Administrator

Administrator

ዱሮ ኪዩባን ከባቲስታን አምባገነናዊ አገዛዝ ነፃ ለማውጣት እነ ካስትሮና እነ ቼጉቬራ የትጥቅ ትግል ላይ በነበሩበት ዘመን (እ.ኤ.አ በ1950ዎቹ በ1990ዎቹ ውስጥ ) ይነገር የነበረ አንድ ወግ ነበር። አሁን ወደ አፈ-ታሪክነት ሳይለወጥ አልቀረም። የጥንት ተማሪዎች።
“ፋኖ ተሰማራ ፋኖ ተሰማ
እንደ ሆቺሚኒ እንደ ቼጉቬራ” ኢያሱ ይዘምሩለት የነበረ እንቅስቃሴ ማለት ነው።
ወጉ እንዲህ ነው።
 የኪውባው መሪ የነበሩት ፊደል ካስትሮ፣ የባቲስታን አገዛዝ ሊዋጋ ኃይል ሊያደራጅ ወደ ሜክሲኮ ይሄዳል። እዚያም አርጀንቲና የተወለደውንና ኋላ የኪውባ አብዮተኛ የሆነውን ቼ ጉ ቬራን ያገኛል። ሁለቱ ከአንድ ጠንካራ የኪውባ ተዋጊ ወታደር ጋር ጫካ ውስጥ ይመሽጋሉ። የትጥቅ ትግሉን በማፋፋም ላይ ናቸው። ከድጡ ወደ ማጡ እንዲሉ ከስፔይን ተገላግሎ በአሜሪካ እጅ መውደቅን ለመታገል እየጣሩ ነው።
የአሜሪካ መንግስት አሻንጉሊት የነበረው የባቲስታ ፉልጂኒቺዮ ጦር እጅግ አድርጎ እየበረታ፣ በአንጻሩ የታጋቾቹ ጦር እየተመናመነ ምን ማድረግ እንዳለባቸው  በጨነቃቸው ሰዓት ካስትሮ አንድ ሃሳብ አመጣ ይባላል።
“እንግዲህ ጓዶች ትግሉ እየመረረ፣ የጠላት ኃይል እያየለ እየመጣ ነው። ዕውነተኛ ታጋይነታችን፣ ቆራጥነታችን፣ ለነጻነታችን ከልብ የመቆማችን እውነተኛነት የሚለይበት ሰዓት ደርሷል። ስለዚህ ቃል እንግባ?”
“ምን የሚባል ቃል?” አለ ቼ።
“ምናልባት የጠላት ኃይል ከባድ ጥቃት አድርሶ ድንገት በእጁ ካስገባን፣ የሚያደርስብን ቅጣት፣ እኛ በሱ ላይ ያደረስንበትን ጥቃት ያህል ነው። ያው በእኛ ላይ ያለውን የጥላቻውን መጠን ያህል መሆኑ መቼም ጥርጥር የለውም። ባቲስታ ዓይኑን ካጠፋኸው ዓይንህን ያጠፋሃል። በጥይት ከቆላኀው በጥይት ይቆላሃል። እንዲያውም በዕጥፍ-ድርብ አብዝቶ፣ አንዱን በሺ መንዝሮ ነው ዋጋህን የሚሰጥህ። ስለዚህ ሁላችንም ለዓላማችን ስንል እኩል ጥቃት ማድረሳችን ከሆነ ብቻ ነው። አለበለዚያ ግን ከኛ መካከል ትንሽ ቅጣት የተቀጣ ሰው ዓላማችንን ክዷል ማለት ነው። ስለዚህ ዓላማችንን ላንክድ እንማማል።” ቼጉቬራም፣ ጠንካራው ታጋይም፣ በሃሳቡ ተስማሙ። ተማማሉ።ካስትሮ እንደፈራው ሦስቱም ተዋጊዎች ጠላት እጅ ወደቁ።
ከዚያም ለፍርድ ቀረቡ። ተፈረደባቸው። እንደየጥፋታቸው በቁማቸው እንዲቀበሩ ተወሰነ።አቀነባበራቸው የሚከተለውን ዓይነት ሆነ።
ቼ ጉቬራ ጨርሶ አይታይም። ካስትሮ ጉልበቱ ድረስ ብቻ ነው የተቀበረው። ጠንካራው ተዋጊ ወታደር ግን እደረቱ ድረስ መሬት ተቀብሯል። ይሄ ወታደር የካስትሮን እጉልበቱ ድረስ ብቻ መቀበር ባየ ጊዜ እንዲህ ሲል ወቀሰው።
”ካስትሮ ተማምለን ነበር። ከዳኸኝ። እኔን ደረቴ ድረስ ቀበሩኝ። አንተን ጉልበትህ ድረስ። የእኔን ያህል ጥቃት አላደረስክባቸውም ማለት ነው። ከሀዲ ነህ!”
ካስትሮም እንዲህ ሲል መለሰ!
“የለም የለም! አትሳት ጓድ። ጉልበት ድረስ ብቻ ወደ መሬት የገባሁበትን ምክንያት አላወቅህም። የቆምኩት!ኮ ቼ ጉቬራ ጭንቅላት ላይ ነው።
