page 4 of 700