Administrator

Administrator

የፒያሳ ነዋሪዎች በ3 ወራት ጊዜ ውስጥ አካባቢውን እንዲለቁ ተነግሯቸዋል

በአዲስ አበባ አስተዳደር አራዳ ክፍለ ከተማ፣ የፒያሳና አራት ኪሎ ነዋሪዎች ለልማት ከመኖሪያቸው እንደሚነሱ የክፍለ ከተማው አስተዳደር  ገልጿል።
አስተዳደሩ  በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ እንዳስታወቀው፤ ሁለቱን አካባቢዎች መልሶ በማልማትና ነዋሪዎችን በማስነሳት ዙሪያ ሰሞኑን  ከነዋሪዎች ጋር ውይይት አድርጓል። ውይይቱ፣ በንግድ የሚተዳደሩ ነዋሪዎች ንግዳቸውን በሚቀጥሉበትና ሌሎች ነዋሪዎች በመልሶ ማልማቱ ዕቅድ በሚስተናገዱበት ኹኔታ ላይ ያተኮረ ነበር ተብሏል።
ነዋሪዎችን ለልማት የማንሳቱን ሂደት የሚከታተል ከአመራሩና ከነዋሪዎች የተውጣጣ ኮሚቴም እንደተዋቀረ ተገልጧል። በተለይ የፒያሳ ነዋሪዎች በሦስት ወራት ውስጥ አካባቢውን እንዲለቁ እንደተነገራቸው ምንጮች ጠቁመዋል። ነባር ነዋሪዎቹን የማስነሣቱ ስራ በሦስት ወራት ውስጥ ተጠናቆ የግንባታ ስራው ይጀመራል ተብሏል።በተያያዘ ዜናም፣ ከቀበና እስከ አራት ኪሎ  እንዲሁም  ፒያሳ ደጎል አደባባይ ድረስ  የመንገድ ኮሪደር ግንባታ ሥራው ሠሞኑን  ተጀምሯል፡፡
 የከተማ አስተዳደሩ  ካቢኔ የካቲት 15 ቀን 2016 ዓ.ም ባካሄደው የ3ኛ ዓመት 8ኛ መደበኛ ጉባኤ፣ ግንባታቸው እንዲጀመር ውሳኔ ካስተላለፈባቸው አምስት  የከተማዋ የመንገድ ኮሪደሮች መካከል በአራዳ ክፍለ ከተማ የሚገኘውና  ከቀበና አደባባይ - አራት ኪሎ - ፒያሳ ደጎል አደባባይ ኮሪደር አንዱ ነው።
 የመንገድ ኮሪደር  ግንባታው በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገባ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የአራት ኪሎው  ባለፈው ረቡዕ  ተጀምሯል፡፡

የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ ”የሥራ መልቀቂያ አስገቡ“ በሚል የተሰራጨው መረጃ ሃሰተኛ መሆኑን የባንኩ ባለድርሻ አካላት ገለጹ፡፡

የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ የሥራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን የሚገልጹ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች መሰራጨታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ሆኖም  መረጃው ሙሉ በሙሉ ሃሰተኛ ነው ብለዋል - ለባንኩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች፡፡

የባንኩ ፕሬዚዳንት የሥራ መልቀቂያ አስገቡ በሚል የተሰራጨው ሃሰተኛ መረጃ የባንኩን ጥቅም እንደሚጎዳ የጠቆሙት የባንኩ ባለድርሻ አካላት፤ ሃሰተኛ መረጃውን ያሰራጩ ማህበራዊ ሚዲያዎችንና ግለሰቦችን በህግ እንደሚጠይቁ አመልክተዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ  አዲሱ ገበያ ሸገር መናፈሻ አካባቢ የተገነባውና  ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ የግንባታ ወጪ  ተደርጎበታል የተባለው  ናሁሰናይ ኢንተርናሽናል ሆቴል፤ ከነገ ወዲያ  ቅዳሜ የካቲት 23 ቀን 2016 ዓ.ም ይመረቃል።