***
የራሳቸው ጭንቅላት የሌላቸው መሪዎች፣አለቆች፣ ኃላፊዎች በሌሎች ጭንቅላት መኖራቸው የተለመደ ነገር ነው። ሆኖም ውሎ ሲያድር የሌሎቹ ጭንቅላት፣ የሌሎቹ ስም፣ የሌሎቹ ታሪክ ለመኖሪያነት የሚያገለግበት ጊዜ ያልፍና ሁልህም በየራስህ ጭንቅላት ኑር የተባለ እለት የሚይዙት የሚጨብጡት የሚጠፋባቸው አያሌ ይሆናሉ። “አፍረው የተውት፣ ፈርተው የተውት ይመስለዋል” እንዲሉ፣  ለጊዜው የሚመጻደቅ ይኖራል። ቀኑ የደረሰ ጊዜ ግን ሁሉም ወደ ተገቢ ቦታው፣ ወደ ተገቢ ዕሴቱ የሚሄድበት፣ ተፈረካከሰ ያለውም ወደሚበታተንበት አቅጣጫ መጓዙ አይቀሬ ይሆናል።
አምባገነንነት ከልሂቅ እስከ ደቂቅ መከሰቻው ብዙ ነው። የየሰፈሩ ጌታ አለ እንደማለት ነው።
 የመሪ ጌታ አለ፣ የገንዘብ አለ። አምባገነንነትን አስመልክቶ ብሪታኒያዊው ባለሃብትና ታዋቂው ሰው ሪቻርድ ብራንሰን፤ “እኔ በጥሩ አምባገነንነት አምናለሁ። ዋናው ነገር አምባገነኑ እኔ ራሴ መሆን አለብኝ።” ብሏል። አምባገነኑ እኔ መሆን አለብኝ ብለው በይፋ የሚናገሩ አምባገነኖች ብዙ አይደሉም። በየውስጠ-ልቡናቸው የመጨቆን፣ የመግፋት፣ የማፈን፣ የማን-አለብኝ ባህሪ ያላቸው ሙልሙል አምባገነኖች ብቅ ብቅ በሚሉበት ጊዜ አገር ተኮነነች ማለት ነው። ሀሳዊ-ዴሞክራት የማታለያ ስብከትን (Demagogue) ያበዛል። ስሜታዊነትን ከምክንያታዊነት ያስቀድማል። በትንሽ ነገር ኩፍ ይላል-ገፁ ይለዋወጣል።
 ለማገዱ፣ ለማገቱ፣ ለማሰሩ፣ ለመግደሉ ወዘተ ሁሉ ምክንያት ይሰጣል። በየትኛውም ደረጃ ይሄን ባህሪ ይዞ የሚገኝ እሱ አምባገነን ነው። ከእንዲህ ያለው ይሰውረን ዘንድ ነው “ዕውነተኛ ዲሞክራሲ ሆይ፤ ከእኛ አትራቂ” እያልን የምንጸልየው። “የመናገር የመጻፍና ሃሳብን የመግለጽ ነጻነት ሆይ፣ ከእኛ አትራቂ” እያልን ሱባዔ የምንገባው ለዚህ ነው። ጉባዔ ሲያቅት ሱባኤ እንዲሉ።ሁሉን በእርጋታ፣ ሁሉን በትዕግስት መከወን፣ የብልህነትና የብስልነት ምልክት ነው ይላሉ። “ተመልሰህ ለምታፍሰው፣ ቸኩለህ አታፍስሰው” ነው ነገሩ። ቸኩሎ ድምዳሜ ላይ መድረስ፣ ቸኩሎ መውቀስ ቸኩሎ ማወደስ፣ ቸኩሎ መራገም ከንቱ ሆኖ ሳለ፣ ኃይለኛ አለቆችና መሪዎች የዕለት መፈክራቸው ያደርጉታል። ይህ አገርን አያሳድግም። ህዝብን ነፃ አያደርግም። ጥንቃቄ ያሻዋል።ለህዝብ ተቆርቋሪ፣ ለሀገር አሳቢ የሚመስሉ በርካታ ግለሰቦች፣ ቡድኖችም ሆኑ መንግሥታት፣ እንደሚኖሩ አለመርሳት ተገቢ ነው። በርካታ ሃሳዊ-መሢሃን እንዳሉ ልብ ማለት ያስፈልጋል።
 የበግ ለምድ የለበሰ ቀበሮ ብቻ ሳይሆን፣ የቀበሮ ቆዳ የሚለብስ በግም እንደማይጠፋ ማወቅ ደግ ነው። ከነጋ ለማጨብጨብ ከመሸ ለመሳደብ የማይተኙ በርካታ የአለቃ ሚዜና አጃቢዎች “ሽቶው ውሃ ነው”  እስኪባሉ አንደኛ ማዕረግ ቦታ ሊቀመጡ ይችላሉ። የዛሬ ዕድሜ ግን በውሃ መስላ ሻማ ናት።
በሀገርና ህዝብ ጉዳይ የቲዮሪ አንጓች፣
የፖሊሲ መካሪ፣ የህግ አማካሪ፣ የቅርብ ተጠሪ፣ የሩቅ ተጧሪ የሆኑ ሰዎች፣ ቡድኖች፣  ፓርቲዎች፣ ሀገሮች ፍሬያቸው ብስል መስሎ ጥሬ፣ ምክራቸው አዛኝ መስሎ ገዳይ ከሆነ፣ “የሚስቴን ወገብ ይዞ የሚጨፍር ሚዜዬ አይደለም” የሚል ህዝብ እንዳለ ሊገነዘብ ይገባል።

ግራር፣ የጠቢባን መናኸሪያ ከተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) – አሽበርግ ፕሮግራም ጋር በመተባበር፣ “ሠዓሊትን ፍለጋ የተሰኘ ሴት ሠዓሊያንን  ማብቃት ላይ ያተኮረ ፕሮጀክት በይፋ አስጀምሯል።
ይህ ፕሮጀክት ሁሉን አቀፍ የሴት የሥነ ጥበብ ሙያተኞችን ብራንዳቸውንና የዲጂታል ሰብዕና ከማጎልበት ባሻገር ሚዛናዊ የባህል ምርቶችና አገልግሎቶች ስርጭት እንዲሁም የአርቲስቶችና የባህል ሙያተኞች ተንቀሳቀሶ የመስራት ዕድሎችን ለማጎልበት አንዲቻል፣ ሴት ሠዓሊያን በብራንዲንግ፣ ዲጂታል አካታችነትና የንቅናቄ መፍጠሪያ መድረኮች ያካተተ ነው።
“ሠዓሊትን ፍለጋ” የዘመኑ የዲጂታል አሰራር የፈጠረውን ዓለም አቀፍና የባሕልና ጥበብ እንዱስትሪ ትስስር ያለውን ዕድል በአግባቡ የተገነዘበ ፕሮጀክት ነው። በመሆኑም በዚህ ፕሮጀክት የሴት ሠዓሊያንን የብቃት ደረጃ ማጎልበትን፣ መሰረታዊ መብቶቻቸውን ለመጠበቅና በዲጂታል ሥነ ምህዳር ያለውን የተሳትፎ  ክፍተት ማጥበብ፤ የአርቲስቶች የፈጠራ ሃሳቦቻቸውን በነፃነት የሚገልፁበትን፣ በነፃነት ተንቀሳቅሶ የመስራትና ተመጣጣኝ  የገበያ እድሎችን ተደራሽ ማድረግን፣ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ጥበቃን እንዲሁም ፍትሃዊ ክፍያ ለጥበብ የፈጠራ ስራዎች እንዲኖር  አስተዋጽኦ ያበረክታል  ተብሏል። ይህ ፕሮጀክት የዲጂታል ክህሎት ስልጠናን በመስጠት የ20 ሴት ሠዓሊያንን በዲጂታል ስርዓት ውስጥ ያለውን የሥርዓተ ጾታ  ኢ-ፍትሃዊነት በማጥበብ፣ ስኬታማ የሙያ እድገት እንዲኖራቸው  እንደሚያስችል ተገልጿል ።
በፕሮጀክቱ  ለ20ዎቹ ሴት ሠዓሊያን ጋር በቅርበት በሚሰሩና ድጋፍ በሚያደርጉ ባለሙያዎች  በብራንዲንግ፣ በማህበራዊ ሚዲያ አመራር፣ ድረ ገጽ አጠቃቀም የይዘት ዝግጅትና የገበያ ልማት ስልቶች ላይ ያተኮሩ ስልጠናዎች  እንዲያገኙ ይደረጋል። ይህም ሠዓሊያኑ ስራዎቻቸውን ለታዳሚ ለማቅረብ ለሰፊው የጥበብ አፍቃሪው ማህበረሰብ ተደራሽ ለመሆንና በዓለም አቀፍ የዲጂታል ሥነ ምህዳር ውስጥ ያሉ አዳዲስ የገበያ ዕድሎችን ለመጠቀም ያስችላቸዋል።
ፕሮጀክቱ በፈጣን እድገት ላይ የዲጂታል ሽግግርና የሰብዕና ግንባታ ያለውን ሚና በመገንዘብ የሴት የጥበብ ሙያተኞችን ተሰሚነትን ከማጎልበት ባሻገር፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የባህል ምርቶች ማስፋፋትና የባህል ትውውቅን ለማጎልበት ይሰራል።
በተጨማሪም ሠዓሊትን ፍለጋ ለ100 በጥበብ ና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ወጣቶች የሥራ ዕድሎች የሚፈጥር ነው። ፕሮጀክቱ እያደጉ  የመጡ የቴክኖሎጂና ፈጠራ አቅሞችን በመገንዘብ፣ ቀጣዩን ትውልድ ለፈጠራ ማነሳሳትን ታሳቢ አድርጎ ይሰራል ተብሏል። ይህ ፕሮጀክት የባህልና የጥበብ ዘርፉ ላይ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ የፈጠራና ጥበባትን ስራዎች በማበረታታት፣ ብዝሃ ባህልን የሚያጎለብቱ ስራዎች ለመደገፍ ያለውን ቁርጠኝነት  በተግባር የሚያሳይበት እንደሆነም ተነግሯል ፡፡
የግራር፣ የጠቢባን መናኸሪያ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሴሚናስ ሀደራ እንደገለፁት፤ “ ሠዓሊትን ፍለጋ ፕሮጀክት ሴት ሠዓሊያን ያላቸው ፈጠራና ተሰጥኦ ተገቢውን እውቅና አንዲያገኙ የሚያስችል ፕሮጀክት  ሲሆን   ግራር፣ የጠቢባን መናኸሪያ  ከዩኔስኮ - አሽበርግ ፕሮግራም ጋር በመተባበር  ሴት የሥነ ጥበብ ሙያተኞችን አቅም ለማጎልበትና ለማብቃት እንሰራለን ብለዋል ።
በዚህ ፕሮጀክት የዲጂታል ክህሎት ስልጠናን በመስጠት፣ የዲጂታል ሰብዕና መገንቢያ አሰራሮችን በማልማትና በመተግበር የሴት ሠዓሊያ በዲጂታል ስርዓት ውስጥ ያለውን የሥርዓተ ጾታ ኢፍትሃዊነት በማጥበብ እንዲሁም አካታች እና ፍትሃዊ የጥበብ እና ፈጠራ ሥነ ምህዳር እንዲጎለተ በመስራት ሴት ሠዓሊያኑ በዘመናዊው የዲጂታል ዓለም ውስጥ ጉልህ ድርሻ አንዲኖራቸው ድጋፍ ይደረግላቸዋል ተብሏል፡፡