የሆቴሉ ባለቤቶች አቶ እሱባለው ናሁሰናይና  ባለቤታቸው ወ/ሮ ሒሩት ምህረቴ እንዲሁም የሆቴሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መላኩ ካሳሁን በጋራ በሰጡት መግለጫ፤ ሆቴሉ  ደረጃውን የጠበቀ፣ ምቹ ስፍራ ላይ የተገነባና ለደንበኞቹ የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት በሚያስችል መልኩ የተደራጀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሆቴሉ  46 የመኝታ ክፍሎች  ያሉት ሲሆን፤ እንግዶች ምግባቸውን እዚያው እያበሰሉ የሚመገቡበት የተሟላና የተደራጀ የገስት ሃውስ ክፍሎችንም ያካተተ ነው። አገልግሎቱንም  ከአካባቢው አንፃር ተመጣጣኝ በሆነ ዋጋ ለማቅረብ  በሚያስችል መልኩ መደራጀቱ ተጠቁሟል፡፡

የሆቴሉ ግንባታ  ሦስት ዓመታትን  እንደፈጀ የተገለፀ ሲሆን፤ ናሁሰናይ ኢንተርናሽናል ሆቴል ሙሉ በሙሉ ሥራ ሲጀምር ከ70 እስከ 100 ለሚሆኑ  ሠራተኞች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ተነግሯል፡፡

ሆቴሉ  ከነገ ወዲያ ቅዳሜ  የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት እንደሚመረቅ ተገልጿል።

በአዲስ አበባ ከተማ  አዲሱ ገበያ ሸገር መናፈሻ አካባቢ የተገነባውና  ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ የግንባታ ወጪ  ተደርጎበታል የተባለው  ናሁሰናይ ኢንተርናሽናል ሆቴል፤ ከነገ ወዲያ  ቅዳሜ የካቲት 23 ቀን 2016 ዓ.ም ይመረቃል።

የሆቴሉ ባለቤቶች አቶ እሱባለው ናሁሰናይና  ባለቤታቸው ወ/ሮ ሒሩት ምህረቴ እንዲሁም የሆቴሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መላኩ ካሳሁን በጋራ በሰጡት መግለጫ፤ ሆቴሉ  ደረጃውን የጠበቀ፣ ምቹ ስፍራ ላይ የተገነባና ለደንበኞቹ የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት በሚያስችል መልኩ የተደራጀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሆቴሉ  46 የመኝታ ክፍሎች  ያሉት ሲሆን፤ እንግዶች ምግባቸውን እዚያው እያበሰሉ የሚመገቡበት የተሟላና የተደራጀ የገስት ሃውስ ክፍሎችንም ያካተተ ነው። አገልግሎቱንም  ከአካባቢው አንፃር ተመጣጣኝ በሆነ ዋጋ ለማቅረብ  በሚያስችል መልኩ መደራጀቱ ተጠቁሟል፡፡

የሆቴሉ ግንባታ  ሦስት ዓመታትን  እንደፈጀ የተገለፀ ሲሆን፤ ናሁሰናይ ኢንተርናሽናል ሆቴል ሙሉ በሙሉ ሥራ ሲጀምር ከ70 እስከ 100 ለሚሆኑ  ሠራተኞች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ተነግሯል፡፡

ሆቴሉ  ከነገ ወዲያ ቅዳሜ  የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት እንደሚመረቅ ተገልጿል።

•  የክ/ከተማው አመራሮች መርሃ ግብሩን አወድሰውታል

"ልምዴን ለወጣቱ" በሚል መሪ ቃል ዛሬ የካቲት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ሳኦል የኩነቶች አዘጋጅና ሌጀንድ ኢንተርናሽናል ፕሮ ቴኳንዶ፣ ከልደታ ክፍለ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር ባዘጋጁት የወጣቶች መድረክ ላይ ታዋቂው የህይወትና ስኬት አሰልጣኝና አማካሪው ዳዊት ድሪምስ ልምዱን አካፈለ።