Saturday, 09 March 2024 20:06

11ቢሊየን

ሰሞኑን ለመጀመሪያ ጊዜ 20 ግዙፍ ቦይንግ 777X-9 አውሮፕላኖች ለመግዛት ከቦይንግ ጋር ተፈራርሟል።
የአውሮፕላኖቹ ዋጋ እስከ 11ቢ. ዶላር ይገመታል
አውሮፕላኑ 50 የቢዝነስና 390 የኢኮኖሚ መቀመጫዎች አሉት
አየር መንገዱ አውሮፕላኖቹን በማዘዝ ከአፍሪካ ቀዳሚው ነው
እ.ኤ.አ ከ2027 እስከ 2030 አውሮፕላኖችን ይረከባል

መልዕክተኛው የፕሪቶሪያው ስምምነት አፈጻፀምን ይገመግማሉ ተብሏል

የአሜሪካ መንግሥት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር፣ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች የተከሰቱ  ግጭቶች በድርድር እንዲፈቱ ለማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮችና   በመንግሥትና  በህወሓት መካከል የተደረሰው ስምምነት አፈጻጸም  ግምገማ ዙሪያ በአዲስ አበባ እየመከሩ ነው ። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው መግለጫ ላይ እንደተጠቆመው፤ ልዩ መልዕክተኛው  በአሁኑ ጊዜ በተባባሰው የአማራ ክልል ግጭትና ዓመታትን ባስቆጠረው የኦሮሚያ ክልል አለመረጋጋት ዙሪያ ሰላም ለማምጣት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር  ይመክራሉ ተብሏል፡፡
በትግራይ ሲካሄድ የነበረውን ጦርነት ለማስቆም በተደረገው ጥረት ውስጥ ጉልህ ሚና እንደነበራቸው የሚነገርላቸው አምባሳደር ማይክ ሐመር፤ ደም አፋሳሹን የሰሜን ኢትዮጵያን የእስር በርስ ጦርነት ያስቆመውን የፕሪቶሪያውን ስምምነት አፈጻጸም በተመለከተ በአፍሪካ ኅብረት አስተናጋጅነት፣ ከየካቲት 28 አስከ መጋቢት 4 ቀን 2016 ዓ.ም. በሚካሄደው ግምገማ ላይ ተሣታፊ እንደሆኑም ተገልጿል። ከተፈረመ አንድ ዓመት ያለፈውን የፕሪቶሪያው ስምምነት የአፈጻጸም ሂደት በተመለከተ የስምምነቱ አሸማጋዮችና ታዛቢዎች የሚሳተፉበት ግምገማ እንደሚካሄድ ሲነገር ቆይቷል፡፡ ልዩ መልዕክተኛው  አምባሣደር ሐመር፣ ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር  በመገናኘት  በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ውስጥ ያለውን ግጭት ለማብቃት የሚደረጉ ጥረቶችን ለማፋጠን በሚያስችሉ ሁኔታዎችንና ግጭቱን በድርድር ለመፍታት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩ የአሜሪካው  የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት፣ የአምባሳደር ሐመርን ጉዞ በተመለከተ ባወጣው መግለጫ ላይ አመልክቷል።
ካለፈው አመት ሐምሌ ወር ጀምሮ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስር በሚገኘውና  ከፍተኛ አለመረጋጋት ውስጥ በገባው የአማራ ክልል ውስጥ በፌደራል መንግሥቱ ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የሚካሄደው ግጭት መባባሱን ተከትሎ ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት  አሜሪካ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ  እንደምትገኝም መግለጫው ጠቁሟል፡፡
በኦሮሚያ ክልል በመንግሥትና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት እያለ በሚጠራው ታጣቂ ኃይል  መካከል  ያሉ ግጭቶችን ለማስቆምና ሰላም ለማውረድ የተደረጉ ሙከራዎች ውጤት ሳያመጡ መቅረታቸው አይዘነጋም፡፡ የፊታችን ረቡዕ ይጠናቀቃል ተብሎ በሚጠበቀው ውይይት፤ ግጭት ውስጥ ያሉ ሃይሎች ወደ ሠላማዊ  መንገዶች የሚመጡበትንና ችግሮቻቸውን በውይይት ለመፍታት የሚችሉበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ዕድል ይፈጠራል ተብሎ ይጠበቃል።

በቅርቡ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ረቂቁ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ፣ ለሕዝብ ቀርቦ ዜጎች ውይይት እንዲያደርጉበትና  እንዲተች  የሚጠይቅ ምክረሃሳብ ለፍትህ ሚኒስቴር ቀረበ ። ”ስብስብ ለሰብዓዊ  መብቶች በኢትዮጵያ“  የተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት፣ ከሌሎች በሰብዓዊ መብቶች ላይ ከሚሠሩ አገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር በመተባበር፣ ለረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲው  ግብዓት የሚኾኑ ሀሳቦችን የያዘ የምክር ሀሳብ ሰነድ ለፍትህ ሚኒስቴር በጽሁፍ አቅርቧል።
ይኸው ለፍትህ ሚኒስቴር የቀረበው የምክር ሃሳብ ሰነዱ፣ በቅርቡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው  ረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ፣ ለሕዝብ ቀርቦ እንዲተችና ሕዝቡ በጉዳዩ ላይ ሃሣብ እንዲሰጥበት የሚጠይቅ ሲሆን፤  ከሽግግር ፍትህ ፖሊሲው ትግበራ  አስቀድሞ    መንግሥት  በተለያዩ የአገሪቱ  አካባቢዎች በመካሄድ ላይ የሚገኙ  ግጭቶችን  ማስቆም እንዳለበት  እንዲሁም  በፖሊሲው ሂደት አግባብነት ያላቸው ተቋማት ሚና  መካተት እንዳለበት ይጠቁማል፡፡
 በተጨማሪም ሰነዱ የፖሊሲው የተፈጻሚነት ውሰን፣ በሰሜኑ ጦርነት ከባድ ወንጀሎችን የፈጸሙ የኤርትራ ወታደሮችን በልዩ ፍርድ ቤት ማየትን ጭምር እንዲያካትት የሚጠይቁና ሌሎች ምክረ ሃሳቦችንም ይዟል፡፡ ድርጅቱ፤ ከሌሎች በሰብዓዊ መብቶች ላይ ከሚሰሩ ተቋማት ጋር በመተባበር ለፍትህ ሚኒስቴር ባቀረበው ምክረ ሃሣብ፣ ረቂቁ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ፣ በምክር ቤቱ ከመፅደቁ በፊት ለህዝብ ውይይት ሊቀርብ እንደሚገባው  ጠቁሟል፡፡



አገኘሁ_አዳነ_ድልነሣሁ-


በቤልጅዬም የኢትዮጵያ ኤምባሲ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ_የሥነጥበብና_ዲዛይን_ት_ቤት ጋር በመተባበር በቤልጅዬም ከየካቲት 18 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሥዕል ትርዒት አቅርበዋል። ይህ ኤግዚቢሽን መልኩና ፈርጁ ብዙ የሆነውን የዲፕሎማሲ ዓለም በሥነጥበብና ባህል ለማዋዛት፣ ነባሩ የሥነ ጥበብ ብሂል በዘመነኛው የሥነ ሥዕል እንቅስቃሴ ላይ ያሳደረውን ክንደ ብርቱ ተፅዕኖ ለማመላከትና ት/ቤቱ ከቀረው ዓለም አቻ ተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር እንዲችል ታስቦ የተሰናዳ ነበር።  በትርዒቱ መክፈቻ የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ግንኙነት  ቢሮ ዋና ፀሐፊ ስቴፋኖ ሳኒኖ (Stefano Sannino)፣ የቤልጂየም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወካይ፣ አምባሳደር  ባርት ዴ ግሩፍ፣ የአካፓድ ምክትል ዋና ፀሐፊ ዶ/ር ኖርበርት ሪቻርድ ኢብራሂም፣ በብራስልስ የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት የተገኙ ሲሆን፣ የሥነ ጥበብ ልሂቃንና የሥነ ጥበብ አፍቃርያን ታድመውበታል።
በቤልጅዬም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባለሙሉ ስልጣን እንደራሴ አምባሳደር ሒሩት ዘመነ፣ አምባሳደር ሞላልኝ አስፋው እና የሥራ ጓዶቻቸው ዝግጅቱ የተሳካ ይሆን ዘንድ የሚያስመካ ጥረት አድርገዋል። ጥረቱ ፍሬ አፍርቶም በቤልጅዬም የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ፣ የታሪክ፣ የሂስ እና የሥነጥበብ ንድፈ ሐሳብ ልሂቃን በኤምባሲው እንዲሰበሰቡ ሆነዋል።
የአንትወርፕን (Antwerpen) Royal Academy of the Arts መምህራንም በኤምባሲው ተገኝተው ፍሬ ያለው ውይይት ማድረግ ችለናል። ምሑራኑ ትርዒቱን ተመልከተው መደነቃቸውን የገለጹልን ሲሆን፣  በምንተባበርባቸው ተቋማዊ የጋራ ጉዳዮች ላይ መክረናል።  
የቀረበው የሥዕል ትርዒት ተወዳጅነቱ ከፍ በማለቱ ምክንያት ለተጨማሪ አንድ ሳምንት የተራዘመ ሲሆን፣ ለአካባቢው ማኅበረሰብ መነቃቃት መፍጠሩን በዝግጅቱ አካል የሆንነው ሙያተኞች መታዘባችንን እንመሰክራለን።
ሀገራችን ኢትዮጵያ ከሌላው ዓለም ጋር የምትነጋገርበትን የቋንቋ አማራጭ ለማስፋት ሥነጥበብን ወደ ዲፕሎማሲው ዓለም የጋበዙትን አምባሳደር ሒሩት ዘመነን፣ አምባሳደር ሞላልኝ አስፋውንና የሥራ ጓዶቻቸውን  ማመስገን ይገባል።