ዳዊት ድሪምስ ከህይወት ተሞክሮውና ከንባብና ጥናቱ ልምዱን ባካፈለበት የልደታ ክፍለ ከተማ አዳራሽ፣ ወጣቶች ከአፍ እስከ ገደፉ ሞልተውት እንደነበር ተስተውሏል፡፡
   
በዛሬው መርሀ-ግብር ላይ ከዳዊት ድሪምስ ጋር ተገኝተው ልምዳቸውን እንደሚያካፍሉ ሲጠበቁ ከነበሩት ታዋቂ ግለሰቦች መካከል መንሱር ጀማል፣ ግራንድ ማስተር ሄኖክ፣ ማስተር በፍቃዱ (ኢሱ)፣ አቶ ሰኢድ፣ ዮኒ ቬጋስ እና ደራሲ መሐመድ ብርሀን ተጠቃሽ ሲሆኑ፤ በፕሮግራም መደራረብ ምክንያት መገኘት ያለመቻላቸውን ለማወቅ ተችሏል።

ለወጣቶቹ ልምድ ላከፈሉት ለዳዊት ድሪምስና ለሌሎች አካላትም ከአዘጋጆቹ ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።

የክፍለ ከተማው አመራሮችም ዝግጅቱን ላሰናዱት ሳኦል የኩነቶች አዘጋጅ እንዲሁም ልምዳቸውን ላካፈሉት ግለሰቦች ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፤ እንዲህ ዓይነቱ ወጣቱን የማነቃቃት ፕሮግራም መዘጋጀቱ ወጣቱን በስነ ልቡና ለማንቃትና ለስራ ለማነሳሳት ስለሚያግዝ በየጊዜው መዘጋጀት አለበት ብለዋል፡፡

“ትልቅ ህልም አለኝ” የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ያበቃው ዳዊት ድሪምስ፤ “እኔ የህይወትና ስኬት ምስጢሮች ተመራማሪ፣ አማካሪና አሰልጣኝ ነኝ” ሲል ነው ራሱን የሚገልጸው፡፡

ስለ ህልሙ ሲናገርም፤ “የኔ ትልቁ ህልም ለዘመናት የተደበቁ የህይወትና ስኬት ምስጢሮችን በጥልቀት በማጥናት፣ በመጠቀምና በማስተማር ኢትዮጵያንና አፍሪካን መቀየር ነው” ይላል፡፡

በሚሰጣቸው ተከታታይ የስኬትና የሰብአዊ ግንባታ ሥልጠናዎች የበርካቶችን ህይወት እንደቀየረ የሚነገርለት ዳዊት ድሪምስ፤ በጥረታቸውና በትጋታቸው ለድል የበቁ ስኬታማ ሰዎችን እየጋበዘ ልምዳቸውን እንዲያጋሩና ሌሎችን እንዲያነቃቁ በማድረግም ይታወቃል፡፡

ዛሬ ደግሞ እርሱ በተራው በልደታ ክፍለ ከተማ ተገኝቶ ከልምዱ በማካፈል ወጣቶችን አነቃቅቷል፡፡

ጠላቶቻችን ኢትዮጵያ ላይ የሚረባረቡት ተስፋ ስላላት ነው ያሉት ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፤ ኢትዮጵያውያን ሃገራቸውን ስለሚወዱና የመጨረሻው የቁርጥ ጉዳይ ከመጣ ህይወታቸውን ገብረውም ቢሆን እንደ አባቶቻቸው አገር ስለሚያስቀጥሉ ኢትዮጵያን የማፍረስ ፕሮጀክት አይሳካም ብለዋል፡፡