አገኘሁ_አዳነ_ድልነሣሁ-


በቤልጅዬም የኢትዮጵያ ኤምባሲ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ_የሥነጥበብና_ዲዛይን_ት_ቤት ጋር በመተባበር በቤልጅዬም ከየካቲት 18 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሥዕል ትርዒት አቅርበዋል። ይህ ኤግዚቢሽን መልኩና ፈርጁ ብዙ የሆነውን የዲፕሎማሲ ዓለም በሥነጥበብና ባህል ለማዋዛት፣ ነባሩ የሥነ ጥበብ ብሂል በዘመነኛው የሥነ ሥዕል እንቅስቃሴ ላይ ያሳደረውን ክንደ ብርቱ ተፅዕኖ ለማመላከትና ት/ቤቱ ከቀረው ዓለም አቻ ተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር እንዲችል ታስቦ የተሰናዳ ነበር።  በትርዒቱ መክፈቻ የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ግንኙነት  ቢሮ ዋና ፀሐፊ ስቴፋኖ ሳኒኖ (Stefano Sannino)፣ የቤልጂየም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወካይ፣ አምባሳደር  ባርት ዴ ግሩፍ፣ የአካፓድ ምክትል ዋና ፀሐፊ ዶ/ር ኖርበርት ሪቻርድ ኢብራሂም፣ በብራስልስ የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት የተገኙ ሲሆን፣ የሥነ ጥበብ ልሂቃንና የሥነ ጥበብ አፍቃርያን ታድመውበታል።
በቤልጅዬም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባለሙሉ ስልጣን እንደራሴ አምባሳደር ሒሩት ዘመነ፣ አምባሳደር ሞላልኝ አስፋው እና የሥራ ጓዶቻቸው ዝግጅቱ የተሳካ ይሆን ዘንድ የሚያስመካ ጥረት አድርገዋል። ጥረቱ ፍሬ አፍርቶም በቤልጅዬም የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ፣ የታሪክ፣ የሂስ እና የሥነጥበብ ንድፈ ሐሳብ ልሂቃን በኤምባሲው እንዲሰበሰቡ ሆነዋል።
የአንትወርፕን (Antwerpen) Royal Academy of the Arts መምህራንም በኤምባሲው ተገኝተው ፍሬ ያለው ውይይት ማድረግ ችለናል። ምሑራኑ ትርዒቱን ተመልከተው መደነቃቸውን የገለጹልን ሲሆን፣  በምንተባበርባቸው ተቋማዊ የጋራ ጉዳዮች ላይ መክረናል።  
የቀረበው የሥዕል ትርዒት ተወዳጅነቱ ከፍ በማለቱ ምክንያት ለተጨማሪ አንድ ሳምንት የተራዘመ ሲሆን፣ ለአካባቢው ማኅበረሰብ መነቃቃት መፍጠሩን በዝግጅቱ አካል የሆንነው ሙያተኞች መታዘባችንን እንመሰክራለን።
ሀገራችን ኢትዮጵያ ከሌላው ዓለም ጋር የምትነጋገርበትን የቋንቋ አማራጭ ለማስፋት ሥነጥበብን ወደ ዲፕሎማሲው ዓለም የጋበዙትን አምባሳደር ሒሩት ዘመነን፣ አምባሳደር ሞላልኝ አስፋውንና የሥራ ጓዶቻቸውን  ማመስገን ይገባል።