ጠ/ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ሰሞኑን ከሶማሌ፣ አፋር፣ ሐረሪ፣ ጋምቤላ፣ ቤኒሻንጉልጉሙዝ ክልሎችና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ተወካዮች ጋር ባደረጉት ውይይት ነው፡፡

ድሮ እኛ እንዳንገነጠል ትሰጉ ነበር፤ አሁን እኛ እየሰጋን ነው አገራችንን እንዳትበትኗት እንዳታፈርሷት የሚል ተገቢ ስጋት ከሶማሌ ክልል መነሳቱን የጠቆሙት ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ፤ ኢትዮጵያን ማፍረስ የሚፈልጉ ብዙ ሃይሎች ቢኖሩም ኢትዮጵያ ግን አትፈርስም ብለዋል፡፡

ማፍረስ ቢችሉማ ዓምናም ካቻምናም፣ የዛሬ 20 ዓመትም ሞክረው ነበር፤ ግን አይችሉም ብለዋል - ጠ/ሚኒስትሩ፡፡

ለምንድን ነው ኢትዮጵያ ላይ ጠላቶቻችን የሚረባረቡት ያላችሁ እንደሆነ ተስፋ ስላላት ነው፤ ሲሉም አስረድተዋል፡፡

ጠላቶቻችን ኢትዮጵያን ለማፍረስ በሁሉም መንገድ ሞክረዋል፣ የትኛውም ሙከራ ግን ኢትዮጵያን ማፍረስ አይችልም ያሉት ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፤ ኢትዮጵያውያን ሃገራቸውን ስለሚወዱና የመጨረሻው የቁርጥ ጉዳይ ከመጣ ህይወታቸውን ገብረውም ቢሆን እንደ አባቶቻቸው አገር ስለሚያስቀጥሉ ኢትዮጵያን የማፍረስ ፕሮጀክት አይሳካም ብለዋል፡፡

8ኛው ኢትዮ ኸልዝ አውደ ርዕይና ጉባኤ በመጪው ሳምንት በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል  


8ኛው ኢትዮ ኸልዝ አውደ ርዕይና ጉባኤ የአልጀሪያ ብሔራዊ ተሳትፎን ጨምሮ በ12 አገራት መሰረታቸውን ባደረጉ ኩባንያዎች ተሳትፎ በመጪው ሳምንት ከየካቲት 28 – 30 ቀን 2016 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ  እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡

በዚህ አውደ ርዕይና ጉባኤ ላይ ከ4ሺ የሚበልጡ የጤና ባለሙያዎችና የዘርፉ የንግድ ባለድርሻ አካላት ከዓለማቀፍ የዘርፉ መሪዎችና ስመጥር የሃገር ውስጥ ኩባንያዎች ጋር የንግድ ትስስር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል ተብሏል፡፡

በዘንድሮው ኹነት በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ40 በላይ ነጥብ የሚያሰጡ የተከታታይ የሙያ ማጎልበቻ ሥልጠናዎችና ጉባኤዎች ከ22 የሙያና የዘርፍ ማህበራት ጋር በመተባበር እንደሚሰጥ ተጠቁሟል፡፡

ይህ ልዩ አውደ ርዕይና ጉባኤ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችንና አቅራቢዎችን ለሀገራችን በማስተዋወቅ፣ የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግርን በማምጣት ለዘርፉ ልማት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ቁልፍ መድረክ መሆኑን ያስመሰከረ ነው የተባለ ሲሆን፤ በዘርፉ ተዋናዮች መካከል የንግድ ልውውጥን በማሳደግና የገበያ ትስስርን በመፍጠር ደረጃ ቀጣይነት ያለው ዕድል የፈጠረ ኹነት እንደሆነ  ተነግሯል፡፡

ኢትዮ ኸልዝ አውደ ርዕይና ጉባኤን ለ8ኛ ጊዜ ያዘጋጀው በበርካታ ዘርፎች የንግድ ትርኢትና አውደ ርዕዮችን በማዘጋጀት የሚታወቀው ፕራና ኢቨንትስ ነው፡፡