ዳሸን ባንክ ሸሪክ የተሰኘ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት የጀመረበትን 6ኛ ዓመት ባከበረበት ዕለት ከደንበኞች በበጎ አደራጎት ፈንድ በአደራ የሰበሰበውን 12.5 ሚሊዮን ብር ለ18 አገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ለገሰ፡፡  

ዳሸን ባንክ በሚሰጠዉ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ብቻ አሁን ላይ ከ1 ሚሊየን በላይ ደንበኞችን ማፍራት የቻለ ሲሆን፤ይህንንም በተለያዩ ስነ-ስርዓቶች አክብሯል፡፡

የዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ዓለሙ በስነ-ስርዓቱ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ ለባንኩ አመኔታቸውን ለሰጡ ደንበኞች ከፍ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበው፣ ወደፊትም ለላቀ ስኬት የሸሪዓህ መርህን በመከተል አዳዲስ የባንክ አገልግሎቶቸን እንደሚያቀርብ ገልፀዋል፡፡

አቶ አስፋው አክለውም፤ በአደራ የተሰጣቸውን ገንዘብ የተረከቡ 18 አገር በቀል በጎ አድራጎት ድርጅቶች የማህበረሰቡን ችግር ለመቅረፍ በሚያስችሉ ስራዎች ላይ እንዲያውሉት አደራ ብለዋል፡፡ በቀጣይም ባንኩ እነኚህንም ሆነ መሰል ሌሎች ተቋማትን የማህበረሰቡን ችግሮች በዘላቂነት በሚፈቱ ስራዎች ላይ በጋራ ለመስራት የሚሻ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ዳሸን ባንክ፤ የካቲት 26 ቀን 2010 ዓ.ም በአንድ መስኮት መስጠት የጀመረው አገልግሎት አድጎ ዛሬ ላይ ከ70 በላይ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በሚሰጡ ቅርንጫፎች እንዲሁም ከ800 በላይ በሆኑ ቅርንጫፎች ደግሞ በመስኮት ለደንበኞቹ የተሟላ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ ከደንበኞቹም ከ9.5 ቢሊየን ብር በላይ ማሰባሰብ የቻለ ሲሆን፤ ከዚህም ውስጥ ከ6 ቢሊየን ብር በላይ በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ ለተሰማሩ ደንበኞቹ ፋይናንስ አድርጓል፡፡

ባንኩ ከወለድ-ነፃ የባንክ አገልግሎት የሚጠይቀውን ሙያዊና ሸሪዓዊ ስነ-ምግባር ተግባራዊ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በዚህም ረገድ እ.ኤ.አ ህዳር 28 ቀን 2023 በባህሬን ማናማ በተካሄደው 9ኛው የኢስላሚክ ሪቴል ባንክ ሽልማት ላይ ጠንካራው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በኢትዮጵያ የሚሰጥ ባንክ (The strongest Islamik Retail Banking Window in Ethiopia 2025) በሚል ተቀማጭነቱ ሎንዶን በሚገኘውና  በፋይናንስ ዘርፍ ጥናትና ምርምር በሚሰራዉ  ኬምብሪጅ አይ ኤፍ ኤ(Cambridge IFA) የተሰኘ ተቋም ሽልማት አግኝቷል፡፡ ባንኩን ለዚህ ሽልማት ካበቁት መሰፈርቶች አንዱ  ጠንካራ የሸሪዓህ አስተዳደር ማዕቀፍ በመተግበሩ ነው፡፡

ባንኩ በአለም አቀፍ ደረጃ የእስላማዊ ፋይናንስ ተቋማትን የሂሳብ፣ ኦዲትና ሸሪዓህ መስፈርቶችን የሚያወጣው ተቋም (AAOIFI) ቋሚ አባል የሆነ፣ በኢትዮጳያ ብቸኛው የፋይናንስ ተቋም መሆኑ ይታወቃል፡፡

በሙዚቃው ኢንዱስትሪ ውስጥ ከሚገኙ አለም አቀፍ ተቋማት ጋር  በጋራ እየሰራ የሚገኘው ሰዋሰው መልቲሚዲያ፣ በትውልደ ኢትዮጵያውያን በተመሰረተውና በተለያዩ የአሜሪካን ግዛቶች በስፋት በዲጂታል ማስታወቂያው ዘርፍ ላይ እየሰራ ከሚገኘው አድ ቴክ ሶሉሽን ጋር  በጋራ ለመስራት በዛሬው ዕለት ከስምምነት ላይ ደረሱ፡፡

የዛሬው ስምምነት ኢትዮጵያውያን አርቲስቶችን ወደ ዓለም አቀፉ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ እንዲሁም በሙዚቃው ዘርፍ የተሰማሩ ግዙፍ አለም አቀፍ ተቋማትን ደግሞ ወደ ሀገራችን የኪነ-ጥበብ ዘርፍ ለማስገባት አልሞ ለሚሰራው  ሰዋሰው መልቲሚዲያ ወሳኝ ምዕራፍ ነው ተብሏል፡፡

በተለያዩ የአሜሪካን ግዛቶች በኢትዮጵያውያን በሚዘጋጁ ትልልቅ ፕሮግራሞች፣ በአብዛኞቹ የሀገሪቱ ግዛቶች በሚገኙ ሞሎች፣ አደባባዮች፣ ሆቴሎችና በርካታ ሰዎች በሚሰበሰቡባቸው ጎዳናዎች ላይ የዲጂታል ማስታወቂያ ስራን የሚሰራው አድ ቴክ ሶሉሽን፣ በሰዋሰው በኩል የሚወጡ አልበሞችን፣ የተለያዩ አርቲስቶችን ስራዎች እንዲሁም ከሰዋሰው ጋር በጋራ የሚሰሩ ተቋማትን አገልግሎቶች የሚያስተዋውቅ ይሆናል፡፡

የሰዋሰው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሀብቱ ነጋሽ፤ በመላው አለም የሰዋሰው አርቲስቶችንና ስራዎችን ለማስተዋወቅና ለማስፋፋት ከምናደርጋቸው ስራዎች መካከል ይህ አንደኛው መሆኑን ጠቅሰው፣ በስምምነቱም ደስተኛ መሆናቸውን ገልፃዋል፡፡

በኢትዮጵያ የአድ ቴክ ሶሉሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አማኑኤል ኪዳኔ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያን የሙዚቃ ኢንዱስትሪ በተለየ መልክ ለማሻሻልና ለመለወጥ ከሚሰራው ሰዋሰው ጋር በጋራ ለመስራት በመስማማታችን ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶናል ብለዋል፡፡

ሁለቱ ድርጅቶች በቀጣይ በአውሮፓ የተለያዩ ሀገራት በጋራ የመስራት ውጥን እንዳላቸውም ተጠቁሟል፡፡

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ፕሮጀክት አፈፃፀም 95 በመቶ መድረሱን የሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ገለጸ።

ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ  በዛሬው ዕለት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተነገረው፤ የሲቪል ሥራው 98 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮሜካኒካል ሥራው 78 በመቶ ደርሷል፡፡

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታው አሁን ላይ 95 በመቶ የደረሰ ሲሆን፤ ሀይል የማመንጨት ምዕራፍ ላይም ይገኛል።

መላ የኢትዮጵያ ህዝብ ካለው ላይ በማዋጣት ግድቡን  ለዚህ እንዳደረሰው ያመለከተው ጽ/ቤቱ፤ በ13 አመታት ውስጥም ከ18.9 ቢሊዮን ብር በላይ ማሰባሰብ ተችሏል ብሏል።
 
ግድቡ አሁንም ከፍጻሜው እስኪደርስ ህዝቡ የሚያደርገውን ርብርብ እንዲያጠናከር ጽ/ቤቱ ጥሪ ቀርቧል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ  የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ግድብ የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠበትን 13ኛ ዓመት በተለያዩ ዝግጅቶች ለማክበር መዘጋጀቱን የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡


   የቴሌግራም ቻናልችንን  በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

Page 9 of 701