መጋቢት 05 ቀን 2016 ዓ/ም ፤ በአዲስ አበባ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ያካሂዳል ።
...
ወ/ሮ ሙሉ ግርማይ ተወልደው ያደጉት በቀድሞው አጠራር በወሎ ክፍለ ሀገር በሰቆጣ ከተማ ነው።  በ 1973 ዓ/ም የቀድሞው ኢህዴን / ብአዴን የአሁኑ አዴፓ ፖለቲካ ድርጅት ተመስርቶ ደርግን ለመጣል የትጥቅ ትግሉን በዋግ አካባቢ ሲጀምር እርሳቸውም እንደ ዘመኑ ወጣቶች የደርግን መንግስት አምርረው ይጠሉ ስለነበር የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አቋርጠው በ 1975 ዓ/ም የትጥቅ ትግሉን ተቀላቀሉ።

የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል ከ ጊዜ ወደ ጊዜ እየጠነከረ ሄዶ በ 1983 ዓ/ም የደርግ መንግስት ከስልጣን ሲባረር ቀደም ሲል ከአራት ድርጅቶች ጥምረት ኢህአዴግ ተብሎ በተመሰረተው ድርጅት የበላይነት የሽግግር መንግስት ሲቋቋም ባለቤታቸው አቶ ታምራት ላይኔ የሽግግር መንግስቱ ጠቅላይ ሚንስትር እርሳቸው ደግሞ የአዲስ አበባ ሪጅን ፅ/ቤት የኢህአዴግ ድርጅት ጉዳይ ሃላፊ ሆነው እየሰሩ ቆዩ።

እርሳቸው እንደሚሉት በ 1989 ዓ/ም " በስልጣን ያለአግባብ መጠቀም " በሚል የፖለቲካ ሴራ ኢህአዴግ አቶ ታምራትን ለእስር እንዲዳረጉ አደረገ። ይህኔ ታዲያ ወ/ሮ ሙሉ በህይዎቴ ይገጥመኛል ብለው ከማይገምቱት ፈተና ላይ ወደቁ። የአቶ ታምራት ሚስት በመሆናቸው  ከስራ ቦታቸው እና ከሃላፊነታቸው ያለአንዳች ርህራሄ ተባረሩ። በወቅቱ ምንም አይነት ገቢ ወይንም ጥሪት ሳይኖራቸው አራት ዓመት ከሆነው የመጀመሪያ ልጃቸው እና የአንድ ወር ጨቅላ ህፃን ከነበረቸው ሁለተኛ ልጃቸው ጋር ሲኖሩበት ከነበረው የመንግስት ቤትም ሳይቀር እንዲወጡ ተደረገ።

ከእለት ወደ እለት ማወከቦች ፣ የማፈን ሙከራዎች፣  ማስፈራሪያዎችና ልዩ ልዩ ፈተናዎች እየጨመሩባቸው ሲሄዱ በ 1992 ዓ/ም ሁለት ልጆቻቸውንና ታናሽ እህታቸውን ይዘው ወደ ኬንያ በግፍ ተሰደዱ።

ከሦስት ዓመታት የኬንያ አስቸጋሪ የስደት ቆይታ በኋላ በ 1995 ዓ/ም ወደ አሜሪካ በስደት እንዲገቡ ተፈቅዶላቸው በኮሎራዶ ግዛት ዴንቨር ከተማ መኖር ጀመሩ ። በአሜሪካን ሀገርም ብቻቸውን ሆነው ልጆቻቸውን እንደሚያሳድግ እናት የጋዝ ማደያ ፣ የልብስ መሸጫ መደብርና የመሳሰሉት እየሰሩ ልጆቻቸውን ማሳደግና ማስተማር ቀጠሉ።

በ 2000 ዓ/ም ባለቤታቸው አቶ ታምራት ላይኔ ከእስር ተፍትተው ወደ አሜሪካን ሀገር በመጡበት ወቅት ወ/ሮ ሙሉ ጋዝ ማደያ ተቀጥረው ይሰሩ እንደነበር ያስታውሳሉ።

ለ አስራ ሁለት ዓመታት ልጆቻቸውን ያለአባት ማሳደጋቸውና ልጆቻቸውም እነዛን ረጅም ዓመታት ያለ አባት ማደጋቸው እርሳቸው ባለፉበት የመከራ ህይዎት ውስጥ የሚያልፉ ልጆችና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው እናቶችን በተለየ መንገድ እንዲያስቡ አደረጋቸው። በሚወዷቸውና የኔ በሚሏቸው ሰዎች መጠላትና መገለል አሳዛኝ የህይዎት ክስተት መሆኑን ተገነዘቡ ። እናም የተቸገረን ሰው ቀርቦ ማፅናናትና መደገፍ ምንያህል የተቀደሰ ተግባር መሆኑን ከህይዎታቸው ተማሩ።

ከዛም የእርሳቸው እና የቤተሰባቸው የመከራ ውጤት የሆነው እንዲሁም ለችግር የተጋለጡ ፤ ወላጆቻቸውን ያጡ ልጆችና መበለቶችን የሚያግዘው ላይፍ ሴንተር ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ድርጅት በ 2005 ዓ/ም ሊመሰረት ቻለ።

ላይፍ ሴንተር ኢትዮጵያ ፤ በአዲስ አበባ ፣ በአማራ ክልል ዋግህምራ ሰቆጣ ከ400 በላይ መበለቶችንና ከ280 ወላጆቻቸውን ያጡ ለችግር የተጋለጡ ልጆችን በመርዳት ላይ የሚገኝ ድርጅት ሲሆን መጋቢት 05 ቀን 2016 ዓ/ም በከተማችን አዲስ አበባ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አዘጋጅቷል ። ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል የዚህ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም በሚችለው ሁሉ አጋር እንዲሆንና ከፍተኛ ችግር ውስጥ ያሉ ሴቶችና ህፃናትን እንዲያግዝ በማዕከሉ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ጥሪ ቀርቧል።

በአዲስ አበባ ወሎ ሰፈር ጎርጎሪዮስ አደባባይ ፊት ለፊት የተገነባው ባለ 15 ፎቅ ዓለማቀፍ ሆቴል፤ የፊታችን ቅዳሜ  የካቲት 23 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚመረቅ ተገለጸ፡፡
ለግንባታ 7 ዓመት የፈጀውና የኩራዝ ወንዝ ኃ.የተ.የግ. ድርጅት አጠቃላይ ፕሮጀክት አንደኛው እህት ኩባንያው ነው የተባለው ሽታዬ ስዊት ሆቴል፤ አባት አርበኞች፣ የመንግሥት ባለሥልጣናትና አምባሳደሮች በተገኙበት ይመረቃል ነው የተባለው፡፡
በ600 ካ.ሜ ቦታ ላይ ያረፈው ሆቴሉ G†15 ከአንድ ቤዝመንት ጋር ያለው ሲሆን፤ በቂ የመኪና ማቆምያ ቦታም ያካተተ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
ሆቴሉ የራሳቸው ማብሰያ ክፍሎች ያላቸው ሰፋፊ ምቹና ዘመኑ ያፈራቸውን መገልገያዎች የያዙ መኝታ ክፍሎች ያሉት ሲሆን፤ ለየት የሚያደርገውም የፔንት ሃውስ ክፍል ምርጫ ያለው ነው ተብሏል፡፡
የባህል ምግብ አዳራሽ፣ የመዋኛ ሥፍራና የሰርግ ስብሰባ አዳራሾች ያካተተው ሽታዬ ስዊት ሆቴል፤ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ተነግሯል፡፡
በሆቴሉ የምረቃ ሥነስርዓት  ላይ ለአባት አርበኞች ምስጋናና ዕውቅና እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡

Page 11 of 701